ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 399 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 564 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 183 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 399 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 21، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.61‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.23‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 327 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 576 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 399
المشتركون
+124 ساعات
+307 أيام
+2130 أيام
أرشيف المشاركات
#ጾመ_ነቢያት_ (#የገና_ጾም_) የ2014 ዓ.ም. የገና (የነቢያት) ጾም፤ ፠ #ጾሙ_ኅዳር_15_ይጀምራል_!! #Share ፠ ከ7ቱ አጽዋማት (ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ፍልሠታ፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌ ና ጾመ ገሃድ) መካከል አንዱ ነው፡፡ ፠ ኅዳር 15 ቀን ተጀምሮ እስከ ልደት ዋዜማ ለአርባ ሦስት ቀናት የሚጾም ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ ፠ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤ † ፩. #ጾመ_አዳም_፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገት ከተባረረ በኋላ; በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ፤ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡ † ፪. #ጾመ_ነቢያት_፤ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8, ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል:: † ፫. #ጾመ_ሐዋርያት_፤ ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡ † ፬. #ጾመ_ማርያም_፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡ † ፭. #ጾመ_ፊልጶስ_፤ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡ † ፮. #ጾመ_ስብከት_፤ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡ † ፯. #ጾመ_ልደት_፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡ ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ጻድቁ አባ ተክለሐዋርያት ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉበት ደብረ ጽሙና ገዳም ተዘረፈ ኅዳር 12 ቀን 2014 ዓ. ም. ማንነታቸው ባልታወቀ አካላት በዚያ የሚገኙ መነኰሳትን ድብደባ በማድረስ እና በማንገላታት በገዳሙ ዝርፊያ ፈጽመዋል፡፡ በመጡበት ሠዓት አበምኔቱን እና በጸሐፊነት የሚያገለግሉትን እማሆይ ፈልገው አላገኟቸውም ፤ ለውል ባልታወቀ ጉዳይም ሲፈልጓቸው እንደነበር ተረድተናል፡፡ ፠የቤተ መቅደሱን ቁልፍ ተቀብለው የቻሉትን ያኸል ዘርፈዋል፡፡ ፠ገንዘብ ካዝና ሰብረው ወስደዋል፡፡ ፠ገዳሙ በሕጋዊነት የተረከባቸውን ለመጠበቂያ አገልግሎት የሚውሉትን መሣሪያዎች ወስደዋል፡፡ ፠በጥበቃው ላይም ድብደባ ፈጽመዋል ፠ወደ መቅደስም ገብተው ያገኙትን ሁሉ ሲወስዱ አምሽተው ሄደዋል ፡፡ ከዚህ በፊት ኀዳር 27 እንደጻፍንላቹህ፡፡--› https://t.me/medihanaelem/5361 የአቡነ ተክለ ሐዋርያት ገዳም ፤ ገዳመ ደብረ ጽሙና የሚገኘው በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ነው ፡፡ አቡነ ተክለሐዋርያት በምድረ አፋር (ለ14ዓመታት ) ፣ እንዲሁም በምድረ ሸዋና ጐጃም የሰበኩና ያስተማሩ አባት ናቸው፡፡ የአባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ ልጅ ናቸው ፡፡ 15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወለዱና በዘመኑ ካሉ ዐበይት ጻድቃን አንዱ ናችው ደብረ ጽሙና ✤ 318ቱ ሊቃውንት በ395 ዓ.ም እንደጎበኟት የሚነገርላት፣ ✤ ስውራን ዋሻዎች እና እልፍ አእላፍ ስውራን ቅዱሳን ያሉባት ፣ ✤አባታችን ተክለሐዋርያት ብዙ ተጋድሎ ያደረጉበት መና እየወረደላቸው ይመገቡባት የነበርች ፣ ✤እርኵሳን መናፍስት በአባታችን ጸሎት የተባረሩባት ፣ ✤እንስሶቹ ሳይቀር ቦታ እየመሩ እንግዳ የሚቀቡሉባት ፣ ፣ ✤ንግሥት ዘውዲቱ እንደምትነግሥ ትንቢት ተነግሮላት ቤ/ክቲያን በዚው ያሰራችበት ይህም የቅድስት ሥላሴ ቤ/ክርስቲያን የ105 ዓመት ዕድሜ ያለው ነው ፡፡ ከገዳሙ መልክአ ምድር አቀማማጥ አንፃር ይህ ዝርፊያ ገዳሙ መልሶ እንዲቋቋም ለማድርግ ለአባቶቻችን እጅግ ፈተና ስለሚሆንባችው ከታች በጠቀሰው አካውንት የቻላቹሁትን መርዳት ትችላላቹህ፡፡ ( ለመርዳት 1000324249633 አቡነ ተክለሐዋርያት ገዳም ) ፡፡ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

✤ 318ቱ ሊቃውንት በ395 ዓ.ም እንደጎበኟት የሚነገርላት፣ ✤ ስውራን ዋሻዎች እና እልፍ አእላፍ ስውራን ቅዱሳን ያሉባት ፣ ✤አባታችን ተክለሐዋርያት ብዙ ተጋድሎ ያደረጉበት መና እየወረደላቸው ይመገቡባት የነበርች ፣ ✤እርኵሳን መናፍስት በአባታችን ጸሎት የተባረሩባት ፣ ✤እንስሶቹ ሳይቀር ቦታ እየመሩ እንግዳ የሚቀቡሉባት ፣ ፣ ✤ንግሥት ዘውዲቱ እንደምትነግሥ ትንቢት ተነግሮላት ቤ/ክቲያን በዚው ያሰራችበት ይህም የቅድስት ሥላሴ ቤ/ክርስቲያን የ105 ዓመት ዕድሜ ያለው ነው ፡፡ በአሁነ ሰዓት አርጅቶ የሚገኝ ( ለመርዳት 1000324249633 አቡነ ተክለሐዋርያት ገዳም ) ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ጻድቁ አባ ተክለሐዋርያት ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉበት ደብረ ጽሙና ገዳም ተዘረፈ ኅዳር 12 ቀን 2014 ዓ. ም. ማንነታቸው ባልታወቀ አካላት በዚያ የሚገኙ መነኰሳትን ድብደባ በማድረስ እና በማንገላታት በገዳሙ ዝርፊያ ፈጽመዋል፡፡ በመጡበት ሠዓት አበምኔቱን እና በጸሐፊነት የሚያገለግሉትን እማሆይ ፈልገው አላገኟቸውም ፤ ለውል ባልታወቀ ጉዳይም ሲፈልጓቸው እንደነበር ተረድተናል፡፡ ፠የቤተ መቅደሱን ቁልፍ ተቀብለው የቻሉትን ያኸል ዘርፈዋል፡፡ ፠ገንዘብ ካዝና ሰብረው ወስደዋል፡፡ ፠ገዳሙ በሕጋዊነት የተረከባቸውን ለመጠበቂያ አገልግሎት የሚውሉትን መሣሪያዎች ወስደዋል፡፡ ፠በጥበቃው ላይም ድብደባ ፈጽመዋል ፠ወደ መቅደስም ገብተው ያገኙትን ሁሉ ሲወስዱ አምሽተው ሄደዋል ፡፡ ከዚህ በፊት ኀዳር 27 እንደጻፍንላቹህ፡፡--› https://t.me/medihanaelem/5361 የአቡነ ተክለ ሐዋርያት ገዳም ፤ ገዳመ ደብረ ጽሙና የሚገኘው በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ነው ፡፡ አቡነ ተክለሐዋርያት በምድረ አፋር (ለ14ዓመታት ) ፣ እንዲሁም በምድረ ሸዋና ጐጃም የሰበኩና ያስተማሩ አባት ናቸው፡፡ የአባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ ልጅ ናቸው ፡፡ 15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወለዱና በዘመኑ ካሉ ዐበይት ጻድቃን አንዱ ናችው ደብረ ጽሙና ✤ 318ቱ ሊቃውንት በ395 ዓ.ም እንደጎበኟት የሚነገርላት፣ ✤ ስውራን ዋሻዎች እና እልፍ አእላፍ ስውራን ቅዱሳን ያሉባት ፣ ✤አባታችን ተክለሐዋርያት ብዙ ተጋድሎ ያደረጉበት መና እየወረደላቸው ይመገቡባት የነበርች ፣ ✤እርኵሳን መናፍስት በአባታችን ጸሎት የተባረሩባት ፣ ✤እንስሶቹ ሳይቀር ቦታ እየመሩ እንግዳ የሚቀቡሉባት ፣ ፣ ✤ንግሥት ዘውዲቱ እንደምትነግሥ ትንቢት ተነግሮላት ቤ/ክቲያን በዚው ያሰራችበት ይህም የቅድስት ሥላሴ ቤ/ክርስቲያን የ105 ዓመት ዕድሜ ያለው ነው ፡፡ ከገዳሙ መልክአ ምድር አቀማማጥ አንፃር ይህ ዝርፊያ ገዳሙ መልሶ እንዲቋቋም ለማድርግ ለአባቶቻችን እጅግ ፈተና ስለሚሆንባችው ከታች በጠቀሰው አካውንት የቻላቹሁትን መርዳት ትችላላቹህ፡፡ ( ለመርዳት 1000324249633 አቡነ ተክለሐዋርያት ገዳም ) ፡፡ ✤#_አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት_ዘደብረ_ጽሙና_(_ዘገበርማ) አቡነ ተክለሐዋርያት በምድረ አፋር(ለ14ዓመታት)፣ እንዲሁም በምድረ ሸዋና ጐጃም የሰበኩና ያስተማሩ አባት ናቸው፡፡ ከአባታቸው እንድርያስ (የአናዕርት ሃገረ ገዥ)ና ከእናታቸው እሌኒ፤ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወለዱና በዘመኑ ካሉ ዐበይት ጻድቃን አንዱ ናቸው፡፡ ገና በእናታቸው ማኅጸን ሳሉ አጋንንትን ያቃጥሉና ያጠፉም ነበር፡፡ #Like እና #share ያድርጉ *በዲቁናም ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመግባት እስከ ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ ደርሰዋል፤ ሥውራን የኾኑ ቅዱሳንም እየተገለጡ ምሥጢራትን ይነግሯቸው ነበር፡፡ ከስግደታቸው ብዛት የተነሣ የእጆቻቸው አጥንቶች እስከ መሠበር፥ ከቁመታቸውም ብዛት የተነሣ እግሮቻቸው እስከማበጥ ደርሰዋል፡፡ *ሲቀመጡና ሲሰግዱ የጌታችንን መከራ እንዲያስቡ፤ 8 ጦሮች ያሉበትን ሰንሰለት በአራቱ አቅጣጫ በወገባቸው ታጠቁ፡፡ ከልደት፣ ከጥምቀትና ከትንሣኤ በቀርም ከወገባቸው አይፈቱም ነበር፡፡ *ቅዱስ ሚካኤልም ዕፀ ገነት አምጥቶ ካሸተታቸው በኋላ ምድራዊን ነገር ለመቅመስ የሚጸየፉ ኾኑ፡፡ *ቅስናን እንዲሾሙ አበምኔቱ ሲጠይቃቸው እምቢ በማለታቸው ወደ ሊቀ ጳጳሱ መልእክት አድርሱልኝ ብለው በላኳቸው ጊዜ ጳጳሱ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ቅስናን ሹሟቸዋል፡፡ *ወደ ደብረ ጽሙና ጻድቁ አቡነ አትናቴዎስ መቃብር ሂደው በሚጸልዩበት ጊዜም ብርሃን ይወርድላቸው ነበር፤ እግራቸው በረገጠበት ቦታም ጸበል ፈልቆላቸው ቦታውን ላሳየቻቸው እግዚእ ክብራ ለተባለች ጻድቅት በጽዋ ሞልተው ሰጧት እርሷም መካን ለነበረችው አገልጋይ ብትሰጣት ልጅ ወለደች፤ ይህ ጠበላቸው እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ገቢረ ተዓምራትን እየሠራ በገዳማቸው ገኛል፡፡ መልአኩም ወደ በረሃ እንዲወርዱ በነገራቸው መሠረት ወደ ምድረ ሐጋይ በመሄድ ለ41ዓመታት በጽኑ ተጋድሎ ቆይተዋል፡፡ ወደተለያዩ ገዳማት በመሄድም 40 ቀን (ከሰንበት ውጪ ሳምንቱን ሙሉ እያከፈሉ) ይጾሙና ይጸልዩ ነበር፡፡ ወደ ታላቁ ገዳም ወደ ዋልድባ ገብተው ሲወጡም ወደ ድባብ ገዳም ገዳም ሄደው 40ቀን ሲጾሙ ጌታችን ወዳልተጠመቁ ሄደው እንዲያስተምሩ አዝዟቸው አስተምረዋል፡፡ * ጻድቁ 3ት ነገሮችን እፈልጋለሁ፤ እነርሱም፤ ከሐሜት መራቅን፤ ክፉ ነገርን ከማየት መራቅን፤ ከንቱ ነገርን ከመስማት መራቅን፤ እያሉ ይናገሩ ነበር፡፡ *ሰማዕት እንዲኾኑም ይለምኑ ነበረ፤ እመቤታችንም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በመምጣት ‹‹የጳውሎስ አበባ፥ የጴጥሮስ ፍሬ፥ የልጄ ተክል›› የለመንከውን ታገኛለህና በርታ አለቻቸው፤ አርሳቸውም በነገረ ሠሪ ከንጉሡ ጋራ እንዲጣሉ አደረጓቸው፤ በንጉሡ ዘርዐያዕቆብና በሠራዊቶቻቸው ብዙ መከራን ተቀብለው በ71 ዓማታቸው በሰማዕትነት አረፉ ፡፡ አመቤታችን ግን ለአባታችን አጼ ዘርዓ ያዕቆብን ይቅር በልልኝ ልጄ ፊት ያደረሰብኝን በደል እይልኝ አትበል አላችው ፡፡ አባታችንም ስለ ርኅራሄዋ ተደንቆ እመቤቴ ሆይ አኔስ ይቅር እላለሁ ነገር ግን ያንቺ ጸሎት ሁላችንንም ይማረን ብሏታል፡፡፤ ከ14 ዓመት በኋላም በንጉሡ ዘርዐ ያዕቆብ ወንበር ልጁ በዕደ ማርያም በነገሠ ጊዜ ሥጋቸውን አፍልሶ በደብረ ጽሙና በክብር አሳረፈው፡፡ ጻድቁ በታላቁ ገዳማቸው በደብረ ጽሞናና በደብረ ሊባኖስ አጠገብ በሚገኘው በአጋት መድኀኔ ዓለም ክብረ በዓላቸው ይከበራል፡፡ ***ጻድቁ በተባሕትዎም ኾነ በትሩፋት እጅግ የተደነቁ አባት ነበሩ፡፡ ለአብነትም ያህል፤ * በትራቸው እንደ ሙሴ በትር ተዓምራትን ታደርግ ነበር፡፡ በብርሃን ሠረገላም ይጓጓዙ ነበር፡፡ * ክርስቶስን በመከራው ይመስሉት ዘንድ ዘወትር ይተጉ ነበር፤ *ሥጋ ወደሙ የተቀበለ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲያስመልሰው ተመልከተው ሁሉ ተጸይፎ ሲሸሽ እሳቸው ግን የፈጣሪን ሥጋና ደም በመመልከት ደስ እያላቸው እንደ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ተመግበውታል፤ በዚህ ጊዜም ጌታ ከሰማይ ወርዶ በግንባራቸው ላይ ፀሐይን ስሎባቸዋል፤ በዚህ ምክንያትም ፊታቸው ያበራ ነበር፡፡ *በገዳማቸው አንድ ዶሮ ለእንግዳ ሊያርዱት ሲሉ አፍ አውጥቶ ‹‹በአባ ተክለ ሐዋርያት ተማጽኛቹሃለሁ›› በማለቱ ትተውታል፡፡ ✤ንግሥት ዘውዲቱ እንደምትነግሥ ትንቢት ተነግሮላት ቤ/ክቲያን በዚው ያሰራችበት ይህም የቅድስት ሥላሴ ቤ/ክርስቲያን የ105 ዓመት ዕድሜ ያለው ነው ፡፡ በአሁነ ሰዓት አርጅቶ የሚገኝ ( ለመርዳት 1000324249633 አቡነ ተክለሐዋርያት ገዳም ) ፡፡ Like እና share ያድርጉ #ደብረ_ጽሙና

ኅዳር 13 በዓለ እግዚአብሔር አብ ወአእላፍ መላእክት ፤ በደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር ካቴድራል የዚህ ደብር ታሪክ እነዲህ ነው፤ በደብሩ የሚገኝው የእግዚአብሔር አብ ታቦት በደብራችን በቀጨኔ ደብረሰላም ይገኝ ነበር፡፡ በታላላቅ አባቶችም ይህ ታቦት ወጥቶ ወደ አሁኑ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ ሥፍራ እንደሚሄድ የበቁ አባቶች ይናገሩ ነበር፡፡ እንደተናሩትም ሐምሴ 29 ፤1969 ዓም ታቦተ ሕጉ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወጥቶ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ቤት አረፋ፣ ቤተhርስቲያኑም እራሱን ችሎ እስኪቆም ድረስ የደብራችን የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም አገልጋዮች በቅዳሴ በማኀሌት በሰዓታት ያገለግሉ ነበር :: ከዚህም በኃላ ጥር 19 ቀን 1971 ዓ.ም የመጀመሪያው ቤተከርስቲያን አልቆ ተመርቋል፡ የቤተክርስቲያኑ ዲያቆናት ፣ ቀሳውስት እና መሪጌቶችም በጊዜያዊነት ተቀጠርው ነበር ሆኖም የአገልግሎት ፍቅር ያደረባቸው የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቃውንት አልግሎታቸውን አላቆም ነበር። ታላቁ ሊቅ አለቃ ኤልያስ ነቢየ ልዑል ከመኖርያ ቤታቸው ቀጨኔ ድረስ በምጣት ለደብሩ ታላቅ አሰተዋጾዖ አድርገዋል። እሁን ያለው ሕንፃ ቤ.ክ የደብተራ ኦሪት እና የኖኀ መርከብን ቅርጽ ይዞ በቅድስቱ አካባቢ ያለው አሠራር ደግሞ ክቧን ቤ.ክ ሆኖ ተሰረቶ በ2009 ዓም ብፁዑ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ተመረቋል፡፡ የቅዱሰ እግዚአብሔር አብ ታቦትም ኅዳር 13 እልፍ አእላፋት መላእክት በሚከሩበት ዕለት ይከብረል። በዚሁ ደብር ኅዳር 25 የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በዓልም ይከበራል ( ታቦቱ በድርብነት አለ) የእግዚአብሔር ቸርነት የአእላፍ መላእክት ተራዳኢነት አይለየን! #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#አንኳን_ለቅዱስ_አግዚአብሔር አብ በዓልና_ለአእላፍ_መላእክት_በዓለ_ሢመት እንዲሁም #ቅዱስ_ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 ጀምሮ እስከ 13 ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን ለሚለምንበት) በዓል በሰላም አደረሳቹህ፡፡ ፨ ፨ ፨ #ኀዳር_13 ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት #አእላፍ መላእክት እየተባለ ይጠራል ፤ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከብሩብት ቀን ነው እንዚህም ሥጋ የሌለቸው ረቂቃንና ለዓለም ሁሉ የሚማልዱ ናቸው ፡፡ #Share ያድርጉ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ 100 በክፍለ ነገድ 10 አድርጓቸዋል ፡፡ በ3 ሰማያትና በ10 ዓለማት ላይም ይገኛሉ፡፡ መላእክት ያሉባቸው ከተሞች #ኢዮር #ራማ #ኤረር ይባላሉ ፡፡ አሥሩ ነገዶች ከነአለቆቻቸው አንዲህ ናቸው 1. #አጋዕዝት (ቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል የነበረ ፤ አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ስር ናቸው) 2. #ኪሩቤል (አለቃቸው ቅዱስ #ኪሩብ ፤ ለበለጠ ኀዳር 7 የጻፍነውን ይመልከቱ) 3. #ሱራፌል (አለቃችወ ቅዱስ #ሲራፊ ፤ ለበለጠ ኀዳር 24 ይጠብቁን) 4. #ኃይላት (አለቃቸው ቅዱስ #ሚካኤል ) 5. #አርባብ (አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ) 6. #መናብርት (አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል) 7. #ሥልጣናት (አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ) 8. #መኳንንት (አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ) 9. #ሊቃናት (አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል) 10. #መላእክት (አለቃቸው ቅድስ አናንኤል) ናችው፡፡ ከእነዚህም ፨ አጋዕዝት ፣ኪሩቤል ፣ ሱራፌልና ኃይላት መኖርያቸው በኢዮር(3ኛው ሰማይ ) ነው ፡፡ ፨አርባብ ፣መናብርትን ሥልጣናት መኖርያቸው በራማ ነው ፡፡ ፨መኳንንት ፣ሊቃናት ፣ መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር ነው (1ኛው ሰማይ ) ———- (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤ #ሚካኤል_ወገብርኤል፥ #ሱራፌልወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥ #ዑር(ራ)ኤል_ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ #ሱርያል_ወፋኑኤል፥ #አፍኒን_ወራጕኤል፥ #ሳቁኤል_ወአቅናኤል፥ #ብርናኤል_ወሱባኤል፥ #ፍናኤል_ወሰላታኤል፥ #ሰዳካኤል_ወኤልናኤል፥ #አናንኤል_ወኢየሩማኤል፥ #ግርማኤል_ወድርማኤል ፥ #ድማህኤል_ወአድማኤል፥ #ሙራኤል_/ምናቴር_አብያቴር/፥ #ሱታ(ስቱ)ኤል_ወሱርያል፤ ……. ፨ ፨ ፨ ፨ የመላእክት ተፈጥሮ እመኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደመኖር ) ነው ፡፡ አይራቡም አይጠሙም ፤አይዋለደሙ ፣ አይሞቱም ፣ ዕረፍት የላቸውም ፤ምስጋናቸው እረፍታቸው ፤እረፍታቸው ምስጋናችው ነው አንጂ(አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ) እንዲል፡፡ ተፈጥሯቸው እጅግ ረቂቅ ነው፡፡ ተግባረቸውም ዘውተር እግዚአብሄርን ማመስገን ነው፡፡ —— #መላአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም ፤ ለመዓትም ይላካሉ፡፡ ምሕረትን ያወረዳሉ ፡፡ ልመናን ያሳርጋሉ ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ አንዲዚሁም ሁሉ ወቅትንም የሚቆጣጠሩ አሉ ፤ ስለ ሰው ልጆች ይማልዳሉ (ዘካ 1÷12 ) ምሥጢርም የሚገልፁም አሉ(ዳን 9÷21) መላእክት ተራዳኢም ናቸው (ኢያ 5÷13)፣ እነዳንሰናክል ይጠብቁናል (መዝ 90÷11 ) ፣ያድናሉ ( መዝ 33÷7 ) ፣የፀጋ ስግደትም ይገባቸዋል (መሳ 13÷20) በፍርድ ቀንም ኀጥአንን ከጻድቃን ያለያያሉ (ማቴ 25 ÷31) እነሆ እግዚአብሄር ይፈርድዘንድ ቅዱሳን መላእክቶቹን አስከትሎ ይመጣል እንዲል ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ፨፨፨ እልፍ አእላፋት ወትእልፊት ቅዱሳን ንጹሐን መላእክት ቆሙ በአገልግሎት ጸንተው በአንድነት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አምላክ በማለት፡፡ ምልጃቸው እና ጠብቆታቸው አይለየን አሜን ፡፡ —————— ኀዳር 13 ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ ከፎቶ ጋር …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like