ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
إظهار المزيد638
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1130 أيام
أرشيف المشاركات
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፭ (15) ቀን።
❤ እንኳን #ለመጥምቁ_መለኮት_ለሰማዕቱ #ለቅዱስ_ዮሐንስ ነፍሱ ከተቆረጠች ራሱ ጋራ በአየር ውስጥ #እየዞረች_ዐሥራ_አምስት_ዓመት ካስተማረች በኋላ ተለይታ ለወጣችበት መታሰቢያ በዓል፣ ከሰባ ሁለቱ አርድእት ለአንዱ #ለሐዋርያ_ቅዱስ_አጋቦስ ለመታሰቢያው በዓሉና ለከሀዲ ለዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት ለከበረች #ቅድስት_እለእስክድርያ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የአገረ ሜራ ኤጲስቆጶስ በሆነ #በአባ_ ኒቆላዎስ ስም ለያዕቆባውያን ወገን በግብጽ አገር ያለች ቤተ ክርስቲያን ከከበረችበትና #ከአቡነ_አቢብ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_አጋቦስ፦ እርሱም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ይታወሳል በሐዋርያው በቅዱስ ጳውሎስ ትንቢት እንደተናገረ ሁለተኛም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ታላቅ ረኃብ እንደሚመጣ ተናገሮ ትንቢቱም ተፈጸሞ ረኃብ ቸነፈር መጥቶ ብዙዎች ሕዝቦችን አጠፋቸው። እነሆ ከገድሉ የቀረውን የካቲት አራት ቀን ጽፈናል። ከቅዱስ አጋቦስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_እለእስክድርያ፦ ይችም ቅድስት ለከሀዲ ለዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት ናት። ሰማዕነት የቀበለችበት ምክንያት ይኸውም ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ መስሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘበተበት ጊዜ ዝንጉዕ ዱድያኖስም ዕውነት መስሎት ራሱን ሊስም ተነሣ። ቅዱሱ ግን ለአማልክት ከመሠዋት አስቀድሞ አይሆንም ብሎ እንዳይስመው ከለከለው። ከዚህም በኋላም ዱድያኖስ ወደ ቤተ መንግሥቱ አዳራሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስገባው በዚያም በንግሥት እለእስክድርያ ፊት የዳዊትን መዝሙር በማንበብ ጸለየ። በስማችም ጊዜ ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው ያን ጊዜም ተረጐመላት የክብር ባለቤት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነቱን ገለጠላት ትምህርቱም በልቡዋ አድሮ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነች።
❤ ከዚህ በኋላ ሲነጋ ለአማልክት ወደሚሠዋበት ቅዱስ ጊዮርጊስን ወሰዱት እርሱም የረከሱ አማልክትን ትውጣቸው ዘንድ ምድርን አዘዛት ምድርም ዋጠቻቸው። ንጉሥ ዱድያኖስም አፈረ እየአዘነና እየተከዘ ወደ ሚስቱ ወደ እለእስክድርያ ዘንድ ገባ። እርሷም "ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነው አላልኩህምን" አለችው። ይህንንም ሰምቶ በእርሷ ላይ ተቆጣ ያሠቃዩዋት ዘንድ ጡቶቿንም ሠንጥቀው ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ። የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች። እግዚአብሔር በጸሎቷ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ዕለት #የመጥምቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ ነፍሱ ከተቆረጠች ራሱ ጋራ በአየር ውስጥ እየዞረች ዐሥራ አምስት ዓመት ካስተማረች በኋላ ተለይታ የወጣችበት ሆነ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን የአገረ ሜራ ኤጲስቆጶስ በሆነ #በአባ_ኒቆላዎስ ስም ለያዕቆባውያን ወገን በግብጽ አገር ያለች ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት መታሰቢያ ሆነ።
❤ ይህም ኒቆላዎስ ስለ ከሀዲው አርዮስ በኒቅያ ከተማ ከተሰበሰቡት ከሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ሃይማኖታቸው ከቀናች ኤጲስቆጶሳት አንዱ ነው። ይቺም በእስክንድርያ ምሥራቅ ያለች ቤተ ክርስቲያን በአባ ሲኖዳ ገድል የታወቀች ናት።
❤ ይህም ቅዱስ በተጋድሎው እጅግ ከፍ ከፍ አለ በዲዮቅልጥያኖስ መኳንንት ፊት እምነቱን በመግለጥና በመታመን ብዙ መከራና ሥቃይ ደረሰበት። ከሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት የከበሩ ሊቃውንት ጋራ በአንድነት ለመሰብሰብ እስቲደርስ እግዚአብሔር ጠብቆ አተረፈው። የዚህአባት ተአምራቶቹ የብዙና በአራቱ ማዕዘን የተገለጡ ናቸው በሰላም በፍቅር ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 15 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለዮሐንስ_እንተ_ዐብየ_ሞገሱ። እምትውልደ አንስት ኵሉ እለ ዘበሕግ ተፀነሱ። ወከመ ታውፊ ሰጊዶ ለልዑል ስብሐት ንግሡ። ለሠርቀ ወርኅ ቀዳማይ አመ ሠላስ ታሕማሱ። እምነ ሠራሪት ርእሱ ተፈልጠት መንፈሱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_15።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ አንተ ረዳእየ እግዚኦ። ውስተ እዴከ አመኃፅን ነፍስየ። ቤዝወኒ እግዚአብሔር እምላክ ጽድቀ። መዝ 30፥4። 2ኛ ቆሮ 2፥8-1-10 እና የሐዋ ሥራ 11፥27-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 14፥1-13። የሚቀደው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው መልካም የበዓለ ሃምሳ ሰሞንና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፬ (14) ቀን።
❤ እንኳን #በእስክንድርያ_ለተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ አምስተኛ ለሆነ ለከበረ አባት #ለአባ_መክሲሞስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_መክሲሞስ፦ ይህም አባት መንፈሳዊና በሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን የሚፈራ ነው። እርሱም ከእስክንድርያ ሰዎች ወገን ነው ወላጆቹም ሃይማኖታቸው የቀና ነበር የዮናውያንንም ጽሕፈትና መጽሐፋቸውን ጥበባቸውንም ሁሉ ተምሮ ፍጹም አዋቂና አስተዋይ ሆነ በዮናኒ ቋንቋ። ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ልዑል እግዚአብሔር የሠራውን ሕግና ሥርዓት ተማረ። አባት ያሮክላም ዲቁና በእስክንድርያ ሾመው ከዚያም በኋላ ዲዮናስዮስ ቅስና ሾመው በተሾመባት ሁሉ ላይ ተጠምዶ የሚያገለግልና የሚጋደል ሆነ። አባ ዲዮናስዮስም በዐረፈ ጊዜ አዋቂዎች ኤጲስቆጶሳትና ካህናት ማኅበሩም ሁሉ መረጡት በእግዚአብሔርም በፈቃድ በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት።
❤ ዲዮናስዮስም ስለ ጳውሎስ ሳምሳጢ በአንጾኪያ ከተማ የተጀመረው የኤጲስቆጶሳት ማኅበር ጉባኤ ተጀምሮ ሳይፈጸም ዐረፈ። ይህም አባት መክሲሞስ በተሾመበት ወንበር በተቀመጠ ጊዜ በማኅበሩ ጉባኤ ስለ ተወሰነውና ከሀዲው ጳውሎስ ሳምሳጢን እንደአወገዙት በጉባኤው ሹማምንት መልክቶች ወደርሱ ደረሱ። በትምርቱ ያመኑትንም መልክቶቹንም ካህናቱ በአንድነት በተሰበሰቡበት አነበበው። ከዚያም በኋላ ዳግመኛ ከራሱ መልእክቶችን ጽፎ የጳውሎስ ሳምሳጢን ስሕተት ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲጸልዩና እንዲማልዱ እያዘዘ ወደ ግብጽ አገሮች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያና ወደ ኖባ አገር ላካቸው። የክብር ባለቤት ጌታችን ልመናቸውን ተቀበለ ይህም ከሀዲ ከጥቂት ቀኖች በቀር አልኖረም በፍጥነት አጠፋው እንጂ የረከሰች ሃይማኖትንም ከዓለም አስወገደ አራቀ።
❤ በዚህም አባት ዘመን ከምሥራቅ አገር ማኒ የሚባል ራሱን የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስን ያደረገና ክፉ ስሕተትን የሳተ ሰው ተገለጠ። ወደ ሶርያ ምድርም ደረሰ አርኬላዎስ የሚባል ኤጲስቆጶስም ከእርሱ ጋራ ተከራከረ ስሕተቱንም ገላልጦበት አሳፍሮ ከአገሩ አሳደደው። ከዚያም ተመልሶ ወደ ፋርስ ሔደ ራሱንም ነቢይ አደረገ የፋርስ ንጉሥ ብህራምም ይዞ ከሁለት ሠነጠቀው። ተከታዮቹ የሆኑ ሁለት መቶ ሰዎችን ዘቅዝቆ እስከ ወገባቸው በምድር ውስጥ ተከላቸው እነሆ ከሰው አትክልትን ተከልሁ አለ።
❤ ይህም አባት መንጋውን በመጠበቅ ሲጋደልና በቀናች ሃይማኖትም ሲያጸናቸው ኖረ ከመናፍቃንና ከከሀዲያን ችግር እስከ አረፈባት ቀን ድረስ በድርሳናትና በተግሣጻት ጠብቆ አዳናቸው። በቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ስድስት ዓመት ኑሮ ሚያዝያ14 ቀን በሰላም ዐረፈ። የአባ መክሲሞስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ14 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ሰላም_ለመክሲሞስ_ልዑል። በመንበረ #ማርቆስ_ሰባኬ_ወንጌል። ዕሩቅ ትስብእት እምተዋሕዶ ቃል። በትምህርተ ካህድ ለብእሲ ዘይብል። መጽሐፈ ግዘት አንበረ በኵ ደውል"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_14።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወኢዐቀቡ ስምዖ። ተመይጡ ወዐለዉ ከመ አበዊሆሙ። ወኮነ ከመ ቀሥት ጠዋይ። መዝ 77፥56-57 ወይም መዝ 50፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ተሰ 2፥1-11፣ 1ኛ ዮሐ 4፥1-9 እና የሐዋ ሥራ 5፥35-38። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥8-15 ወይም ማቴ 12፥22-38። የሚቀደው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ። መልካም የበዓለ ሃምሳ ሰሞንና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፫ (13) ቀን።
❤ እንኳን #ሐዋርያት_ለሾሙዋት ለዲያቆናዊት ለሰማዕት ለሆነች #ለቅድስት_ዲዮኒስ ለመታሰብያዋ በዓል፣ ለከበሩ ለመነኰሳት #ለአባ_ሜልዮስ አርድእት ለሆኑ #ለአባ_ኢያሱና_ለአባ_ዮሴፍ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰማዕቱ #ቅዱስ_መናድሌዎስ_ከአባት_አኮሊሳሞስና_ከዐራት_መነኰሳም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን ሁለት የከበሩ የመነኰሳት #የአባ_ሚልዮስ_አርድእት_አባ_ኢያሱና_አባ_ዮሴፍ በሰማዕትነት ዐረፉ። እርሱም አባ ሚልዮስ በኮራሳን ተራራ በሰማዕትነት የዐረፈ ነው። እነሆ መላው ምስክረነታቸው ከመንፈሳዊ አባታቸው ከአባ ሚልዮስ ጋራ በዚህ ወር በሃያ ስምንት ቀን ተጽፎ አለ። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትሩር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 13 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ዕብል_ለዲያቆናዊት_ዲዮኒስ። እለ ሤምዊ #አርድእተ_ክርስቶስ። በስእለተ ዛቲ ቅድስተ በሥጋ ወነፍስ። በትንባሌሆሙ ለሰማዕት መናድሌዎስ። መንገለ የማኑ ያቁመነ መሐሪ ንጉሥ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_13።
✝️ ✝️ ✝️
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "አምላክነሰ ኃይልነ ወፀወንን። ወረዳኢነ ውእቱ ለምንዳቤነ ዘረከበነ ፈድፋደ። በእንተዝ ኢንፈርህ ለእመ አድለቅለቀት ምድር"። መዝ 45፥1-2 ወይም መዝ 11፥5። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥9-11፣ 1ኛ ጴጥ 2፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥1-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥8-15 ወይም ዮሐ 20፥19-ፍ.ም።። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ሰሞንና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፪ (12) ቀን።
❤ እንኳን ለመላእክት አለቃ #ለቅዱስ_ሚካኤል_እግዚአብሔር_ወደ_ነቢዩ_ቅዱ_ኤርምያስ ለላከበት (ንጉሥ ሴዴቅያስ ጠባብና ረግረግ ከሆነ ጒድጓድ በጣለው ጊዜ #ኢትዮጵያዊው_ቅዱስ_አቤሜሌክ ከጒድጓድ ውስጥ ላወጣው) ወራዊ መታሰቢያ በዓልና ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #ለአባ_እለእስክድሮስ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከአገረ ጠመው ኤጲስቆጶስ ከከበረ #ከአባ_እንጦንስና_ከአውሳንዮስ ከመታሰቢያቸው፣ #መጥምቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ ከተገለጠላቸው #ከቅዱሳን_ጋይዮስና_ኤስድረስ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ዕለት #የመላክት_አለቃ_ቅዱስ_ሚካኤልን_እግዚአብሔር_ወደ_ነቢዩ_ቅዱስ_ኤርምያስ ላከው ጠባብና ረግረግ ከሆነ እሥር ቤት ሴዴቅያስ ንጉሥ በአሠረው ጊዜ የንጉሡ ባለሟልና የጭፍራ አለቃ የሆነው አቤሜሌክ አወጣው። ያንጊዜም የኢየሩሳሌምን ጥፋት እንዳያይ መራራ ምርኮንም እንዳይቀምስ ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ መረቀው እንዲሁም ሆነ። ስሳ ስድስት ዓመትም ተኝቶ ኖረ ከእርሱ ጋራ ወይንና በለስ ነበር አልተለወጠም የእስራኤል ልጆች ምርኮ እስቲመለሱ በለሱንም ከደብዳቤ ጋራ ወደ ኤርምያስ ባቢሎን አገር ላከው።
❤ ስለዚህ የዚህን የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን መታሰቢያውን እንድናደርግ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙን። የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነቱ ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ አባ እለእስክድሮስ፦ ይህም ቅዱስም አስቀድሞ በቀጰዶቅያ አገር ኤጲስቆጶስነት ተሹሞ ነበር። እርሱም የከበሩ ቦታዎችን ተሳልሞ በረከት ተቀብሎ ወደ አገሩ ሊመለስ አስቦ ኢየሩሳሌም መጣ።
❤ በኢየሩሳሌምም ስሙ በርኪሶስ የሚባል መቶ ዐሥር ዓመት የሆነው ጻድቅ ሰው ነበር ሹመቱንም ሊተው ይወድ ነበር ወገኖቹ ግን አልለቀቁትም። ቅዱስ እለእስክድሮስም ሥራውን ፈጽሞ ወደ አገሩ ቀጰዶቅያ ሊመለስ በፈለገ ጊዜ እግዚአብሔር እንዲህ የሚል ቃል እንሆ ከሰማይ አሰማ። "ወደ እገሌ በር ውጡ አስቀድሞ የሚገባውን ይዛችሁ በላያችሁ ኤጲስቆጶስነት ሹመት"። ያን ጊዜም ሲወጡ አባ እለእስክድሮስን አገኙትና ያዙት። እርሱም "እኔ የቀጰዶቅያ ኤጲስቆጶስ ነኝ የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ በእነርሱ ላይ የሾመኝን መንጋዎቼን ልተው አይቻለኝም" አላቸው። እነርሱም ከሰማይ ስለሰሙት ስለዚያ ቃል ስለርሱም እንደአመለከታቸው ነገሩት። ይህ ነገር ከእግዚአብሔር እንደሆነ በተረዳ ጊዜ ለበዓሉም የተሰበሰቡ አባቶች መከሩት ቃላቸውንም ተቀበለ ወደ አገሩ ቀጰዶቅያም እንዲህ ብሎ መልክት ጽፎ ላካት "ይቅርታ አድርጉልኝ በእኔ ላይ አትዘኑ በእናንተ ላይም ኤጲስቆጶስ በእኔ ፈንታ ሹሙ እናንተም የተፈታችሁ ናችሁ" ያቺን መልእክትም ከእርሱ ጋራ አብረው ከመጡ ከቀጰዶቅያ ሰዎች ጋራ ላከ።
❤ ከዚህም በኋላ እየተራዳው አምስት ዓመት ያህል ከአባ በርኪሶስ ጋራ ኖረ። ከዚህም በኋላ ሽማግሌው አባ በርኪሶስ ዐረፈ። አባ እለእስክድሮስም መንጋውን ተረክቦ እንደ ሐዋርያትን በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው።
❤ ከሀዲ መክስምያኖስም በነገሠ ጊዜ ይህን አባት ይዞ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ አሠቃየው። ከዚያም በላዩ የሚያደርግበትን እስከሚያስብ ድረስ አሠረው። ጌታችንም ይህን ከሀዲ ፈጥኖ አጠፋው ወገኖቹም ይህን አባት እለእስክድሮስን ከእሥር ቤት አወጡት።
❤ ገርድያኖስም በነገሠ ጊዜ ጸጥታና ሰላም ሆነ ከክርስቲያን ወገኖች ላይም ጥቂት ወራት መከራው ጸጥ አለ። ገርድያኖስም በሞተ ጊዜ በርሱ ፈንታ አማኒ የሆነ ፊልጶስ ነገሠ። እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ስለሚያምን በክብር ባለቤት በጌታ ክርስቶስ ስም የታሠሩትን ምዕመናን ፈታቸው እጅግም አከበራቸው ይህም አባት በጸጥታ ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ ከሀዲ ዳኬዎስ ተነሣ ፊልጶስንም ገድሎ መንግሥቱን ወሰደ ክርስቲያኖችንም እጅግ አሠቃያቸው ይህንንም አባት ያዘው ብዙዎችንም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጽኑ ሥቃይም አሠቃያቸው። ይልቁንም ይህን አባት አብዝቶ አሠቃየው ጽኑ ግርፋትንም ገርፎ ስለት በአላቸው በትሮች የጐኑ አጥንቶች እስመታው። ከዚህም በኋላ እስከ እሥር ቤት ጐትተው በዚያ እንዲጥሉት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት። እግዚአብሔር ለመረጣቸው ያዘጋጀውን መንግሥተ ሰማይ እስከ ወረሰ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ እስከ ሰጠ ድረስ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ በዚያ ወድቆ ኖረ። ከአባ እለእስክድሮስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ12 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለከ_ዘተረሰይከ_በክብር። መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ ለእግዚአብሔር። #ሚካኤል_ረዳኢ ለእለ ውስተ የብስ ወባሕር። ለረድኤትከ ዘየዓፅቦ ነገር። አልቦ በሰማይ ወአልቦ በምድር። #ሊቀ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_12።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምሰባክ፦" ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዓውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታምእሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር"። መዝ33፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥30-36።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወአድኅነኒ እምእለ ሮዱኒ እስመ ይኄይሉኒ። ወአውፅአ እሞቅሕ ለነፍስየ። ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ"። መዝ 141፥7 ወይም 67፥1-2። የሚነበቡ መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 4፥9-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥13-17 እና የሐዋ ሥራ 24፥14-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 16፥13-20 የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ሰሞንና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
✝ ✝ ✝
❤ #ከቊርባን_በኋላ_የዕለቱ_አቡን፦ " ሃሌ ሉያ በ፪ "#በከመ_ይቤ_እግዚእነ_በወንጌል_ግብረ_ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ ወነገርኩ ስመከ ለሰብእ፤ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ፤ #አባ_ወአቡየ_ሰብሐኒ በስብሐቲከ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ። ትርጉም፦ #ጌታችን_በወንጌል_እዲህ_እንዳለ የሰጠኸኝን ሥራ ፈጸምኩ ለሰዎች ስምህን ተናገርኩ #አባት_አባቴ_ሆይ_በምስጋናህ_አመስግነኝ።
✝ ✝ ✝
❤ #ከቊርባን_በኋላ_የዕለቱ_አቡን፦ ሃሌ ሉያ በ፬ "#ይቤ_ክርስቶስ ነገርኩ ስመከ ለሰብእ ከመ ያእምሩከ #ለአምላክ_ሕያው ቀድሶሙ አባ ከመ ይኩኑ ቅዱሳነ ዘእምኀቤከ ኀበ ሀሎኩ አነ ህየ የሀልዉ ምስሌየ #ወይንግሩ_ስብሐትየ_ወዘአቡየ ዘሀሎ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም። ትርጉም፦ #ክርስቶስ_እንዲህ_አለ፤ አባት ሆይ ሕያው አምላክ አንተን ያውቁ ዘንድ ስምህን ለሰው ተናገርኩ፤ አባት ሆይ በአንተ ዘንድ ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ ቀድሳቸው፤ #ዓለም_ሳይፈጠር_የነበረ_የአባቴን ጌትነት የእኔንም ጌትነት ይናገሩ ዘንድ፤ እኔ ባለሁበት ደግሞ በዚያ ከእኔ ጋራ ይኖራሉ #ቅድመ_ዓለም_በነበረ_ክብርሬ_አክብረኝ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለክብር ባለቤት ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለዳግም ትንሣኤ በዐል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሉ ሉያ "#ይትፌሣሕ_ሰማይ_ወትትሐሠይ_ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ኅምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሓ በሰማያት #ወምድርኒ_ትገብር_ፋሲካ_ተሐጺባ_በደመ_ክርስቶስ። ትርጉም፦ ምድርና ሰማይ ይደሰቱ፣ ቀርነ መለከትም ይነፋ፤ ተራሮችና ኮረብቶችም የዱር ተክሎችም ይደሰቱ፤ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ፣ #ምድርም_በክርስቶስ_ደም_ታጥባለችና_ፋሲካ (ደስታን) ታደርግ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
✝ ✝ ✝
❤ #ዳግም_ትንሣኤ፦ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤ ሳምንት ለሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ተገለጠለት በእጆቹና በእግሮቹ ውስጥ የችንካሮቹን ምልክትም አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጐኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የተወጋበትን ቦታ አሳየው ቶማስም "ጌታዬና ፈጣሪዬ መነሣትህን አመንኩ" አለ። ጌታችንም "ብታየኝ አመንከኝ የሚመሰገንስ ሳያየኝ የሚአምንብኝ ነው" ብሎ መለሰለት። ስለዚህ፦ ዳግመኛ ጌታችን ለሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ባለበት ለሁለተኛ ጊዜ ስለተገለጠ ዕለቱ "ዳግም ትንሣኤ" ተባለ። ዮሐ 20፥24-29።
❤ በትርጓሜ ወንጌልም እንዲህ ይላል ቶማስ በመድኃኒታችን ጐን ውስጥ እጁን በአስገባ ጊዜ እጁ በመለኮት እሳት ተቃጠለ በመለኮቱም ደግሞ በታመነ ጊዜ እጁ ከመቃጠል ዳነች። ምንጭ፦ የሚያዝያ 6 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ"። መዝ 77፥65-66። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 28፥1-ፍ.ም፣ ማር16፥1-ፍ.ም፣ ሉቃ 24፥1-13።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ይትነሣ እግዚአብሔር ወይዘረዉ ፀሩ። ወይጒየዩ ጸላዕቱ አምቅድሙ ገጹ። ከመ የሐልቅ ጢስ ከማሁ የሐልቁ"። መዝ 67፥1-2 ወይም መዝ 117፥24-25 ። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 15፥1-20 ወይም 1ኛ ቆሮ 15፥20-41፣ 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም ወይም 1ጴጥ 1፥1-13 እና የሐዋ ሥራ 23፥1-10 የሐዋ ሥራ 2፥22-37። የሚነበው ወንጌል ዮሐ 20፥20-ፍ.ም ወይም ዮሐ 20፥1-19 ወይም ዮሐ20፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው።
✝ ✝ ✝
❤ #ከቊርባን_በኋላ_ምስባክ፦ "እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዓረብ። ይትአኰት ስሙ እግዚአብሔር። ልዑል እግዚአብሔር መልዕልተ ኵሉ አሕዛብ"። መዝ 112፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ17፥1-ፍ.ም።
❤ መልካም የዳግም ትንሣኤ በዐል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፩ (11) ቀን።
❤ እንኳን #ለከበረችና_ለነጻች አምላካዊ ራእይንም ታይ ዘንድ ለተገባት፤ መላእክትን ለምታይና የሰይጣናትንም ሥራቸውን ለይታ ታውቅበትና የምትፈትንበት እውቀት ለተሰጣት ለእመ ምኔት #ለቅድስት_ታዖድራ ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከጋዛ ኤጲስቆጶስ #ከአባ_ዮሐንስ_ከእስክንድርያው_ከአባ_በኪሞስ፣ #ከስምዖን_ዘለምጽና_ከመኰንኑ_ታዖድራ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #እመ_ምኔት_ቅድስት_ታዖድራ፦ ይቺም ቅድስት ከእስክንድርያ አገር ከታላላቆች ባለጸጎች ወገን ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው። እነርሱም ዋጋው ብዙ በሆነ በወርቅና ብር ያጌጡ የከበሩ ልብሶችን አሠሩላት ከእርስዋ በቀር ልጅ ስለሌላቸው ሊአጋቡአት እነርሱ ያስባሉና። እርሷን ግን የምንኵስና ልብስ ለብሳ በክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልትጋደል ትወዳለች መከራ መስቀሉንም ልትሸከም ትወድ ነበር የዚህ የኃላፊውን ሰርግ አልፈለገችም።
❤ ከዚህም በኋላ የወላጆቿን ዕቃ ገንዘብ ወስዳ ለሚሸጥላት ሰጠችው ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተች በቀረውም ከእስክንድርያ ውጭ በስተምራብ አብያተ ክርስቲያናትን አነፀች። ወደ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ አትናቴዎስም ሔዳ ራሷን ተላጭታ ከእርሱ ዘንድ መነኰሰች። ከደናግል ገዳማትም ወደ አንዱ ገብታ በገድልም ተጸምዳ ጽኑዕ ገድልን ተጋደለች አምላካዊ ራእይንም ታይ ዘንድ ተገባት መላእክትን ታያለችና የሰይጣናትንም ሥራቸውን ለይታ ታውቅበትና የምትፈትንበት እውቀት ተሰጣት።
❤ ቅዱስ አትናቴዎስም በእርሷ ፈጽሞ ደስ ይለው ነበር ወደርሱም ይጠራታል እርሱም ሊጐበኛት ወደርሷ ይሔዳል ኀሳቧንም ትገልጥለታለች እርሱም የጠላት ዲያብሎስን ወጥመዱንና ምትሐቱን ያስገነዝባታል። ከመንበረ ሢመቱ ከእስክንድርያ በአሳደዱትም ጊዜ ብዙዎች ድርሳናትን ጽፎ ላከላት።
❤ ይቺም ቅድስት እጅግ እስአረጀች ድረስ ኖረች በመንፈሳዊ ተጋድሎም የጸናች ናት እርስዋ ከአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ተምራለችና። እሊህም እለእስክድሮስ፣ አትናቴዎስ፣ ጴጥሮስ፣ ጢሞቴዎስና ቴዎፍሎስ ናቸው።
❤ ይቺም ቅድስት በላይዋ በአደረ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ጥቅም ያላቸውን ብዙ ድርሰቶችን ደረሰች። እንዲህም ብለው ጠየቋት "ሰው ተርታ ነገር ቢናገር ዝም በል ሊሉት ወይም እንዳይሰሙት ጆሯቸውን መክደን ይገባልን?" እንዲህ ብላ መለሰች ምንም ምን ሊሉት አይገባም ነገሩ ደስ እንዳላቸው ሁነው ዝም ይበሉ እንጂ ሰው ማዕዱን በፊትህ ቢያኖር በላይዋም በጎ የሆነና ብላሽ የሆነ ምግብ ቢያኖር ይህን ብላሹን ከእኔ ዘንድ አርቀው አልሻም ልትለው አይቻልም መጥፎውን ትተህ ከምትፈቅደው ትበላለህ እንጂ ያለ ትሕትና ያለ ጾምና ጸሎት ሰይጣንን ድል የሚነሣው የለም"። አለች።
❤ መላ ዕድሜዋም መቶ ዓመት ሁኖዋት ሚያዝያ11 በሰላም ዐረፈች። የ እመ ምኔት ቅድስት ታዖድራ ጸሎቷ በረከቷ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ11 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለታዖድራ_ዘሐነፀት_ጠረጴዛ። ለብሩር ወርቅ እንዘ ትሠይጥ ዓራዛ። እስከ ደናግል ተስሕባ በዘዚአሃ መዓዛ። ወሰላም ዕብል ለኢፍሉጠ ግዕዝ እምግዕዛ። #ለኤስቆጶስ_ዮሐንስ_ዘጋዛ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_11።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲፩ (11) ቀን።
❤ እንኳን #ለሰማዕታት_ዘኢትዮጵያ በሊቢያ በርሀ በአረመኔው የአይ ሲስ (isis) ኢስላማዊ አሸባሪ ቡድን ሰማዕትነት ለተቀበሉ ለዚህ ዘመን ሰማዕታት ወንድሞቻችን ለዐሥራ አንድኛ (11ኛ) መታሰቢያ ቀን በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕታተ_ኢትዮጵያ፦ አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
❤ ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡
❤ ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢሱስ ክርስቶስ፡፡
❤ ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡
❤ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡
❤ ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡"
❤ አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡
❤ አሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡
❤ ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡"
❤ በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡"
በረከቶሙ ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
ትርጉም፦
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ሰማዕታተ_ኢትዮጵያ፦ በሚያዝያ ዐሥራ አንድ ቀን፣ በዚህ ቀን የኢትዮጵያ ሰማዕታት አረፉ። በረከታቸው ለዘላለም ከእኛ ጋር ይሁን፤ አሜን። ይህም ነገር በሊቢያ ሀገር በ2007 ዓ.ም ተከሰተ። በዚያን ዘመን “አይሲስ” የተባሉ ክፉ ሰዎች በኢራቅ፣ በሶርያ፣ በሊቢያ እና በየመን ተነስተው ሰዎችን ይገድሉ ነበር፤ በተለይም ክርስቲያኖችን በእምነታቸው ምክንያት ይጨክኑና ይገድሉ ነበር።
❤ ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በመቆረጥ ተሰዉ፣ የሰማዕትነትንም ክብር ተቀበሉ። በዚያን ጊዜ ደግሞ ወደ ጣሊያን ለመሄድ በመንገድ ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሊቢያ አግኝተው አይሲስ ያዙአቸው።
እነዚህ ክፉዎች፣ እንደ አራዊት ያሉ፣ እነርሱን አስፈራቸው እና እንዲክዱ ስም የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዘዙአቸው።
❤ ከዚያም በብዙ መከራ አደንድነው በመደብደብ አሰቃዩአቸው፤ ምክንያቱም ክርስቲያኖች ነበሩና በአንገታቸው ላይ የመስቀል ምልክት ነበረ። ነገር ግን እነርሱ እምነታቸውን አልካዱም፤ በረሃብ፣ በጥም፣ በሌሎችም መከራዎች ቢፈትኑአቸውም አልተናወጡም።
ከዚያም እስኪደክሙ ድረስ ወደ ምድረ በዳ ወሰዱአቸው፤ እንዲሁም ምግብና ውኃ ከሌለበት ቦታ አቆዩአቸው እንዲያምኑ ተስፋ በመቁረጥ። እንደገናም “መስቀላችሁን አውልቁ፣ እምነታችሁንም ካዱ” አሏቸው፤ ነገር ግን እነዚህ ሰማዕታት አልተስማሙም።
እንዲህም አሉ፦ “እናንተ አይሲስ፣ ሥጋችንን ብትገድሉ ነፍሳችንን ግን ልታጠፉ አትችሉም። ከሰይፋችሁ አንፈራም፤ ጌታችን አስቀድሞ እንዲህ ብሎናል፦ ‘ሥጋን የሚገድሉትን አትፍሩ፤ ነፍስን ግን ማጥፋት አይችሉም"። እንዲሁም “የሚገድላችሁ ሁሉ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እያቀረበ መስሎታል” ብሎናል። እናንተም የዲያብሎስ መልእክተኞች ናችሁ፤ የሰይጣን ሥራችሁን ፈጽሙ፤ እኛ ግን ንጹሕ ራሳችንን ለፈጣሪያችን መሥዋዕት እናቀርባለን፤ እርሱም በትንሣኤው እንደሚያስነሣን እናምናለን።” ከዚያም አይሲስ ራሳቸውን በሰይፍ ቆርጦ ገደላቸው፤ እነርሱም በዚህ ቀን ሰማዕታት ሆኑ።
❤ ከዚያ በኋላ መላው ኢትዮጵያ እና ዓለም ተናወጠ፤ ሰዎችም በቴሌቪዥን ያዩትን ክፉ ነገር እየተመለከቱ እጅግ አዘኑ። ኢትዮጵያውያንም በከተሞችና በመንገዶች ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ፤ እጅግ አለቀሱ። “አይሲስ ንጹሓንን የምታገድል፣ ደማቸውን እንደ ውሃ የምታፈስ፣ በሰማያዊ ፍርድ ፊት ትቆማለህ” አሉ።
በዚያን ጊዜ የሕዝቡ ልብ በኀዘን ተሞላ፤ እንዲህም አሉ፦
“ፍትሕ ከምድር ተነስታ ወደ ሰማይ ወጣች፤ በምድር ላይ የሚቀመጥበት ቦታ አጣች። የሰማዕታቱ ደም በክርስቶስ ፊት ይጮኻል፤ ፍትሕ ይመጣ ዘንድ።”
የእነዚህ ሰማዕታት በረከትና የገድላቸው ጽናት ለዘላለም በእኛ ላይ ይሁን፤ አሜን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለትንሣኤ_ሰባተኛ_ቀን_ለቅዱሳት_አንስት መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላከክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_መዝሙር፦ "ሰበካ ትንሳኤ
አዋልዳ ለጽርሐ ጽዮን" (፪)። ትርጉም፦ የጽዮን ሴት ልጆች ትንሣኤው ሰበኩ (አስተማሩ)። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ።
❤ #ዕለተ_ቅዳሜ።
❤ #ቅዳሜ_ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፦ በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
❤ #ምስባክ_መልዕክታት_ቅዳሴ_ወንጌል እንደ ብርሃነ ትንሣኤ። መልካም የበዓለ ትንሣኤ ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲ (10) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_አባትለአባ_ዕብሎ_ረድእ ለሆነው የቊርባን ቅዳሴ ጸሎትም እስኪፈጸም ሁለት እጆቹን የኋሊት ታሥረው ራሱን አዘንብሎ እያለቀሰ ይቆም ለነበረ #ለቅዱስ_ይስሐቅ ለዕረፍቱ በዓልና ለእስክንድርያ ሰብዓኛ ሊቀ ጳጳሳት #ለአባ_ገብርኤል ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ይስሐቅ፦ ይህም ቅዱስ ይህን ዓለም ተድላ ደስታውን ምቾቱን ጣዕሙን ትቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥቶ መነኰሰ። ለአባ ዕብሎይ ረድእ ሁኖ ሃያ አምስት ዓመት ሲያገለግለው ኖረ። ሥጋውም እስኪደርቅ ድረስ ጽኑዕ ተጋድሎን ተጋደለ። ከሰውነቱም ሥጋዊ ፍላጎትን ሁሉ አጠፋ ባሕርዩ ቀንቶለት ኖረ በጸሎትና በቅዳሴም ጊዜ ጸጥታን አጸና። የቊርባን ቅዳሴ ጸሎትም እስኪፈጸም ሁለት እጆቹን የኋሊት ታሥረው ራሱን አዘንብሎ እያለቀሰ ይቆማል። ከቅዳሴም በሚወጣ ጊዜ በዚያች ዕለት ከሰው ወገን ከማንም ጋራ አይገናኝም "በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ከአንተ ጋራ መነጋገር ከሚፈልግ ሰው ጋራ ለምን አትነጋገርም" ብለው በጠየቁ ጊዜ "እንደሚገባ በሁሉ ጊዜ አለው" ብሎ መለሰ።
❤ ዕረፍቱት በቀረበ ጊዜ በረከት ከርሱ ሊቀበሉና በጸሎቱም ሊማጸኑ መነኰሳት ወደርሱ ተሰበሰቡ። "ከሰው ለምን ትሸሻለህ" ብለው ጠየቁት እርሱም "ከሰይጣን እንጂ ከሰው የምሸሽ አይደለም አንድ ሰው መብራት እያበራ በነፋስ ውስጥ ቢቆም መብራቱ የሚጠፋ አይደለምን። እንዲሁ እኛም በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ልባችን ብሩህ ሁኖ ሳለ ከሰው ጋራ ተገናኝተን እርስበርሳችን በተነጋገርን ጊዜ ልባችን ይጨልማል" ብሎ መለሰ።
❤ ይህም አባት መልካም ገድሉን ፈጽሞ በገድሉም እግዚአብሔር ደስ በአሰኘው ጊዜ ጌታችንም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ድካም ሊአሳርፈው ወደደ። ጥቂትም ታሞ ሚያዝያ10 ቀን በሰላም ዐረፈ። አባ ይስሐቅ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ለአባ_ገብርኤል፦ ይህም አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰብዓኛ የሆነ ነው። ይህም ቅዱስ የምስር አገር አለቆች ከሆኑት ከልጆቻቸው ውስጥ ነው። በግብጽ ባለች በቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያንም ዲቁና ተሾመ ዐዋቂና ጥበበኛም ስለሆነ ጸሐፊ ሁኖ ብዙዎችን መጻሕፍቶች ጻፈ የሚበዙትንም በዐረብና በቅብጥ ቋንቋ ተረጐመ።
❤ ከመሆኑ በፊት ሁሉን አይቶ በመንፈስ ቅዱስ የሚናገር የእግዚአብሔር ጸጋ በላዩ ያደረች ሶርያዊ አባ ዮሴፍ የሚባል አንድ አረጋዊ ሰው ነበር። አረጋውያን መነኰሳትና ኤጲስቆጶሳት ወደርሱ ተሰብስበው ለዚች ለከበረች የሊቀ ጳጳስና ሹመት ማን እንደሚሻል ይገልጥላቸውና ይነግራቸው ዘንድ ለመኑት። እርሱም "የታሮይክ ልጅ አንድ ሰው አለ" ብሎ መለሰላቸው ምልክቱንም አምለከታቸው መነኰሳቱና ኤጲስቆጶሳቱም በዚህ ወደው ተስማሙ ከዓመተ ሰማዕታትም በስምንት መቶ ዓመት የካቲት21 ቀን ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
❤ ወደ አስቄጥስ ገዳምም በሔደ ጊዜ መታመንን ጨመረ ይቺም ባስልዮስ ቅዳሴ ፍጻሜ ከመለኮቱ ጋር አንድ ሆነ የምትል ናት። "መለኮት ከትስብእቱ ተጨመረ ብሎ እንዲህ እንዳያስብ መነኰሳቱ ስለፈሩ እኛስ ልማዳችን እንዲህ አይደለም" አሉት። ከብዙ ምርምርም በኋላ ይች ቃል ከሚከተላት ያለ መለያየት ያለ መጨመርና ያለ መደባለቅ ከሚለው ጋራ ተሠራች በበጎ አቀባበል ተቀብለዋት እስከዚች ቀን ጸንታ ኖረች።
❤ በሹመቱ ወራትም ብዙዎች በጎ ሥራዎች ተሠሩ ሙታንን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዳይቀብሩዋቸው በውግዘት ከለከለ ሁለተኛም ዕቁባቶችን በእነርሱ ዘንድ ያኖሩትን አውጥተው እንዲረዱ አወገዘ። ይህም አባት ስለሙታን ርስትና ስለሌሎች ሥራዎች የሕግና ሥርዓት መጽሐፍን ደረሰ። ከቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትም ብዙዎችን ተረጐመ በዘመኑም ኃምሳ ሦስት ኤጲስቆጶሳትንና ብዙ ካህናትን ሾመ ነገር ግን ከእርሳቸው አንድ አላድ እንኳ አልተቀበለም።
❤ የግብጽ ንጉሥም በግፍ ከእርሱ ገንዘብ ሽቶ አሠቃየው እንዲጠባበቁትም ሰላዮችን በላዩ አኖረ። ጸሐፊዎችና ሹሞች ከሕዝቡም ታላላቆች ከሕዝቡም ሆነ ከአብያተ ክርስቲያናት ወይም ከገበሬዎች ምንም ምን እንዳልወሰደ በአወቁ ጊዜ ስለዚህ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ሰብስበው ስለርሱ ለንጉሥ ሰጡት።
❤ የዕረፍቱም ጊዜ ሲቀርብ እግዚአብሔርም ትሩፋቱንና ጽድቁን ለሰው ሊገልጽ ወደደ ጥቂትም ታመመ ብዙ ካህናትና መነኰሳትም ወደ ርሱ እንደ መጡ በሌሊት ራእይ አየ። እነርሱም ወንጌሎችን መስቀሎችንና ማዕጠንቶችን በእጆቻቸው ይዘዋል። እንዲህም አሉት "እኛ ልንጎበኝህ መጣን ከዓመትም ፍጻሜ በኋላ ወደአንተ ተመልሰን መጥተን ከእኛ ጋራ እንወስድሃለን"። በነቃም ጊዜ ከእርሱ ዘንድ ላሉ መነኰሳትና ኤጲስቆጶሳት ለካህናትም እንዴት እንዳየ ነገራቸው ከደዌውም ዳነ። ከዓመት ፍጻሜም በኋላ ጥቂት ታመመ አስቀድመው ወደርሱ መጥተው የነበሩትን ካህናትና መነኰሳት ደግሞ አያቸው ሰላምታም ሰጡት። ከእርሳቸውም ጋራ ደስ አለው በዚያን ጊዜም ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጥቶ ሚያዝያ10 በሰላም ዐረፈ። በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ አራት ዓመት ከኖረ በኋላ ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በላያችንም ቸርነቱና ይቅርታው ለዘላለሙ ይደረግልን አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ10 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለይስሐቅ_መፍቀሬ_ጽሙና_ወጸሎት። ሶበ ይብልዎ አኃው ትነፍጹ ለምንት። እምተራክቦ አኃወ በበኵሉ ዕለት። ይክልኑ ይብሎሙ አብርሆ ግሩም ጽልመት። ማዕከለ ነፋስ ቀዊሞ ማኅቶት"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_10።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፲ (10) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ ካመነኰሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ ለልደታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ፡- ሀገራቸው ትግራይ ቆየጻ ከተባለው ቦታ ነው፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኰሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ይህ ጻድቅ በተለየ ሁኔታ በሊቅነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ መነኮሳት ነበሯቸው፡፡ 120 የሐረግ ሥዕላት ያሉት ትርጓሜ ወንጌል በ4 ዓምድ አድርገው በብራና ላይ ጽፈው እንደ አይሁድ 70ው ሊቃውንት እሳቸውም 70 እውቅ የሀገራችንን ሊቃውንት ሰብስበው እጅግ ትልቁን ትርጓሜ ወንጌል በጉባኤ አስወስነዋል፡፡ በጉባኤውም ካስወሰኑ በኋላ ወስደው ከሙታን መቃብር ላይ ቢጥሉት 211 ሙታን ተነሥተው ነአምን በአምላከ ጻድቃን ወሰማዕታት በጸሎተ ሳሙኤል ተንሣዕነ ብለው መስክረዋል፡፡ ወንጌላቸውንም በሊቃውንት ሲያጽፉ ቀለሙን ቅዱሳን መላእክት ያመጡላቸው ነበር፡፡
❤ ጻድቁ ባረፉ ጊዜ 5 ነብሮች መጥተው መቃብራቸውን ቆፍረው ቀብረዋቸዋል፡፡ ትልቁ ገዳማቸው በትግራይ ክፍለ ሀገር እንዳ ሥላሴ ቆሪሮ ወረዳ ውስጥ ይገኛል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ እግዚአብሔር ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
