ወሬ ይሻላል❓ ምክር
ለምን ወሬ ዝባዝንኬ፣ ስድብ ጭቅጭቅ የሚበዛበት ቦታ ላይ እንሰባሰባለን ❓ለምን❓
እንደው ለዲናችን ጠቃሚ ነገራቶችን ልናገኝባቸው የሚችሉ ጥሩ ጥሩ ግሩፖች እያሉ ለምን በፊትና የተሞሉ በስድብና በዘለፋ የታጨቁ ጉሩፕችን ታሞቃላቹ ። አንድ ነገር እወቁ ምታዩትን ነገር ኢንካር ማድረግ ካልቻላቹ ወይም ካልጠላቹ ወይም ደግሞ ትታችሁ ካልወጣችሁ ቀስ በቀስ የሰዎቹን በሽታ መሸከማቹ አይቀርም ልብ ደካማ ናት ሹብሃ ደግሞ ትቀጥፋለች❗️ ውሸት ሲደጋገም እውነት እየመሰለ ይሄዳል ውስጥህ ይሸረሸራል ትጎዳለክም
መጎዳት ብቻም አይደለም በጣም ከባድ የሆነ የአመለካከት ችግር ውስጥ ትገባለህ ።
ማመን ያለብህን ትተህ ማመን የሌለብህን ሰው ታምናለክ የእሱ ጭራ ትሆናለክ ምን ይሄ ብቻ አግዝፈህ ምታያቸው እንደው ስታያቸው ሁላ በስስት የምትመለከታቸውን ዑለሞች ለመጥላት ትገደዳለህ ዑለማን መጥላት ዲንን መጥላት ነው፣ ዑለማን መስደብ ዲንን መስደብ ነው።
ምክንያቱም የተሸከሙት ዲንን ስለሆነ
ወንድሜ እንዲህ አይነት ዑለሞችን የሚያንቋሽሽ መጅሙዓ መከታተተል ልብህን ያደርቅብሃል።
ትሰማለህ ወንድሜ ሁሉ ነገር ልክ አለው የተበደለ ሰው በደሉን ሚገልፅበት መንገድ አለው እውነት ይህ አካል ተበድሎ ከሆነ ። ዑለሞቹ በህይወት አሉ ።
እነዚህ አካሎች እውነት ከዳዕዋው ጋር የመሄድ ፍላጎት ቢኖራቸው ኖሮ መክፈል የነበረባቸውን መስዋእት ይከፍሉ ነበር። ግና ሁሉም አትንኩኝ ባይ ሆነ ። ኡስታዞቻችን ከሚባለው በላይ ትግስት አድርገዋል ባይሆን ኖሮ ድሮ ነበር የራሱ ጉዳይ ብለው ሚተውት ነገር ግን ከዛሬ ነገ ይስተካከላል አንድ አቋም ላይ ይደረሳል በማለት በጣም ብዙ ጥረት አድርገዋል።
አንዳንድ ሰዎች ከሩቅ ሆናችሁ አትፍረዱ ኡስታዞቻችሁ ነገሩን ተኝተው አይደለም ያሳለፉት ወላሂ ታግለዋል እንቀልፍ አጥተዋል መስራት ያለባቸውን ነገር ጥግ ድረስ ሰርተዋል። አመድ አፋሽ አታድርጓቸው እነሱም እንደኛ ቤተሰብ አላቸው ቤተሰቦቻቸውን ጥለው ሳይተኙ ሚያድሩት ብር ሊሰበስቡ አይደለም ዑማውን ለመሰብሰብ ቢሆን እንጂ
አንድ ነገር ሳናደርግ ዘሎ አስተማሪዎቻችንን መጠራጠር ትልቅ ድፍረት እንዲሁም አሳፋሪ ተግባር ነው።
አንድ ሁለት ቀን ቁጭ ብለህ ተወያይ ብትባል ምን አልባትም ራስህን ሊያምህ ይችላል ።
እናስብ እንጂ ወገን ውለታ ሚባል ነገር አለ ስንት ትምህርት ወስደህባቸዋል ስንትና ስንት አመት አብረካቸው አሳልፈሃል ዛሬ ስለ ምንም ነገር ግድ የማይሰጠው "ሰው ጤፉ" ከሆነ አካል ጋር አሸሼ ገዳሜ ማለት ያሳፍራል።
ወንድሜ ነገሩ የስሜት አይደለም❗️
ተበድሏል ካልክ ጠይቅ ዑለሞችን እነሱን መጠየቅ ካልቻልክ በጉዳዩ ላይ ለረጅም ጊዜ ያለውን ነገር ሲከታተሉ የነበሩ ወንድሞችን ጠይቅና ተረዳ።
ከዛም ተበድለዋል የሚልን ነገር ከተረዳክ የተበደለ ሰው በዚህ ልክ በምንም ከማይገናኛቸው ዓሊሞች ጋር እንዲህ አፍ መካፈት አለበት❓
ነገሩን ማስተካከያ መንገድ የለምን ❓
እንዴት በዚህ ልክ ለጆሮ በሚሰቀጥጥ መልኩ ስድብና ዘለፋ እንዲሁም ማንቋሸሽ ይከሰታል
ትላንትና ስታወድሳቸው የነበሩ ዑለሞች ዛሬ ተራ ሰው ሆነው ለተራ ሰው ራሱ ማይባሉ ስድቦች ተሰደቡ ❗️እስቲ ማናቹ ❓እናንተ ለደዕዋ ሰለፊያ ምን አደረጋቹ❓ እስቲ መፅሃፎቻችሁን አሳዩን፣ ወዘተ
ሚገርመው ግን ብዙ ጊዜ እንዲህ አይነት ነገር ሲከሰት ወጣ ይሉና ድሮም እናውቃችኋለን እነ ኢብን ሂዛም ከዳዕዋው የወጡት ተገፍተው ነው እነ ዓብድረህማን አል ዐደኒ እነ ፉላን እያሉ ለራሳቸው ማስረጃ ያደርጋሉ ። ሱዳን ላይ ያሉ ሰዎች ከነ ሸይኽ አቢ ዓምር ጋር ሳይስማሙ ሲቀሩ ወዲው የሄዱት ዑለሞችን ወደ መዝለፍ ነበር ከዛም እነሱን ትተው እነ ዑበይድ አልጃቢሪን፣ እነ ረስላንን ማወደስ ጀመሩ ።
ነገሩ እንዲህ ነው እነዚህ ሰዎችማ ጭራሽ አብሰውታል ዑለሞችን በጣም እያሳነሱ እያንቋሸሹ ጭራሽ እንደ ጭራቅ እንድትቆጥራቸው ለማድረግ በጥረት ላይ ናቸው።
ወንድሜ ይህን ዳዕዋ የወደድነው በዑለሞች ነው የነሱ መልካም ስብእና ነው ከተለያዩ የአለም ክፍሎች ሰውን በአንድ ቦታ እንዲሰበሰብ ያደረገው❗️
ምንኛ ያማረ ደዕዋ ነው በእዝነት የተሞላ ወላሂ ዑለሞቻችን ሙተዋዲዕ ናቸው በጣም ዝቅ ብለው ተናንሰው የሚኖሩ ናቸው። ሀገራቹ መጥተው አይተሃል መቼም አትክድም ባለ 5 ኮከብ ሆቴል ላይ አይደለም ያረፉት አንተን መስለው አንተን ሆነው ነው አስተምረውክ የተመለሱት። መቼም ይህን አትረሳውም ዛሬም ብዙ ደረሶች ያሉት አንተ እንደ ቆሻሻ የምትገልፃቸው ዑለሞቻችን ዘንድ ናቸው እንደው ትንሽ አያሳፍርም የአስተማሪያችሁን ምግብ እየበላችሁ እዛው እያደራችሁ ደርስ ላይ ለመውጣት ስትሞክሩ ይሄ ጨለምተኝነት ነው ። ካልፈለክ ለቀህ መውጣት ወይም ስርኣት ይዘክ ተቀመጥ ባሉክ መሰረት መቀመጥ እንጂ በዚህ ልክ አስተማሪህን እየዘረጠጥክ ከጎናቸው ለመቀመጥ መሞከር በራሱ የሆነ የተዛባባቹ ነገር እንዳለ ያመላክታል።
ለዳዕዋ ምታስቡ እንዲሁም አንድነትንት ምትፈልጉ በነበር የተመከራችሁትን ምክር ለመተግበር ትሞክሩ ነበር። ።።።።።።።።።
እንደው ትንሽ እንኳን ለተሸከማችሁት ዳዕዋና ከኋላ ለሚከተላቹ ሰው እንኳን አታስቡም ለምን ተነካው ብላችሁ መጮሁ መሳደቡ የሆነ የተደበቀ አጀንዳ ያለ ያስመስላል።
👉
በመጨረሻም ውድ ሰለፍዮች ዑለሞችን እንዲሁም ዱዓቶችን አክብረህ ይህን ከብዙ ነገር በአላህ ፍቃድ የጠበቀህን ዳዕዋ እንደወደድከው መቀጠል ከፈለክ ነገ ዛሬ አትበል አሁኑኑ ይህን መንጀኒቅ የተባለ የስድብ ቋት ለቀህ ውጣ ይህን ካላረክ እመነኝ ነገ ዑለሞች መጡ ሲባል ግድ አይሰጥህም ለዛ ነው ኢብን ዑሰይሚን ዑለሞችን ስለመሳደብ ሲናገሩ እንዲህ ያሉት፦እነሱን መስደብ አንድ ተራ ሰውን እንደመስደብ አይደለም ዑለሞችን መስደብ ዲንን መስደብ ነው። አንድ ተራ ሰውን ብትሰድብ ስድቡ እሱ ላይ ይቀራል ዑለሞችን ስትሰድብ ግን እነሱን በሚከተሉ ሰዎች ዘንድ ያላቸውን ተቀባይነትና ተሰሚነት ያሳጣል ይሄ ደግሞ ዲንን ይጎዳል ❗️
ነገሩ ይህ ከሆነ ወንድሜ የዚህ ወንጀል ተካፋይ አትሁን ቶሎ ለቀህ ውጣ ❗️
👉https://t.me/AbuEkrima