ar
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

الذهاؚ إلى القناة على Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

إ؞هار المزيد
2 174
الم؎تركون
لا توجد ؚيانات24 ساعات
-27 أيام
-1930 أيام
أر؎يف الم؎اركات
ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፀ «ሁሉም ህዝቊቜ ዘንድ ፈተና አለ። ዹኔ ኡማ ፈተና ደግሞ ገንዘብ ነው!» ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒም ሰሆህ ብለውታል @abujunaidposts
ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፀ «ሁሉም ህዝቊቜ ዘንድ ፈተና አለ። ዹኔ ኡማ ፈተና ደግሞ ገንዘብ ነው!» ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒም ሰሆህ ብለውታል @abujunaidposts

🌿ሙራቀበቱላህ! 🌿 ዹአላህ ፍራቻ "ተቅዋ" ን ለመላበስ እና ኢማንን ለማበልፀግ ኚሚያግዙ ብዙ ነገሮቜ መካኚል ዹአላህን ተቆጣጣሪነት ማሰብ እና ለምንሰራው ስራ ሁሉ አላህ እንደሚያዚን ማሰብ "ሙራቀበቱላህ" በብዙ ኡለማዎቜ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። አላህ ተመልካቜ መሆኑን በማስታወስ አላህን በራሳቜን ላይ ተቆጣጣሪ ማድሚግ ስንልፀ ስራን መገምገም፣ በግልፅም ይሁን በድብቅ ዚምንሰራዉን ሁሉ አላህ እንደሚያውቅ ማስተዋል ማለት ነው። አላህ ኚፍጥሚታቱ ጋር ነውፀ ለእርሱ ዚታዘዙትን እና እርሱን ብቻ ዚተገዙትን በእርዳታው ኚነሱ ጋር ነው። ዚካዱትም ቢሆን በአላህ ቁጥጥር ውስጥ ና቞ው። አላህን ባናዚው እንኳ እርሱ ያዚናልና ስናመልኚው እንደምናዚው አድርገን መሆን አለበት። ኢህሳን ዹምንለው ዚመልካም ስራ እርኚን ይህ ነው። ኹአላህ እይታና ቁጥጥር መራቅ አንቜልም። ስለዚህምፀ ለምንናገሹውና ለምንሰራው ሁሉ አላህን እንፍራ! መልካም ስራን ስንፈፅምም ፍፁም ለአላህ ብቻ ይሁን። በተለይ ኚሰዎቜ እይታ በራቅንበት ወቅት አላህን በኛ ላይ ተቆጣጣሪ ማድሚግ ተቅዋን በእጅጉ ኚሚያበለፅጉ ነገሮቜ አንዱ ነው። አል አንደሉሲይ ልጃቾውን ለመምኹር ዚቋጠሯ቞ው ስንኞቜ ተኚታዩን መልእክት ያዘሉ ነበሩፀ وإذا خلوت ؚريؚة في ؞لمة والنفس داعية إلى الطغيان فاستحيي من ن؞ر الإله وقل لها إن الذي خلق ال؞لام يراني በጹለማ አሻሚ ቊታ ላይ ሆነህ ነብስህ ድንበር እንድትጥስ ስትገፋፋህፀ ጌታህ ያይሀልና ሀፍሚት ይሰማህ ለነብስህም በላትፀ ጹለማን ዹፈጠሹው አምላክ ይመለኹተኛል!! 🌿 በጌታህ ታገዝ... አትሳነፍ!! 🔗 ኚአቡሁሚይራ በተዘገበ ሀዲስ ነብያቜን ï·º እንዲህ ብለዋልፀ عَنْ أَؚِي هُرَيْرَةَ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ ï·º : ”...احْرِصْ عَلَى مَا يَنْفَعُكَ وَاسْتَعِنْ ؚِاللهِ وَلَا تَعْجَزْ، وَإِنْ أَصَاَؚكَ ؎َرٌّ فَلَا تَقُلْ لَوْ أَنِّي فَعَلْتُ كَذَا وَكَذَا قُلْ قَدَّرَ اللهُ وَمَا ؎َاءَ اللهُ فَعَلَ، فَإِنَّ لَوْ تَفْتَحُ عَمَلَ ال؎َّيْطَانِ“ رَوَاهُ مُسْلِم ٌ «በሚጠቅምህ ነገር ላይ ጉጉት ይኑርህፀ በአላህ ታገዝፀ አትሰላቜፀ መጥፎ ነገር ባጋጠመህ ጊዜፀ ‘ይህን ነገር እንዲህ ወይም እንዲያ ባደርገው ኖሮ ’ አትበል። ነገር ግን ‘አላህ ዹወሰነው ሆነፀ አላህ ዹፈለገውን ይሰራል’ በል። ‘እንዲህ ቢሆን ኖሮ’ ዹሚለው ንግግር ለሰይጣን ስራ በር ይኚፍታል» ሙስሊም ዘግበዉታል አላህ ተቅዋን እና መልካም ስራን ያግራልን! وصلَّى الله على نؚينا محمد وعلى آله وصحؚه وسلَّم ✍ አቡጁነይድ t.me/abujunaidposts

____________________ ** ሶስት አስገራሚ ጉዳዮቜ ** """"""""""""""""""""""""""""""""""""""""" ① «ሀይማኖተኛ» ሆነው ሰበካ቞ውን በውሞት ላይ ዚሚገነቡ! ሀይማኖተኛም ይሁን ሌላፀ መቌም ሰው ነውና በግል ጉዳዮቜ አንዳንድ ጊዜ ውሞት ኚአንደበቱ ሊያመልጠው ይቜላልፀ ግድዚለም! በተደጋጋሚ ሆን ብሎ መሰሚት ዹሌለውን ዚሀሰት ወሬ ኹመቅጠፍ አልፎ በትጋት ዚሚያሰራጭ «ሀይማኖተኛ» ግን እንደ አሾን ፈልቷል። በማስሚጃ መርታት ዚተሳና቞ውን አካል «ሊያርዳቜሁ ነው»፣ «ሊያጠፋቜሁ ነው» ሲሉ ተቀናጅተው ስሙን ያጠፋሉ። ዹሌላውን እምነት ተኚታዮቜ ለማጠልሞት ዚውሞት ፎቶም ያቀናብራሉ። (ባሁን ዘመን ማንም ሊለዹው ዚሚቜለውን ዹለማጅ ፎቶሟፕ ስራ ያቀርባሉ።) ሙሰይለማህ ዚተባለው በታላቁ ነብያቜን ዘመን ነብይነትን ዹሞገተው ሀሰተኛ ግለሰብ «አላህ ለኔም ያወሚደልኝ አንቀፅ አለ» ብሎ ለዐምር ኢብኑ'ል‐ዓስ መነባነቡን ሲያሰማው ዐምር እነዲህ ነበር ያለው፡‐ «በአላህ እምላለሁፀ እዚዋሞህ መሆኑን እኔ እንደማውቅ አንተ በርግጥ ታውቃለህ!» ዚሀይማኖት አንዱ መገለጫ እውነተኝነትን ማስተማር አልነበር?! ወገን ሆይ! ሀይማኖት ዚእልህ መወጫ አይደለም! ዚርካሜ ፖለቲካ መደበቂያም አይሆንም። ————— ② ኹላይ ዚጠቀስኳ቞ው ቅቀ አንጛ቟ቜ በተለያዚ አጋጣሚዎቜ ሀሰታ቞ው ተጋልጩ ጭምብላ቞ው ሲወልቅ ያለምንም ሀፍሚት መልሰው ዚበፊቱን ጭምብላ቞ውን ማጥለቃ቞ው! ደግሞ ስለወደፊቱ ሲተነብዩ ጊዜው ሲደርስ ቅጥፈታ቞ው እንደሚጋለጥ እያወቁ በድፍሚት መዘላበዳ቞ው! ክስተቱ ካለፈም በኋላ አይናቾውን በጹው አጥበው፣ በለምዳ቞ውን ተጀቡነው መቆሚባ቞ው! ዚእኛ ነብይ እንዲህ ብለዋል፡‐ «ሰዎቜ ኚደሚሱበት ዚመጀመሪያዎቹ ነብያት ንግግር አንዱ፡‐ "ዚማታፍር ኹሆነ ያሻህን ስራ!"» ————— ③ (ኹሁሉም ይበልጥ ዹሚደንቀው) በውሞትና በስርአት አልበኝነት ዚታወቀ ግለሰብን በጭፍን ዹሚደግፈውና ኹኋላው ዹሚጉተለተለው መሃይም ብዛት! እንደምሳሌ፡‐ ዚነእንትናን ፖስት ላይክ እና ሌር ዚሚያደርጉትን ቁጥር ተመልኚት! መቌም ተጣሪ ሁሉ ተኚታይ አያጣም። በእልህና በጎጠኝነት ዹሚገፋ ጭፍን ተኚታይነት ግን ዚማህበሚሰብ ነቀርሳ ነው። ‐ በእኛ መፅሀፍ ላይ ኚእውነተኞቜ ጋር እንድንሆን ታዘናል፡‐ { يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَكُونُواْ مَعَ ٱلصَّٰدِقِينَ } {እናንተ ያመናቜሁ ሆይ! አላህን ፍሩፀ ኚእውነተኞቹም ጋር ሁኑ} ‐ ዚሌሎቹን ባላወቅም ዚእኛ መመሪያ ኹጭፍን ወገንተኝነትና ለጠላትም ይሁን ፍትህን ኚማዛባት ይኚለክላል፡‐ { يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ كُونُواْ قَوَّٰمِينَ لِلَّهِ ؎ُهَدَآءَ ؚِٱلۡقِسۡطِۖ وَلَا يَجۡرِمَنَّكُمۡ ؎َنَـَٔانُ قَوۡمٍ عَلَىٰٓ أَلَّا تَعۡدِلُواْۚ ٱعۡدِلُواْ هُوَ أَقۡرَُؚ لِلتَّقۡوَىٰۖ وَٱتَّقُواْ ٱللَّهَۚ إِنَّ ٱللَّهَ خَؚِيرُۢ ؚِمَا تَعۡمَلُونَ } {እናንተ ያመናቜሁ ሆይ! በፍትህ መስካሪዎቜ ሆናቜሁ ለአላህ ዚቆማቜሁ ሁኑ! ሰዎቜን መጥላት ፍትህን እንዳትተገብሩ አይገፋፋቜሁፀ ፍትህን ተግብሩፀ እርሱ ለአላህ ፍራቻ በጣም ዹቀሹበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩፀ አላህ ስለምትሰሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነውና} والسلام #ማህበሹ_ቅዱሳን #ZemedkunBekele #እዩጩፋ #ወዘተ t.me/ustazilyas

🔖 ተውሒድ እና ዹሐጅ ፍሬዎቜ 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ @abujunaidposts

📝 ለምን ወቅፍ እናደርጋለን? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ T.me/abujunaidposts

ኢድ ሙባሚክ ለሁሉም ሙስሊም ወንድም እህቶቌ አላህ ዚተባሚኚ ዒድ ያድርግልን تقؚل الله منا ومنكم صالح الأعمل @abujunaidposts

ስለ ዓሹፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቊቜ [1] በኢድ ዋዜማው ዹዓሹፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው ዚሚዘክሩ ሀዲሶቜ ሀጅ ላይ ዹሌሉ ሰዎቜንም ይመለኚታሉን?? ዹአላህ መልእክተኛ «ኚዱዓዎቜ ሁሉ በላጩ (ዚኢድ ዋዜማ) ዹአሹፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታ቞ውን ቲርሚዚይ ኚአብዱላህ ኢብኑ ኡመር ዚዘገቡ ሲሆንፀ ሌሎቜ ተመሳይ ይዘት ያላ቞ው ሀዲሶቜም ይገኛሉ። ታዲያ ዹዓሹፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን ዚሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው ዹዓሹፋ ምድር ዹተገኘ ሰው ዹጊዜንም ዚቊታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት ዹቀሹበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው ዚኡለማዎቜ አቋም መሰሚትፀ እነዚህ ኹአሹፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ ዚዱአ ተቀባይነትን ዚተመለኚቱ ሀዲሶቜ በማንኛውም ቊታ ዹሚገኙ ሙስሊሞቜን ይመለኚታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ ዹሌሉ ሰዎቜም በዱዓ ሊበሚቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሞይኜ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት ዚሚባሉ በሀዲስ ዹተላለፉ ዱአዎቜን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎቜ መሆኑን ተጠይቀው ተኚተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻቜን እንደገለፅነውፀ ይህ ለሁጃጆቜንም ይሁን ሌሎቜን ዹተመለኹተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎቜ ይበልጥ ዚተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆቜ በዚህ እለት በዓሹፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ኚሌሎቜ በበለጠ ዱዓ቞ው ተቀባይነት ለማግኘት ዹቀሹበ ነው። ስለዚህም ዹዓሹፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ ዹሌሉ ሰዎቜ እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድሚግ ጊዜያ቞ውን ያሳልፋሉፀ ሁጃጆቜንም በኢባዳ ይካፈሏ቞ዋል ማለት ነው።» ኚሞይኹ ድሚገፅ ዹተወሰደ ዚድምፅ ፈትዋ [2] በዓሹፋ እለት ሁጃጆቜ በአሹፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለኚተፀ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎቜ እንደፈፀሙት ዹተሹጋገጠ ነው። ኚነሱም መካኚል ኢብኑ አባስ ይገኙበታልፀ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግሚዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ኚቢድአ ዚመደቡትም አሉ። ዚኡለማዎቻቜንን ማብራሪያዎቜ ስንፈትሜ ተኚታዮቹ ድምዳሜዎቜ ላይ ያደርሱናልፀ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ቜግር ዚለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ ዚኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ ዹሚወገዝ ተግባር አይሆንም። ዹፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ኚምድሚ አሹፋ ውጭ ባሉ ዚዚሀገሩና ዹዹኹማው መስጂዶቜ መሰባሰብን ዹተመለኹተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድሚግ አይፈቀድም። አላህ ዹአሹፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመሚጠው በዚሀገሩ አንዳንድ ቊታዎቜን፣ መስጅዶቜንና ቀብሮቜን በመምሚጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ ዚነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኞትና ሱና ያልሆኑ ዚጋራ አምልኮዎቜ ኚታኚሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞቜና መንዙማዎቜን ለዚህ መለያ ማድሚግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቊቜ በዝርዝር ለመሚዳት ዚሚያስቜሉ ማብራሪያዎቜን ኚኡለማዎቜ ድርሳናት እንደሚኚተለው እናያለን። ቀሪዉን ዹፅሁፍ ክፍል ተኚታዩን ሊንክ በመኹተል ያንብቡት https://www.facebook.com/682494683/posts/10158937378539684/ t.me/abujunaidposts @abujunaidposts

አላሁ አክበር አላሁ አክበር አላሁ አክበር @abujunaidposts
አላሁ አክበር አላሁ አክበር አላሁ አክበር @abujunaidposts

ኡድሂያ ለማሚድ ካቀዱ ኚወዲሁ ጥፍርና ጾጉርዎን ኚመቁሚጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ ዚማያደርግ ኹሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማሚድ ካሰበ ዹዙልሂጃ ወር ኚገባበት ዚምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጞጉሩን አይቆርጥምፀ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተኚታዩን ዚኡሙሰለማ ሀዲስ መሰሚት ያደሚገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النؚي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لف؞ : "إذا دخلت الع؎ر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن ؎عره وأ؞فاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لف؞ : " فلا يأخذ من ؎عره وأ؞فاره ؎ي؊اً حتى يضحي ". وفي لف؞ : "فلا يمس من ؎عره ولا ؚ؎ره ؎ي؊اً ". ኚኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ ዹአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋልፀ «ዚዙልሂጃ ወርን ጹሹቃ ካያቜሁና ኹናንተ መካኚል አንዱ ኡድሂያ ለማሚድን ካቀደፀ ፀጉሩንና ጥፍሩን ኚመቁሚጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድሚስ ኚፀጉሩና ኚጥፍሩ ምንንም አይቁሚጥ» ብለዋል። እንደዚሁፀ «ኚሰውነቱ ቆዳ ወይም ኚፀጉሩ ምንንም አይቁሚጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎቜ ጋር ዚሚያመሳስልበት እና ዹተወሰኑ ዚኢህራም ክልኚላዎቜን ኚነሱ ጋር ዚሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጾጉርንና ጥፍርን ኚመቁሚጥ ዹሚኹለኹለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ ዚሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ ዹሚመለኹተው ዚሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባልፀ በወኪልነት ለሌላ ስው ዚሚያርድን ሰው አይጚምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጞጉሩን ዹቆሹጠ ወንጀል ፈጜሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋልፀ ኡድሂያው ግን አይበላሜም ማካካሻ ኚፋራም ዚለበትም። አንዳንዶቜ እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማሚዱን መተው ዚለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን ዹቆሹጠ ሰው ምንም ወንጀል ዚለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ቜግር ዚለውም። ለምሳሌ ዚተጎዳን ዚሰውነት ቆዳ ለማኹም ወይም ዹተሰበሹ ጥፍሩን ለማስተካኚል መቁሚጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጚማሪ ነጥቊቜ 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ኚተወደዱ ተግባሮቜ መካኚል ኡድሂያን በማሚድ ወደ አላህ መቃሚብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ኚጠነኚሩ ዚነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎቜ መካኚል ነው። ኡድሂያ ዚነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ኚማድሚግ በተጚማሪ ለድሆቜ እና ቜግሚኞቜ መድሚስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለኹተ አላህ ኹኛ ዹሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጜ ማድሚጋቜንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏልፀ {ﻟَﻊ ﻳَﻚَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺀُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻊ ﻳَﻚَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻚﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺚَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺞِّﺮِ اﻟْﻀُﺀْﺎِﻚِﻎﻊَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጜሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ኚእናንተ ዹሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራቜሁ ላይ ልታኚብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎቜንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ ዚሚታሚደው ኚዒድ ሰላት በኋላ ነው። ዹአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ኚኢድ ሰላት በፊት ያሚደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው ዚኡለማዎቜ አቋም መሰሚት ዚዒድ ሰላት ኚተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ዚሶስተኛው ቀን ጾሀይ እስክትጠልቅ ድሚስ ኡድሂያን ማሚድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሎት ግመል፣ ዚቀንድ ኚብቶቜ፣ በግና ፍዹል ለኡድሂያ ይታሚዱሉ። 7- ዹአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንኚን ያለባ቞ውን እንስሳት እንዳናርድ ኚልክለዋል። አንድ አይኑ ዚታወሚ፣ ስብራት ያለበት፣ ዚኚሳና ዹደኹመ ወይም ዚታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማሚድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቀተሰቊቹ አስቊ ሊያርድ ይቜላል። 10- ዚኡድሂያውን ስጋ፣ ለቀት፣ ለስጊታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቊታ መኹፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቊታዎቜ ይኹፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts