ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 381 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 582 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 381 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 09 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 38، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.91‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 370 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 449 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 25.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 381
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
#ኅዳር 25_በዓለ_ዕረፍቱ_ለሰማዕት_ቅዱስ_መርቆሬዎስ(#ፒሉፓዴር)፤ (ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው ያዳርሱ፡፡) *አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡ *የወላጆቹ (አባቱን ኖህ እናቱን ታቦት) አገር አስሊጥ የምትባል ስትኾን እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ የመጀመሪያ ስሙ ፒሉፓዴር ነው፡፡ * ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሯቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሯቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡ መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብረውት ነበሩ፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሯቸውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ **በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡ ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጰዶቅያና የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡ ✤ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እንዲሁም ጎርጎርዮስን ረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ በስዕሉ ላይ ያለው የቅዱስ መርቆሬዎስ ይዞ ከተሳለው ጦር ጫፍ ላይም ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡ ✤ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡ መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓዝ መስሏቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ አገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና አምጥቷል፡፡ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ አበ ምኔትም ሆኖ ብዙ መነኰሳትን አፍርቷል፡፡ /ምንጭ፤ ከገድላት አንደበት/ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ስዕሉ_የሚያሸበሽበው_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ስዕል_፤ በጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና) የሚገኝ፡፡ መርቆሬዎስ መርቆሬዎስ ገባሬ ተአምር፡፡ #ቪዲዮውን_ሁሉም_ሊያየው_የሚገባ_የተዓምር_ተዓምር፡፡ የቻላችሁ በአካል ሰሜን ሸዋ (የ100ብር የትራንስፖርት መንገድ ነው) ሂዳችሁ፤ ያልቻላችሁ ቪዲዮውን እንድታዩት አቅርበንላችኋል፤ ዛሬም ድረስ ተዓምር አድራጊውና በበዓለ መርቆሬዎስ እለት የሚያሸበሽበው የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል፤ (ቀድሞም ባስልዮስና ጎርጎርዮስ ዑልያኖስ የሚባል ጠላት ሲመጣባቸው ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ጸለዩ፤ ቅዱስ መርቆሬዎስም ከስዕሉ ላይ ወጥቶ ዑልያኖስን ገደለላቸው)፤ ዛሬም ድረስ የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ተዓምራትን ያደርጋል፡፡ በጻድቃን ሰማዕታት፤ በመላእክት በእመቤታችን ላይ አድሮ እግዚአብሔር እንደሚመሰገን አስተውሉ፡፡ ✣✤✣ #ቅዱሳት_ሥዕላት_በቅዱሳት_መጻሕፍት -‹‹የስርየት መክደኛ ስራ ፣ ሁለት ኪሩቤልን ከተቀጠቀጠወርቅ ስራ፣ በምስክሩ ታቦት ላይ በሁለቱ ኪሩቤል መካከል መክደኛውም ላይ ሆኜ አነጋግርሃለሁ፡፡›› ዘጸ25፣18-22፤ 37፣7-9 -በቅድስቲቱና በቅድስተ ቅዱሳኑ መካከል መለያ በሆኑት መጋረጃዎች “ብልህ ሠራተኛ እንደሚሠራ ኪሩቤልን አድርጉባቸው” ዘጸ 26፥31፤ 36፣ 8-35፡፡ -እግዚአብሔር ማዘዝ ብቻ ሳይሆን በጥበብና በማስተዋል መንፈሱን እንደመላባቸው፤ የኡሪ ልጅ ባስልኤል፥ የአሂዳምኒክን ልጅ ኤልያብን ዘጸ 31:1-6 -‹‹እስከ መነነቶ ሜልኮል ቅድመ ታቦተ ሕግ ከመ ዘፈነ፣ንጉሠ እስራኤል ኪያኪ ዘጸገየ ሥነ፣ቅድመ ሥዕልኪ ድንግል እዘፍን አነ. . .፤ የዓለም የድኅነት ጌጥ የሆነ ጌታን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ አንቺን ያስገኘ የእስራኤል ንጉስ ዳዊት ሚስቱ(ሜልኮል) እስከምትንቀው ድረስ በእግዚአብሔር የቃልኪዳን ታቦት ፊት እንዳመሰገነ እኔም በሥዕልሽ ፊት ቆሜ እዘምራለሁ፤. . .›› ‹‹ኢየኀፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ ወርኀ ጽጌረዳ አመኀ ኀልቀ . . .፤ማርያም ሆይ የጽጌረዳ ፣የአበባ ወራት ባለፈ ጊዜ ብዙ ምስጋናሽን ሳመሰግን በሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም፣ ስምሽን መጥራት የወደቀውን ያነሣል ፣ ኀጥኡንም ጻድቅ ያደርጋልና።›› /አባ ጽጌ ድንግል/ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#በሃገራችን_ከሚገኙ_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ክብረ_በዓል_ከሚከብርባቸው_ዋነኞቹ_፡፡ ✥1. ደብረ ጽባሕ ጸዶየ መርቆሬዎስ፤ በአጼ ይኵኖ አምላክ ዘመን የተመሠረተ፡፡ ✥2.ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም፤ ‹‹ደ
+7
#በሃገራችን_ከሚገኙ_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ክብረ_በዓል_ከሚከብርባቸው_ዋነኞቹ_፡፡ ✥1. ደብረ ጽባሕ ጸዶየ መርቆሬዎስ፤ በአጼ ይኵኖ አምላክ ዘመን የተመሠረተ፡፡ ✥2.ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም፤ ‹‹ደጃች ውቤ ደረስጌ ደብረ ጽዮንን በወርቅና በዕንቊ ከመሥራታቸውም በላይ ታቦተ መርቆሬዎስን ማምጣታቸው ተብሎ የሚነገርለት›› ተዓምር አድራጊ ስዕል የሚገኝበት ቤ.ክ (ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠበት)፤ ራስ ደጀን አጠገብ፤ ጃናሞራ (መካነ ሰላም ከተማ) ✥3. ጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቋም ማርያም፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥4. ጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና)፤ ስዕሉ በበዓለ መርቆሬዎስ ቀን የሚያሸበሽበው፡፡ ✥5. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኡል (አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥6. ደብረ ሲና ቅ.እግዚአብሔር አብ(አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥7. አዲስ አበባ ጎፋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወዮሐንስ መጥምቅ ቤ.ክ (በአዲስ አበባ በመርቆሬዎስ ስም የጠሰየመ ብቸኛው ቤ.ክ.) LIKE & INVITE our Facebook Page በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል_፩ ፠ ‹‹እነሆ በትዕግስት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደፈጸመለት አይታችኋል፡፡›› ያዕ. ፭፥፲፩ ሰይጣንን በዘመናቸው ታግሰው ያሸነፉ ሰዎች ልቡናቸው አስተሳሰባቸው አጠቃላይ አኗኗራቸው ንጹሕና ቅዱስ ስለሚሆን ፍጹም ይቅር ባይና ቸሮች ርኅሩኆችና አዛኞች ናቸው፤ ሐዘኔታቸውም ለወዳጆቻቸውም ብቻ ሳይሆን ለጠላቶቻቸው ጭምር ነው (ቅዱስ ዳዊት /፩ኛ ሳሙ. ፳፬፥፲፰/ ና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን /ሐዋ. ፯፥፰/ ልብ ይሏል) ቅዱሳን ከሰው ልጆች አልፈው ለአራዊት፣ ለአዕዋፍና ለእንስሳ እንዲሁም ለታላቁ ጠላት ለሰይጣን ሳይቀር የሚያዝኑ ናቸው፡፡ (ነቢዩ ሳሙኤል /፩ኛ ሳሙ. ፲፮፥፩/፣ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን /ገድለ ክርስቶስ ሰምራ/ ልብ ይሏል::) ፠ ቅዱሳን ሰዎች እንዲህ ዓይነቱን ጸጋ ሊያገኙ የሚችሉት የሰይጣንን ክፋት ለይተው ተረድተው ሰይጣንን በፍጹም ትዕግስትና ትሕትና ማሸነፍ በመቻላቸውና ከሰይጣን ባርነት ነጻ ወጥተው የእግዚአብሔርን መንፈስ ገንዘብ በማድረጋቸው ነው፡፡ ፠፠ በተቃራኒ ደግሞ በዓለም ላይ ለተፈጠሩትና እየተፈጠሩም ላሉት ችግሮች መንስኤያቸውና ምንጫቸው የሰይጣን ሰለባና ማደሪያ በሆኑ ሰዎች አማካይነት የሚከሠት ነው፡፡ (ቃዔልን /ዘፍ.፬፥፰፣ ሄሮድስን /ማቴ. ፪፥፲፮/፣ አምኖንን /፪ኛ ሳሙ. ፲፫፥፩/፣ ሰዶማውያንን /ዘፍ. ፲፱፥፩፣ ሮሜ. ፳፮፥፳፱፣ ፪ጴጥ. ፪፥፮/ …. ሌሎችንም …. ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም፤ *ሰይጣን ተዘክሮተ እግዚአብሔርንና መንፈሳዊ ተግባራትን ካስተወ በኋላ በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዲጨምሩ እንጂ *ሰይጣን ኃጢአትን በቃኝ እንዳይሉ ስለሚያደርጋቸው ነው /ዘዳ. ፮፥፲፫/፡፡ *ሰይጣን ኃጢአትንም ተዉ ብሎ በሚመክራቸው ሰው ላይ በጠላትነት እንዲነሳሡ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቀና የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ክፉ አስመስሎ ስለሚያሳያቸው ቅን አሳቢዎችንና ለመልካም ሥራ የተሰለፉትን እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቅን አስተሳሰብን መንፈሳዊ ሥራን ሰላምን ፍቅርን ርኅራኄን ከውስጣቸው አሟጦ አውጥቶ የራሱን መንፈስ ስለሚሞላባቸው ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢሠሩ ወንጀል የሠሩና ጥፋት ያጠፉ አይመስላቸውም፡፡ እውነተኛ ሕይወት እንደሚኖሩ ያስመስላቸዋልም፡፡ *ሰይጣን ዲያብሎስ የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው ስለሚያደርጋቸው ለጥፋታቸው ገደብ የለውም፡፡ ፠ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደው ሰው ሁሉ የሰይጣንን የክፋት ሥራ ተረድቶ ከሰይጣን እንዲሸሽና የእግዚአብሔርን ልጅነት አግኝቶ የዘለዓለም ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን እንዲወርስ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፡፡ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፤ ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔር ተወልዷልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፡፡›› ፩ዮሐ.፫፥፰/ /‹‹ክፉ ፍሬ የሚያፈራ መልካም ዛፍ የለምና እንዲሁም መልካም ፍሬ የሚያፈራ ክፉ ዛፍ የለም፡፡ ዛፍ ሁሉ ከፍሬው ይታወቃልና፤ …. መልካም ሰው ከመልካም ልቡ መልካሙን ያወጣል፡፡›› ሉቃስ ፮፥፵፫/ #ማንኛውም ሰው በሚሠራው ሥራ የማን ወገንና የማን ማደሪያ እንደሆነ ለመረዳትና ራሱንም ለመፈተሸ ይችላል፡፡ ፠ ##ጠላት ዲያብሎስ ንስሐ ገብተን መንግሥተ ሰማይትን እንዳንወርስ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በሥጋዊ ኑሯችንም ቢሆን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ ተምረን ተገቢውን እውቀት ይዘን ሥራችንን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ እንዳንሠራ በማድረግ፤ ሠርተንም እንዳንጠቀም ዕንቅፋት በመፍጠር (በስንፍናና በውሸት፤ በዝሙትና በስካር፤ በቃሚነትና በአጫሽነት፤ በጨፋሪነትና በዳንሰኛነት፤ በስርቆትና በአጭበርባሪነት፤ …. በተለያዩ የኃጢአት አሸክላዎች ተብትቦ ይይዘናል፤ እንዲህ ካደረገን በኋላም ሰይጣን በሚያመነጭልን አእምሯዊ ስሜትና ጭፍን አስተሳሰብ እየነዳን መልካም ሥራን ለሚሠሩ ለእውነተኛ ሰዎች እንቅፋት እንድንሆን በመሣሪያነት ይጠቀምብናል፡፡ /‹‹ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበር … አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን አዘገየን፡፡›› ፩ተሰ. ፪፥፲፰/ /አንተ (ኤልማስ የተባለ አስማተኛን/ ተንኮልንና ክፋትንም ሁሉ የሞላብህ የዲያብሎስ ልጅ የጽድቅም ሁሉ ጠላት የቀናውን የጌታን መንገድ ከማጣመም አታርፍምን?›› ሐዋ. ፲፫፥፮/ /እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ፡፡ እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለሌለ በእውነት አልቆመም፡፡ ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፡፡ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና፡፡›› ዮሐ. ፰፥፵፬/ #ከላይ ባየነው ዓይነት ሕይወት ሰይጣን በእጁ ያደረጋቸውን ሰዎች፤ **ለሕይወታቸው ጠቃሚ ምክርና ትምህርት በሚሰጣቸው ሰዐት ወዲያው እንዲዘነጉትና እንዳይቀበሉት ያደርጋል፡፡ /‹‹ወዲያው እንደሰሙ ሰይጣን መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል፡፡›› ማር. ፬፥፲፭/ **ቢመከሩም ምክርን አይሰሙም አይቀበሉምም፤ /ይሁዳ ሕይወት የሚሆን የጌታን ትምህርት አልሰማ ብሎ ነው ጌታን አሳልፎ የሰጠው፡፡ ማቴ. ፳፮፥፵፱/ /አምኖንም የእኅቱን የትዕማርን ምክር አልሰማ ብሎ ነው አስነዋሪ ጥፋት በእኅቱ ላይ የፈጸመው፡፡ ፪ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ /እንዲሁም ደግሞ ሳዖልም የነቢዩ ሳሙኤልን ምክር አልሰማ ብሎ ነው ከአማሌቃውያን ለማረከው ምርኮ በመሣሣት ክፉ መንፈስ ሊያድርበትና በጠላት እጅ ሊወድቅ የቻለው፡፡ ፩ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል_፪_ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ .… ይቀጥላል ከነገ ወዲያ ይጠብቁን/ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #የኅዳር_ጽዮን_ወረቦችን_በዚህ_በቴሌግራም_አድራሻችን_ያገኛሉ_፤ https://t.me/medihanaelem

ኅዳር 24 #የ24ቱ_ካህናተ_ሰማይ_(የሱራፌል)ና በቆብ አያትና የልጅ ልጅ የኾኑት #አቡነ_ተክለሃይማኖትና_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ዕለት ነው፨ እንዲሁ
ኅዳር 24 #የ24ቱ_ካህናተ_ሰማይ_(የሱራፌል)ና በቆብ አያትና የልጅ ልጅ የኾኑት #አቡነ_ተክለሃይማኖትና_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ዕለት ነው፨ እንዲሁም ሌሎችም ቅዱሳን መንበረ ሥላሴን ያጠኑ አሉ፡፡ ለምሳሌም፤ አቡነ ዮሴፍ ዘጂፋት፣ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ናቸው፡፡ ፨ካህናተ ሰማይ የዐውዶ ሡራሄ፤ ሎቱ ለባህቲቱ ይደሉ ስባሔ፨ /ሰዐታት/ ፨ ብፁዕ ሳሙኤል መንበረ ልዑል የዐጥን። /ሥርዐተ ማኅሌት ዘታኅሣሥ 12/::

ለፌስቡክና ቴለግራም አባላቶቻችን በሙሉ፤ ከዚህ በፊት በተከታታይ ክፍል ‹‹ #ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ_››/) በሚል ርዕስ ያቀረብንላችሁን ትምህርት፤ ደ
+1
ለፌስቡክና ቴለግራም አባላቶቻችን በሙሉ፤ ከዚህ በፊት በተከታታይ ክፍል ‹‹ #ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ_››/) በሚል ርዕስ ያቀረብንላችሁን ትምህርት፤ ደግመን እንድናቀርብላችሁ ከፌስቡክና ቴሌግራም አባላቶቻችን በተደጋጋሚ ስለተጠየቅን ከነገ ማክሰኞ ኅዳር 23 ጀምሮ በየ2ት (ሌላ ጽሑፍ ስንለጥፍ በየ3ት) ቀኑ የምናቀርብ መሆኑን እናበስራለን፡፡ ሰላም ለአባ ጳውሊ፤ ዘንጉሥ ወዓሊ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ፤ ርዕሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም፡፡ ትርጉም፤ በበረሃ ላሉ ባሕታውያን(መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል፡፡ ምንጫችን፤ * ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከግእዝ ወደ አማርኛ ያሳተመው መጽሐፍ፣ * ፍኖተ ቅዱሳን /FINOTE KIDUSANZETWAHIDO እና ዋልድባ ዋሊ የቴሌግራም ገጽ፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #የቴሌግራም_አድራሻችን_ https://t.me/medihanaelem #በክፍል_፩#የምናያቸው_፤ ፠ በትዕግስት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ሐዘኔታቸውም ለወዳጆቻቸውም ብቻ ሳይሆን ለጠላቶቻቸው ጭምር እንሆነ፤ ለታላቁ ጠላት ለሰይጣን ሳይቀር የሚያዝኑ መሆናቸውን:: ፠ በዓለም ላይ ለተፈጠሩትና እየተፈጠሩም ላሉት ችግሮች መንስኤያቸውና ምንጫቸው ምንድን ነው? ፠ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደው ሰውን ሁሉ ምን ለማድረግ ነው? ፠ ጠላት ዲያብሎስ በነፍስና በሥጋዊ ኑሯችን ምን ሊያደርገን ይፈልጋል? /ነገ ኅዳር 23 ይጠብቁን/

5.(6).2፤ #ማርያም_ጽዮን_ታቦተ_ኃይለ_መለኮት_ወምኒልክ_ታቦተ_ቃለ ጽድቅ፤ ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ አፈቅራ እምዕጐሊሆን፡፡