ar
Feedback
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

الذهاب إلى القناة على Telegram

💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።

إظهار المزيد
9 056
المشتركون
-1124 ساعات
+317 أيام
-6930 أيام
أرشيف المشاركات
~ግቡና ቅሯት እህቶች የቀራችኋትም ቀርተነዋል ብለን ችላ ማለት የለብንም።ሙራጃአ ይሆናል።

📮 አስደሳች ዜና ▫️ለሁሉም ሙስሊም እህቶች እነሆ ዛሬ (እሁድ ነሃሴ 11/2017) ሴቶችን የሚመለከቱ ህግጋቶችን አቅፋ የያዘቸውን የ [ተንቢሃት] ኪታብ ደርስ እንጀምራለን። ▫️ደርሱ የሚሰጠው በ"አህሉል አሠር የሴቶች መድረሳ" ሲሆን የደርስ ሰዓት ከጁሙዓ ቀን ውጭ ዘወትር ከምሽቱ 3:00pm በኢትዮ መሆኑን እናሳውቃለን። ▫️ መድረሳው የሴቶች ብቻ ስለሆነ ወንዶች አላህን ፍሩና ወደ ግሩፑ ከመግባት ታቀቡ። 🔺 ት/ቱ ከምንም አይነት ክፍያ ነፃ ነው። 🚫 የሴቶች ብቻ 🚫 t.me/Ahlul_aser    t.me/Ahlul_aser

رسالة صوتية02:42

اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎ ዛሬ ምሽት ከ3:20 ጀምሮ ወሳኝ ዳዕዋ አለን ርእሳ፦ የሰሞንኛው ብዥታ { ሙዚቃ በሸሪዓችን } ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ...👇👇👇 http://t.me/abuUseyminabdurehman

••• شرح حديث "....... ويجزئ من ذلك ركعتان يركعهما من الضحى" 🎙 فضيلة الشيخ عبدالرزاق البدر- حفظه الله تعالى- •••🌳

“አዕምሮህ ሰላም እንዲሆን ከፈለግክ  ምንም እንዳልገባህ ሆነህ ዝም በል። ምንም እንዳላየህ ሆነህም እለፍ።” ሸይኽ ዓሊይ ጠንጧዊ t.me/abdu_rheman_aman

ሰው ሲሄድ የምትሄዱ፤ ሰው ሲቆም የምትቆሙ ደካማ ፍጡር አትሁኑ። ሕይወታችሁን በማንም ላይ፣ ከማንም አንፃር አትመስርቱ። ከአላህ ቀጥሎ በራሳችሁ ተማመኑ። ራሳችሁን ቻሉ።መመካት በአላህ ብቻ በቃ።

«ለምን አላገባሽም ለምን የትዳር ጥያቄውን ውድቅ አደረግሽ ተብላ ተጠየቀች። እሷም እንድህ ብላ መለሰች ««««»«««««««««««««««« 🔵 በጣም ድሃ ነው ከገንዘብ ውጭ ምንም ነገር የለውም አለች። https://t.me/Abuebrahim22322 https://t.me/Abuebrahim22322

🔖አዲስ ሙሓደራ!! ➡የልቦና ንፅህና የአማኝ መገለጫ ነዉ። 🎙በኡስታዝ ኸድር አህመድ

🔀 የተጅዊድ ትምህርት       📌👌👌👌የሀምዘህ ምንነት ➡ ሀምዛህ በአጠቃላይ በሁለት ይከፈላሉ። 1)ሀምዘቱል ቀጥዕ (أ) ፦ ማለት ከአሊፍ ሱኩን አናት ላይ የሀምዛ ምልክት ያላት ሲሆን ቀጥለንም ስናነብ (በቃል መካከል ላይ ስትመጣ) ሆነ መጀመሪያ ላይ እንድሁም መጨረሻ ላይ ስትመጣ የምትነበብ ሀምዛህ ናት። 2) ሀምዘቱል ወስል (ٱ) ፦ ማለት ከአሊፍ ሱኩን አናት ላይ የሷድ ምልክት ያላት ስትሆን በሷ ጀምረን ስናነብ የምትነበብ ፤ በቃል መካከል ላይ እና መጨረሻ ላይ ስትመጥታ ግን የማትነበብ ሀምዛህ ናት። 🍎 የሀምዘቱል ወስል ምንነት እና ህጎች 💠 መጀመሪያ ላይ ሀምዘቱል ወስልን ከያዘ ቃል የምንጀምር ከሆነ ሀምዘቱል ወስል የምትነበብ ስትሆን እሷን (ሀምዘቱል ወስልን) ከያዘው ቃል በፊት ሌላ ቃል ኖሮ ሁለቱንም (ሀምዘቱል ወስልን የያዘው ቃል እና ከሀምዘቱል በፊት ያለውን ቃል) አያይዘን በምናነብበት ጊዜ ደግሞ የማትነበብ የሆነች ሀምዛ ነች። 💠 በቃላት መጀመሪያ ላይ ሱኩን በሚመጣበት ጊዜ ሀምዘቱል ወስልን ፈትሀ፣ ከስራ ወይም ዶማ በማድረግ ንባቡን ቀለል ለማድረግ ትመጣለች።  ምክንያቱም በአረበኛ ፅሁፍ ወይም ንባብ በሱኩን የማይጀመር ስለሆነ ነው። በዚህ የማያያዝ ፋይዳዋ አያያዥ ሀምዛ (ሀምዘቱል ወስል) በመባል ትታወቃለች። ♦️ሀምዘቱል ወስል በግስ (الفِعْل)፣ በስም (الإسم) እና በትርጉም ላይ ጠቋሚ በሆኑ ፊደሎች (حَرْفُ المَعْنَى) ላይ ትመጣለች። ➨ሀምዘቱል ወስል መጀመሪያ ላይ በመጣችበት ቃል ጀምረን በምናነብበት ጊዜ ሊኖራት የሚችለው ሁኔታዎች በሶስት ከፍለን ማየት ይቻላል። ❶. ከላም አት-ተዕሪፍ ፊደል (ከላመል አል) በፊት የመጣች ሀምዘቱል ወስል ➯ በዚህን ጊዜ ሀምዘቱል ወስል ፈትሀ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦ ٱلْحَمْدُ ، ٱلرَّحِيمِ 👈 ❷.በስም መጀመሪያ ላይ የመጣች ሀምዘቱል ወስል ➯ በስም ላይ የመጣች ሀምዘቱል ወስል ሁል ጊዜ ከስራ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦ ٱمْرَأَتٌ ، ٱبْنَتِ👈 ❸. በግስ መጀመሪያ ላይ የመጣች ሀምዘቱል ወስል ➯ በግስ ላይ ሀምዘቱል ወስል ስትመጣ የሚኖራት ሁኔታ ሁለት ብቻ ነው። እነርሱም፦ ዶማህ እና ከስራህ የመሆን ሁኔታ ናቸው። ➊. ሀምዘቱል ወስል ግስ በሆነ ቃል ላይ መጥታ ዶማህ ተደርጋ የምትነበበው በአንድ ሁኔታ ብቻ ነው። ➤ ቃሉ ከሀምዘቱል ወስል ተጀምሮ ሲቆጠር የግሱ ሶስተኛ ፊደል መሰረታዊ የሆነ ዶማህ ከሆነ ሀምዘቱል ወስል ዶማህ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦ ٱجْتُثَتْ ، ٱدْخُلُوا ، ٱسْجُدُوا ، ٱتْلُ👈 ➋.ሀምዘቱል ወስል ግስ በሆነ ቃል ላይ መጥታ ከስራህ ተደርጋ የምትነበበው በሶስት ሁኔታ ብቻ ነው። ➀) ከሀምዘቱል ወስል ተጀምሮ ሲቆጠር የግሱ ሶስተኛ ፊደል ከስራህ ከሆነ ሀምዘቱል ወስል ከስራህ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦ ٱصْبِرُ ، ٱكْشِفْ، ٱرْجِعُوا👈 ➁) ከሀምዘቱል ወስል ተጀምሮ ሲቆጠር የግሱ ሶስተኛ ፊደል ፈትሀ ከሆነ ሀምዘቱል ወስል ከስራህ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦  ٱسْتَغْفِرُوا ، ٱقْرَأ ، ٱنقَلَبُوا ، ٱذْهَبْ👈 ➂) ከሀምዘቱል ወስል ተጀምሮ ሲቆጠር የግሱ ሶስተኛ ፊደል ምክንያታዊ ዶማ (ዋው መድያን የያዘ ዶማ) ከሆነ ሀምዘቱል ወስል ከስራህ ተደርጋ ትነበባለች። ምሳሌ፦ ◆ ٱبْنُوا👈 ◆ ٱقْضُوا👈 ◆ ٱمْشُوا👈 ◆ ٱئْتُوا👈 ◆ ٱمْضُوا👈 -------------------------------------------------------------------- --------------------------------------------------------------------             ✍️ የቀጥላል ሼረ አድርጉ

🔖ሸይኽ ሙቅቢል አል ዋድዒይ ረሒመሁሏሁ ተዓላ እንዲህ ይላሉ: كلمة الحقِّ لَا تَمْنَعُ عَنْكَ رِزْقًا ، وَلَا تُقَرِّبُ لَكَ أَجَلًا !‍‍" البشائر ٣٨ «የዕውነት ንግግር ሪዝቅህን አያሳጣም, አጀለህንም አያቃርብም»። 👉ስለዚህ ወንዲሜ“የማንንም ትችትና ወሬ ፈርተህ የምታውቀውን ሐቅ ከመናገር”ወደ ዃላ አትበል።

*خطبة الجمعة* ╭─┅───══───┅─╮ *بعنوان*~ *《من علامات محبة النبي صلى الله عليه وسلم》*

~ባለህ ከተደሰትክ የሌለህ ትዝ አይልህም። የሠጠኸንን ፀጋ ማየትን አትጋርድብን ኢላሂ! ~

👉ምን ያማረ ምክር ነዉ። ከስራው በፊት ልብሽ ሊረጋጋ ይገባል።ሪዝቅ ከአላህ መሆኑን በፅኑ እመኚ።በማታውቂው የሰው ሀገር ለዓመታት የጠበቀሽና የረዘቀሽ ጌታ፣ገዛ ሀገርሽና በቤተሰቦችሽ መካከል በፍጹም አይተውሽም። ስለዚህ የመጀመሪያው ተግባርሽ ልብሽን በአላህ ላይ ማንጠልጠል ነው። ~

የብዙ እህቶች ጥያቄ! ከአመታት ስደት በኋላ ወደ ሀገሬ ስመለስ፣ በኑሮዬ እና በሃይማኖቴ ላይ የሚያጋጥሙኝን ተግዳሮቶች ተቋቁሜ እንዴት ራሴን መቻልና በእምነቴ መፅናት እችላለሁ?? 🖊ወንድምሽ አቡ ሱፍያን t.me/AbuSufiyan_Albenan t.me/AbuSufiyan_Albenan

✅ አላዋቂ ሴት ማለት ይቺ ናት ~ ~ 【من أحمق النساء امرأة اضطرت زوجها إلى أن يسيء إليها بعدما كان يعاملها بالحسنى】 ~ሞኝ ወይም ቂል ሴት ማለት ባሏ በ
አላዋቂ ሴት ማለት ይቺ ናት ~ ~ 【من أحمق النساء امرأة اضطرت زوجها إلى أن يسيء إليها بعدما كان يعاملها بالحسنى】 ~ሞኝ ወይም ቂል ሴት ማለት ባሏ በመልካም እየተኗኗራትና መልካም እየሰራላት ሳለ በንግግሯ ወይም በተግባሯ በሷ ላይ መጥፎ እንዲሆንና መጥፎ እንዲሰራባት ያስገደደችው ሴት ናት። ~ t.me/https_Asselfya

~ጥቆማ !! ~ፓስፖርታችሁ እጃችሁ ላይ ያለ እህትና ወንድሞች ኢንባሲ ሂዳችሁ አሳድሱ ። በዚህ በኦላይ የሚደረጉ ነገሮች ቢቀርባችሁ ይሻላል። በቅናሸ ዋጋ እናሳዲሳለን የተለያዩ ነገሮች እየተባለ የሚዘዋወሩ ቴክስቶችን እንዳላየ ሁናችሁ እለፏቸዉምክንያቱም አድስ ፓስፖርት በሚወጣበት ዋጋ በላይ ነዉ እየጠየቁ ያሉት!! 👉ስለዚህ ብልህ ሠዉ ጥቆማ ይበቀዋል።

«ስንቶች ነን የማታ ዚክርና የጧት ዚክር የምንለው? አላህ ካዘነልን በስተቀር ። ወንድሜ ልጅህን ሚስትህን በምትችለው ዚክርን አስተምር። አስታውስ ዚክር የልብ ቀለብ ነው። አላህን የሚያወሳ ሰው ልቡ ሰላም ነው ሰይጣን እሱን አይነካውም። 🖊አቡ ዓኢሻ t.me/Abuebrahim22322