ar
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

الذهاب إلى القناة على Telegram
805
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
“የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤” — ኤፌሶን 5፥9-10

#ምዝገባ #ተጀመረ ሞጆ ሱባኤ ሴንተር ከ ነሐሴ 17 እስከ 20 የአዲስ ዓመት ልዩ ዝግጅት ሱባኤ “እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ።” — ኢሳይያስ 43፥19 #የሚኖሩን #ፕሮግራሞች ቅዳሴ : የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት : በቃሉ ውይይት : ዝማሬ (አምልኮ) የቅዱስ ቁርባን ስግደት (አዶሬሽን) : ንስሐ: የግል የፀጥታ ግዜ ይኖረናል። ቀድመው ለሚመዘገቡ ከአዲስ አበባ ለሚነሱ 22 ሰዎች የደርሶ መልስ ትራንስፖርት ማህበሩ ይሸፍናል። በሴንተሩ ለሚኖር ቆይታ ሙሉ ወጪ ዶርም 1650 ብር አዲሱ ፎቅ ላይ መጠቀም ለሚፈልጉ 2250 ይሆናል። 0911958019

ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሳምንታዊው መደበኛ የእሁድ ፕሮግራማችን (በ16/11/15) በፊሶን የመዝሙር ኮንሰርት ምክንያት የማይካሄድ በመሆኑ ሁላችንም ኮንሰርቱ ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።

ኢሳይያስ 43 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ የፊተኛውን ነገር አታስተውሉ፥ የጥንቱንም ነገር አታስቡ። ¹⁹ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ። ²⁰-²¹ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል። #ሰላም ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ? ከነገ ሰኞ ጀምሮ ለቀጣዮቹ #21 ቀናት የፆም ፀሎት ፕሮግራም ይኖረናል። ሁላችሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ እንድትሳተፉ አደራ እንላለን። በድካም ውስጥ ላለን ሁሉ ልዩ የሆነ ጉብኝትና ኃይል የምንቀበልበት ልዩ የሆነ ግዜ ይኖረናል። ቦታ ቅዱስ ሚካኤል ቻፕል ሰዓት ከ 11 እሰከ 1:30

ኢሳይያስ 43 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ የፊተኛውን ነገር አታስተውሉ፥ የጥንቱንም ነገር አታስቡ። ¹⁹ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ። ²⁰-²¹ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል። #ሰላም ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ? ከነገ ሰኞ ጀምሮ ለቀጣዮቹ #21 ቀናት የፆም ፀሎት ፕሮግራም ይኖረናል። ሁላችሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ እንድትሳተፉ አደራ እንላለን። በድካም ውስጥ ላለን ሁሉ ልዩ የሆነ ጉብኝትና ኃይል የምንቀበልበት ልዩ የሆነ ግዜ ይኖረናል። ቦታ ቅዱስ ሚካኤል ቻፕል ሰዓት ከ 11 እሰከ 1:30

photo content

photo content

photo content

ኑ እንስገድለት በሚል ርዕስ ነገ እሁድ መጋቢት 17 ከቀኑ 10 ሰአት ላይ በቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ በሚዘጋጀው ልዩ የቅዱስ ቁርባን ስግደት ምክንያት የእሁድ መደበኛ ኘሮግራማችን ስለማይኖር በቦታው ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ስንል እናሳስባለን።

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

“ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ንስሐ ግቡ ከጣዖቶቻችሁም ተመለሱ፥ ፊታችሁንም ከርኵሰታችሁ ሁሉ መልሱ።” — ሕዝቅኤል 14፥6 በቀጣይ እሁድ በሚኖረን የንስሐ እና የዕርም ልዩ የፀሎት ፕሮግራም ሁላችንም በንስሐ መንፈስ ተዘጋጅተን ራሳችንን በመመርመር ንስሐ ገብተን እንድንመጣ አደራ እንላለን።

ንስሐ እና ዕርም “ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።”   — ምሳሌ 28፥13 ብዙ ሰው መለወጥ ማደግ መቀየር ይፈልጋል። ለውጥ ለምንፈልግ ሰዎች ትልቅ ትኩረት በመስጠት ማወቅ የሚገባን ነገር በመንፈሳዊ ሕይወት እውነተኛ ለውጥ ለማምጣት ቀዳሚው ነገር እራስን በመመርመር ለንስሐ የተዘጋጀ ልብ ሲኖረን ነው። እግዚአብሔርን በማያስከብር ሕይወት ውስጥ እየኖርን ልባችንን የሚወቅስ ሐጢአት ውስጥ ሆነን ሳለ እግዚአብሔር ይወድሃል ይሆንልሃል ይሳካልሀል በሚሉ አይነት ዘመናዊ በሚመስሉ ስብከቶች በሐጢአታችን ተወቅሰን ንስሐ እንዳንገባ እያደረገን ካለን ይህ ትልቅ የለውጥ እንቅፍት አንደሆነ ልንረዳ ይገባል።  በንስሐ መመለስ የግድ ነው ። የንስሐ ሕይወት ካለን የለውጥ ሕይወት ይኖረናል። ልባችንን በመፈተሽ ንስሐ በመግባት መንፈሳዊ ሕይወታችንን ማስቀጠል እንችላለን። ኃጢአት እንደፈፀምን ልናውቅ እንችላለን ነገር ግን ስለዚያ ምንም አናደርግም ይሆናል። ነገር ግን ኃጢአታችንን በእርሱ ፊት መቀበል ብቻ ሳይሆን ከኃጢአታችን በመመለስ እና ለእርሱ ለመታዘዝ በመሻት ኃጢአታችንን በኑዛዜ እና ንስሐ በመግባት ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ማምጣት አለብን። ከመፅሐፍ ቅዱስ ታላላቅ የተስፋ ቃሎች አንዱ 1ኛ ዮሐንስ 1:9 ነው። “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።”— 1ኛ ዮሐንስ 1፥9 ነብዩ ኢሳያስ የንስሐ አስፈላጊነት ያስረዳናል። “ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።” — ኢሳይያስ 55፥7

ኑ እንስገድለት በሚል ርዕስ እሁድ የካቲት 19 ከቀኑ 10 ሰአት ላይ በቀበና ኪዳነምህርት ቤ/ክ በሚዘጋጀው ልዩ የቅዱስ ቁርባን ስግደት ምክንያት የእሁድ መደበኛ ኘሮግራማችን እንደማይኖርና በዚሁ ቀን በቦታው ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ስንል እናሳስባለን።

photo content

#የ_21_ቀን_ፆም_ፀሎት_ልዩ_ፕሮግራም መንፈሳዊ መነቃቃት ለብዙ ክርስቲያኖች ከሁሉም የላቀ አስፈላጊ ነገር ነው። ዛሬ እንዴት እናገኘዋለን? በራሳችን ሕይወትም ሆነ በሌሎች ሰዎች እነኚህ የመነቃቂያ መንገዶች ምን ምን ናቸው። መንፈሳዊ መነቃቃት ወይም መታደስ ማለት ያለንን ነገር እንደገና ማስነሳት ማነቃቃት ያለንን ነገር በአዲስ መልኩ ትኩረት በመስጠት እንደገና ማሰራት ማስቀጠል ወይም ደግሞ የሆነ ሕይወታችን ላይ ደክሞ የታየን ነገር በአዲስ መልኩ ማሰራት ማስጀመር ብለን ልንገልጠው እንችላለን። በፀሎት ደክመን ከሆነ እንደገና ወደ ፀሎት ሕይወት ለመመለስ ወደ እግዚአብሔር ፀጋዎች የምንቀርብበት በመንፈሳዊ ሕይወት ቀዝቅዘን ከሆነ በመንፈሳዊ ሕብረት ውስጥ ለመሳተፍ ሞራል አጥተን ከሆነ ያንን ኃይል እንደገና የምንቀበልበት። ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ሕብረት አቋርጠን ከሆነ ከቃሉ ጋር ሕብረታችንን የምናስቀጥልበት። በመንፈሳዊ ድካም የተነሳ በስጋ ስራ እየተፈተንን ከሆነ በኃይሉ ነፃ የምንወጣበት። “እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።”   — ኢሳይያስ 40:31 ሰኞ ታህሳስ 3 ይጀምራል ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት እስከ ቀኑ 9:00 ሰዓት ቦታ ዶንቦስኮ ቤተ ፀሎት የምትችሉ ሁሉ በዚህ ፆም ፀሎት ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል። ታህሳስ 3 ርዕስ “በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።” — 2 ዜና 7፥14 እንዴት ፆም ፀሎት ማድረግ አለብን? የፆም ፀሎት ፍሬዎች ምንድን ናቸው?

photo content