ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 378 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 573 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 378 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 32، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 22.44‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.50‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 449 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 461 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 20.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 378
المشتركون
-424 ساعات
-257 أيام
+3230 أيام
أرشيف المشاركات
ግራ አጋቢው የኮሮና ጠባይ !! (በዘመድኩን በቀለ፡፡) *~★★~* #ETHIOPIA | ~ እኔምለው ጤፍ ግን ስንት ገባ ? ••• ቀደም ባለው ወራት አንድ በኮሮና የተያዘ ሰው ተገኘ ተብሎ ዜናው ወሬው ከተሰማ ሀገር ሙሉ ዝግ ይሆን ነበር። በሰማይም፣ በየብስም፣ በባህርም እንቅስቃሴ አይኖርም ነበር። ጦር ሰራዊት አየር ሀይል፣ ምድር ጦር በተጠንቀቅ ይቆም ነበር። ነበር ነው ያልኩት። ••• የሰው ልጅ ከቤቱ እንዳይወጣ፣ በአደባባይ እንዳይታይ፣ እጁን በሳሙና እንዲታጠብ፣ ሳኒታይዘር እንደ እምነት እንዲቀባ፣ እንዲተሻሽ ይደረግም ነበር። በግድም፣ በዱላ በጥፊም ከቤቱ ይቀመጥ ዘንድ ይታዘዝ ነበር። አፍህን ሸፍን፣ ርቀትህንም ጠብቅ ትእዛዙ ገራሚ ነበር። ••• ትምህርት ቤቶች ይዘጉ፣ ትራንስፖርት ይጠረቀም፣ ሆተል፣ ኪዮስክ፣ መዝናኛ፣ መገናኛው ሁሉ ይጠረቀም ነበር። ( በኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ትምህርት ቤት እስከአሁን ዝግ ነው። ቡናቤት ግን ለአዲስአበባ ፖሊስ የቀን ገቢውን በጉቦ መልክ እያካፈለ እስከአሁን ክፍት ናቸው አሉ። ፖሊሶች የአዲስ አበባ ቡናቤቶችን በየወረዳው ተከፋፍለው የቀን ገቢ ይከፋፈላሉ አሉ። ደካማ መንግሥት መገለጫው ፖሊሱ ሌባና ያገኘውን ወጋሪ፣ ቀማኛ ይሆናል። ) ••• በቀደመው ወራት የኮሮና ሟቾች የዜናቸው ብዛት ለሰሚው ያስደነግጥ ነበር። የሟቾች ቀብራቸው ባይታይም የሟቾቹ ቁጥራቸውግን አስደንጋጭ ነበር። የኦሎምፒክ ውድድር ይመስል ነበር። ቻይና አንደኛ፣ ጣልያን አንደኛ፣ ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ አንደኛ 50 ሺ፣ መቶ፣ ሺ ሲባል ለሰሚው ያስደነግጥ ነበር። በሽታው አለ። የሞቱም፣ የታመሙም፣ የዳኑም አሉ። ነገር ግን ኡን ምንተገኝቶ ይሆን? ቀዝቀዝ ያሉት እነ አማሪካ። ••• ጸሎቱም ልዩ ነበር። እንባ የተቀላቀለበት፣ መንበርከክ ያለበት፣ ደረት እየተደቃ፣ እየወደቀ እየተነሣ ጸሎት ይደረግ ነበር። ቴሌቭዥን ሬድዮኑ ሁሉ ጸሎት፣ ንስሐ ያውጅ ነበር። ቤተሰብ ከመኝታ በፊት አደግድጎ ለጸሎት ይቆም ነበር። ያው ነበር ነው እንግዲህ። አሁንስ? ••• በአማሪካ ሰዉ ከቤቱ ተቀምጦ ይነገር የነበረው የሞት መርዶ አሁን ሰዉ ለሰልፍ ከቤት ወደ ደጅ ወጠቶ በደጅ ውሎ እያደረ፣ ከፖሊስ ጋር ሲተሻሽ፣ ሲተቃቀፍ ውሎ እያደረ፣ የሟች ዜና መጥፋቱ፣ የኮሮና ዜና ቁጥሩ መቀነሱ፣ ጭራሽ ዜናው ያለመኖሩን ስታይ የሆነ ነገር ጠርጥር ጠርጥር ያሰኝሃል። መድኃኒቱ ሰልፍ ነበር እንዴ? ሆሆይ!! ••• በኢትዮጵያም እንደዚያው ነው። የቀደመው ፍርሃት ጠፍቷል። የቀደመውም የሚድያ የጸሎት መርሐግብርም በወሀቢይ እስላም ድንቁርናና ጥጋብ ሌሎች ሃይማኖቶችን በስብከት ስም በመሳደቡ ምክንያት አሁን ቆሟል፣ ተቋርጧል። ይቅርታም አልጠይቅም ብሎ ሁሉን ነገር እኔ ከሞትክ ሰርዶ አይብቀል ብሎ አፈር ከደቼ አብልቶታል። ••• በኮሮና የተያዙ ሰዎች የሞት ቁጥር በዜና ሲነገር እያየን ነው። ቁጥሩ በአዲስ አበባ ከፍ ብሏል። አሻቅቧል። ሟቾቹ በቁማቸው ሳይመረመሩ አስከሬናቸው እየተመረመረ በኮሮና የመያዛቸው ዜና መነገሩ ደግሞ የበለጠ አስቂኝ፣ አስገራሚም ነገር ሆኗል። ይታያችሁ አስከሬን መርምረህ ሀገር ምድሩን ስታሸማቅቅ። በቁም ሳትመረምር አስከሬን እየመረመረች መርዶ የምታረዳ ብቸኛ የምድራችን ጉደኛ ሀገርም ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አትቀርም። ••• ደግሞም ደግሞ የታከለ ኡማን አፉን ሳይሸፍን በድፍረት በከተማዋ ውስጥ መንቀሳቀስ ስታይ፣ የዐቢይ አሕመድን 5ቢልዮን ችግኝ ትከሉ ማለትን ስታይ፣ የህወሓትን ማንአባቱ ያገባዋል? ምርጫ በክልሌ አደርጋለሁ የምን ኮረና ነው ማለቷን፣ እስቲ የሚናገረኝን አያለሁ ማለቷን ስታይ፣ ( ለምርጫ መስፈጸሚያ ብሩ እንኳን አላት። አይቸግራትም። በኮንቴነር አይደል እንዴ የምታስቀምጠው። ብሩ ከተቀየረ ነው ህወሓት የምትከስረው። እንጂ አሁን እንኳ በፈረንካ በኩል ችግር የለባትም።) እናም ይሄን ይሄን ስታይ ኮረና የለም እንዴ? ትልና ጠርጥር ጠርጥር ያሰኝሃል። ••• እዚህ ባለሁበት በሀገረ ጀርመን ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በቀር ሁሉ ነገር እንደ ድሮው ነው። መስክ የሚደረገው እንኳ ትራንስፖርትና ሱፐር ማርኬት ሲገባ ብቻ ነው። በባለፈው ሳምንት ከአንድ ጓደኛዬ ጋር በምንኖርበት ከተማ ወደ አንዲት ፒዛ ቤት ገብተን ነበር። እናም ሁሉም ነገር እንደድሮው ነው። ወይ ኮሮና። ••• ለማንኛውም በአማሪካ፣ በአውሮጳ፣ በካናዳ ከባድ ሰልፎች ተደርገዋል። በአሜሪካ እስከአሁንም ሰልፉ አልቆመም። የኮሮና ዜና ግን ቆሟል? በኢትዮጵያ በኮሮና የሚያዘው ሰው ዜና ከፍ ብሏል። በኢትዮጵያ ሟቾች በኮሮና መሞታቸው የሚታወቀው አስከሬን ሲመረመር ብቻ ነው። እንደ ዜናው አዲስ አበባ የኮሮና ማከፋፈያ ሳትሆን አልቀረችም። ••• እስቲ የዛሬውን የአዲስ አበባ የኮሮና ዜና እንመልከት። ደግሞ የሟቾች ስም አይነገርም። ዕድሜና ጾታ ብቻ ነው። እንዴት እንደሚቀበሩም አይታወቅም መሰለኝ። በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 47 ደረሰ! ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የሰባት (7) ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸውና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 47 ደርሷል። ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ 1. የ75 ዓመት ወንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ በህክምና ማዕከል በህክምና ላይ የነበሩ። 2. የ70 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባቸው። 3. የ80 ዓመት ወንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባቸው። 4. የ29 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባት። 5. የ48 ዓመት ወንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘበት። 6. የ85 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባቸው። 7. የ21 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባት። • ለማንኛውም፦ • ጸሎቱ አይቋረጥ። • ንስሐ እንግባ • እጃችንን በሳሙና እንታጠብ • ርቀታችንን እንጠብቅ • አፋችንን እንሸፍን። ፈ ቀ ቅ ታ !! ፨

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኃ ግንቦት ፱/፳፻፲፪ ዓ
+1
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኃ ግንቦት ፱/፳፻፲፪ ዓ.ም ጋብቻህን የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታችን አባል ወንድማችን፤ #ኢዩኤል_ተዘራ #ከናፍያድ_ንጋቱ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

** #ፃዓና_በደመና (#ጣና)ና #ማይ_ሹም (#አኵሱም)ን ባሰብን ጊዜ፡፡ 👉 ለጣናና ለአኵሱም ያልሆነ የመንግሥት ገንዘብ (ከሕዝብ ተሰብስቦ) ለማን ሊሆን ነው? 👉 ለጣናና ለአኵሱም ሥራ ያልሠራ መንግሥት ለማን ሊሠራ ነው? 👉 ለጣናና ለአኵሱም ሥራ ያልተባበረ ክንድ ለማን ሊተባበር ነው? 👉 ለጣናና ለአኵሱም ያልሆነ ውይይት ለማን ሊሆን ነው? 👉 ጣንና አኵሱምን መጠበቅ የሚገባው መሥሪያ ቤት ምን እያደረገ ነው?፤ ምንስ እየሠራ ነው???:: #ጣና_፤ ፠ እመቤታችን በስደቷ ወቅት በደመና ተጭና የተጓዘችበት ፠ በ2007 በዩኔስኮ የተመዘገበ ፠ በቀድሞ ዘመን ጎንደር ላይ ያሉ 44ት ታቦታተ ጎንደር ሳይተከሉ በፊት 44ቱ ታቦታተ ጣና የሚባሉ ነበሩ፤ አብዛኛው ጠፍ ሆነዋል፡፡ ለምስክርነትም 44ት ጠበሎች እስከሁን በጣናና ጣና ዙርያ ይገኛሉ፡፡ ፠ ከ40 በላይ ገዳማት፣ አድባራትና ታሪካዊ ቦታዎች፤ በጣና ላይ ባሉ ደሴቶችና በጣና ባሕር ዳርቻ ላይ ይገኛሉ፡፡ እነርሱም፤ ★ በጎንደር ጎርጎራ በኩል 👉 ብርጊዳ ማርያም 👉 ደብረ ሲና ማርያም 👉 መንዳባ ያሳይ መድኀኔ ዓለም 👉 ማርያም ግንብ 👉 ጎርጎራ ግንብ 👉 ገሊላ አቡነ ዘካርያስ 👉 መትራሃ 👉 ባርየ ግንብ (ሚካኤል) 👉 አብርሐ ወአጽብሐ ግንብ 👉 እንፍራንዝ 👉 ቆጋ ልደታ 👉 ጋርኖ ወንዝ ድልድይ 👉 ጉዛራ ግምብ 👉 ሰንዳባ ኢየሱስ 👉 ዋሻ አቡነ እንድርያስ 👉 ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 👉 ጬቅሊ ደሴት 👉 ታራግ ህዳም ማርያም ★👉 በባህርዳር በኩል 👈★ ★ ደቅ ደሴት (የ7ት አድባራት ደሴት) 👉 ናርጋ ሥላሴ 👉 ደቅ ቆላ ቅድስት አርሴማ 👉 ደጋ ቅ/እስጢፋኖስ ወአቡነ ሂሩተ አምላክ ገዳም 👉 ኮታ ማርያም 👉 ዝባድ ኢየሱስ 👉 ጋደና ቅ/ጊዮርጊስ 👉 ጆጋ ቅ/ዮሐንስ ★ በፎገራ 👉 ጣና ፎገራ ቅ/ሥላሴ 👉 ጣና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ገዳም 👉 ቆራጣ ቅ/ወለተ ጴጥሮስ ገዳም 👉 ቆራጣ ጨርቆስ ገዳም 👉 ጎጎቤ ገብርኤልና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ገዳም ★ በልሳነ ምድር ጣና ቂርቆስ ደሴት 👉 ጣና ጽዮን ማርያም 👉 ጣና ቅ/ያሬድ 👉 ደንበዣ ቊስቋም 👉 ርእሰ አድባራት ወገዳማት ጣና ቅ/ቂርቆስ ★ በዘጌ ደሴት 👉 መሐል ዘጌ ቅ/ጊዮርጊስ 👉 አቡነ በትረ ማርያም 👉 ዑራ ኪዳነ ምሕረት 👉 አዝዋ ማርያም 👉 ይጋንዳ አራራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ★ በምፅሌ ደሴት 👉 ምጽሌ ቅ/ፋሲለደስ ★ በአባ ኖብ ድንግል (ሬማ) ደሴቶች 👉 ሬማ መድኀኔ ዓለምና ቅ/ወለተ ጴጥሮስ ገዳም ★ በቅ/ዘዮሐንስ ደሴቶች 👉 ክብራን ገብርኤል (የአባቶች ገዳም) 👉 እንጦንስ ኢየሱስ (የእናቶች ገዳም) ★ በታዴዎስ ደሴት 👉 ደብረ ማርያም ገዳም፤ እንተ ይእቲ ሙፃዕ ለግዮን (የዐባይ ወንዝ ከጣና መውጫ መሿለኪያ) ይገኙበታል። #ማይ_ሹም (አኵሱም) ፨ የሥልጣኔ ማማችን፥ ሕያው ምስክራችን፤ ፨ አንደ ብረት የጠነከረን ግራናይት ደንጊያ አባቶችችን ዕፁብ ድንቅ በሚባል ሁኔታ ለትውልደ ተውልድ እንዲሆን ያቆሙልን ሕያው ምስክር፤ ፨ እንዴት አድርገው፤ በምን ጭነው፤ በምን ዓይነትስ ሁኔታ ተከሉት፤ ….. ዕፁብ ዕፁብ የሚያስብል፤ ነገር ግን .. ፨ ረምሃይ በተባለው የወቅቱ ንጉሣችን የቆመ፤ ፨ ለአኵሱም ጽዮን አጠገቧ ያለ፤ ፨ ዛሬም ድረስ ኢትዮጵ፤ 👉 የጠቢባን መፍለቂያ፥ የሊቃውንት መናኸሪያ፥ የቅዱሳን ሃገር፥ የጥበብ ማዕከል …. አልዋጥ ለሚላቸው ምላሽ መስጫና ማሳፈርያ፤ ፨ ገና እንዳዩት ልቡናዎትን የሚመሰጥ፤ የጥበብ ጫፍ፤ ….. ስለ አኵሱም ስንቱን ተናግረን እንጨርሰዋለን፤ …. ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፱_ #የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንን ሕዝቡን (በካህናት አንጻር)፤ ነገሥታት፥ መኳንንትና መሳፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በምን ሥራ ትዋጋቸዋለህ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ክፉ ሥራችንን ይዘን ወደ ቤተክርስቲያን እንገባለን፡፡ በካህናት መካከል ጠብን እንፈጥራለን፡፡ ሳቅንና ስላቅን ዋዛ ፈዛዛን እንዲያበዙ እናደርጋለን፡፡ በማሕሌትና በቅዳሴ ጊዜ ኩራትን፥ ትምክህትን፥ ትዕቢትን፥ ማንቀላፋትን፥ #ክፉ ሐሳብን በልባቸው እንዲያሳድሩ፤ የቅዳሴ የማሕሌት አገልግሎታቸውን እንዲተዉ እናደርጋቸዋለን፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ከቤተክርስቲያን እንዲሸሹ፥ እንዳያስቀድሱ፥ ከክብረ ምሥጢራት እንዳይሳተፉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ይኸውም የመጨረሻ ዘለዓለማዊ ክብራቸውና ሕይወታቸው የሆነው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ ይህንን የምታደርጉት ለምንድን ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ተስፋ ያደረጓትን መንግሥትና ስርየተ ኃጢአትን እንዳያገኙ ነው፡፡ #በቅዳሴ ጊዜ ኃጢአት የሚሰረይባትና ጸጋ የሚገኝባት ስለሆነ ፥ በሚቀድሱትና በሚያስቀድሱት ሁሉ ላይ ምሕረት ይወርዳልና፡፡ ስለዚህ ስለምንቀናባቸው ጥፋታቸውን እንጠባበቃለን ፣ እንሻለን ፤ ከመልካም ሐሳብ እንዲርቁ እናደርጋለን፡፡ በንጹሕ ልብ ሁነው የሚቀድሱ ካህናትና የሚያስቀድሱ ሁሉ በረከትን እንዳያገኙና የኃጢአት ስርየት እንዳይደረግላቸው እንጥራለን፡፡ በከንቱ ነገር እርስ በርሳቸው እንዲጣሉና በዚህ ምክንያት ቂም በቀል በልቡናቸው እንዲኖር እናደርጋለን፡፡ ተስፋ ያደረግዋትን ዘለዓለማዊ ሕይወትንም እንዲያጡና ሕይወታቸውም ኃጢአትና በደል የተሞላ ፍጻሜያቸውም ገሃነመ እሳት እንዲሆን እናደርጋለን፡፡ በልባቸው ውስጥ ቂምና ቅንዓትን ከአሳደርንባቸው በኋላ በዚህ ምክንያት ሥጋውንና ደሙንም እንዳይቀበሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዘወትር በዚህ ምክንያት የኃጢአታቸውን ስርየት አያገኙም፡፡ ከእግዚአብሔር ምሕረትና ከዘለዓለም ጸጋና በረከት እናርቃቸዋለን፡፡ ከቤተ ክርስቲያን እንዳይደርሱ እንዳይገቡ የፈጣሪያቸውን ትእዛዝ እንዳይሰሙ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዳግመኛም ጸሎታቸው ቁመታቸውና ድካማቸው ከንቱ እንዲሆን ሰዓታትና ማሕሌት በሚቆሙበትና በቅዳሴ ጊዜ አንዳቸው በአንዳቸው ላይ እንዲዘባበቱ ትምክሕትን ትዝርኅትን በልባቸው እናሳድራለን፡፡ ከካህናትና ከሕዝብ መካከል ክርስትናቸው እንዲሻር እንደ ዓላውያን ሥርዓት በሥራይና በጥንቆላ በውሃ እንዲታጠቡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ክፉ ሥራቸውንም መልካም አስመስለን እያሳያቸዋለን፡፡ በውስጣቸው ብዙ ወጥመድ እናስቀምጣለን፡፡ ከአንዲቱ ቢያመልጡ በሌላይቱ እንዲያዙ እናደርጋለን፡፡ በማሕሌት በሰዓታት በቅዳሴ ጊዜ በእውቀት እኔ እበልጣለሁ ፡ እኔ ላመስግን ፡ እኔ ልቀድስ ፡ እኔ ልዘምር ፡ እኔ ላንብብ እንዲሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ በዚህ ምክንያት እርስ በርሳቸው እንዲጣሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ #ንጽሕና_ሳይኖራቸው_በድፍረት_እንዲያገለግሉ_እናደርጋቸዋለን፡፡ ቅንዓትና ሽንገላ ቂምና ትዕቢት በልባቸው እያለ ቅዳሴ እንዲገቡ እናደርጋለን፡፡ አንዱ በአንዱ ላይ እንዲዘባበትና እንዲታበይ እናደርጋለን፡፡ በክፉ ሥራቸው ያዩአቸውና የሰሙአቸው ሁሉ ተስፋ እንዲቆርጡ እናደርጋለን፡፡ ካህናትና ዲያቆናት ፣ ምዕመናንም በማይጠቅም ነገር እንዲጣሉ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ #ያልበደሉትን ሰዎች ለምን እንደሚፈትናቸው፤ ነገሥታት፥ መኳንንትና መሣፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፲.… ይቀጥላል ይጠብቁን/

አሳዛኝ ዜና ዕረፍት፤ ‹‹ #እስመ_ተሀጥኦ_ሊቅሰ_ግብር_እኩይ_ውእቱ፤ #የሊቅ_የመምህር_መታጣቱ_ይጎዳል፡፡›› /ድርሳን ዘቅዱስ የሐንስ አፈወርቅ ፴፬/ የዋልድባው ታላቅ አባት፤ የገዳሙ ዓይን፥ ርእሰ መምህራን፥ ርእሰ ገዳማውያን፥ የዋልድባ ኮከብ፥ መጻእያትን ሳይቀር የተገለጸላቸው፤ #፬ #ዓይናው_የኔታ_መምህር_ልዑል_ወልደ_ልዑል_ኀይለ መለኮት (ሣህለ ማርያም ገብረ እግዚአብሔር) በሰላምና በክብር ዛሬ ሰኔ 2/2012 ዓ.ም. ንጋት ላይ በታላቁ ገዳም በዋልድባ አረፉ፡፡ † ታላቁ የዋልድባ አብረንታንት ገዳምን ለ11 ዓመታት በአበምኔት (በመምህርነት ያገለገሉ)፤ ✍️ ለ68 ዓመታት ደግሞ የዋልድባ ገዳም በረሃን (ሐቅለ ዋሊን)፤ ረሃቡንና ጥሙን ችለው፥ ጸብአ አጋንንትን ታግሰው፥ ግርማ ሌሊቱን ደፍረው፥ የቀን ሐሩርን ታግሠው፤ የግሩማን አራዊትን አስፈሪ ድምፅ ታግሠው፥ በየዋሻውና በየፍርክታው መንነው፥ ዕድሜ ዘመናቸውን ቋርፍ ጨብጠው (ተመግበው)፥ በጸሎትና በጽሞና ኖረው፤ ከዋልድባ ገዳም ሳይወጡ ለረጅም ጊዜ በጸሎትና በአጽንኦ በዓት ኖረው፤ ለዋልድባ ገዳም ከፍተኛ አገልግሎት ሰጥተው፤ ትህትና ትዕግስትና ደግነት ማን እንደ የኔታ ልዑል ተብሎላቸው በሰላም አርፈዋል፡፡ ፠ ከ100 ዓመት በላይ የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑና ለሃገርና ለዓለም የሚጸልዩ መናኝ፤ የአቋቋም፣ የቅዳሴና የ4ቱ አንድምታ ትርጓሜ መጻሕፍት ሊቅና መምህር የሆኑና እድሜ ዘመናቸውን ሙሉ ግን እንዳልተማረ በመምሰል በትህትና፣ በትዕግስትና በደግነት የኖሩት፤ ከታላቁና ስመ ጥር ከሆኑት ሊቅ የማነ ብርሃን ትምህርታቸውን በሚገባ የተማሩ፡፡ የጎንደር ሊቃውንት ወልደ ልዑል ፬ት ዓይናው እያሉ በታላቅ ክብር የሚጠሯቸው፤ መዝሙረ ዳዊትን፣ ቅዳሴ ማርያምና መልክአ ማርያምን በቃላቸው የሚጸልዩት፤ የታሪክ ማኅደር፤ ታሪክን ሲያስረዱም የተፈጸመውን ታሪክ ብቻ ሳይሆን እንዴትና በምን ሰዓት በምን ደቂቃ እንደተፈጸመ ጭምር ቁልጭ አድርገው የሚናገሩት፡፡ ከትህትናቸው፣ ከትምህርታቸውና ከምናኔያቸው የተነሣ ከሁሉም የበለጥክ ነህ ሲሉ ‹‹ልዑል›› ብለው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የሰየሟቸው፤ ፠ በ1993 ገደማ ወደ ኢየሩሳሌም በሄዱበት ወቅት ኢየሩሳሌም ይቀመጡ ተብለው ከገዳሙ ቢጠየቁም መምህር ግን ‹‹አይ እኔ ገዳም ነው የምኖረው፤ ከተማ ለኔ አልተፈቀደልኝም ብለው›› የመለሱ፤ የኢየሩሳሌም ገዳማትም ይህም እኮ ገዳም ነው ቢሏቸው፤ አይ ዓይኔ እያየ ብለው አጭር መልስ የመለሱ። ፠ በተመሳሳይ አቡነ ጳውሎስ ዘንድ በገዳሙ ጉዳይ ቀርበው ሌሉቹ ሁሉ የአቅማቸውን ሲናገሩ፤ እርሳቸው ግን አልናገርም እምቢ አሉ፤ አቡነ ጳውሎስም እባክዎ ይናገሩ ብለው ቢማጸኑም ‹‹ምንኮ ልናገርበት ብለው›› ዝም አሉ፡፡ ነገሩ ወዲህ ነው መምህር ልዑል በጸሎት ብርቱ ናቸውና ወደፊት የሚሆነውን አስቀድመው አውቀውና መናገራቸው ለውጥ እንደማያመጣ በማወቅ ነው ዝምታን የመረጡት፡፡ ፠ ክህነታቸውና ንፅህናቸው ልዩ የሆነ፤ ✍️ የዋልድባ አብረንታንትና በሥሩ ከሚገኙት መካከል የሞፈር ቤቶች (የእርሻ ቦታ) መካከል አንዱ የሆነውን የሆነውን ደንዶሮቃ ላይ ቤተ ምርፋቆችን የሠሩ፡፡ ✍️ በዋልድባ ሰቋር ማይፈዴ በተባለ ሞፈር ቤት ጭምር የኖሩና በርካታ ሥራን የሠሩ፤ ✍️ በጎጃም፣ በሙሉ በጌ ምድር፣ በወልቃይት ጠገዴ፣ በሌሎችም የሃገራችን ክፍሎች ትላላቅ አሻራ ያላቸው፤ በተለይ የጠፉ ገዳማትን በማቋቋም ትልልቅ ሥራና የሠሩ፤ (ለምሳሌም፤ የጣና ቂርቆስ ገዳምን አሁን ባለው ቁመና ያወቀሩ፣ የጎጃም ደብረ ገነት መድኀኔ ዓለም ገዳምንና ጎጃም መንቆረር አጠገብ ነጋትራ ቅድስት ሐና ገዳምን አሁን ያሉበት ቁሙና እንዲኖራቸውም የመምህር ልዑል አሻራ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡) ✍️ የቤተ ክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳትን ከተከበሩ ዕጽዋት ፈልፍለው እጅግ በአስገራሚ ሁኔታ የሚሠሩ፡፡ ……… † እኒህ ታላቅ አባት ዛሬ ሰኔ 2/2012 ዓ.ም. ንጋት ላይ በክብርና በሰላም በዋልድባ ደንደሮቃ አርፈዋል፡፡ † ሥርዐተ ግብዐተ መሬታቸውን ለመፈጸምም፤ ‹‹የተቀበረ አይከሰስብሽ፤ የሞቀ የደመቀ አይለበስብሽ፤ የጣመ የላመ አይበላብሽ፤ ሰላምና ፍቅር ይብዛብሽ›› ብሎ በኢትዮጵያ ደረጃ በብቸኝነት ራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኔ ዓለም የመሠረታትና ቃል ኪዳን ወደሰጣት ወደ ዋልድባ አብረንታንት መድኀኔ ዓለም ቅዱስ ቦታ ተወስዷል፤ የኒህ ትልቅ አባትን ሽኝትና ግብዐተ መሬት በማስመልከትም፤ ✤ የገዳመ ዋሊ አበውና አኀው መነኰሳት፤ አኀው አርድዕት ከያሉበት ከየፍርክታው፣ ከየዋሻው፣ ከየበዓታቸው ተሰባስበዋል፤ ገዳመ ዋልድባም ከንጋት ጀምሮ ታላቅ ሠርግን የሚሠርግ መስላ ትገኛለች፡፡ ✤ በዋልድባና አብረንታንት መድኀኔ ዓለም ገዳምና በሥሩ በሚገኙ ገዳማት (በዋልድባ አቴና (መቃብረ ሳሙኤል)፤ በዋልድባ አባ ናፃ የአቡነ ተሥፋ ሐዋርያት ገዳም፤ በዋልድባ ደንደሮቃ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም፤ በዋልድባ ማይ ለበጣ ቤተ እግዚአብሔር፤ በዋልድባ ማይጋባ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም፤ በዋልድባ ደለሳ ቆቋ አቡነ አረጋዊ ገዳም፤ በዋልድባ ማይ ሃርገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም፤ በዋልድባ ዕጣኖ ማርያም ገዳም፤ በዋልድባ ዋልቅስ ኪዳነ ምሕረት ገዳም፤ በዋልድባ አምብላ አቦ) እንዲሁም በሞፈር ቤቶች፣ ሥዕል ቤቶችና የአትክልት ቦታዎች እንዲሁም በሌላ መምምሀር በሚተዳደሩት፤ በዋልድባ ዳልሽህ ገዳም (ዋልድባ ዳልሽህ አባ ሳሙኤል ገዳም)፤ በልድባ ሰቋር ገዳም (የኪዳነምሕረት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና የመድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን) እንዲሁም በታላላቆቹ ገዳማቶቻችን፤ ✤ በማኅበረ ሥላሴ ገዳም፤ ✤ በደብረ ሊባኖስ ገዳም፤ ✤ በአብጠራ አቡነ ሳሙኤል ገዳም፤ ዛሬ በዚህች ቀን ዳዊትና ጸሎተ ማርያም እየተደገመ፤ ስማቸውም በቅዳሴ እየተነሣ ይገኛል፡፡ ‹‹ክብር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፡፡›› መዝሙረ ዳዊት ‹‹ #ያገለገለህን_ሰው_ሞት_ቸል_አትበል_፡፡›› ሲራክ 38፥26፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ፨/

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፰_ #ዲያብሎስ_የሚፈራቸውና_የማይፈራቸው_ሰዎች ✤አባ ጳውሊ፤ በውኑ ከአዳም ልጆች የምትፈራው አለን አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአዳም ልጆች የምፈራቸውም የማልፈራቸውም አሉ አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ የምትፈራቸውና የማትፈራቸው እነማን እንደሆኑ ሳትዋሽ እውነቱን ትነግረኝ ዘንድ በአምላኬ ስም አምልሐለሁ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኩህ፡፡ #ስለ_እግዚአብሔር_ፍቅር_ብሎ_ሥጋውን_ለመከራ_የሚሰጠውን_ሰው_እፈራለሁ፡፡ ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብሎ ሥጋውን ለመከራ የማይሰጠውንና ከመከራ የሚሸሽውን አልፈራውም አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ ዳግመኛ አሁን ከነገርከኝ ሌላ ማንን ትፈራለህ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የቅዱሳንን ዐፅምና ዐፅማቸውን የሚጠብቁ #መላእክትን እፈራለሁ፡፡ ስለ ክርስቶስ ብለው መከራውን በመታገሥ ስለተጋደሉት ተጋድሎ ከእግዚአብሔር ዘንድ ታላቅ ክብር ተዘጋጅቶላቸዋልና፤ ቃል ኪዳንም ተቀብለዋልና፡፡ በቦታቸው እንዳንኖር መላእክት ይከለክሉናል፤ ያባርሩናል፡፡ ኃይላችንም ይደክማል፡፡ #እኛም በዚያ ቦታ የኃጢአት ፍርፋሪ እናገኝ ዘንድ ዘወትር ተግተን እንዋጋለን አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ የተናገርከው እውነት ነው፡፡ በእውነት የቅዱሳንን ምግባርና ትሩፋት ስታዩ በእጅጉ የሚያስፈራችሁና የሚያስደነግጣችሁ አይደለምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ #ፍቅር፥ ቅን ኅሊናና ንጹሕ ልብን፥ ትሕትናን፥ ጾምን፥ ጸሎትን፥ ለመልካም ሥራ መትጋትን ስናይ እንፈራለን፡፡ ይበልጥኑም የድንግል ማርያም ልጅ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸውን #ጸሎት #አቡነ ዘበሰማያትን እንፈራለን አለ፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ የማርያም ልጅ የምትለው ማንን ነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተን የፈጠረ እርሱ ነው አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ በእውነት እርሱን ትፈራለህን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ ስሙን እየጠራህ አታቃጥለኝ፡፡ እንዴት አልፈራውም! እነሆ ኃይሌን አድክሟል፤ ብዙ ነፍሳትን አድኗል፤ ከእጄም ማርኳልና አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ ከነገርከኝ በዚህ ዓለም የምትፈሩት ሌላ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለው፡፡ ✤አባ ጳውሊ፤ እነማን ናቸው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የእርሱ ማደሪያ የሆኑና ደስ የሚያሰኙት ቅዱሳን ናቸው፡፡ ዳግመኛም #እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ሁሉ እንፈራለን፡፡ ዳግመኛም በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው የተናገሯትን #ጸሎተ ሃይማኖትን እንፈራለን፡፡ በውሃ ምንጭ፣ በባድማ፣ በመቃብር ቤት፣ በወንዝ ስንዘዋወር ወይም እኛ ባለንበት ቦታ ሁሉ #የጸሎተ ሃይማኖትን ጸሎት ስንሰማ እንደነግጣለን፡፡ ዳግመኛም አንዱ ወንድሙን እኔ በድያለሁና #ይቅር በለኝ የሚለውን የይቅርታ ቃል ስንሰማ ደንግጠን ከአጠገቡ እንርቃለን፡፡ ዳግመኛም ቅዱስ #መስቀልና የክርስቶስ #ሥጋና ደም፥ #ንጹሕ ጸሎት ካለበት ቦታ መቅረብ አይቻለንም እንሸሻለን አለው፡፡ (ማቴ.፮፥፲፬፤ ፲፰፥፴፭) #የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንን ሕዝቡን (በካህናት አንጻር)፤ ነገሥታት፥ መኳንንትና መሳፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፱.… ይቀጥላል ይጠብቁን/

** ለ‹‹ኦሮሚያ ቤተክህነት››?! የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በየትኛው ሕጋዊ ሰነድ ነው ገንዘብ መሰብሰቢያ የሒሳብ ደብተር የከፈተው?? ✍️ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመንግሥት የልማት ድርጅት ስም የተመዘገበ መንግሥታዊ የሆነ ግዙፍ እና የዳበረ የሥራ ልምድ ያለው የፋይናንስ ተቋም እንደሆነ ይታወቃል። የፋይናንስ ሥርዓቱ ጥንቃቄ በተሞላበት የሚካሄድ ከመሆኑ የተነሳ አሠራሩም ከሌሎች ባንኮች ይልቅ ጥብቅ እንደሆነ በሥራ ሁኔታ ታዝቤዋለውኝ። እንግዲህ ይህን ጥብቅ አሠራሩን በሻረ መልኩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ "የኦሮሚያ ቤተክህነት" ብሎ ራሱን ለሰየመው ስብስብ ገንዘብ ማሰባሰብ እንዲችል በፋይናንስ ሥርዐቱ በኩል ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ✍️ በንግድ ባንክ አሠራር መሠረት ድርጅት የባንክ የሒሳብ ደብተር ሲከፍት በሕጋዊነት የተመዘገበበትን የምዝገባ የምስክር ወረቀትና ወጥ የሆነውን መዋቅራዊ አሠራር ሒደቱ በሰነድ ከተገናዘበ በኋላ፤ የሃይማኖት ተቋማትም ከሆነ ከሃገረ ስብከት ወይም ከቤተ ክህነት በተጻፈ ደብዳቤ እንደሆነ ይታወቃል። ✍️ ነገር ግን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግን በየትኛው ሕጋዊ ሰነድ እንደሆነ ባይታወቅም ‹‹#የኦሮሚያን_ኦርቶዶክስ_ቤተክህነት (LUBUMMAA ORTODOKSI OROMIYA) ›› በሚል ስያሜ የሒሳብ ደብተር ከፍቶ ይህን እኩይ ዓላማውን በመደገፍ ሲኖዶሳዊት የሆነችውን ቤተክርስቲያን ለማፍረስ የሚሰነዘረው ሌላኛው የመንግሥታዊ መዋቅር የሴራ ክንፍ መሆኑን አሳይቶናል። ✍️ የኦሮሚያ ኢንተርናሺናል ባንክ እንኳን "ኦሮሚያ ቤተክህነት" ለሚለው ስያሜ ዕውቅና ነፍጎ የባንክ ደብተራቸውን ከኦሮሚያ ቤተክህነት ስም ይልቅ በግለሰቦች ስም (በሦስት ግለሰቦች ስም) አውጥቶ ትክክለኛ መንግሥታዊ አሠራሩን በሚሠራበት በአሁን ጊዜ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግን የኦሮሚያ ቤተክህነት አደራጅ አካላትን ፍላጓት ተቀብሎ ተቋም አድርጎ በመመዝገብ ግዙፍ ስህተት እየሠራ ይገኛል። ይህን መሰል ግዙፍ ስህተት የሚሠራው ካለማወቅ ሳይሆን ሆን ተብሎ በተወጠነ የጥፋት ዓላማ እንደሆነ ምንም የማያሻማ ሐቅ ነው። ስለዚህ እውነት የንግድ ባንክ ገዢ እና የቦርድ አባላት በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ምንም ዓይነት ፓለቲካዊ ጥላቻ እና ሴራ ከሌላችሁ ስለእዚህ ነገር ማብራሪያ ለቤተክርስቲያኒቷ ሊሰጡ ይገባል። ✍️ እውቅና እና ሕጋዊ ላልሆነ ተቋም በየትኛው መስፈርትና አሠራር ነው ‹‹የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ቤተክህነት›› የሚል ስም ሸልማችሁ የባንክ ደብተር አውጥታችሁ እንደሰጣችሁ ለቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ያስፈልጋል። በሁሉም ክልሎች በሕጋዊ መልኩ በኦርቶዶክሳዊት ስም ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ በሲኖዶስ የሚመራው አንድ ሃይማኖት ብቻ እንዳለ እየታወቀ ‹‹የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ›› በሚል ከፋፋይ አሠራር ንግድ ባንኩ እንዴት እውቅና እንደሠጠ ሊያብራራ ግድ ይለዋል!!። /ምንጭ፤ Kun Demelash/

ሰኔና ሰኞ ያልገጠሙባቸው ዓመታት፡፡ እውነቱን እውነት ፤ ሐሰቱን ሐሰት እንበል፡፡ .. ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመታትም ቢሆን በርካታ መጠፎ ነገሮች የደረሱባቸው ዘመናት አሉ፤ እንዲሁ ደግሞ ሰኔና ሰኞ በገጠሙባቸው ዓመታትም በርካታ መልካም ነገሮች የተፈጸሙበት ዓመታትም አሉ!!!፡፡ ፠ ዓይናማና ዐበይት እንዲሁም በጣት የሚቈጠሩ የአቡሻኽር ሊቃውንት ሰኔና ሰኞ የሚባል ነገር በቀመረ ባሕረ ሐሳብም ሆነ በቀመረ አቡሻኽር እንዲሁም በሌሎች ቀመረ ሊቃውንት እንደሌለ ያሳስባሉ፡፡ መምሰልና መሆን ፤ ነኝ ማለትና ሆኖ መገኘት፤ …. ለየቅል ናቸው፡፡ #መጥፎ_ነገር /ዘመን/ (ቅጣት) የሚመጣው በኃጢአታችንና በስንፍናችን እንጂ ሰኞና ሰኔ ስለገጠሙ አይደለም፡፡ ሰኔና ሰኞ ያልገጠሙበት ዓመታት፡፡ ለምሳሌ፤ ፠ አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመት ነው፡፡ ፠ ደርግ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ ላይ መፈንቅለ መንግሥት ያካሄደው ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመት ነው ዮዲት ጉዲትና ግራኝ መከራ ያደረሱበት ዓመታት፤ በዘመነ መሳፍንት ታላላቅ የሃገራችን ውድቀቶች የተከናወኑበት ዓመታት፤ ደርቡሾች ኢትዮጵያን ወርረው እስከ ጎንደር ደርሰው ከ44ቱ አብያተ ክርስቲያናት 42ቱን ያቀጠሉት፤ አፄ ዮሐንስ መተማ ላይ የተሰዉት ሰኔና ሰኞ ስለገጠሙ አይደለም፡፡ ደርግና ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም. ተዋግተው እልፍ አእላፋት ሕዝቦቻችን የሞቱት፤ የጭና የሃገር ውስት ተብሎ ሲኖዶስ ለ2ት እስከ መፈል የደረሰበት ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመት ነው፡፡ የአንድ ሃገር ሕዝብ የነበሩት ኢትዮጵያና ኤርትራ በጦርነት ተዋግተው በመቶ ሺህ የሚቈጠር ሕዝብ ያለቀው ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመት ነው፡፡ አምና በ2011 ዓ.ም. በሃገራችን በኢትዮጵያ ሰው ተዘቅዝቅ እስመሰቀልና በቁሙ እስከ መቃጠል ፤ አብያተ ክርስቲያናት ከመዘጋትም አልፈው እስከ መቃጠል፤ መስጊድ ሳይቀር እስከ መቃጠል የደሩስት ሰኔና ሰኞ ባልገጠሙበት ዓመት ነው፡፡ (ሰኔና ሰኞ ከገጠመ በኋላ ቀጣዩ ዓመት መጥፎ ነገር ይመጣል ለሚሉን ፤ ለ2011 ዓ.ም. ለተፈጠረው መጥፎ ነገሮች 2010 ዓ.ም. ሰኔና ሰኞ መግጠም ነበረበት) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሰበር ዜና፡፡ ** ቅ/ሲኖዶስ ለሰኔ 3/2012 ዓ.ም. አስቸኳይ ምልአተ ጕባኤ ጠራ፡፡ በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በምስካበ ቅዱሳን ቆጋ ኪዳነ ምሕረት ገዳምና በደ/ጽዮን ጉንደ ወይን ማርያም ቤ/ክ
+1
ሰበር ዜና፡፡ ** ቅ/ሲኖዶስ ለሰኔ 3/2012 ዓ.ም. አስቸኳይ ምልአተ ጕባኤ ጠራ፡፡ በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በምስካበ ቅዱሳን ቆጋ ኪዳነ ምሕረት ገዳምና በደ/ጽዮን ጉንደ ወይን ማርያም ቤ/ክ በተፈጠረው የዶግማና የቀኖና ጥሰት ለመነጋገር ቋሚ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙና73 አባላት የሚደርሱ ሊቃነ ጳጳሳት የያዘውን የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጕባኤን ለሰኔ 3/10/2012 ዓ.ም. እንዲገኙ አስቸኳይ ጥሪ አስተላለፈ፡፡ ጸልዩ በእንተ አበዊነ ቅድስት ጕባኤ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#በዓለ_ጰራቅሊጦስ፤ (#በዓለ_ሃምሳ /#ጰንጠቆስጤ) /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ሥርዐተ ማኅሌቱ በዓለ ጳራቅሊጦስ ከ፱ኙ ዐበይት በዓላተ እግዚእ አንዱ እንደመኾኑ #ግንቦት 30 #ቅዳሜ_ለእሑድ_አጥቢያ_በኹሉም_ገዳማትና_አድባራት_ይከበራል፤ ነገር ግን ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በሐዋርያትና በመንፈስ ቅዱስ ስም በተሰየሙ አብያ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ይልቁንም በአዲስ አበባ ብቸኛ በኾነው #በጽርሐ_ጽዮን_ሐዋርያት_መንፈስ_ቅዱስ_/ኋላ/#ጎላ_ሚካኤል_ (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ) ና በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ ፠ ጰራቅሊጦስ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፥ መጽንዒ (የሚያጸና)፥ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኀጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጕምን ይሰጣል /መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት፣ ገጽ ፪፻፹፫/፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ በኀጢአት ጭቃ የወደቁትንና የሚወድቁትን እንደሚያነጻቸው፤ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ላሉት ኹሉ በፈተናቸውና በመከራቸው ኹሉ እንደሚያበረታቸው (እንደሚያጸናቸው)፤ የሚነዋወፁትን እንደሚያረጋጋቸው፤ ያዘኑትን እንደሚያጽናናቸው፤ የሚደክሙትን እንደሚያበረታቸው፤ የተከዙትንም ሐሴትን እንደሚሰጣቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ጻድቃንን ወደ ተጋድሎ፤ ሰማዕታትን ወደ ደም፣ መነኰሳትን ወደ ገዳም፣ ማኅበረ ክርስቶስን ምዕመናንንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ልቡናቸውን የሚያነሣሣና የሚመራ እርሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ /ዮሐ.፲፮፥፲፪/፡፡ #በዓለ_ሃምሳ_በብሉይ እስራኤል ዘሥጋ በዓለ ኃምሳን የሚያከብሩት ስለ ብዙ ምክንያት ነው፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያኽልም፤ ✍️ ፩ኛ) ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ ምድረ ከነዓን ገብተው ለመዠመርያ ጊዜ እሸት የበሉበትን የሚዘክሩበት ነው፡፡ ዳግመኛም በበረኻ ሳሉ እግዚአብሔር ከሰማያት ኅብስተ መናን አውርዶ፥ ከጭንጫ ውኃን አመንጭቶ እንደመገባቸው ይዘክሩበታል፡፡ በመኾኑም በዚኽ በዓል ቀዳምያት፥ ዐሥራትና በኵራት እያወጡ፣ በየዓመቱ ከሚዘሩት እኽል እሸት (በብዛት ስንዴ) እየበሉ እግዚአብሔርን ስለ ምድር ፍሬ የሚያመሰግኑበት በዓል ነው፡፡ ✍️ ፪ኛ) እግዚአብሔር ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ በሃምሳኛው ቀን በደብረ ሲና ሕገ ኦሪትን ስለተቀበሉበት ይኽን ያስቡበታል፡፡ ✍️ ፫ኛ) እግዚአብሔር ከምድረ ግብጽ በታላላቅ ገቢረ ተአምራት ስላወጣቸው ይኽን ያስቡበታል፡፡ ፠ ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው ይኽ በዓል እኽል በሚታጨድበት በመከር ወቅት የሚከበር በዓል ነው፡፡ መከር ሲገባ መጀመርያ ከሚሰበስቡት እኽል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ታዝዘው ነበር /ዘጸ. ፳፫፡፲፮/፡፡ በመኾኑም ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሰባት ሳምንታት (፵፱ ቀናት) በየዕለቱ አንድ መስፈርያ እኽል ይሰጡ ነበር፡፡ በ፶ኛው ቀን ደግሞ ሊቀ ካህኑ ከተሰበሰበው እኽል በትልቅ መስፈርያ አድርጎ ካቀረበ በኋላ መሥዋዕተ በግ ይሠዋ ስለነበር ታላቅ በዓል ኾኖ ይከበር ነበር /ዘሌ. ፳፫፥፲-፲፯፣ ዘዳ. ፲፪፥፭-፯/፡፡ #አማናዊ_ትርጓሜ_በሐዲስ ፠ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ድኅነተ ዓለምን በፈጸመበት ዓመት ግን፥ እስራኤል ዘሥጋ ከላይ በገለጥነው መንገድ ከያሉበት ተሰባስበው በዓሉን በኢየሩሳሌም ሲያከበሩ፤ ለእሥራኤል ዘሥጋና ለእሥራኤል ዘነፍስ ብርሃን እንዲኾኑ የመረጣቸው ሐዋርያትም ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራቸውን ተስፋ እየተጠባበቁ በደብረ ጽዮን በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት ተሰባስበው ነበር /ሉቃ. ፳፬፡፵፱/፡፡ በዓለ ሃምሳ የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜም ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፤ መንፈስ ቅዱስ ነበር፡፡ በዚኽም ብሉይና ሐዲስ ተገናኙ፤ ተተካኩ፡፡ ፠ የነቢያት ትንቢታቸው፥ የሐዋርያትም ስብከታቸው የኾነው ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በደብረ ታቦር ተራራ እንዳገናኛቸው፥ በዚያም ክብረ መንግሥቱን፥ ብርሃነ መለኮቱን እንደገለጸላቸው የሚታወስ ነው /ማቴ. ፲፮፡፩-፯/፡፡ በምሴተ ኀሙስም በቤተ አልዓኣዛር የብሉይ ፋሲካን እንዳዘጋጁና እርሱም መሥዋዕተ ብሉይን በመሥዋዕተ ሐዲስ እንደተካው የተጻፈ ነው /ማቴ. ፳፮፡፲፯-፳፱/፡፡ በበዓለ ኃምሳ የኾነውም ልክ እንደዚኹ ነው /ሐዋ. ፪/፡፡ ይኽ ኹሉ በኢየሩሳሌም፣ በመዠመርያዪቱ ቤተ ክርስቲያን በተሰየመች በቤተ ማርያም (የማርቆስ እናት) ተፈጸመ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለፊተኞችም ለኋለኞችም እናታቸው እንደኾነችም ታወቀ፤ ተረዳ፡፡ ፠ ቅዱሳን ሐዋርያት በዲድስቅልያ ፴፩ ላይ፤ ‹‹ከዕርገቱ ቀን በኋላ ታላቅ በዓል ይደረግ፤ በዚኽች ቀን በሦስተኛው ሰዓት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና እኛም በርሱ ስጦታዎች ተሞላን፤ አዳዲስ ቋንቋም ተናገርን›› በማለት በዓሉን በቤተ ክርስቲያን ልናከብረው እንዲገባ ሥርዐት ሐዋርያት የሠሩልንም ስለዚኹ ነው፡፡ በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት የታነጸችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንም ይኽንኑ በዓል ከጌታችን ዘጠኝ ዐበይት በዓላት አንዱ በማድረግ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ #ርደተ_መንፈስ_ቅዱስ ፠ ጌታችን እንደነገራቸው መቶ ሃያው ቤተ ሰብእ በቤተ ማርያም ኀይልን ከአርያም እስኪለብሱ ድረስ ተሰብስበው ነበር፡፡ በትዕግሥት ከመጠበቅ ውጪ መንፈስ ቅዱስ መቼ እንደሚወርድም አያውቁም ነበር /ሐዋ. ፪፥፪/፡፡ ጌታችን ባረገ በዐሥረኛው ቀን ግን እኔና እናንተ እንደምንሰማው ዓይነት ያይደለ፥ ነገር ግን ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፡፡ ያሉበትን ቤት ሞላው፡፡ ላንቃ ላንቃ ያለው እሳት ኾኖ ታያቸው፡፡ በበደልን ጊዜ ከእኛ ርቆ ነበርና አኹን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ስለታረቅን በኹሉም አደረባቸው: /ማቴ. ፫፡፲፩/፡፡ ኀይል የሚኾናቸው ሀብትን፣ ሀብት የሚኾናቸው ዕውቀትን ገንዘብ አደረጉ፡፡ #መንፈስ_ቅዱስ ፠ መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር የሚሠለስ፥ የሚቀደስ፥ የሚወደስ የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ እንደ አብና ወልድ ፍጹም ገጽ፥ ፍጹም መልክዕ፥ ፍጹም አካል አለው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ እንጂ ሕጹጽ (ብትን፣ ዝርው) አይደለም፡፡ በተለየ አካላዊ ግብሩም መሥረፅ (መውጣት) ነው፤ መሥረጹም ከአብ ብቻ እንጂ አንዳንዶች (ካቶሊኮችና መካነ ኢየሱሶች) እንደሚሉት ከወልድም ጭምር አይደለም /ዮሐ.፲፭፡፳፮/፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢሠርፅ እንጂ አያሠርጽም፥ አይወልድም፥ አይወለድም፡፡ በባሕርይ፥ በመለኮት፥ በሥልጣን፥ በሕልውና፥ በአገዛዝ፥ ዓለማትን በመፍጠርና በማሳለፍ ከአብና ከወልድ ጋራ የተካከለ ነው /ጸሎተ ሃይማኖት/፡፡ ቀዳሚነትም ኾነ ተቀዳሚነት የሌለው ይልቁንም ከአብና ከወልድ ጋር የተካከለ (ዕሩይ) ነው፡፡ ከአብና ከወልድ ጋር ዓለም ሳይፈጠር ፥ ዘመን ሳይቈጠር፥ ይህ ነው በማይበል ዘመን የነበረ ቀዳማዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አሁንም ያለ ማዕከላዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮ ተካክሎ ይህ ነው ለማይባል ዘመን ወደፊት የሚኖር ደኃራዊ ነው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/

#በዓለ_ጰራቅሊጦስ፤ (#በዓለ_ሃምሳ /#ጰንጠቆስጤ) /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ሥርዐተ ማኅሌቱ በዓለ ጳራቅሊጦስ ከ፱ኙ ዐበይት በዓላተ እግዚእ አንዱ እንደመኾኑ #ግንቦት 30 #ቅዳሜ_ለእሑድ_አጥቢያ_በኹሉም_ገዳማትና_አድባራት_ይከበራል፤ ነገር ግን ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በሐዋርያትና በመንፈስ ቅዱስ ስም በተሰየሙ አብያ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ይልቁንም በአዲስ አበባ ብቸኛ በኾነው #በጽርሐ_ጽዮን_ሐዋርያት_መንፈስ_ቅዱስ_/ኋላ/#ጎላ_ሚካኤል_ (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ) ና በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ ፠ ጰራቅሊጦስ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፥ መጽንዒ (የሚያጸና)፥ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኀጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጕምን ይሰጣል /መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት፣ ገጽ ፪፻፹፫/፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ በኀጢአት ጭቃ የወደቁትንና የሚወድቁትን እንደሚያነጻቸው፤ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ላሉት ኹሉ በፈተናቸውና በመከራቸው ኹሉ እንደሚያበረታቸው (እንደሚያጸናቸው)፤ የሚነዋወፁትን እንደሚያረጋጋቸው፤ ያዘኑትን እንደሚያጽናናቸው፤ የሚደክሙትን እንደሚያበረታቸው፤ የተከዙትንም ሐሴትን እንደሚሰጣቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ጻድቃንን ወደ ተጋድሎ፤ ሰማዕታትን ወደ ደም፣ መነኰሳትን ወደ ገዳም፣ ማኅበረ ክርስቶስን ምዕመናንንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ልቡናቸውን የሚያነሣሣና የሚመራ እርሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ /ዮሐ.፲፮፥፲፪/፡፡ #በዓለ_ሃምሳ_በብሉይ እስራኤል ዘሥጋ በዓለ ኃምሳን የሚያከብሩት ስለ ብዙ ምክንያት ነው፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያኽልም፤ ✍️ ፩ኛ) ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ ምድረ ከነዓን ገብተው ለመዠመርያ ጊዜ እሸት የበሉበትን የሚዘክሩበት ነው፡፡ ዳግመኛም በበረኻ ሳሉ እግዚአብሔር ከሰማያት ኅብስተ መናን አውርዶ፥ ከጭንጫ ውኃን አመንጭቶ እንደመገባቸው ይዘክሩበታል፡፡ በመኾኑም በዚኽ በዓል ቀዳምያት፥ ዐሥራትና በኵራት እያወጡ፣ በየዓመቱ ከሚዘሩት እኽል እሸት (በብዛት ስንዴ) እየበሉ እግዚአብሔርን ስለ ምድር ፍሬ የሚያመሰግኑበት በዓል ነው፡፡ ✍️ ፪ኛ) እግዚአብሔር ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ በሃምሳኛው ቀን በደብረ ሲና ሕገ ኦሪትን ስለተቀበሉበት ይኽን ያስቡበታል፡፡ ✍️ ፫ኛ) እግዚአብሔር ከምድረ ግብጽ በታላላቅ ገቢረ ተአምራት ስላወጣቸው ይኽን ያስቡበታል፡፡ ፠ ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው ይኽ በዓል እኽል በሚታጨድበት በመከር ወቅት የሚከበር በዓል ነው፡፡ መከር ሲገባ መጀመርያ ከሚሰበስቡት እኽል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ታዝዘው ነበር /ዘጸ. ፳፫፡፲፮/፡፡ በመኾኑም ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሰባት ሳምንታት (፵፱ ቀናት) በየዕለቱ አንድ መስፈርያ እኽል ይሰጡ ነበር፡፡ በ፶ኛው ቀን ደግሞ ሊቀ ካህኑ ከተሰበሰበው እኽል በትልቅ መስፈርያ አድርጎ ካቀረበ በኋላ መሥዋዕተ በግ ይሠዋ ስለነበር ታላቅ በዓል ኾኖ ይከበር ነበር /ዘሌ. ፳፫፥፲-፲፯፣ ዘዳ. ፲፪፥፭-፯/፡፡ #አማናዊ_ትርጓሜ_በሐዲስ ፠ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ድኅነተ ዓለምን በፈጸመበት ዓመት ግን፥ እስራኤል ዘሥጋ ከላይ በገለጥነው መንገድ ከያሉበት ተሰባስበው በዓሉን በኢየሩሳሌም ሲያከበሩ፤ ለእሥራኤል ዘሥጋና ለእሥራኤል ዘነፍስ ብርሃን እንዲኾኑ የመረጣቸው ሐዋርያትም ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራቸውን ተስፋ እየተጠባበቁ በደብረ ጽዮን በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት ተሰባስበው ነበር /ሉቃ. ፳፬፡፵፱/፡፡ በዓለ ሃምሳ የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜም ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፤ መንፈስ ቅዱስ ነበር፡፡ በዚኽም ብሉይና ሐዲስ ተገናኙ፤ ተተካኩ፡፡ ፠ የነቢያት ትንቢታቸው፥ የሐዋርያትም ስብከታቸው የኾነው ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በደብረ ታቦር ተራራ እንዳገናኛቸው፥ በዚያም ክብረ መንግሥቱን፥ ብርሃነ መለኮቱን እንደገለጸላቸው የሚታወስ ነው /ማቴ. ፲፮፡፩-፯/፡፡ በምሴተ ኀሙስም በቤተ አልዓኣዛር የብሉይ ፋሲካን እንዳዘጋጁና እርሱም መሥዋዕተ ብሉይን በመሥዋዕተ ሐዲስ እንደተካው የተጻፈ ነው /ማቴ. ፳፮፡፲፯-፳፱/፡፡ በበዓለ ኃምሳ የኾነውም ልክ እንደዚኹ ነው /ሐዋ. ፪/፡፡ ይኽ ኹሉ በኢየሩሳሌም፣ በመዠመርያዪቱ ቤተ ክርስቲያን በተሰየመች በቤተ ማርያም (የማርቆስ እናት) ተፈጸመ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለፊተኞችም ለኋለኞችም እናታቸው እንደኾነችም ታወቀ፤ ተረዳ፡፡ ፠ ቅዱሳን ሐዋርያት በዲድስቅልያ ፴፩ ላይ፤ ‹‹ከዕርገቱ ቀን በኋላ ታላቅ በዓል ይደረግ፤ በዚኽች ቀን በሦስተኛው ሰዓት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና እኛም በርሱ ስጦታዎች ተሞላን፤ አዳዲስ ቋንቋም ተናገርን›› በማለት በዓሉን በቤተ ክርስቲያን ልናከብረው እንዲገባ ሥርዐት ሐዋርያት የሠሩልንም ስለዚኹ ነው፡፡ በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት የታነጸችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንም ይኽንኑ በዓል ከጌታችን ዘጠኝ ዐበይት በዓላት አንዱ በማድረግ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ #ርደተ_መንፈስ_ቅዱስ ፠ ጌታችን እንደነገራቸው መቶ ሃያው ቤተ ሰብእ በቤተ ማርያም ኀይልን ከአርያም እስኪለብሱ ድረስ ተሰብስበው ነበር፡፡ በትዕግሥት ከመጠበቅ ውጪ መንፈስ ቅዱስ መቼ እንደሚወርድም አያውቁም ነበር /ሐዋ. ፪፥፪/፡፡ ጌታችን ባረገ በዐሥረኛው ቀን ግን እኔና እናንተ እንደምንሰማው ዓይነት ያይደለ፥ ነገር ግን ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፡፡ ያሉበትን ቤት ሞላው፡፡ ላንቃ ላንቃ ያለው እሳት ኾኖ ታያቸው፡፡ በበደልን ጊዜ ከእኛ ርቆ ነበርና አኹን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ስለታረቅን በኹሉም አደረባቸው: /ማቴ. ፫፡፲፩/፡፡ ኀይል የሚኾናቸው ሀብትን፣ ሀብት የሚኾናቸው ዕውቀትን ገንዘብ አደረጉ፡፡ #መንፈስ_ቅዱስ ፠ መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር የሚሠለስ፥ የሚቀደስ፥ የሚወደስ የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ እንደ አብና ወልድ ፍጹም ገጽ፥ ፍጹም መልክዕ፥ ፍጹም አካል አለው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ እንጂ ሕጹጽ (ብትን፣ ዝርው) አይደለም፡፡ በተለየ አካላዊ ግብሩም መሥረፅ (መውጣት) ነው፤ መሥረጹም ከአብ ብቻ እንጂ አንዳንዶች (ካቶሊኮችና መካነ ኢየሱሶች) እንደሚሉት ከወልድም ጭምር አይደለም /ዮሐ.፲፭፡፳፮/፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢሠርፅ እንጂ አያሠርጽም፥ አይወልድም፥ አይወለድም፡፡ በባሕርይ፥ በመለኮት፥ በሥልጣን፥ በሕልውና፥ በአገዛዝ፥ ዓለማትን በመፍጠርና በማሳለፍ ከአብና ከወልድ ጋራ የተካከለ ነው /ጸሎተ ሃይማኖት/፡፡ ቀዳሚነትም ኾነ ተቀዳሚነት የሌለው ይልቁንም ከአብና ከወልድ ጋር የተካከለ (ዕሩይ) ነው፡፡ ከአብና ከወልድ ጋር ዓለም ሳይፈጠር ፥ ዘመን ሳይቈጠር፥ ይህ ነው በማይበል ዘመን የነበረ ቀዳማዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አሁንም ያለ ማዕከላዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮ ተካክሎ ይህ ነው ለማይባል ዘመን ወደፊት የሚኖር ደኃራዊ ነው፡፡

ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ሰኞ ይጀመራል፡፡ ከሰኔ 1 - ሐምሌ 5 ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ፤ ወንትፋቀር በበይናቲነ፡፡ (ጾምን እንጹም፥ ጓደኞቻችንን እንውደድ፤ እርስ በርሳችን እንዋደድ፡፡) ፠ በ
ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ሰኞ ይጀመራል፡፡ ከሰኔ 1 - ሐምሌ 5 ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ፤ ወንትፋቀር በበይናቲነ፡፡ (ጾምን እንጹም፥ ጓደኞቻችንን እንውደድ፤ እርስ በርሳችን እንዋደድ፡፡) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w