ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 381 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 584 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 199 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 381 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 21، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.13‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.50‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 250 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 462 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 16.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 381
المشتركون
-724 ساعات
+117 أيام
+2130 أيام
أرشيف المشاركات
#ጌና_እና_ልደት ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹#ቤዛ_ኩሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤

ወዳጆቼ ሆይ #ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ፡፡ /1ኛ ቆሮ. 10/ /ይሁዳ 1፥4/ #የጥድ (#የገና) #ዛፍ #በቤተ_ክርስቲያንና_በመጽሐፍ_ቅዱስ_እይታ_ ፠#የጌታችን_ልደት_December_25 #ወይስ_ታኅሣሥ_29 _(በ4ት ዓመት በ28) ፠ #የጥድ_ዛፍ_መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ወይስ_የአውሮፓውያን_ባህል_? ፠ #የጥድ_ዛፍን_ምዕራባውያን_የሚቀበሉበት_ምክንያትና #_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? ፠ #ሳንታክሩዝ (#የገና_አባት?) #ማነው? #የጌታችን_ልደት_December_25 #ወይስ_ታኅሣሥ_29 _(በ4ት ዓመት በ28) ፠፨፠ ምዕራባውያን የጌታችንን ልደት የሚያከብሩበት ምክንያት፤ 1ኛ) በ December 25፤ የጥንታውያን የግብጽ የፀሐይ አምላክ ‹‹ራ›› የተባለው ጣዖት የተወለደበትና በዘንባባ ዛፎች መሃል የሚመለክ፤ ከታች የሰው ሰውነት ራሱ የአሞራ ጭንቅላቱ ላይ ፀሐይን የከበበ ዘንዶ ያለበት ጣዖት የሚያመልኩበት ነው፡፡ 2ኛ) በDecember 25፤ ሚትራስ፤ በመካከለኛው ምሥራቅ የሚታወቅ ባዕድ አምልኮ የሚመለክበት በመሆኑ፤ 3ኛ) በ December 25፤ ሳተርን ሊያ፤ የጥንት የሮማ የእርሻ አምላክ በመባል የሚታወቅ ነው፡፡ በራቁት ጭምር ብዙ ኃጢአት የሚገበርለት ነው፡፡ በ3ኛውና በ4ኛው ይህን ጣዖት አንቀበለም በማለታቸው በርካቶች ሰማዕትነት ተቀብለውበታል፡፡ (ካቶሊካውያን ከላይ የጠቀስናቸውን የባዕድ አምልኮ እናስተዋለን ሲሉ ነው ዲሴምበር 25 የደነገጉት) ፠፨፠ እኛ ኢትዮጵያውያን ግን የነቢያትን ትንቢት ፥ የአበውን ቀመር (የ15ቱ ሱባኤያትን ቀምረን)፤ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረትነት ነው፡፡ #ምዕራብውያን_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? በምዕራቡ ዓለም ሰዎች በአንድ ዓመት ውስጥ የሚመጣ ሁለት/፪/ ክስተቶች አሏቸው፡፡ 1ኛ) የዘጠኝ ወር ክረምት ሲሆን 2ኛ) ለሦስት ወራት የሚቆይ የበልግ ጊዜ ነው፡፡ በዘጠኝ ወር ክረምት ሲሆን ለዘጠኝ ወር ያህል መሬት ልምላሜ አትሰጥም፡፡ ዛፎች ይሰባበራሉ፡፡ ቅርንጫፎች ቅጠሎች ይወድቃሉ፡፡ ፍሬዎች ይረግፋሉ፡፡ በክረምት ወራት በሚዘንበው ዝናብ በረዶ የቀላቀለ በመሆኑ የበረደው ክምር መሬቱን ስለሚሸፍን መሬት በረከቷን አትሠጥም በእዚህ የተነሳ ለዘጠኝ ወራት ያህል ይራባሉ፡፡ ይጠማሉ፡፡ ታዲያ በእነርሱ አመለካከት ይህንን የክረምት ወቅት የጨለማ እና የክፉ አምላክ ዘመን በመሆኑ ነው እንጂ ደግ አምላክ ቢሆንማ እንደዚህ አያሰቃየንም ብለው ያስባሉ፡፡ በሁለተኛው ክስተት ማለትም ለሦስት ወራት ያህል ፀሐይን የሚያዩበት አርሰው ፥ ዘርዘርተው የሚያመርቱበት ለዘጠኝ ወራት የሚሆናቸውን ቀለብ የሚሰበስቡበት ነው፡፡ በአጠቃላይ የልምላሜ፣ የጥጋብ እና የተስፋ ወራታቸው ነው፡፡ በዚህም እንደ እነርሱ አመለካከት ይህን የበጋ ወቅት የብርሃን የደጉ አምላክ ዘመን ይሉታል፡፡ #ምዕራብውያን_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? በእነርሱ ፍልስፍና ምንታዌ/ሁለት/ አማልክት አሉ ብለው ያስባሉ፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በክረምቱ የዘጠኝ ወራት ውስጥ ብዙ ዛፎች ሲገነደሱ፣ ሲቈረጡ ፣ ፍሬያቸው ሲረግፍ አንድ ዛፍ ግን ፍሬው ሳይረግፍ ሳይገነደስ የዘጠኝ ወር ክረምቱን ያሳልፋል፡፡ ይህም ዛፍ ጥድ ነው፡፡ ጥድ ዛፍ ከሌሎች ዛፎች ሁሉ ጠንክሮ ፀንቶ የሚቆየው በተፈጥሮ ፅኑ ጠንካራ በመሆኑ እንጂ ሌላ ተአምር ኖሮት አይደለም፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ አውሮፓውያን ለገዛ ሓሳባቸው ሲሉ ጥድ ምንም አለመሆኑ ደጉ አምላክ ያንን የክፉ አምላክ ዘመን የሚያሳልፈው በጥድ ዛፍ ውስጥ ስለተሸሸገ ነው፡፡ የጥድ ዛፍ ለደጉ አምላክ ቤተ መቅደስ ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ይህ የጥድ ዛፉን በዓመት በዓመት ክረምቱ አልቆ በጋው ሲገባ የደጉ አምላክን መቅደስ እያስጌጡ በጥድ ያመልኩ ነበር፡፡ የክርስትና ሃይማኖት ሲስፋፋና ሲቀበሉ ይህን አምልኮታቸውን አዲስ ከተቀበሉት ሃይማኖት ጋር በማስተሳሰር ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት አዲስ ስም ሰጥተው ይጠቀሙበት ጀምረዋል፡፡ ከጌታችን ልደት ጋር ያስተሳሰረው ይህ ብቻ ሳይሆን የደጉ አምካቸውን መቅደስ የሚስጌጡበት ማለትም ክረምቱ አልቆ በጋው የሚገባበት /የዘመን መለወጫው/ እና የጌታችን የመድኃኔታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በጊዜ አቈጣጠራቸው መገናኘቱ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የድሮ ባህሎቻቸውን እንዳይረሱ ቀናቶቻቸውንም ጭምር ስማቸውን በአማልክቶቻቸው ሰይመውታል፡፡ ለምሣሌ፤ ቀኑ ስያሜውን ያገኘው *Monday (ሰኞ) --------------------------- Moon day ጨረቃን የሚያመልኩበት ቀን *Sunday (እሑድ) ----------------------- Sun day ፀሐይን የሚያመልኩበት ቀን *Saturday (ቅዳሜ) ----------------------- Star day ኮከብን የሚያመልኩበት ቀን *Tuesday (ማክሰኞ) -------------------- Tues day (“Tues” የተባለ ጣኦታቸውን የሚያመልኩበት ቀን) ** የX MASS tree (የገና ዛፍ) የተጀመረው ከሳተርን ሊያ (የጥንት የሮማ የእርሻ አምላክ) ሲሆን፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በቤቱ ያስገባው የጀርመኑ ሃገር የመናፍቅ ሰባኪ ማርቲን ሉተር ነው፤ ወደ አሜሪካ ደግሞ በ1830ዎቹ ከጀርመን ወደ አሜሪካ የተሰደዱ ፔንሲልቫንያዎች ናቸው ከክርስቶስ ልደት ጋር እያያዙ ማክበር የጀመሩት፤ በ1940ዎቹ በአሜሪካና በሌሎቹም ዓለማት እየተስፋፋ መጣ፡፡ ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች የእነርሱን ተከትለን እንዴት ወደ ስሕተት አንዴት እንገባለን!!፡፡ ነገር ግን ከአንድም ሁለቴ ተሳስተናል፡፡ ፠ አንደኛ ሁለት አምላክ አለ ብለን የምናምን አይደለንም ፠ ሁለተኛ እግዚአብሔር ይህችን ቅድስት ሃገር ስለባረካት ክረምቱ ፪ ወራት ብቻ መሆኑ ነው፡፡ በክረምቱም ይህንን ያህል የበረዶ ግግር የለብንም፡፡ ስላደረገልን ነገር ሁሉ ማመስገን አለብን እንጂ፡፡ #ሳናታክሩዝ_፤ አንዳንዶች በ4ኛው ክ/ዘመን ከተነሣው ቅዱስ ቅዱስ ኒኮላስ ጋር አገናኝተው ለልጆች ስጦታ ከሚሰጠው ጋር ለማገናኘት ይሞክራሉ ግን ይህ ሐሰት ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ አስተሳሰብ፤ *ሳንታክሩዝ መጥቶ ሌሊት ስጦታ ይላል በሚል ሕፃናቱ፤ ሐሳባዊ በሆነ (በስዕል ነጭ ረዥም ጢም ያለውን ሰው አለ ብለው ሐሰት እንዲማሩ) ያደርጓል፤ ስጦታውን የሚሰጡ ቤተሰቦች ሆነው ሳለ፡፡ *ሰዎች በጌታ ልደት መወለዱን ሳይሆን ሳንታክሩዝ ይመጣል ብለው እንዲያስቡ አድርጓል፤ * ከማንኛውም ነገር ነላይ የጌታ ልደት ይበልጣልና መታሰብ ያለበት የጌታ ልደት እንጂ ሳንታክሩዝ መሆን የለበትምና፡፡ እንግዲህ ብርሃን ከጨለማ ጋር ምንም ኅብረት እንደሌለው አውቀን የምናደርገውን ከማድረጋችን በፊት ልንጠይቅ ልንሰማ ልንማር ያስፈልጋል፡፡ አባቶቻችን የልደትን በዓል እንድናከብር ያስተማሩን ዛፍ ቆርጦ በማቆም ሳይሆን የተደረገልንን ድኅነት እያሰብን(አምላክ ሰው ሆኖ እንዳዳነን) ፥ እንደ መላእክት እንደ እረኞች በስብሐተ ለእግዚአብሔር ፥ እጅ መንሻ አምሃ በመስጠት ፥ በመረዳዳት ፥ የታመመን በመጠየቅ ሊሆን ይገባል፡፡ ስለ ቅዱስ ኒቆላዎስ (የገና አባት) በቀጣዩ ጽሑፋችን ይጠብቁን ወዳጆቼ ሆይ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ፡፡ /1ኛ ቆሮ. 10/ /ይሁዳ 1፥4/ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ /ምንጭ፤ የፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔትና የመ/ር ለማ ‹ወዳጆቼ ሆይ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ› የሚል ስብከት፡፡)

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡
+1
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡

የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡፡
+2
የ2013 ዓ.ም የታኀሣሥ ወር ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማስታወሻዎች ፤ከፍቶ ማሕደራችን፡፡