ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 394 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 590 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 197 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 394 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 21، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.61‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.23‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 327 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 576 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 394
المشتركون
+124 ساعات
+307 أيام
+2130 أيام
أرشيف المشاركات
ጥቅምት 14፣ 2014 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርስቶስ መርዓዊ ወሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር የፎቶ ማስታወሻ
+5
ጥቅምት 14፣ 2014 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርስቶስ መርዓዊ ወሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር የፎቶ ማስታወሻ

ጥቅምት 14፣ 2014 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርስቶስ መርዓዊ ወሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር የፎቶ ማስታወሻ
+5
ጥቅምት 14፣ 2014 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርስቶስ መርዓዊ ወሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር የፎቶ ማስታወሻ

ደብረ ዳሞ ዳሕምሞ መላእክትም ለአረጋዊ እንደባልንጀራ አንደ ጓደኛ ሆኑት፤ እሳቸውን ለመጐብኘትና በረከት ለማግኘት አባቶች ብቻ ሳይሆኑ ንጉሡ አጼ ገብረመስቀልም ወደእሳቸው ይመጣ ነበር፡፡ እሱም እሰከዛሬ ምስክር ሁኖ የሚገኘውንና በእመቤታችን ስም የተሰየመውን ድንቅ ገዳም ሲያንጽ ለእንሳሳቱ መመላለሻ እንዲሆን ተራራን አሠራ፤ ሕንጻው ቅዱስ ያሬድ በተገኘበት ተመረቀች፤ ኋላ ግን ንጉሡ ከአረጋዊ ተባርኮ ሲመለስ ‹‹ተራራውን ላፍርሰው፤ ወይስ ልተወው?›› አለ፤ አቡነ አረጋዊም በግዕዙ ‹‹ ዳሕምሞ ›› አሉት፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አካባቢው ዳሞ ገዳሙ ደግሞ ደብረዳሞ ተባለ፡፡ አቡነ አረጋዊም ንጉሡን ‹‹ስለዘንዶው ጅራት ፈንታ ሰዎች ይወጡበት ዘንድ ገመድ አብጅ፡፡ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆንና ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ፡፡›› አሉት፤ ለመወጣጫ ይሆን ዘንድ ገመድ ተሰራለት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ገመዱ የታሠረበት ግንድ እስካሁን ከ1500 ዓመታት በላይ አለ፤ ኋላ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለ12 ዓመታት በደብረ ዳሞ ቆይተው በዚሁ ገመድ ሲወርዱ ነው ሰይጣን ቀንቶ ገመዱን ቢበጥስባቸው እግዚአብሔር አምላክ ክንፍ የሰጣቸው፡፡ (ስዕሉን እይ ) ደብረ ዳሞ ዙርያው ገደል ሆኖ የጠረጴዛ ቅርጽ ያለው አምባ ሲሆን 500*1000 ሜትር የሚሆን ስፋት አለው፡፡ ከባህር ወለልም በላይ 2216ሜ. ከፍ ይላል፡፡ ወደ ገዳሙ መውጣት አና መውረድ የሚቻለው 16ሜ. በሚረዝመው በአምሳለ ዘንዶ በተሰራው ገመድ ብቻ ነው፡፡ ንጉሡም ከተራራው እንደወረደ እንደታዘዘው አፈረሰ፡፡ አሁን የምናየው ዓይነት ገመድንም አዘጋጅቷል፤ የገመዱም ስም ‹‹ዘንዶ›› ይባላል፡፡ በዚህ ገዳም ሴቶች በአፀደ ሥጋ እያሉ አይገቡም፤ ካረፉ በኋላ ግን እንደ አባ ጳኩሚስ ገዳምና ሥርዓት ከተከዜ ማዶ ከሚኖሩ የሴት መነኮሳት መካከል አንዲቱ የሞተች እንደሆነ ወደ ወንድሞች መነኰሳት አምጥተው በነሱ ዘንድ በሚገኘው የመቃብር ቦታ ይቀብሯቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የአቡነ አረጋዊ እናት የነበረችው ልጂ በሕፃንነቱ ሳለ መመንኰሱን አውቃ ከልጇ ሕይወቱን ተምራ ገና ከመጀመሪያ ወደ አባ ጳኵሚስ ገዳም ሄዳ መንኵሳ ነበርና በቅድስና በትሕትና ደናግሉ በፍቅር ስታስተዳድር ኖራ መንፈሳዊ ግዳጇን በጐ አገልግሎቷን ፈጽማ ጥር 4 ቀን ስታርፍ ለመቀበሪያዋ ይሆን ዘንድ አባታችን አቡነ አረጋዊ ባሰራላት አዲስ መቃብር ተቀብራለች፡፡ ሆኖም ግን በግራኝ አህመድ ወረራ ወቅት ንግስት ሰብለ ወንጌል እና ደንገጡሮቻ እዚህ አምባ ላይ በመጠለል ከሞት ድነዋል። ተራራው ላይ ምንጭና እህል የሚዘራበት ሰፊ መሬት ስለነበር ፖርቱጋሎቹ እነ ክሪስታቮ ደጋማ ከአምባው ደርሰው ንግስቲቱ እንድትወርድ እስከአሳመኗት ድረስ የግራኝን ሰራዊት ከዚህ አምባ ላይ ሆና መከላከል እንደቻለች መጻሕፍት ይናገራሉ።" #የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤ ይኸውም የበሶ እምነት ለብዙ ችግሮች ፈውስ ነው፡፡ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያትም በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናንም እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ #የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል፤ ፠ በደብረ ዳሞ፣ ፠ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ (አለርት ሆስፒታል አጠገብ፤ ወደ አለም ባንክ መስመር) ፠ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም፣ (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት ይገኛል) (ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ክብረ በዓል በደብራችን ሲከበር 100 ዓመታት ሞልቶታል፤፡፡) ፠ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በጎንደር አቡነ አረጋዊ ቤ.ክ. (ብሉኮ አካባቢ) ፠ ላምበረት ደብረ ፀሐይ አቡነ አረጋዊ፥ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወቅድስት አርሴማ ቤ/ን፤ ፠ ቃሊቲ ደብረ መድኀኒት መድኃኔ ዓለምና አቡነ አረጋዊ ቤ/ን፤ ፠ ሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን ፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ፤ ፠መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ ፠ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፠ ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ፤ ፠ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ፤ ፠ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ን፤ ፠አፍሪካ ኅብረት፥ ደብረ ምሕረት ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ን፤ ፠ ሽሮሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ ፠መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ፤ ፠ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ፤(የፊሊጶስ በዓልም ይከብራል) ፠ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔ ዓለም፥ መጥምቁ ዮሐንስና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ፤ ፠አያት መካነ ሕይወት መድኀኔ ዓለምና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ ፠ፉሪ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ ፠ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ ፠ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ ፠ጃቴ መካነ ሕይወት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ ፠መሪ ቅድስት ሥላሴ፥ ቅዱስ ዑራኤል፥ ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ ፠ቦሌ (ገርጂ) ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ ፠ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

፠ አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ እርሱ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤ በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም #ተሠወረዋል፡፡ ይህም እንዲህ ነው አባታችን አቡነ አረጋዊ ማትያስ ለተባለው ደቀ መዛሙር ጌታችን ተገልጦ የሰጣቸውን ቃል ኪዳንና ይህ መጽሐፍ ተጽፎ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ነገሩት፤ (መዝ ፻፲፩/፻፲፪፥፮) ወንድሞቹ ደቀ መዛሙርቶቹ በተሰበስቡበትም ሁሉንም ከአስተማሩ በኋላ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም በመሪር ኃዘን እግራቸው ሥር ወድቀው አለቀሱ፤ አባታችን አቡነ አረጋዊም አጽኗኗቸው፡፡ ጥቅምት ፲፬ ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ በ፺፱ (99) ዓመታቸው ተሰወሩ፤ በዚያም #ከመቋሚያና #ከመስቀል በስተቀር ምንም የተገኘ የለም፡፡ ገድላቸውንም ደቀ መዛሙርታቸው ማትያስ እና ዮሴፍ ጽፈዋል፡፡ ከዚያም አባ ማትያስ ደብረ ደሞን ለማስተዳደር ተሾመዋል፡፡ ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡ #_ እግዚአብሔር አምላክህ አንተን መርጦሃልና እንደ ኹለቱ ነቢያት ለተከወነ መሠወርህ ሰላምታ የሚገባህ ደግ አገልጋይና የታመንህ መጋቤ ቤቱ ቅዱስ አረጋዊ ሆይ በዐሥሩ አህጉር ተሹመህ ኀምስቱን መካልይ የተቀበልህ አንተ አይደለህምን?፡፡ _# #መልክአ አቡነ አረጋዊ ፨#ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ #ዕረፍታቸው_፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው(ቅዱስ ያሬድ ለእመቤታቸን ( ትዕግሥትኪ ፈድፈደ እምትዕግሥተ ኢዮብ ጻድቅ ፤ወእማርቆስ #ዘቶርማቅ ፤ ወገብረ ክርስቶስ መርዓዊ ተወካፌ ሕማም መጽዕቅ፡፡ ) ብሎ እንደጻፈው ቅዱስ ቶማስ ዘቶማርቅ እንደ ኢዮብ ታጋሽ የሆነ ጻድቅ ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔር ሰው የተባለ ትዕግሥኛው ቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ ፠፠ ፠፠፠ ፠፠፠ ፠ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#ጥቅምት_14 አቡነ #_ አረጋዊ የተሰወሩበት፤ ቅዱስ #_ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍት፤ ቅዱስ #_ ሙሴ_እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ #_ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ጥቅምት 14 ፤ አቡነ አረጋዊ ( ዘሚካኤል ) ወቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር #አቡነ_አረጋዊ (#ዘሚካኤል) ፠ ከእንጦንስ ከመቃርስ እና ከጳኵሚስ የምንኵስና ሐረግ አራተኛ ትውልድ ናቸው፣ ፠ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም 6 ሺህ የደረሱ ናቸው፣ ፠ ከቅዱስ ያሬድ ጋር እጅግ ይዋደዱ የነበሩ ፣ ዝማሬውንም ለመስማት ከጐንደር ለመጣ ሲል በጸጋ አይተው ደብረ ዳሞ ላይ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ሰብሰበው ይጠብቁ የነበሩ ፡፤ ፠ ታላላቅ የኢትዮጵያ ነገሥታትን ለባረኩ ይመጠላቸው የነበረ .. ፠ አጼ ገብረ መስቀል በተመስጦ የቅዱስ ያሬድን እግር በጦር በወጋው ጊዜ ታለቅ ግብዣን አድርገ የዛኔም አቡነ አረጋዊ ቀድሰዋል፣ ቅዱስ ያሬድም ዘምሯል ፤ ታላቅ ሥርዓትንም አስጀምረዋል፡፡ ___________________________________________ ፠ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው #ይስሐቅና ከእናቸው #እድና የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው ፤ ወንድሞቹም #ቴዎድሮስ እና #ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡ ፠ የቀድሞው ስማቸው #ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡ ፠ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኵሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ #እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡ ፠አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ #_ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ )፣ አባ #_ ይምዓታ (ገዳማቸው በኃውዜን የሚገኝ (ትግራይ) ከሀገረ ቁስያ፣ አባ #_ ገሪማ ከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ፣ ከአንፆኪያ አባ #_ ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ #_ ጉባ፣ ከእስያ አባ #_ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ #_ ጴንጠሌዎንከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ) ፣ ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትንማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን #ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸውሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ #አረጋዊ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትም ቀን ጥቅምት 11 ነበር ፡፡ አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደ ላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም ፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ ቢዚያችም ሰዓት ተራራዋ ደብረ ታቦርን መስላ ነበር:: በዚህችም ላይ ንጉሥ አጼ ገብረ መስቀል ቤ/ክ ከአነጹ በኃላ የቅዳሴ ቤቱ ዕለት አቡነ አረጋዊ ቀድስው ንጉሡም ሠራዊትም ሕዝቡም ጳጳሳቱም ጭምር ሥጋ ወደሙን ተቀብለዋል፡፡ ንጉሡም በረከተን ከአባታችን ተቀብሉ ወደ አኵሱም ተመልሷል፡፡ ሲመለስም ሰርቶት የነበረውን ድልድላይ ላፍረሰው ወይ ሲላቸው ዳሕምሞ ብለውታል ትርጕሙም ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ፡፡ ከዚ በመነሳት ዳሞ ተብላለች፡፡ እግዚአብሔርም ሰማያዊ ኅብስት ትሁነህ ብሎ ደብረ ዳሞን ስጥቶዋቸዋል ይህም በመንፈስ ለሚወለዱት ልጆቹ እስከ ዘለዓለም ማርፍያ እንድትሆን ነው ፡፡

፠ አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ እርሱ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤ በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም #ተሠወረዋል፡፡ ይህም እንዲህ ነው አባታችን አቡነ አረጋዊ ማትያስ ለተባለው ደቀ መዛሙር ጌታችን ተገልጦ የሰጣቸውን ቃል ኪዳንና ይህ መጽሐፍ ተጽፎ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ነገሩት፤ (መዝ ፻፲፩/፻፲፪፥፮) ወንድሞቹ ደቀ መዛሙርቶቹ በተሰበስቡበትም ሁሉንም ከአስተማሩ በኋላ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም በመሪር ኃዘን እግራቸው ሥር ወድቀው አለቀሱ፤ አባታችን አቡነ አረጋዊም አጽኗኗቸው፡፡ ጥቅምት ፲፬ ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ በ፺፱ (99) ዓመታቸው ተሰወሩ፤ በዚያም #ከመቋሚያና #ከመስቀል በስተቀር ምንም የተገኘ የለም፡፡ ገድላቸውንም ደቀ መዛሙርታቸው ማትያስ እና ዮሴፍ ጽፈዋል፡፡ ከዚያም አባ ማትያስ ደብረ ደሞን ለማስተዳደር ተሾመዋል፡፡ ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡ #_ እግዚአብሔር አምላክህ አንተን መርጦሃልና እንደ ኹለቱ ነቢያት ለተከወነ መሠወርህ ሰላምታ የሚገባህ ደግ አገልጋይና የታመንህ መጋቤ ቤቱ ቅዱስ አረጋዊ ሆይ በዐሥሩ አህጉር ተሹመህ ኀምስቱን መካልይ የተቀበልህ አንተ አይደለህምን?፡፡ _# #መልክአ አቡነ አረጋዊ ፨#ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ #ዕረፍታቸው_፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው(ቅዱስ ያሬድ ለእመቤታቸን ( ትዕግሥትኪ ፈድፈደ እምትዕግሥተ ኢዮብ ጻድቅ ፤ወእማርቆስ #ዘቶርማቅ ፤ ወገብረ ክርስቶስ መርዓዊ ተወካፌ ሕማም መጽዕቅ፡፡ ) ብሎ እንደጻፈው ቅዱስ ቶማስ ዘቶማርቅ እንደ ኢዮብ ታጋሽ የሆነ ጻድቅ ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔር ሰው የተባለ ትዕግሥኛው ቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ ፠፠ ፠፠፠ ፠፠፠ ፠ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#ጥቅምት_14 አቡነ #_ አረጋዊ የተሰወሩበት፤ ቅዱስ #_ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍት፤ ቅዱስ #_ ሙሴ_እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ #_ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ጥቅምት 14 ፤ አቡነ አረጋዊ ( ዘሚካኤል ) ወቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር #አቡነ_አረጋዊ (#ዘሚካኤል) ፠ ከእንጦንስ ከመቃርስ እና ከጳኵሚስ የምንኵስና ሐረግ አራተኛ ትውልድ ናቸው፣ ፠ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም 6 ሺህ የደረሱ ናቸው፣ ፠ ከቅዱስ ያሬድ ጋር እጅግ ይዋደዱ የነበሩ ፣ ዝማሬውንም ለመስማት ከጐንደር ለመጣ ሲል በጸጋ አይተው ደብረ ዳሞ ላይ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ሰብሰበው ይጠብቁ የነበሩ ፡፤ ፠ ታላላቅ የኢትዮጵያ ነገሥታትን ለባረኩ ይመጠላቸው የነበረ .. ፠ አጼ ገብረ መስቀል በተመስጦ የቅዱስ ያሬድን እግር በጦር በወጋው ጊዜ ታለቅ ግብዣን አድርገ የዛኔም አቡነ አረጋዊ ቀድሰዋል፣ ቅዱስ ያሬድም ዘምሯል ፤ ታላቅ ሥርዓትንም አስጀምረዋል፡፡ ___________________________________________ ፠ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው #ይስሐቅና ከእናቸው #እድና የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው ፤ ወንድሞቹም #ቴዎድሮስ እና #ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡ ፠ የቀድሞው ስማቸው #ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡ ፠ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኵሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ #እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡ ፠አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ #_ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ )፣ አባ #_ ይምዓታ (ገዳማቸው በኃውዜን የሚገኝ (ትግራይ) ከሀገረ ቁስያ፣ አባ #_ ገሪማ ከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ፣ ከአንፆኪያ አባ #_ ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ #_ ጉባ፣ ከእስያ አባ #_ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ #_ ጴንጠሌዎንከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ) ፣ ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትንማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን #ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸውሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ #አረጋዊ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትም ቀን ጥቅምት 11 ነበር ፡፡ አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደ ላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም ፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ ቢዚያችም ሰዓት ተራራዋ ደብረ ታቦርን መስላ ነበር:: በዚህችም ላይ ንጉሥ አጼ ገብረ መስቀል ቤ/ክ ከአነጹ በኃላ የቅዳሴ ቤቱ ዕለት አቡነ አረጋዊ ቀድስው ንጉሡም ሠራዊትም ሕዝቡም ጳጳሳቱም ጭምር ሥጋ ወደሙን ተቀብለዋል፡፡ ንጉሡም በረከተን ከአባታችን ተቀብሉ ወደ አኵሱም ተመልሷል፡፡ ሲመለስም ሰርቶት የነበረውን ድልድላይ ላፍረሰው ወይ ሲላቸው ዳሕምሞ ብለውታል ትርጕሙም ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ፡፡ ከዚ በመነሳት ዳሞ ተብላለች፡፡ እግዚአብሔርም ሰማያዊ ኅብስት ትሁነህ ብሎ ደብረ ዳሞን ስጥቶዋቸዋል ይህም በመንፈስ ለሚወለዱት ልጆቹ እስከ ዘለዓለም ማርፍያ እንድትሆን ነው ፡፡

የአቡነ አረጋዊ ፣ የገብረ ክርስቶስን እና የሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ ንግሥ ----- ፨ደብራችን ሲመሠረት ይቀድሱ እና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ መነኮሳት ናቸው፡፡ ፨በደብራችን የገብረ ክርስ
የአቡነ አረጋዊ ፣ የገብረ ክርስቶስን እና የሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ ንግሥ ----- ፨ደብራችን ሲመሠረት ይቀድሱ እና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ መነኮሳት ናቸው፡፡ ፨በደብራችን የገብረ ክርስቶስ በዓል መከበር ከጀመረ ከ100 ዓመት በላይ አስቆጥራል፡፡ ፨የየሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር እና የሁለቱ ቅዱሳን ታቦት በድርብነት አለ ፡፡ በደብረ ዳሞ ፈዋሽ የሆነው የበሶ እምነት እንሚሰጠው ሁሉ የደብራችን ካህናት እና የአጥቢያችን እናቶች በየዓመቱ ይህንን ተመሳሳይ ሥርዓት ይፈጽማሉ፡፡ ፨ በዓለ ንግሡን በቀጨኔ ደብረሰላም መድኀኔዓለም እና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ በማኀሌት በሰዓታት በኪደን በቅዳሴ በዑደተ ታቦተ ሕጉ ያክብሩ ፡፡