ar
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

إظهار المزيد
2 212
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
-3230 أيام
أرشيف المشاركات
የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ሁሉም ህዝቦች ዘንድ ፈተና አለ። የኔ ኡማ ፈተና ደግሞ ገንዘብ ነው!» ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒም ሰሆህ ብለውታል @abujunaidposts
የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ሁሉም ህዝቦች ዘንድ ፈተና አለ። የኔ ኡማ ፈተና ደግሞ ገንዘብ ነው!» ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒም ሰሆህ ብለውታል @abujunaidposts

🌿ሙራቀበቱላህ! 🌿 የአላህ ፍራቻ "ተቅዋ" ን ለመላበስ እና ኢማንን ለማበልፀግ ከሚያግዙ ብዙ ነገሮች መካከል የአላህን ተቆጣጣሪነት ማሰብ እና ለምንሰራው ስራ ሁሉ አላህ እንደሚያየን ማሰብ "ሙራቀበቱላህ" በብዙ ኡለማዎች በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። አላህ ተመልካች መሆኑን በማስታወስ አላህን በራሳችን ላይ ተቆጣጣሪ ማድረግ ስንል፤ ስራን መገምገም፣ በግልፅም ይሁን በድብቅ የምንሰራዉን ሁሉ አላህ እንደሚያውቅ ማስተዋል ማለት ነው። አላህ ከፍጥረታቱ ጋር ነው፤ ለእርሱ የታዘዙትን እና እርሱን ብቻ የተገዙትን በእርዳታው ከነሱ ጋር ነው። የካዱትም ቢሆን በአላህ ቁጥጥር ውስጥ ናቸው። አላህን ባናየው እንኳ እርሱ ያየናልና ስናመልከው እንደምናየው አድርገን መሆን አለበት። ኢህሳን የምንለው የመልካም ስራ እርከን ይህ ነው። ከአላህ እይታና ቁጥጥር መራቅ አንችልም። ስለዚህም፤ ለምንናገረውና ለምንሰራው ሁሉ አላህን እንፍራ! መልካም ስራን ስንፈፅምም ፍፁም ለአላህ ብቻ ይሁን። በተለይ ከሰዎች እይታ በራቅንበት ወቅት አላህን በኛ ላይ ተቆጣጣሪ ማድረግ ተቅዋን በእጅጉ ከሚያበለፅጉ ነገሮች አንዱ ነው። አል አንደሉሲይ ልጃቸውን ለመምከር የቋጠሯቸው ስንኞች ተከታዩን መልእክት ያዘሉ ነበሩ፤ وإذا خلوت بريبة في ظلمة والنفس داعية إلى الطغيان فاستحيي من نظر الإله وقل لها إن الذي خلق الظلام يراني በጨለማ አሻሚ ቦታ ላይ ሆነህ ነብስህ ድንበር እንድትጥስ ስትገፋፋህ፤ ጌታህ ያይሀልና ሀፍረት ይሰማህ ለነብስህም በላት፤ ጨለማን የፈጠረው አምላክ ይመለከተኛል!! 🌿 በጌታህ ታገዝ... አትሳነፍ!! 🔗 ከአቡሁረይራ በተዘገበ ሀዲስ ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፤ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ : ”...احْرِصْ عَلَى مَا يَنْفَعُكَ وَاسْتَعِنْ بِاللهِ وَلَا تَعْجَزْ، وَإِنْ أَصَابَكَ شَرٌّ فَلَا تَقُلْ لَوْ أَنِّي فَعَلْتُ كَذَا وَكَذَا قُلْ قَدَّرَ اللهُ وَمَا شَاءَ اللهُ فَعَلَ، فَإِنَّ لَوْ تَفْتَحُ عَمَلَ الشَّيْطَانِ“ رَوَاهُ مُسْلِم ٌ «በሚጠቅምህ ነገር ላይ ጉጉት ይኑርህ፤ በአላህ ታገዝ፤ አትሰላች፤ መጥፎ ነገር ባጋጠመህ ጊዜ፤ ‘ይህን ነገር እንዲህ ወይም እንዲያ ባደርገው ኖሮ…’ አትበል። ነገር ግን ‘አላህ የወሰነው ሆነ፤ አላህ የፈለገውን ይሰራል’ በል። ‘እንዲህ ቢሆን ኖሮ’ የሚለው ንግግር ለሰይጣን ስራ በር ይከፍታል» ሙስሊም ዘግበዉታል አላህ ተቅዋን እና መልካም ስራን ያግራልን! وصلَّى الله على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلَّم ✍ አቡጁነይድ t.me/abujunaidposts

____________________ ** ሶስት አስገራሚ ጉዳዮች ** """"""""""""""""""""""""""""""""""""""""" ① «ሀይማኖተኛ» ሆነው ሰበካቸውን በውሸት ላይ የሚገነቡ! ሀይማኖተኛም ይሁን ሌላ፤ መቼም ሰው ነውና በግል ጉዳዮች አንዳንድ ጊዜ ውሸት ከአንደበቱ ሊያመልጠው ይችላል፤ ግድየለም! በተደጋጋሚ ሆን ብሎ መሰረት የሌለውን የሀሰት ወሬ ከመቅጠፍ አልፎ በትጋት የሚያሰራጭ «ሀይማኖተኛ» ግን እንደ አሸን ፈልቷል። በማስረጃ መርታት የተሳናቸውን አካል «ሊያርዳችሁ ነው»፣ «ሊያጠፋችሁ ነው» ሲሉ ተቀናጅተው ስሙን ያጠፋሉ። የሌላውን እምነት ተከታዮች ለማጠልሸት የውሸት ፎቶም ያቀናብራሉ። (ባሁን ዘመን ማንም ሊለየው የሚችለውን የለማጅ ፎቶሾፕ ስራ ያቀርባሉ።) ሙሰይለማህ የተባለው በታላቁ ነብያችን ዘመን ነብይነትን የሞገተው ሀሰተኛ ግለሰብ «አላህ ለኔም ያወረደልኝ አንቀፅ አለ» ብሎ ለዐምር ኢብኑ'ል‐ዓስ መነባነቡን ሲያሰማው ዐምር እነዲህ ነበር ያለው፡‐ «በአላህ እምላለሁ፤ እየዋሸህ መሆኑን እኔ እንደማውቅ አንተ በርግጥ ታውቃለህ!» የሀይማኖት አንዱ መገለጫ እውነተኝነትን ማስተማር አልነበር?! ወገን ሆይ! ሀይማኖት የእልህ መወጫ አይደለም! የርካሽ ፖለቲካ መደበቂያም አይሆንም። ————— ② ከላይ የጠቀስኳቸው ቅቤ አንጛቾች በተለያየ አጋጣሚዎች ሀሰታቸው ተጋልጦ ጭምብላቸው ሲወልቅ ያለምንም ሀፍረት መልሰው የበፊቱን ጭምብላቸውን ማጥለቃቸው! ደግሞ ስለወደፊቱ ሲተነብዩ ጊዜው ሲደርስ ቅጥፈታቸው እንደሚጋለጥ እያወቁ በድፍረት መዘላበዳቸው! ክስተቱ ካለፈም በኋላ አይናቸውን በጨው አጥበው፣ በለምዳቸውን ተጀቡነው መቆረባቸው! የእኛ ነብይ እንዲህ ብለዋል፡‐ «ሰዎች ከደረሱበት የመጀመሪያዎቹ ነብያት ንግግር አንዱ፡‐ "የማታፍር ከሆነ ያሻህን ስራ!"» ————— ③ (ከሁሉም ይበልጥ የሚደንቀው) በውሸትና በስርአት አልበኝነት የታወቀ ግለሰብን በጭፍን የሚደግፈውና ከኋላው የሚጉተለተለው መሃይም ብዛት! እንደምሳሌ፡‐ የነእንትናን ፖስት ላይክ እና ሼር የሚያደርጉትን ቁጥር ተመልከት! መቼም ተጣሪ ሁሉ ተከታይ አያጣም። በእልህና በጎጠኝነት የሚገፋ ጭፍን ተከታይነት ግን የማህበረሰብ ነቀርሳ ነው። ‐ በእኛ መፅሀፍ ላይ ከእውነተኞች ጋር እንድንሆን ታዘናል፡‐ { يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَكُونُواْ مَعَ ٱلصَّٰدِقِينَ } {እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ሁኑ} ‐ የሌሎቹን ባላወቅም የእኛ መመሪያ ከጭፍን ወገንተኝነትና ለጠላትም ይሁን ፍትህን ከማዛባት ይከለክላል፡‐ { يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ كُونُواْ قَوَّٰمِينَ لِلَّهِ شُهَدَآءَ بِٱلۡقِسۡطِۖ وَلَا يَجۡرِمَنَّكُمۡ شَنَـَٔانُ قَوۡمٍ عَلَىٰٓ أَلَّا تَعۡدِلُواْۚ ٱعۡدِلُواْ هُوَ أَقۡرَبُ لِلتَّقۡوَىٰۖ وَٱتَّقُواْ ٱللَّهَۚ إِنَّ ٱللَّهَ خَبِيرُۢ بِمَا تَعۡمَلُونَ } {እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በፍትህ መስካሪዎች ሆናችሁ ለአላህ የቆማችሁ ሁኑ! ሰዎችን መጥላት ፍትህን እንዳትተገብሩ አይገፋፋችሁ፤ ፍትህን ተግብሩ፤ እርሱ ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩ፤ አላህ ስለምትሰሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነውና} والسلام #ማህበረ_ቅዱሳን #ZemedkunBekele #እዩጩፋ #ወዘተ t.me/ustazilyas

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ @abujunaidposts

📝 ለምን ወቅፍ እናደርጋለን? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ T.me/abujunaidposts

sticker1 (26073).webp0.84 KB

ኢድ ሙባረክ ለሁሉም ሙስሊም ወንድም እህቶቼ አላህ የተባረከ ዒድ ያድርግልን تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمل @abujunaidposts

ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://www.facebook.com/682494683/posts/10158937378539684/ t.me/abujunaidposts @abujunaidposts

አላሁ አክበር አላሁ አክበር አላሁ አክበር @abujunaidposts
አላሁ አክበር አላሁ አክበር አላሁ አክበር @abujunaidposts

ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወር ከገባበት የምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም፤ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተከታዩን የኡሙሰለማ ሀዲስ መሰረት ያደረገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النبي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لفظ : "إذا دخلت العشر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن شعره وأظفاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لفظ : " فلا يأخذ من شعره وأظفاره شيئاً حتى يضحي ". وفي لفظ : "فلا يمس من شعره ولا بشره شيئاً ". ከኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «የዙልሂጃ ወርን ጨረቃ ካያችሁና ከናንተ መካከል አንዱ ኡድሂያ ለማረድን ካቀደ፤ ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩና ከጥፍሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። እንደዚሁ፤ «ከሰውነቱ ቆዳ ወይም ከፀጉሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎች ጋር የሚያመሳስልበት እና የተወሰኑ የኢህራም ክልከላዎችን ከነሱ ጋር የሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጸጉርንና ጥፍርን ከመቁረጥ የሚከለከለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ የሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባል፤ በወኪልነት ለሌላ ስው የሚያርድን ሰው አይጨምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም ማካካሻ ከፋራም የለበትም። አንዳንዶች እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማረዱን መተው የለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን የቆረጠ ሰው ምንም ወንጀል የለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ችግር የለውም። ለምሳሌ የተጎዳን የሰውነት ቆዳ ለማከም ወይም የተሰበረ ጥፍሩን ለማስተካከል መቁረጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጨማሪ ነጥቦች 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፤ {ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። 7- የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ ወይም የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። 10- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቦታ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts