ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
إظهار المزيد636
المشتركون
-124 ساعات
-37 أيام
-1330 أيام
أرشيف المشاركات
🌹 ከዚህ በኋላ ቅዱስ ንጉሥ በሰላምና በበረከትና በፍቅር 40 ዘመን፡፡ ከነገሠ በኋላ የቅዱስ ላሊበላ ልጅ ዐፄ ይትባረክ ትምህርት ቤት ሆዶ ስለ ነበር ከአለበት አስፈልጎ አስመጥቶ አነገሠው እርሱም የቀኖና የቱሩፍት ስራውን በበለጠ አጠጋክሮ በጽሞና በጸሎት ተወስኖ ሳለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአእላፍ መላእክት ጋር መጥቶ "ከአይነ ሞት የምትሰወርበት ጊዜ ስለደረሰ ቃል ኪዳን ልስጥህ ዘንድ የምትፈልገው ለምነኝ" አለው። እርሱም ለቅዱሳን የሰጠው ምክንያተ ድኅነት የሆነው ልመና ስራቀረበ የሚከተለው ቃል ኪዳን ተቀብላል።
🌹 "ዝክረ ስዋሬህን በማሰቡ በየወሩና በየዓመቱ ያከበረ ስምህ የጠራ ዝክርህን የዘከረ ቤተ መቅደስህ የሠራ ያሠራ መጽሐፈ ገድልህን ያጻፈንና የተረጐመውን የሰማውንና ያሰማውን እስከ 7 ትውልድ ምሕረትን እሰጠዋለሁ።
🌹 ስለ እኔ ፍቅር መከራ መስቀሌን በማሰብ ስለፈፀምከው መከራ አንድ ክረምት የበቀለውን ቡቃያ የሚያህል ነፍሳትን ምሬልሃለሁ።
🌹 መላ ዘመንህን ሁሉ ከአይንህ እንባ ሳታቋርጥ ያፈሰስከውን ምሳሌ ከቤተ መቅደስህ የሚጠባጠብ ጠበልን እሰጠዋለሁ። ይህም የእምባህ ምሳሌ ነው። ጠበልህ ብዙ ድውያንን እስከ ዕለተ ምጽዓት ሲፈውስ ይኑር።
🌹 በቃል ኪዳንህ የተማፀኑ ሁሉ የአንተን ልጆችና ወዳጆች መሆናቸው እንዲታወቅ በቅዱስ ገብርኤል እጅ ቀኝ ግራ እጃቸው ታትሞ መንግሥተ ሰማያት ይግብልህ። እድል ፈንታቸው ፅዋ ተርታቸው ከአንተ ጋር ይሁንልህ" በማለት ቃልኪዳኑን አደረገለት (ከሰጠው በኋላ) ከአይነ ሞት የምትሰወረው ኅዳር 3 ቀን ነው ብሎ ወደ ሰማይ ዐረገ።
🌹 እንደተባለውም በሰባ ዓመቱ ኅዳር 3 ቀን ማዕጠንት በማጠን ላይ እያለ በ7 ሰዓት ገብረ ክርስቶስ የተባለው ዲያቆን በመስቀሉ ባርኮት ኤልሳዕ ኤልያስን እያየ ወደ ሰማይ እንደወጣ እርሱ እያየው ከአይነ ሞት ተሰውሯል። ከጻድቁ ንጉሥ ከቅዱስ ነአኵቶ ለአብ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ ቅዱሳንና ሥራቸው የአራቱ ቅዱሳን ነገሥታት ታሪክ ከሚለው መጽሐፍ።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ፡- ከደጋግ ክርስቲያኖች ከቀሲስ ሰንበት ተስፋነ እና ከኅሪተ ማርያም በ 1180 ዓ.ም በሥዕለት የተወለዱት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅግ አስደናቂ ገድልና ትሩፋት ያላቸው ጻድቅ ቢሆኑም ብዙው ሕዝበ ክርስቲያን እንደሚገባቸው መጠን ያላወቃቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መዘንጋታቸው እጅግ ከሚያስቆጩን አባቶች መካከል ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት የደብረ በንኰሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ እስቲ ቀጥሎ ስማቸውን የጠቀስኳቸውን እነዚህን ቅዱሳን አባቶች ታሪካቸውንና የጽድቅ ሕይወታቸውን አስታውሱት፡- እነርሱም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ ዘማንዳባ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየፃ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ፣ አቡነ ታዴዎስ ዘባልታርዋ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ እና አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄ እነዚህን የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን አስተምረውና አመንኵሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡
🌹 አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እነዚህን ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኵሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን ደብረ በንኰልን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ላይ የመነኰሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን "ሰባቱ ከዋክብት" እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህም ሰባቱ ከዋክብት የጣናን ባሕር በእግራቸው ጠቅጥቀው ተሻግረው ብዙዎቹን ደሴቱ ላይ ያሉ አስደናቂ የጣና ገዳማትን የመሠረቱት ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው ወደ ደሴት የገቡ አሉ፡፡ በእግራቸውም እየረገጡ ባሕሩን የተሻገሩ አሉ፡፡ በሌላም ቦታ በየብስ የተሰማሩትም ቢሆኑ መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፡፡
🌹 በደብረ ሊባኖሱ ሐዲስ ሐዋርያ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኰሱ በኋላ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በተራቸው ያስተማሯቸውና ያመነኰሷቸው መነኰሳት ቁጥራቸው በውል አይታወቅም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ "ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን" በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት ተናግረውላቸው ነበር፡፡ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን ጨምሮ አባታችን መድኃኒነ እግዚእ ብርሃን ሆነው በጣም ብዙ ቅዱሳንን ያመኰሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን" ይባላሉ፡፡
🌹 የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ልጆች ዛሬ ግሸን ላይ በክብር ተቀምጦ ሀገራችንን ከመዓት እየጠበቀ ያለውን የጌታችንን ቅዱስ መስቀል ያመጡትም እነርሱ ናቸው፡፡ ዐፄ ዳዊት በዘመናቸው ረኃብ ስለነተሳ የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስን ከገዳማቸው አስጠርተው "ምን ባደርግ ይሻለኛል?" ብለው አማከሯቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስም "የጌታችንን መስቀል ያስመጡ" ብለው መከሯቸው፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም ከኢየሩሳሌም፣ ከቍስጥንጥንያና ከእስክንድርያ መንግሥታት ጋር ተጻጽፈው ዓሥሩን ታላላቅ ቅዱሳን መርጠው ይዘው ሄደው መስቀሉን መስከረም 10 ቀን አምጥተውታል፡፡ በጽድቅ ሥራቸውና ተአምራትን በማድረግ በወቅቱ ታዋቂ የነበሩትና ቅዱስ መስቀሉን ያመጡት ዐሥሩ ቅዱሳንም የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ ኂሩተ አምላክ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ እንድርያስ፣ አቡነ በትረ ማርያም፣ አቡነ ዮሐንስ፣ አቡነ ታዴዎስ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ያሳይና አቡነ ቶማስ ናቸው፡፡
🌹 የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ተአምራታቸው እጅግ ብዙ ነው፡፡ አራዊት ሁሉ እንደሰው ያገለግሏቸው የነበር፡፡ ውኃ የሚያመላልስላቸውንና የሚያገለግላቸውን አህያ አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን ድፍን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ አስቀድተውታል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ለአባታችን ውኃ የሚያመላልስላቸውና የሚያገለግላቸው አንድ አህያ ነበራቸው፡፡ ውኃው የሚገኘው እርሳቸው ካሉበት በጣም እርቆ በእግር የሦስት ሰዓት መንገድ ከተሄደ በኋላ ነው፡፡ ነገር ግን አህያቸው እንደ ሰው እየተላላካቸው ይቀዳላቸው ነበር፡፡ አንድ ግን ከመንገድ አንበሳ አግኝቶት ግማሽ አካሉን በልቶት ሄደ፡፡ አባታችንም የአህያቸውን ተረፈ በድን አግኝተው በማዘን "ውኃ የሚያመላልስልኝ ረዳቴ ይህ አህያ ብቻ ነበር፣ አሁንም አህያዬን የበላህ አውሬ እንድታነጋግረኝ እፈልጋለሁ" ቢሉ በአንበሳ ተበልቶ የሞተው የአህያው ግማሽ አካል አፍ አውጥቶ አንድ አንበሳ እንደበላው ነገራቸው፡፡
🌹 አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በዚህ እጅግ ደስ ተሰኝተው ፈጣሪያቸውን ካመሰገኑ በኋላ አህያቸውን የበላውን አንበሳ ከጫካው ውስጥ ጮኸው ጠሩት፡፡ አንበሳውም ከሌሎቹ አንበሳ ተለይቶ ወደ እርሳቸው በመምጣት እግራቸው ሥር ወድቆ ሰገደ፡፡ አባታችንም "አህያዬን የበላኸው አንተ ነህን?" ብለው ሲጠይቁት አንበሳውም በሰው አንደበት "ዎ እኔ ነኝ" አላቸው፡፡ እርሳቸውም ፈጣሪያቸውን በድጋሚ ካመሰገኑ በኋላ አንበሳውን "በል ና ተከተለኝ በአህያዬ ምትክ ታገለግለኛለህ" አሉት፡፡ አንበሳውም ተከትሏቸው ወደ በዓታቸው በመግባት ለ7 ዓመታት እንደ አህያቸው ውኃ እየቀዳ አገልግሏቸዋል፡፡ የአንበሳው ቆዳ ዛሬም በገዳማቸው ደብረ በንኰል በክብር ተቀምጠቷል፡፡
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ኅዳር ፫ (3) ቀን።
🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን አኲሱም አካባቢ የሚነኘውን #ታላቁ_ገዳም_ደብረ_በንኰልን ለመሰረቱት ሰባቱን ከከዋክብት የተባሉት እነ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባን_አስተምረው ላመነኰሱትና ውኃ ይቀዳላቸው የነበረውን አህያቸውን አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ #አንበሳውን_7ዓመት_ለገዳማቸው_ውኃ_ላስቀዱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለጻድቁ የኢትዮጵያዊው ንጉሥ #ለቅዱስ_ነአኵቶ_ለአብ እንደነ #ሄኖክና_ኤልያስ_በሞት_ፈንታ_ለተሰወረው_ዕለት ለመታሰቢያ በዓሉና #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው ለነበሩት ሰማዕቱ #አቡነ_ዓምደ_ሚካኤል ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ጻድቁ_ንጉሥ_ቅዱስ_ነአኵቶ_ለአብ፦ ከዐሥራ አንዱ ነገሥታተ ዛጕዬ መካከል በዐሥረኛ የሚገኝ ቅዱስ ስመ ጥሩ ንጉሥ ነው። አባቱ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም ሲሆን እናቱ ደግሞ ቅድስት መርኬዛ ትባላለች። ቅዱሱ ፍጥረት ነአኵቶ ለአብ ከነዚህ ቅዱሳን ሰዎች የተወለደው በብስራተ መልአክ ነው። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤ ወደ ቅዱስ ላሊበላ ወጥቶ ከወንድምህ የሚወለደው ልጅህ ቅዱስና ደግ ነው የአንተም ወራሽ እርሱ ነው አለው። ቅዱስ ላሊበላም ይህን ሰምቶ "ይትባረክ እግዚአብሔር አምላክ እስራኤል ወይትባረክ ስመ ስብሐቲሁ ቅዱስ" እያለ ጸልዮ ሲጨርስ ወደ ነአኵቶ ለአብ እናት "ሰላም ለኪ ወሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስሌኪ ኢትፍርሂ ወኢትህዝኒ በከመ ዐወፀ ማሕፀኖን ለሣራ ወለሐና ከማሁ ሀወፀ እግዚአብሔ ማህፀንኪ በፍሬ ሰናይ" ብሎ ላከ እርሷም ይህን ስትሰማ መካን ሆና ትኖር ነበርና በእውነት ፈጣሪ በማህፀኔ ፍሬ ሊያሳድርብኝ ይሆን እያለች ብትጠረጥር ቅዱስ ገብርኤል እራሱ ለቅዱስ ላሊበላ እንደነገረው መልእክተኛው አረጋግጦላት ሲሆድ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤ እንደ ገና ለእናቱ ተገልጦ ልጅ እንደምትወልድ አበሰራት።
🌹 በዚህም መሰረት ቅድስት መርኬዛ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን በብስራተ መልአክ ልክ ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን ወለደችው። ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ አባቱም እናቱም በህፃንነቱ ነበር የሞቱት በሆኑም ቅዱስ ላሊበላና ቅድስት መስቀል ክብራ በቤተ መግሥታቸው በጥበብና በሞገስ እንዲሁም በእንክብካቤ አሳደጉት ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ አባ ይስሐቅ የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ሲማር መንፈስ ቅዱስ ያደረበት በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ጨርሶ ተማረ። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ላሊበላ ሞግዚትም ጓደኛ እንዲሆንና የቤተ መግሥት ሥርዓት እንዲያስተምረው ገብረ ክርስቶስ የሚባል አገልጋይ ሰጠው።
🌹 ነአኵቶ ለአብም በዚህ ሲኖር ዲቁና ተቀብሎ ፈጣሪው እያገለገለ በቅድስና ኖረ ሃያ ዓመት ሲሆነው በፍቃደ እግዚአብሔር ቅዱስ ላሊበላ በሱባኤ ጠይቆ የጥንት ስሟ አምባጌ የዛሬ እምባጽዮን በመባል ከምትታወቀው አካባቢ ቄስ እስጢፋኖስና አቅሌስያ ከሚባሉ ደናግ ሰዎች የምትወለደው ንጽሕት የምትባ ልጅ ለሚስትነት አጩለት፡፡ የሠርጉ ስርዓትና ቁርባን ከተፈጸመ በኋላ ሕገ መርዓዊ ወመርዓት ይፈጽሙ ዘንድ መጋረጃ ጥለውላቸው ሲወጡ "እህቴ ወይ እባክሽ ድንግልናችንን እንደነ ድሜጥሮስ እንጠብቅ ብሎ ለባለቤቱ ነገራት በዚሁም ተስማምተው እሰከ ሃያ አምስት ዓመት ድረስ በድንግልና ኖሩ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብም በዘመኑ ሁሉ ከመላእክት ጋር ይነጋገር ነበር። በየቀኑም ብረትና ድንጋይ ተሸክሞ ሺህ ጊዜ ይሰግድ ነበር። በዚህም የቅድስና ተግባሩም የአባቶቹ በረከት አደረበት። በተለይም ቅዱስ ላሊበላ ላይ የነበረው ጸጋና ስጦታ በእርሱም ላይ አደረ። በዚህ መሠረት አባቱን ቅዱስ ላሊበላን አስፈቅዶ እርሱ ጀምሮት የነበረውን የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያንን እንደሰራ በገድሉ ተጽፏል። ያነጻትንም ቤተ ክርስቲያን ደብረ ጽዮን ብሎ ሰይሞ ህዳር 21 ቀን ታቦቷ ገባች።
🌹 ከዕለታት አንድ ቀን እቴጌይቱ ቅድስት መስቀል ክብራም በመንፈስ ቅዱስ ተመርታ ለቅዱስ ላሊበላ እንዲህ አለችው። "እንግዲህ የመግሥትህ ፍፃሜ እየደረሰ ነውና ለነአኵቶ ለአብ ትሰጠው ዘንድ ከወዲሁ አስተዳደር እንዲማር የአንድ አውራጃ ገዥ አድርገህ ሹመው አለችው። ቅዱስ ላሊበላም ነአከኵቶ ለአብን ጠርቶ መርቆ ሥርዓተ ንግሥና ፈጽሞ ሾመው ነአኵቶ ለአብ ግን አይገባኝም በማለት አብዝቶ ከተከራከረ በኋላ በሐዘንና በለቅሶ ተሾመ ቅዱስ ላሊበላ ባርኮ መርቆ ከሠራዊት ጋር ወደ ቆቅህና (ብሔረ ቆቅህና) ሰደደው።
🌹 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ላሊበላ ሊያርፍ አቅራብያ ነአከኵቶ ለአብን እንደገና አስጠርቶ ይስሐቅ ያዕቆብን እንደመረቀው መንበረ ዙፋኑን አስቀምጦ በመሉ መንግስቱ በኢትዮጵያ ላይ አነገሠውና ከቅዱስ ላሊበላ ጥቂት ቀይቶ ሞተ፡፡ ነአኵቶ ለአብም እስከዚህ ድረስ እርሱም ሚስቱም በድንግልና ሲኖሩ ቅዱስ ሩፋኤል በራዕይ ተገልጦ ልጅ ተወልዳላችሁ ብሎ አበሰረው ነአከኵቶ ለአብም ድግልናው እንዳይሻርበት እያዘነ እያለቀሰ ሲጸልይ እመቤታችን ተገልጻ በራዕይ ድንግልናው እንደ ማይሻር ገልጣ አጽናናችው። ስለዚህ ለመጀርያ ጊዜ ሚስቱን ንጽሕትን አወቃት እርሷም ወንድ ልጅ ወለደች ስሙም በሀይለ መስቀል ተባለ ይህ ልጅም በደምግባቱና በውበቱ የሚመስለው የሌለ በጣም መልከ መልካም በመሆኑ ነአኵቶ ለአብ ይህ "ልጅ በመልኩ እየተመካ ኃጢያት ሰርቶ የሞት ሞት ከሚሞትብኝ እባክ ፈጣርዬ ዛሬውኑ ውሰድልኝና በአንተ ስም ኄሮድስ ከአስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ጨምርልኝ" ሲል በማልቀስ ፈጣሪን ለመነው ጌታም ልመናውን ተቀብሎ የካቲት 16 ቀን በሞት ለይቶ ወሰደው በዚህም ጊዜ ነአከኵቶ ለአብ ደስ ብሎት ታላቅ ግብዣ አደረገ።
🌹 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ነአከኵቶ ለአብ ከባለቤቱ ጋር ከአንድ ቀን በስተቀር ከዚያን በፊት ከዚም በኋላ ግኑኙነት አላደረጉም ምግብም ቢሆን ቀዳሚትና እሑድ እንዳይሻሩ የቤተ ማርያምን አፈርና ጥቂት የዘንጋዳ ቂጣ ይቀምስ ነበር እንጂ ዘወትር የሚዘጋጀውን የቤተ መንግሥት ምግብ አይመገብም ነበር።
🌹 ከዚምህ በኋላ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ በተጋድሎው እየጨመረ በመሄዱ 30ሰው የማይችለው ድንጋይ በአንገቱ ላይ በማሰር ክርስቶስ ለቤዛ ዓለም ብሎ የፈጸመውን ፀዋትኦ መከራ እያሰበ ላቡ ከምድር ወርዶ እስኪ ረጋ ድረስ ይሰግድ ነበር። አይሁድም እየተሳለቁበትና እየተዘባበቱበት የነበረውን መከራ በማስታወስ ዘወትር ያለቅስ ነበር። ቀን ከወርቅ ወንበር ሆኖ ሲታይ ህጋዊ ንጉሥ ይምሰል እንጂ በውስጡ ግን ማቅ ታጥቆ የከሸሎ እሾህ ከሰውነቱ በማስገባት ሲዋጋ ይኖር ነበር።
🌹 ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ እንደ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ የጌታን ሕማምና ሞት በማሰብ በፊቱ ሳቅ ቀርቶ ፈገግታ እንደማያውቅ ቅዱስ ገድል ያስረዳል። በዕለተ ዐርብ የችሎቱን ዙፋኑን አይዘረጋም ከ6 እስከ 9ሰዓት እጁን ዘርግቶ በ9 ሰዓት መራራ ነገር ይቀምስ ነበር። በሥግደትም ጊዜ በፊት በኋላ በቀኝ በግራ የሚዋጉ ጦሮችን በማድረግ የጌታ መወጋትን ያስታውስ ነበር።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ኅዳር ፪ (2) ቀን።
🌹 እንኳን #ከአባ_ጢሞቴዎስ በኋላ ለተሾመ አረማውያን ስለቀናች ሃይማኖቱ ብዙ መከራ ላደረሱበት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት #ሃያ_ሰባተኛው_ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ጴጥሮስ_ለዕረፍቱ_በዓል መታሰቢያና ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት #ስልሳ_አምስተኛ ለሆነ ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ለአባ_ሱንትዩ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦ ከእስክንድርያ ነቢዪት ከሆነች #ከሴቴንዋ_ከቅድስት_አንስጣስያና #ከአባ_ሊባኖስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የእስክንድር_ሊቀ_ጳጳስ_ቅዱስ_አባት #አባ_ጴጥሮስ ፦ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ሰባተኛ ነው ይህንንም ቅዱስ እግዚአብሔር ለሊቀ ጵጵስና ሹመት መርጦ በሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ከአስቀመጠው በኋላ የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አካክዮስ እንዲህ የሚል መልክትን ጻፈለት "እንደ ቅዱሳን ቄርሎስና ዲዮስቆሮስ ሃይማኖት ልዩ ሦስት በሆነ በአንድ አምላክ እናምናለን እናሳምናለን"። ዳግመኛም በዚች መልክት ውስጥ እንዲህ ብሎ ገለጠ "የተዋሕዶ ጥቅም እንዳይሻር ከተዋሕዶ በኋላ የአካላዊ ቃልን መለኮትን ከትስብእቱ ሊለዩት አይገባም"።
🌹 ይህ አባ ጴጥሮስ እንደ ተቀበላት ገልጦ ስለ ቀናች ሃይማኖት ከራሱም ያለውን ጨምሮ ለመልእክቱ መልስ ጽፎ ከሦስት ምሁራን ኤጲስቆጶሳት ጋር ላካት። አባ አካክዮስም ተቀበላቸው በቅዳሴና በቊርባንም አንድ ሆኑ ያቺንም መልእክት በቃሉ በሚያምኑ ሕዝብ ፊት አነበባት።
🌹 ከዚህም በኋላ ሌላ መልክትን ጻፈ በውስጧም ከቅዱሳን መጻሕፍት ብዙ ቃላትን ተርጒሞ ወደ አባ ጴጥሮስ ላካት። ይህም አባ ጴጥሮስ ኤጲስቆጶሳቱን ሰብስቦ ያቺን መልእክት በፊታቸው አነበባት እነርሱም እጅግ ደስ አላቸው ከቃሏና ከትርጓሜዋም የተነሣ አደነቁ በቀናች ሃይማኖትም ከእርሳቸው ጋር አንድነት ያላቸው መሆኑን ተማመኑ።
🌹 ይህንን አባት አባ ጴጥሮስንም ከሀዲያን ከሆኑ አይሁድ ከአረማውያንም ከመንበረ ሢመቱ እስኪያሳድዱት ድረስ ስለቀናች ሃይማኖት ብዙ መከራ ደረሰበት።
🌹 ከጥቂት ወራትም በኋላ ወደ ሹመቱ ወንበር ተመለሰ መንጋውንም በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ አዘውትሮ ያስተምራቸው ነበር ከእነርሱም ርቆ በስደት በነበረበት ጊዜ ከመናፍቃን እንዲጠበቁና በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ መልእክቶችን ጽፎ ይልክ ነበር በሹመቱ ወንበርም ዐሥር ዓመት ኑሮ ኅዳር 2 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጴጥሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 በዚችም ቀን ዳግመኛ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት #ስልሳ_አምስተኛ_የሆነ_የእስክንድርያ_ሊቀ_ጳጳሳት #አባ_ሱንትዩ_ዐረፈ፦ ይህም አባት መንጋዎቹን እያስተማረ በሹመቱ ወንበር ዐሥራ አምስት ዓመት ኑሮ ኅዳር 2 ቀን በሰላም ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 2 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_እብል_ለብፁዕ_ሱንትዩ። #ወለጴጥሮስ ዓዲ ሱታፌ ዕበዩ። ኪያሆሙ ሕዝብ በከመ ሠምሩ ወኀርዩ። ሤሞሙ አብ ጳጳሳተ ቤተ ክርስቲያኑ ይርዐዩ። እንተ አጥረያ በደሙ ወማዩ"። #ሊቁ_አርከ ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር2።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ። ወኢይፈርህ እምነገር እኩይ። ጥቡዕ ልቡ ለተወክሎ በእግዚአብሔር"። መዝ111፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ቈላ 4፥16-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥1-7 እና የሐዋ ሥራ 20፥18-31። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
+9
🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት 🎓🎓🎓
" ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ "
{"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16)
በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ #የ4ኛ , #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል #ከ11_000 በላይ ተማሪዎች በአበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር ተከናውኗል!!!
በዚህም ደብራችን ከ4ተኛ ክፍል ፈተና 100% በማምጣት ተማሪ ክህነት ተሸላሚ ሆና ደብራችንን አስጠርታለች ሁላችሁም ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላቹ እንኳን ደስ አለን!!!
🎓🗓 ጥቅምት_30_2018_ዓ_ም
🎓 📷 ሚዲያና ዕቅበተ ዕምነት ክፍል
🎓 🏢 በሚሊኒየም_አዳራሽ
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🌹 ሌሊት ሲሆንም ይገድሉት ዘንድ እስከሚሰበሰቡ ድረስ ወደ እስር ቤት አስገቡት፡፡ መንፈቀ ሌሊት ሲሆንም በሮች ተዘግተው ጠባቂዎችም ተኝተው ሳሉ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ የእግዚአብሔር መልአክም "የግብጽን አገራት ሁሉ የምታረጋጋ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማርቆስ ሆይ ስምህ በሰማይ ባለ የሕይወት መጽሐፍ ተጽፏል ከሐዋርያት ቁጥርም ተቆጥሮአል፤ መታሰቢያህም አይረሳም፤ በምድርም ስፍር ቁጥር የሌላትን ሥልጣን፣ ጸጋ ኃይል እነሆ ሰጥቶሃልና፤ ነፍስህ በሰማይ ይሆናል ሥጋህም በመሬት አይጠፋም" አለው፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስም ይህን ምሳሌ በተመለከተ ጊዜ እጆቹን ወደ ሰማይ አነሣ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከፊትህ አልጣልኸኝም፣ ከቅዱሳን ማኀበርም ደምረኸኛልና አመሰግንሃለሁ፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እለምንሃለሁ ነፍሴን በሰማይ ተቀበላት፤ ከፊትህም አትተወኝ" አለ፡፡ ይህን በተናገረ ጊዜ ጌታችን አዳኝ ከሆነው ከሕማሙ በፊት በመቃብርም ከመጨመሩ አስቀድሞ በሐዋርያት መካከል እንደነበረ ሆኖ ታየው፡፡ "የመረጥሁህ ማርቆስ ሆየ ሰላሜ ከአንተ ጋር ይሁን፤ በወንጌል አስተማርሁህ፤ እነሆም መከራን ከመቀበሌ አስቀድሞ ከጓደኞችህ ከሐዋርያት ጋር አንደሆንሁት በአርአያ ተገለጥኩልህ፤ ከእነርሱ ምንም ጉድለት እንዳይኖርብህ" አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከጸጋህ ታላቅነት የተነሣ አመሰግንሃለሁ፤ በሥጋህ አንደነበርህ ሁነህ አንዳይህ የተገባኝ አድርገኸኛልና" አለው "ስለተቀደሰው ስምህ መከራን እቀበል ዘንድ ትዕግሥትን አድለኸኛልና" ጌታችንም ሰላምን ሰጠውና በታላቅ ምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ሲነገም የአገሩ ሰዎች ተሰበሰቡ፤ ከእስር ቤትም አወጡት በሰንሰለትም አሰሩት፤ ዳግመኛም በላሞች ቦታ እንደፍየል እንጐትተው እያሉ በከተማው ጐተቱት፡፡
🌹 ብፁዕ ማርቆስም ምስጋናን አቀረበ በሰማይ ተገለጠ፡፡ በየአገሩ ከጎተቱት በኋላም ደሙ በየመንገዱና በየአደባባይዋ ሞላ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን በእጅህ ሰጠሁ" አለ፡፡ ይህን ከተናገረ በኋላም ዐረፈ፡፡ ሁሉም አረማውያን ቅዱስ ማርቆስ አንዳረፈ በተመለከቱ ጊዜም ሥጋውን በእሳት ያቃጥሉት ዘንድ አውበካልዮን በምትባል ቦታ ጽኑ እሳትን አነደዱ፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድም ጨለማና ቀዝቃዛ ነፋስ ሆነ፤ ፀሐይም ብርሃኑን ሰወረ፡፡ በዚች ዕለትም እስከ ምሽት ድረስ መብረቅ፣ ነጎድጓድ፣ ዝናምና ብርድም ሆነ፤ ከአገሩ ሰዎች ከሽማግሌዎች ብዙዎች ወደቁ ከእነርሱም ብዙዎቹ ሞቱ ያን ጊዜ ፈሩ ሂደወም ከአገሩ ሰዎች የቅዱሱን ሥጋ አኖሩት፤ የተዘባበቱበትም አሉ "ታላቁ አምላክ ሆይ የዚህን ሰው ነፍስ ተቀበላት በዚች ዕለት የልደቱ ዕለት ናትና" አሉ፡፡ ምዕመናን ወንዶች ደረሱና የቅዱሱን ሥጋ ከእሳቱ ወሰዱት ጸሎት ወደሚጸለይበት ቦተም አደረሱት በእርሱ ላይም ተሳሉ፣ ምስጋናንም አቀረቡ እንደ ሥርዓታቸውም እንደ አገሩ ሰዎች ገነዙት በቆፈሩለት መቃብርም ቀበሩት፡፡ መታሰቢያውንም በደስታ፣ በምሥጋና አብዝተው አደረጉ፣ አበዙ በአገሩ መሠረታዊ ቦታም አስቀመጡት፡፡
🌹 የሰማዕታት መጀመሪያ በግብጽ ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰ የወንጌላዊው የቅዱስ ማርቆስ ዕረፍቱ በሚያዝያ ወር መጨረሻ በሠላሳኛው ቀን ዕለቱመ ሰኞ ጠዋት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ በተገለጸ 68 ዓ.ም ወደ ሰማይ ባረገ በ35 ዓ.ም በታላቋ አገር በእስክንድርያ ሆነ ፡፡ ከሐዋርያውና ከወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፡፡ በጸሎቱ ይማረን!፡፡ ምንጭ፦ ገድለ ሐዋርያት ፤ ስንክሳር ፤ ክብረ ቅዱስ ማርቆስ ከሚለው መጽሐፍ።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወተጽእልኩ በኀበ ኵሎሙ ጸላእትየ። ወፈድፍደሰ በኀበ ጎርየ። ግሩም ኮንክዎሙ ለአዝማድየ"። መዝ 30፥11-12 ወይም መዝ 26፥6። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 11፥1-7ዐ ወይም ማቴ 16፥24-ፍ.ም።
🌹 ቅዱስ ማርቆስ በኢየሩሳሌም የእናቱ የማርያም ቤት የደቀ መዛሙርቱ መገናኛና መሰባሰቢያ ስለነበር ደቀመዛሙርቱን የበለጠ እንዲያውቃቸውና እንዲቀርባቸው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከማድረጉም በላየ በተለይም ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ባለው የጠበቀ ዝምድናና ቀረቤታ ለቅዱስ ጴጥሮስ የሃይማኖት ልጅ በመሆንና ለአገለግሎቱም ፍጹም መንፈሳዊና እውነተኛ የክርስቶስ ምስክር ለመሆን በቅቷል፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በልጅነቱ በኢየሩሳሌም ለመኖር በመታደሉ በዚያም ዘመን ይሰጥ የነበረውን ትምህርት የማግኘት ዕድል ገጥሞት ነበርና የዕብራይስጥ፣ የላቲንና የግሪክ ቋንቋዎችን ያውቅ ነበር፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስ ወንጌልን መስበክ የጀመረው ገና በወጣትነቱ ነበር በመጀመሪያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብሮ ያስተምር ነበር፡፡ በግብረ ሐዋርያት አንደተገለጸው ቅዱስ ማርቆስ ከቅድስ ጳውሎስና ከቅድስ በርናባስ ጋር ይሰበክ ነበር፡፡ ከዚያም በፊት ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በኢየሩሳሌምና በይሁዳ አስተምሮአል፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስ ንጹሕና ድንግል መሆኑን መልካምነቱንና ትምህርቱን ተመልክቶ ቅዱስ ጴጥሮስ ለግብጽና ለአካባቢዋ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አድርጎ ሾመው፡፡ በግብጽ አገሮች በሎኒያ፣ በመርቅያ፣ በጣውንቄ፣ በበርቃ ለመጀመሪያ አስተማረ እርሱ ነው፡፡ ወንጌልን አስተማራቸው፡፡ አዳኝ በሆነ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንንም አስተማራቸው፡፡ ሁሉም የዚያች አገር ሰዎች ልቡናቸው የደነደነ ነበሩ በርኵሰት ሁሉ የተሞሉ አማልክትንም ያመልኩ ነበር፡፡ ሰይጣንን በማምለክም ይኖሩ ነበር፡፡ በየቦታው በየመንገዱም ሁሉ ምኩራቦችን የአማልክትን ቤት ይሠሩ ነበር፡፡ መድኃኒትን፣ ዝሙትንም ያደርጉ ሕጻናትን ይገድሉ በደማቸው መድኃኒትን ያደርጉ ነበር፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስም ወደ ሐዋርያት በሄደ ጊዜ አስቀድሞ በርቃ ደረሰ፡፡ ዘመዶቹ ከእነርሱ ወገን ናቸውና፡፡ እግዚአብሔርን ቃልም አስተማራቸው በመካከላቸው ብዙ ተአምራትን አደረገ፤ በሽተኞችን ፈወሳቸው ለምጻሞችንም አነጻቸው፤ በእርሱ ላይ በአደረው ጸጋም አጋንንትን አስወጣ፤ ብዙዎችም በትምህርቱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ አምላኮቻቸውንም (ጣዖቶቻቸውንም) ሰባበሩ፤ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስምም አጠመቃቸው፡፡
🌹 በዚያ ቦታም ወደ እስክንድርያ ይሄድ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ተገለጠለት፡፡ በዚያም መልካም ተዘራባት ይኸውም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ወንጌላዊው ብፁዕ ቅዱስ ማርቆስም ለጦርነት እንደተዘጋጀ ጎልማሳ ሆነ "ወንድሞቹንም ሰላም" አላቸው "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ቦታ ቅዱስ ወንጌልን አስተምር ዘንድ ወደ እስክንድርያ እንድሄድ አዝዞኛል" አላቸው፡፡ እነርሱም ሸኙት በመርከብም ተሳፍሮ ወደ እስክንድርያ ሄደ በደረሰ ጊዜም ወደ ከተማው በር ገባ የጫማው ማሠሪያም ተቆረጠ በቅንነትም መንገድ ፈጠነች አለ በዚያም ከከተማው መግቢያ ጫማ ሰፊ ነበር፡፡ ቅዱስ ማርቆስም እንዲሰፋለት ለርሱ ሰጠው ሲሰፋም ጣቱን ወግቶ ሰነጠቀው ከእርሱም ደም ፈሰሰ በዩናኒም ቋንቋ "ኢታስታያስ" አለ ትርጓሜው አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም "ስሙን የምትጠራው አውቀኸው ነውን" አለው "እንጠራዋለን እንጂ አናውቀውም" አለ፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በጣቶቹ ላይ መራቅ ጨመረና አፈር ወሰደ ያን ጫማ ሰፊ ቀባው "በሕያው አግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ስም አጅህ ትፈወስ" አለው፡፡ ስለዚህም ተፈወሰች ጫማ ሰፊውም በሥልጣኑ በቃሉ ያደረገውን ድንቅ ተአምር በተመለከተ ጊዜ "የቸሩ አምላክ አገልጋይ ሆይ እለምንሃለሁ ዛሬ ውጣና በቤቴ እረፍ በአንድነትም እንመገብ መልካም ነገርን አድርገህልኛልና" አለው፡፡
🌹 ብፁዕ ቅዱስ ማርቆስም ተደሰተ፡፡ "እግዚአብሔር ሰማያዊት የምትሆን ሕይወት ኀብስትን ይስጥህም" አለው፡፡ ጫማ ሰፊውም ሐዋርያውም እየተደሰተ ወደ ቤቱ አስገባው፡፡ ሐዋርያውም እየተደሰተ ወደ ቤቱ ገባለት። "የእግዚአብሔር በረከት በዚህ ቤት ይኑር" አለ፡፡ ወንድሞች በአንድነት ጸለዩ ከጸሎት በኋላም ተቀመጡና ደስ እያላቸው ተመገቡ፡፡ ጫማ ሰፊውም ቅዱስ ማርቆስን "አባት ሆይ እለምንሃለሁ ይህንን የምትለው እንዴት ነው፤ ይህ ስምስ ምንድን ነው ይህ እንደዚህ የሚቻለው ነው" አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም "እኔ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ" አለው፡፡ ጫማ ሰፊውም "እኔ ላየው እሻለሁ" አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም "እኔ አሳይሃለሁ" አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም "የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ ነው" እያለ የወንጌሉን መጀመሪያ አስተማረው፡፡ በትንቢት ስለ እርሱ የተናገሩትንም ከመጻሕፍት ተናገረ፡፡ ጫማ ሰፊውም "እኔ የምትለውን ይህን መጽሐፍ እለምንሃለሁ ከረጅም ዘመን ጀምሮ የግብጻውያን ልጆች እንደማይማሩበት አልሰማህምን" አለው ቅዱስ ማርቆስ እንዲህ በማለት የእግዚአብሔርን ነገር ይነግረው ዘንድ አስቀደመ "የዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ዘንድ ናት" አለው ጫማ ሰፊውም የቅዱስን ነገር በሰማ ጊዜ በእግዚአብሔር አመነ ለእርሱም አመለከተው ከእርሱም ኃይላትን ተአምራትን አየ እርሱ ቤተሰቡ፣ ከአገሩ ሰዎችም ብዙዎቹ ተጠመቁ፡፡ የጫማ ሰፊው ስምም አንያኖስ ይባላል፡፡ ያን ጊዜም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ምዕመናን በዙ፡፡ የአገሩ ሰዎች በሰሙ ጊዜም "ይህ የገሊላ ሰው ከዚህ አገር ደርሷል፤ የአማልክትን እጅ መንሻ ለውጧል፤ እንዳይመለኩ ከልክሏል" አሉ ሊገሉትም ፈለጉት ይጥሉት ዘንድም በእርሱ ላይ ፍለጋን አበዙ ብፁዕ ማርቆስ ይህን በተረዳ ጊዜ አስተማራቸውና አንኖስንም ኤጲስ ቆጾስነት ሾመላቸው ሦስት ካህናትንም ሾመላቸው ስማቸውም ወልዮስ፣ መሪደስና በሪሞስ ይባላል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮም ሰባት ዲያቆናትን አንድ ላይ አሥራ አንድ ሰዎችን ሾመላቸው፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስም ወደ ብርቃ ወጣ ለዓመታትም በእርሷ ተቀመጠ፡፡ በሁሉም አገራት ኤጲስቆጶሳትን፣ ካህናትን ሾሞላቸው ወደ እስክንድርያም ተመለሰ፡፡ በእግዚአብሔር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስምም ጸጋና ማመን በዛባት የላም ቦታ በሚባለው በባሕሩ ዳር ካለው ቦታም ቤተ ክርስቲያን ሠሩ ከዚያ ቦታ ከዓለቱ ሥርም ታላቅ ድንጋይ ቁራጭ ነበር፡፡ ጻድቁም ስለ ምዕመናን መልካም ሃይማኖት እግዚአብሔርን አመሰገነ ብዙ ዘመን በቆየ ጊዜም ክርስቲያኖች በዙ አማልክትንም ተዘባበቱባቸው፤ አረማውያንንም ናቋቸው፡፡ አረማውያንም ቅዱስ ማርቆስ እንደሆነ ወደ አገራቸው እንደደረሰ ተረዱ፡፡ ከሰሙት ተአምራት ብዛት የተነሳ ልቡናቸው በቁጣ ተሞላ እርሱ ሕመምተኞችን ይፈውስ፣ ለምጻሞችንም ያነጻ፣ ደንቆሮዎችንም እንዲሰሙ፣ እውራንንም እንዲያዩ ያደርጋል መልካም ተስፋንም ያስተምራቸው ነበር ይይዙት ዘንድም ፈለጉት፤ በየቤታቸውም ጥርሳቸውን ያፋጩ ነበር፤ በአማልክቱ ምኵራብም "እኛ ለዚህ ጠንቋይ ተሸነፍን" እያሉ ጮኹ፡፡ ምዕመናን የሚያከብሩት ዕለት ሰንበት የተባረከው የፋሲካ በዓልም በሰንበት ቀን ሆነ፤ ይህም ዕለት ሚያዝያ 17 ቀን ነው፡፡
🌹 በዚያች ዕለትም በእነርሱ ዘንድ የሰራቢስ የልደቱ ቀን ነበር፡፡ ያማረች ዕለትን አገኙ ሰላዮችን ላኩና ያዙት፡፡ እርሱን የቅዳሴ ጸሎት ሳይፈጽምም በሰንሰለት አሠሩት በላሞች ቦታ እንጐትተው እያሉም እንደ አውራ ፍየል በየመንገዱ ጐተቱት፡፡ ቅዱስ ማርቆስም በጐተቱት ጊዜ አግዚአብሔርን አመሰገነው፡፡ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በተቀደሰው ስምህ መከራን እንድቀበለ አዘጋጅተኸኛልና አመሰግንሃለሁ” አለ፡፡ ሥጋውም በየመሬቱ ተቆራረጠ ደሙም በየዐለቱ ፈሰሰ፡፡
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፴ (30) ቀን።
🌹 እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነ #በእስክንድርያ_በግብፅ ያለቱ አምልኮ ጣኦታት (ላሕም) ላጠፍ ወንጌልን ለሰበከ ለወንጌላዊው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ማርቆስ_ለልደቱ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ሐዋርያው_ወንጌላዊው_ቅዱስ_ማርቆስ ዘአንበሳ፦ የቅዱስ ማርቆስ ወላጆች ስም የአባቱ ስም ቅዱስ አርሰጡጳውሎስ ሲሆን የእናቱ ስም ቅድስት ማርያም ይባላል፡፡ አባቱ ባለፀጋና ያላገባ ነበር የአባቱ ስም ስምዖን ይባል ነበር፡፡ ስምዖንም አርስጡጳውሎስን እንዲያገባ ይገፋፋው ነበር፡፡ አንድ ቀን ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ በቤቷ እንግዶችን የምትቀበልና የምታስተናግድ ማርያም የተባለችውን የወንጌላዊ የቅዱስ ማርቆስ እናት አገኘ፡፡ እሱም እሷመ ሳያስቡት ባዩት ሕልምና በመፈክራነ ሕልም (በሕልም ፈቺዎች) በተነገራቸው መሠረት ተገናኝተው የትዳር ሕይወትን መሠረቱ፡፡
🌹 አርስጡጳውሎስ ከከበረውና በባለጸግነቱ ከታወቀው ከአባቱ ካገኘው ሀብት ለነዳያን የሚመጸውት፣ ዐሥራት በኩራት የሚያወጣና ወደ እግዚአብሔርም ዘወትር የሚጸልይ ደግ አባት ነበር፡፡ እሱም የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስ ዘመድ የአክስት ልጅ እንደሆነና ቅዱስ ጳውሎስም በመልአክቱ የጠቀሰው እሱን እንደሆነ አንዳንድ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ "አብሮ ከእኔ ጋር የታሰረ አርስጥሮኮስ የበርናባስም የወንድሙ ልጅ ማርቆስ ኢዮስጦስም የተባለ ኢያሱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል" ቈላስይስ 4፥10 ነገር ግን አንዳንድ የግሪክ፣ የላቲን፣ የግእዝና የኮኘት ትርጉሞች "የበርናባስ የወንድሙ ልጅ" የሚለውን ሐረግ አይጠቅሱም ይህም ምንአልባት አንዳንድ የግሪክ ቃላት ከአንድ በላይ ትርጉም ስላላቸው ይሆናል፡፡
🌹 የቅዱስ ማርቆስ እናት ማርያም ተብለው ከተጠሩት ብዙ ቅዱሳት አንስት መካከል አንዷ ናት፡፡ ቤቷ በኢየሩሳሌም እንደነበረና ምዕመናንም በቤቷ በጸሎት ይሰበሰቡ እንደነበር በሐዋ 12-12-17 በሰፊው ተገልጾአል፡፡ ይህም በጥንት ወይም በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በኋላ ካሉት መንፈሳውያኑ ሴቶች (ቅዱሳት አንስት) ከፈተኛ ቦታ ያላት እንደነበር ያመለክታል። በዚያን ጊዜ የነበሩ ምዕመናን በአንድነት በክርስቶስ ስም ይሰባሰቡ ስለነበር ክርስቲያን የሚለውን ስም ያገኙትም በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ "በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፤ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርቱም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ"፡፡ ሐዋ ሥራ 11፥26
🌹 የቅዱስ ማርቆስ እናት የማርያም ቤት የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ለጸሎት የሚሰበሰቡበት ነበር፡፡ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት በጽርሐ ጽዮን ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ እንደተገለጸላቸውና መንፈስ ቅዱስን እንደላከላቸው በቅዳሴ ዲዮስቆሮስ እንዲህ ተጽፏል "አመ ሣልስት ዕለት ተንሥአ እሙታን ወቦአ ኀበ ሀለው አርዳኢሁ ጉቡአን ወአስተርእዮሙ በጽርሐ ጽዮን … ወበ ፶ ዕለት ፈነወሎሙ መንፈሰ ቅዱስ ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኩሉ በሐውርት … በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ የተሰበሰቡ ደቀ መዛሙርት ባሉበት ገባ በጽርሐ ጽዮንም ታያቸው …በ50ኛው ቀንም በእሳት አምሳል መንፈስ ቅዱስን ሰደደላቸው በአገሩ ቋንቋ ሁሉ ተናገሩ"
🌹 በኢየሩሳሌም ውስጥ የማርያም ቤት የሐዋርያት መገናኛና መሰባሰቢያ ነበር፡፡ ስለዚህም የማርቆስ እናት የማርያም ቤት የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ኀብረት መለያ ሆኖ ይታወቃል፡፡
🌹 ቅዱስ ማርቆስ የተወለደው በአባቱ ወገን ከነገደ ይሁዳ ሲሆን የተወለደበት ቦታ ከአምስቱ የምዕራብ ከተሞች አንዷ በሆነችው በሊቢያ በሲርኔ ይኸውም አብራይሮሎስ በተባለች ትንሽ መንደር ተወለደ፡፡ ትውልዱ ዕብራዊ ቤተሰቦቹም ይኖሩበት የነበረው በሰሜን አፍሪካ በጥንታዊቱ ፔንዲፓሊስ ሲሪኒካ (ቀሪና) በተባለችው በዛሬው ሊቢያ ምዕራባዊ ጠረፍ በተቆረቆረችው ደማቅ ከተማ ስለነበር ቅዱስ ማርቆስ አፍሪካዊ ነው የሚባለውም ለዚህ ነው የሚሉ አሉ፡፡ ሉሌ መላኩ ቤተክርስቲያንህን እወቅ።
🌹 ቅዱስ ማርቆስ ሰኔ 3 ቀን በዕለተ ረቡዕ ተጸንሶ መጋቢት 3 ቀን በዕለተ ዐርብ ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ተወለደ፡፡ ነገር ግን በዓለ ልደቱ የሚከበረው መጋቢት ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል የሚከበረው ጥቅምት 30 ቀን ነው።
🌹 የቅዱስ ማርቆስ የስሙ ትርጓሜ ማርቆስ ማለት ንህብ ማለት ነው ንብ ከሁሉ እንዲቀስም አስቀድሞ ከክርስቶስ በኋላም ከሐዋርያት ተምሮአልና፡፡
🌹 አንድም አንበሳ ማለት ነው አንበሳ ለላሕም ጌታው እንደሆነ እንዲሰብረው እርሱም አምልኮተ ላሕምን ከግብጽ አጥፍቷልና፡፡
🌹 አንድም ካህን ልዑክ ማለት ነው፡፡ ብሥራተ ማሪ ማርቆስ ይላል የተደራረበ ቀለም ነው፡፡ ሁሉም ካህን ማለት ነው፡፡ እመልአክተ ሲኖዲቆስ ባለ ጊዜ መልእክትም ሲኖዲቆስም ክታብ ማለት እንደሆነ ….።
🌹 የቅዱስ ማርቆስ ሁለተኛ ስሙ ዮሐንስ ይባላል። "ባስተዋለም ጊዜ እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለ ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ" ሐዋ12፥12
🌹 የቅዱስ ማርቆስ ተክለ ቁመናና መልክ
እንዲሁም አለባበሱን እንዲህ በማለት ተጠቅሷል፡፡ "የግብጽና የኢትዮጵያ ኮከብ ብፁዕና ቅዱስ ማርቆስ መልኩ ቀይ ቅንድቦቹም ከበድ ያሉ ዓይኖቹም እንደሰማያዊ ኀብር የጠሩ ቁመቱ ረጅም ከአንገቱም ስር ስርጉድ የሆነ እንደ ነቢዩ ኤልሳዕ ራሰ በራህ የሆነ ቀሚስ (ልባልባውም) በወገቡ የሆነ የግብጽና የኢትዮጵያ አባት የቅዱስ ማርቆስ ምልክቱ ይኸ ነበር፡፡
🌹 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዊ በሚሰብክበት ጊዜ ቅዱስ ማርቆስ ወጣት ነበር፡፡ ልቦናው የቀና እንደሆነም አውቆ ከሰባ ሁለቱ አርድእት በፊት የመጀመሪያ አድርጐ መረጠው ከዚህ በኋላ የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሆኖ ጌታ ወንጌልን ሲያስተምር፤ ተአምራት ሲያደርግ ያስተውል ነበር ፡፡ በምሴተ ሐሙስ በአይሁድ ሲያዝና መከራን ሲቀበል ቅዱስ ማርቆስ በኢየሩሳሌም መንገድ ላየ ሆኖ በርቀት ድርጊቱን ይከታተለ ነበር፡፡ በወንጌሉም እንዲህ ተብሎ የተጻፈው ስለ አርሱ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ "ዕርቃኑን በነጠላ የሸፈነ አንድ ጐበዝ ይከተለው ነበር ጎበዛዝቱም ያዙት፤ እርሱ ግን ነጠላውን ትቶ ዕራቁቱን ሸሸ"፡፡ ማር 14፥51-52
🌹 ቅዱስ ማርቆስ በቤቱ መጻፊያ ይዞ የጌታን ተአምራት ይጽፍ ነበር፡፡ የግሞ ሊናሮስ የሚባል አገልጋዩን ጌታን እንዲከተልና የሚያደርገውንም ተአምራት እንዲጽፍ ያደርግ ነበር ፡፡ "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዓለ ፋሲካን ሲያከብር ተከተሉት" የተባለውም ቅዱስ ማርቆስን እንደሆነ እንዲህ ተጽፍል፤ "ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ላከ እነዲህም አላቸው ወደ ከተማ ሂዱ ማድሃ ውሃ የተሸከመ ሰውም ያገኛችኋል ተከተሉት የሚገባበትንም የቤቱን ጌታ መምህሩ፣ ከደቀመዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ወዴት ነው ይላል በሉት፡፡ እርሱም በደርብ ላይ ያለውነ የተሰናዳና የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፣ በዚህም አሰናዱልን፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ወጡ ወደ ከተማም ሄደው እንዳላቸው አገኙ ፋሲካም አሰናዱ" ማር 14፥13-15፤ ሉቃ 22፥10-12።
በዚያ በእንደግብጦን አውራጃ ሁሉ ላይ ፓትርያርክ አድርጎ ሾመው፡፡ በእነስድስታይ አገር ላሉ ሰዎችም ሁሉ አባት ሆናቸውና የመንፈስ ቅዱስ ልጁንም ታዲዮስን መምህርና አባት አድርጎ ሾመላቸውና ጽላልሽ ሄዶ እናቱን ይዞ ጽጋጋ ምድረ ወገግ ወስዶ አመነኰሳት፡፡
🌹 አቡነ ሳሙኤል ወደ ምድረ ርስቱ ደብረ ወገግ እየሄደ በዚያ ያሉ ልጆቹን እያጽናና ወደ እንደግብጦን አውራጃም እየተመለሰ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ ጣዖት አምላኪዎችን ወደ ክርስትና እየቀየረ፣ አጋንንትንና መመለኪያ ቦታዎቻቸውን እያጠፋ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እያነጸ በብዙ ተጋድሎ ኖረ፡፡ በቅዱስ ገድሉ ውስጥ በጣም አስገራሚ በሆነ መልኩ እጅግ ብዙ ታሪኮች ተጠቅሰዋል፡፡ እነዚህም ታሪኮች ውስጥ አቡነ ሳሙኤል በሀገራችን በጣም ብዙ ጣዖታትንና መመለኪያ ቤቶቻቸውን እያጠፉ፣ በሰዎች (በጠንቋዮች) ላይ፣ በዛፍና በባሕር ውስጥ አድሮ ይመለኩ የነበሩ ሰይጣናት አጋንንትን በሚያመልኳቸው ሰዎች ፊት እያጋለጡና እያዋረዱ ሰዎቹን አስተምረው አጥምቀው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሷቸው ቤተክርስቲያንም በመሥራት ሐዋርያትን መሰሉ፡፡
🌹 ሰይጣን አድሮባቸው የነበሩ ጠንቋዮች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ዕቃዎችን ጻድቁ እየባረኩና እየቀደሱ ለቤተክርስቲያን መሥሪያና መጠቀሚያነት ያውሉት ነበር፡፡ ይህም ገና ሳይወለዱ በአቡነ ተክለሃይማኖት ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖት "ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ይሆናል" ብሎው ትንቢት እንደተናገሩላቸው አቡነ ሳሙኤል በሰዎች፣ በባሕርና በዛፍ ላይ እያደሩ ይመለኩ የነበሩ በጣም ብዙ አጋንንትን አጠፏቸው፡፡ ጠንቋዮችንም በውስጣቸው ካደረባቸው ሰይጣን እያላቀቁ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያደርጓቸውና ያመነኩሷቸው ነበር፡፡
🌹 ጻድቁ አባታችን አባ ሳሙኤል ወንጌልን ዞረው በማስተማር ሐዋርያትን መሰሉ፣ ከዓላውያን ጋር ለመዋጋት ሰውነታቸውን ለሞት በመስጠት ሰማዕታትን መሰሉ፣ በጾም በጸሎት በስግደት በተጋድሎ ቅዱሳን ጻድቃንን መሰሉ፣ ይህን ኃላፊና ጠፊ ዓለም ንቀው በመተው ባሕታውያንን መሰሉ፣ በደልንና ኃጢአትን በማስተሠረይ ካህናትን መሰሉ፣ በጽሕናና በቅድስና መላእክትን መሰሉ እንደዚሁም ሌሎች ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ በትእምርተ መስቀል አድርገው እንደሙሴ ባሕርን ለሁለት ከፍለዋል፣ እንደ ኢያሱ በጸሎታቸው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ተጋድሎአቸውን ፈጽመው ከጌታችን ታላቅ ቃኪዳን ተቀብለው በዚህች ዕለት በሰላም ዐርፈዋል፡፡
🌹 በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ አቡነ ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያንኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ከአባታችን አቡነ ሳሙኤል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የደብረ_ዘኸኝ_መምህር_አባ_ጸቃውዐ_ድንግል፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ ካህን ነው በጥበብና በበጎ ተግሣጽም አሳድገው መለኮታዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማረው አድጎ አርባ ዓመትም በሆነው ጊዜ አባቱ ከአንድ ገዳም ውስጥ መነኰሰ ለመምህርነትም ተመርጦ በአባ ገብረ ማርያም ወንበር ላይ ተሾመ። በዚያንም ጊዜ አባቱ ለልጁ የምንኵስና ልብስ አለበሰው ስሙንም ጸቃውዐ ድንግል ብሎ ሰየመው ከዚያችም ጊዜ ጀምሮ ያለማቋረጥ በጾም በጸሎት ብዙ በመስገድም ታላቅ ተጋድሎንም ተጋደለ።
🌹 ከዚህም በኋላ አባቱ በዐረፈ ጊዜ በአባቱ ፋንታ ተሾመ መንጋዎቹንም እንደ ሐዋርያት ሥርዓት በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው። በሌሊቱም ሁሉ ከባሕር ውስጥ ቁሞ ያድራል ከባሕሩ ሲወጣ ወዙ በምድር ላይ እስከሚንጠፈጠፍ ሥግደትን ያዘወትራል ምግቡም ደረቅ እንጀራ ነው ጠጅ ወይም ጠላ አይጠጣም እግዚአብሔርም በእጁቹ ላይ ተዓምራትን አደረገ በጎዳናም ሲጓዝ ከታናሽነቱ ጀምሮ ሔዶ የማያውቅ መፃጒዕን አገኘ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ" ብሎ የተጸለየበትን ውሃ በላዩ ረጨ በመስቀልም ምልክት አማተበ በዚያን ጊዜ ዳነ።
🌹 ከዚህም ዓለም የሚለይበት ሰዓት በደረሰ ጊዜ ጥቂት ታሞ ጥምቀት 29 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጸቃውዐ ድንግል ጸሎት ይማረ በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር። ምንጭ፦ የጥቅምት 29 ስንክሳር።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፱ (29) ቀን።
🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያኑ_ጻድቃን ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽ_ግመልን_በመርፌ_ቀዳዳ አሳልፈው ሙት አስነስተው ብዙ ሕዝብ ላሳመኑበት ለተአምራት በዓላቸው፣ በምዕራብ ሐርጌ በሜኤሶ ወረዳ የሚገኘውን #ታላቁ_ገዳም_አሰቦት_ደብረ_ወገግ_ቅድስት_ሥላሴ ለመሰረቱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሳሙኤል_ዘደብረ_ወገግ ለዕረፍታቸው በዓልና ለተመሰገነና ለከበረ ለዘኸኝ መምህር #ለቅዱስ_ጸቃውዐ_ድንግል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_ታዴዎስ_ያደረጉት_ተአምር_ይህ_ነው፦ በአቡነ ታዴዎስ አላምንም የሚል ኢሳ የሚባል አንድ የእስላም ንጉሥ ተነሳ እና እንዲህ አላቸው "ስም ታዴዎስ ነው ሐዋርያው ታዴዎስ ግመል በመርፌ ቀዳዳ አስወጥቷል ይባላል አስወጣና ልመንብህ" አላቸው። ይህን ቃል ሲናገራቸው አቡነ ታዴዎስ ሳቁበት "በል ግመልና መርፌ አምጣ እኔ አሳይሃለው" ሲሉት ሠላሳ ግመል አመጣ አቡነ ታዴዎስም "በል መርፌውን በእጅህ ያዘው ቀዳዳውን ወደ ግመሊቱ አዙረህ" አሉት ወደ ግመሊቱ ቀርበው "በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አዝዝሻለሁ" ሲሏት አንገቷን በመርፌው አስገብታ ከልጇ ጋር ወጣችና ሃያ ስምንቱን መጀመሪያ የወጣችቱ ግመል እንደ ሰው እየጠራቻቸው ወጡ ይህንን ድንቅ ስራ ያየ መርዩጥም ሆነ ሰራዊቱ የደብረ ማርያም ህዝብ ሲያደንቁ።
🌹 በዚያን ጊዜ የኢሳ ልጅ ሙሳ ሳቀ "በምትሃት እንጂ በብቃት አላወጣም" ብሎ ሲጠራጠር አንዲቱ ግመል ሆዱን በእርግጫ ስትመታው ሞተ አንጀቱ ተጎለጎለ በዚያን ጊዜ ሰው ሁሉ ደነገጠ ንጉሡም ደነገጠ ወዲያ ወዲህ እየሮጠ "አባቴ ሆይ እማፀንሃለው ማረኝ እንደሙሳ አልሳቅሁም" አቡነ ታዴዎስም "መዩጥ ሆይ ከልብህ እመን ከዚህ በላይ ታያለህ ከእግዚአብሔር የሚሆንን ነገር ምንም የሚያገኝህ ነገር የለም አትፍራ ከልብህ ካመንክ የሞተው ይነሳል ስላንተ አምላኬ ያነሳዋል" በዚህ ጊዜ መዩጥ አቡነ ታዴዎስን "እንዴት ሆኖ የሞተ ሰው ይነሳል በል አንተ አስነሳው የደራ ህዝብ ያምን ዘንድ በአምላክህ" አቡነ ታዴዎስ መዩጥን "ይቅበሩት እዘዝ ነገ ያነሳዋል ከተቀበረ በኋላ ነገ ሁሉ ሰው ከዳር እስከ ዳር ወንድ ሴት ትልቅ ትንሽ ሳይባል ይሰብሰብ ይህ ሬሳ የተነሳ እንደሆነ በአምላኬ እንድታምኑ ካልተነሳ እኔን ግደለኝ ከዚህ በኋላ ቅበሩት በዚች ቀን ጠዋት ከደብረ ማርያም ያልተገኘ ክፉ ሞት ይሞታል" አለ በዚች ሌሊት አቡነ ታዴዎስ ከደብረ ማርያም ቤተ ክክርስቲያን ውስጥ ከቅድስት ሆነው በየሰዓቱ መቶ መቶ ስግደት እየሰገዱ "ከመቃብር አላዓዛርን እንዳስነሳህ ይህንንም ሙት አንሳው" መዩጥ እንዲምን ብሎ እየጸለዩ ሳሉ ከሌሊቱ 11ሰዓት ጥቅምት 29 ቀን መልአከ እግዚአብሔር ወርዶ "የሞተው ይነሳል ስለ አንተ ጸሎት ብሎ ይችን ደብረ ማርያምን አሥራት አድርጌ ሰጥቸሃለሁ በእኔም ስም ስላገኘህ ችግር በጾም በጸሎት ሃይማኖትን በማስተማር ከአጋንንት ጋር በመጋደልህ ከክፉ ሰዎች ጋር በመጋደልህ ደብረ ማርያምን የልጆችህ ርስት አድርጌ ሰጥችሀለሁ እስከ መጨረሻው ድረስ" ብሎት መልአከ እግዚአብሔር ወደ ሰማይ አረገ።
🌹 አቡነ ታዴዎስም እስከ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ሲጸልዩ አደሩ ህዝቡ ተሰብስበው ሳለ መዩጥ መጣና ከሰራዊቱ መካከል ተቀመጠ አቡነ ታዴዎስም ጠራቸው "አባቴ ሆይ ትናት እዳልከኝ አድርግ በህዝቤ መካከል የሰበሰብኋቸው ስላንተ ነውና" ሲላቸው "በል የሙቱን አባት አምጣው ወደ እኔ" ሲሉ አቀረቡላቸው አቡነ ታዴዎስም ለአባቱ መስቀላቸውን ሰጡትና እንደ "አላዓዛር ተነስ በለው ይነሳልሃል" አሉትና የአቡነ ታዴዎስን መስቀል ይዞ ተነሳ ሲለው ሙቱ ተነስቷል ከዚህም በኋላ የደራ ህዝብ በመላው አምኖ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቀው ሃይማኖትን አስተምረው 12 ቤተ ክክርስቲያን አሳነጹ። ከአባታችን አቡነ ታዴዎስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን። ምንጭ፦ የጣና ሐይቅ ደብረ ማርያም ገዳም አጭር ታሪክ ከምትላው መጸሐፍ።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_ሳሙኤል_ዘወገግ፡- ጻድቁ አቡነ ሳሙኤል እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡ የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል፡፡ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው "እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ" ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡ በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡
🌹 አቡነ ተክለሃይማኖትም በአባቱ እንድሪያስ በኩል የሥጋ ዘመዱ ሲሆኑ የመንፈስ ቅዱስም አባት ሆኑትና በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናውን "ሳሙኤል" አሉት፡፡ ትርጓሜውም "እግዚአብሔር ጸለቴን ሰማኝ" ማለት ነው፡፡ ከሕፃንነትም ጀምረው በምግባር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳድገው ለዲቁና አብቅተው በኋላም አመንኵሰውታል፡፡ የመሠረቱት ገዳም "ደብረ ወገግ" የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ አስቦን የብርሃን ውጋጋን ሲያጥለቀልቀው መላእክትም "ቦታውን ደብረ ወገግ" (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም "ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት" ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት" እንዳረገ ድርሳነ ዑራኤል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡
🌹 በቦታው ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡
🌹 ንጉሥ ዓምደ ጽዮን በክፉዎች ምክር የአባቱን ሚስት እንጀራ እናቱን በማግባቱ ምክንያት አቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው ያወገዙትን የቅዱስ ተክለሃይማኖትን ወገኖች በየአውራጃው በተናቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስንም ደሙ በምድር ላይ እስከሚንጣለል ድረስ ገርፈው ወደነበረበት ቤቱ ወሰዱት፤ ፊሊጶስም በሚሄድበት ቦታ ላይ ሳይደርስ በመንገድ ሞተ፡፡ እንድርያስ፣ አኖሬዎስና ተክለ ጽዮን ሁላቸው ከተከታዮቻቸው ጋር በሰማዕትነት አርፈው እነስድስተይ በምትባል ምድር ተቀበሩ፡፡ ጳጳሱን አቡነ ያዕቆብንም ደሙ በምድር ላይ እንደውኃ እስኪወርድ ድረስ ገርፈው ወደ ሀገሩ እንዲሰደደ አደረጉት፡፡ ከዚያም በኋላ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ ንጉሥ ዳዊት በነገሠ ጊዜ አባታችን ሳሙኤል ዘወገግን አገኘውና "መማጸኛ እንዲሆነኝ በእንድርያስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ሥራልኝ" ብሎ ለመነውና የሩፋኤልን ቤተ ክርስቲያን ሠራለት፡፡ የእንድርያስንም አጽም ከመቅደሱ ስር አኖረው፡፡ ንጉሡም
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፰ (28) ቀን።
🌹 እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ_ለሆኑት በሞት በዐረፉ ጊዜ የሥጋቸው ሥርዓተ ግንዘት በቅዱሳን መላእክት እጅ ለተከናወነው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ይምዓታ_ዘጎሕ_ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_ይምዓታ_ዘጎሕ፦ አቡነ ይምዓታ ከዘጠኙ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ እጅግ አስገራሚው ቤተ መቅደሳቸው ትግራይ ገርዓልታ ልዩ ስሙ "ጎሕ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ሰማይን እንደ ምሰሶ ደግፈው የያዙ የሚመስሉ በጣም ረጃጅም ተራሮች መካከል በአንደኛው ጫፍ ላይ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ከባሕር ወለል በላይ በ2300 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ያለበት የተራራው ርዝመት ብቻውን 300 ሜትር ነው፡፡ ቤተ መቅደሱ በር ላይ ለመድረስ በጭንቅና በፍርሃት ሆኖ ተራራውን እንደዝንጀሮ በእጅ እየቧጠጡ መውጣት ይጠይቃል፡፡
🌹 ቤተ መቅደሱ እጅግ የሚደንቀው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ ብቻ አይደለም ውስጡ ያሉት የግድግዳ ላይ ሥዕሎችም በ15 ኛው መ/ክ ዘመን የተሣሉ እጅግ ድንቅና ጥንታዊ ናቸው፡፡ ስለዚሁ የአቡነ ይምዓታ እጅግ አስደናቂ ቤተ መቅደስ ገድለ አቡነ አረጋዊ" በሞት በዐረፉ ጊዜ የሥጋቸው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ ነው የተከናወነው፡፡ ይልቁንም ቁመቱና ርዝመቱ ከታላላቅ ገደል እጅግ በጣም የሚበልጥ የድንጋይ ዓምድ ከወንዝ ማዶ ዘንበል ብሎ መጥቶ ሥጋቸውን በክብር ተቀብሎ በተራራው ጫፍ ላይ እስከዛሬም ድረስ ፈጽሞ ሳይነቃነቅና ሳይናወፅ ቀጥ ብሎ ቆሞ ይገኛል" በማለት ይገልጻል፡፡ ከአቡነ ይምአታ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
