የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹
@Tewahdo27 ✞ በየጊዜው አዳዲስ መንፈሳዊ † ➢ ፅሁፎች ➢ መዝሙሮች ➢ ኦርቶዶክሳዊ መልእክቶች ➢ መንፈሳዊ ነገሮችን ሁሉንም ለማግኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞ ለአስተያየቶ @Tewahdo27 ይጠቀሙ ➢ ሁሉም እንዲያነበው SHARE ያርጉ ! እናመሰግናለን !
إظهار المزيد3 167
المشتركون
-124 ساعات
-77 أيام
-6930 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Repost from የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹
ወር በገባ በ...➍ ...
ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው።
ጥበቃው አይለየን ወቶ ከመቅረት ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን።🙏❤
@ortodox_27
Repost from Orthodox picture ✝
Photo unavailableShow in Telegram
ባታለብሰኝ ኖሮ ነውሬን ሸፍነህ
ባታቆመኝ ኖሮ በደሌን ከድነህ
በጠፋ ነበር ስም አጠራሬ
ድካሜ ብዙ ነው እንደራስ ፀጉሬ ❤️🙏🏽
#Share
💚 @orthodox_photo💚
💛 @orthodox_photo💛
❤️ @orthodox_photo❤️
إظهار الكل...
Repost from የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹
🕰🔔
6:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@ortodox_27
Photo unavailableShow in Telegram
የሰንበትን ቀን ትቀድሳት ዘንድ አስብ።
ዘፀአት-20:8
💐እንዴት አደራችሁ💐
@Mezmure_tewahdo
ሰኔ 2/2016 #መጥምቀ_ዮሐንስ
"በእዉነት #ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል"
👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት ሰኔ ሁለት የመጥምቁ #ቅዱስ_ዮሐንስ ሥጋ የቀናተኛው ኤልያስ ደቀ መዝሙር ከሆነው #ከነቢዩ_ኤልሳዕ ሥጋ ጋር በአንድነት ተገኘ
👉ከሀዲው ንጉሥ ዑልያኖስ የጥጦስ ልጅ አስባስያኖስ ከአፈረሰው በኋላ በዘመኑ በኢየሩሳሌም የአይሁድ ምኵራባቸውን ሊሠራ በወደደ ጊዜ እርሱ በቅዱስ ወንጌል ደንጊያ በደንጊያ ላይ ተቀምጦ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም የተባለውን #የእግዚአብሔርን ቃል ሊሽር ፈልጎ መሥራት በጀመረ ጊዜ ሦስት ጊዜ ፈረሰበት
👉አይሁድም እንዲህ አሉት የደጋግ ክርስቲያኖች ዐፅሞቻቸው በዚህ ቦታ ስለሚኖሩ ከዚህ ካላወጣሃቸውና ካላቃጠልኻቸው በዚህ ቦታ ምኵራብ አይሠራም በዚያንም ጊዜ #የቅዱሳንን ዐፅሞቻቸውን አውጥተው በእሳት እንዲአቃጥሉት አዘዘ
👉በአፈለሱም ጊዜ የመጥምቁ #ቅዱስ_ዮሐንስንና የነቢዩ #ኤልሳዕን ሥጋቸውን አግኝተው በእሳት ሊአቃጥሉ ፈለጉ ምእመናንም መጥተው ለወታደሮች ብዙ ገንዘብ ሰጡ ንጉሡም ሰምቶ እንዳያጠፋቸው በዚያች አገር እንዳያስቀሩ ከአማሏቸው በኋላ #የቅዱሳንን ሥጋ ወሰዱ
👉የዑልያኖስም ዜናው እንዲህ ሆነ የጳጳሳት አለቆች ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በአሠራቸው ጊዜ እነርሱ #በቅዱስ_መርቆሬዎስ ሥዕል ዘንድ እያለቀሱ ጸለዩ የክብር ባለቤት የሆነ የጌታችንን የከበረ ስሙን ሰድቧልና ያን ጊዜ #እግዚአብሔር ቅዱስ መርቆሬዎስን በአካለ ነፍስ ላከው ዑልያኖስንም በጦር ወጋው ከደሙም ዘግኖ #ኢየሱስ የሰጠኸኝን ነፍስ ተቀበል እያለ ወደ አየር ረጨ ወዲያውኑም በክፉ አሟሟት ሞተ
👉የከበሩ #የዮሐንስንና_የኤልሳዕን ሥጋ ግን እሊያ ሰዎች በእስክንድርያ ከተማ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ አባ አትናቴዎስ አደረሱ እርሱም በእርሳቸው ታላቅ ደስታ ደስ አለው ቤተ ክርስቲያንም እስኪሠራላቸው ድረስ በርሱ ዘንድ አኖራቸው
👉በአንዲት ዕለትም አባ አትናቴዎስ በአባቶቹ ቦታዎች ላይ ስለ ጸሐፊው ቴዎፍሎስም አብሮት ሳለ #እግዚአብሔር መልካም ዘመን ቢሰጠኝ ሥጋቸውን በውስጧ አኖር ዘንድ ለቅዱሳን #መጥምቁ_ዮሐንስና_ለነቢዩ_ኤልሳዕ በስማቸው በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እሠራለሁ አለ ቴዎፍሎስም ሰማው
👉አባ ቴዎፍሎስም በተሾመ ጊዜ አባ አትናቴዎስ የተናገረውን ያንን ቃል አስቦ ቤተክርስቲያን ሠራ ከርሱ ጋራም ብዙዎች ካህናትንና የክርስቲያን ወገኖችን ይዞ የቅዱሳን የመጥምቁ #ዮሐንስና_የነቢዩ_ኤልሳዕ ሥጋቸው ወዳለበት ሔደ በታላቅ ክብርም ተሸክመው አምጥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገቡ
👉ሥጋቸውንም ይዘው በሚጓዙበት ጊዜ በጐዳናቸው አቅራቢያ ቤት ካለበት ቦታ ደረሱ በውስጡም በምጥ ተይዛ አራት ቀናት እየጮኸች ለሞት የተቃረበች ሴት ነበረች እርሷም አረማዊት ነበረች #በቅዱሳኑም_ሥጋ ዘንድ ካህናቱ የሚያመሰግኑትን ሰምታ በቤቷ መስኮት ተመለከተች ይህ ምንድን ነው ብላ ጠየቀች
👉የቅዱሳን #የመጥምቁ_ዮሐንስና የነቢዩ ኤልሳዕ ሥጋቸው ነው አሏት እርሷም ከዚህ ሥቃይ ከዳንኩ ክርስቲያን እሆናለሁ አለች ገና ቃሏ ከአፉዋ ሳይፈጸም ያን ጊዜ መልካም ሕፃን ወለደች ስሙንም #ዮሐንስ ብላ ጠራችው ከዚህም በኋላ ከቤተሰቦቿ ሁሉ ጋራ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀች።
👉የቅዱሳኑንም ሥጋቸውን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖሩት ከእርሳቸውም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ በቅዳሴ ቤተ ክርስቲያኑም ጊዜ ከሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ ጋራ ብዙዎች ሰዎች #ቅዱሳን_መጥምቁ_ዮሐንስንና_ነቢዩ_ኤልሳዕን ሲዞሩ አዩአቸው በቀድሞ መልካቸው ያውቋቸዋልና የመጥምቁ ዮሐንስ መልክ ሁለመናው ፀጉር ሲሆን ኤልሳዕም ቁመቱ ረጅም ራሱ በራ ነበር
👉ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሱ #አባ_መቃርስ በሰማዕትነት በሞተ ጊዜ ሥጋውን #ከቅዱሳን_ዮሐንስና_ኤልሳዕ ሥጋ ጋራ አደረጉ #የነብዪ_ኤልሣና_የመጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ ምልጃና ፀሎታቸዉ ይጠብቀን የተባረከ #ሰንበተ_ክርስቲያን ይሁንልን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️
@ortodox_27