ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 381 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 582 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 381 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 09 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 38، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.91‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 370 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 449 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 25.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 381
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
#እንኳን_ለኅዳር_21_ታቦተ_ጽዮን_(#ጽላተ_ኪዳን_ወይም_ታቦተ_ሕጉ_) #ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_አደረሰን_አደረሳችሁ፡፡ ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦቿንም ቅጠሩ፥ አዳራሿን ተመልከቱ፥ በብርታቷ የልባችሁን ተስፋ አኑሩ፡፡ /መዝ. 47፥12/ #ኅዳር_21_የታቦተ_ጽዮን_(#ጽላተ_ኪዳን_ወይም_ታቦተ_ሕጉ_) #ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_የምናከብርበት_ምክንያት_፤ ፩ኛ. በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን በሕዝበ አስራኤል(በአፍኒን ፊንሐስ) ኀጢአት ምክንያት፤ ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካ፤ ዳጐን የተባለ የአሕዛብ ጣዖትን ቀጥቅጣ አድቅቃ ወደ እስራኤል የተመለሰችበት በመኾኑ፡፡ (1ሳሙ. ከ1-6) ፪ኛ. ታቦተ ጽዮን መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰሎሞን ወዳሠራው ቤተ መቅደስ (በዓለም ላይ እስካሁን ያልታየ ድግስ ደግሶ) የገባችበት እለት በመኾኑ፡፡ / (1ኛ ነገ. 8፥2፣ 2ኛ ዜና. 5፥1፣ ስንክሳር ዘሐምሌ 23) ፫ኛ. በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ (ዕብነ ሐኪም) አማካኝነት ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር በ318ቱ ሌዋውያን ካህናት ፥ በሊቀ ካህናቱ አዛርያስ እየተመራች ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ የገባችበት በመኾኑ፡፡ /ክብረ ነገሥት፣ መጽሐፈ ምሥጢር፣ መጻሕፍተ ሰሎሞን ወሲራክ አንድምታ መቅድም፣ …/ ፬ኛ. ነቢያት ስለ እመቤታችን በተለያየ ኅብረ መልክእና አምሳል (ዕዝራ በቅድስት ሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተ መቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ፣ ……) ያዩበት በመኾኑ፡፡ /ሕዝ. 44፥1፣ መጽ. ዕዝራ/ ፭ኛ. በንጉሥ አፄ ባዜን (በ4 ዓ.ም. አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ዋልድባን፣ ደብረ ዐባይን፣…… ሌሎችንም የኢትዮጵያ መካናት በስደት ከልጇ ጋር ባርካ አኵስም ጽዮን ላይ መጥታ የገባችበትና የባረከችበት፤ በወቅቱም አኵስምና አካባቢዋ በብርሃን ጎርፍ የተጥለቀለቁበት በመኾኑ፤ /ታሪከ ዋልድባ፣ ታሪከ አኵስም፣ ድርሳነ ዑራኤል፣ ....) ፮ኛ. በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱሳን ጻድቃን ነገሥታት አብርሐ ወአጽብሐ አማካኝነት መሥዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት የቆየችው አኵሱም ጽዮን፤ ጽዮን ማርያም ተብላ ባለ 12 መቅደሶች ባሏት በወርቅና በዕንቊ ያሸበረቀች ቤ.ክ ሠርተው ቅዳሴ ቤቷ የተከበረበትና ክርስትና ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ የታወጀበት፡፡ ፯ኛ. በየጊዜው (በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ) ወደ ዝዋይ፣ ወደ ጣና ቂርቆስ፣ …… ተሰድዳ ቆይታ፤ ተመልሳ (ከዮዲት በኋላ በአንበሳ ውድምና፤ ከግራኝ በኋላ በአፄ ፋሲል የታነጹት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን) ቅዳሴ ቤቷ የተከበረበት በመኾኑ፡፡ ፰ኛ. ወደ አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም በቦታው ርቀት ለመሳለም ላልቻሉ ክርስቲያኖች ዳግሚት ደብረ ጽዮን በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አዲስ አለም ላይ የተሠራችበት በመኾኑ፡፡ ፱ኛ. ሴቶችም ወንዶችም የሚያስቀድሱበትና ያለ ዐምድ ዕፁብ ድንቅ በኾነና በሃግያ ሶፍያ ቤ.ክ. አምሳል የተሠራው የጽዮን ቤተ ክርስቲያን (ኅዳር 21 ጾም በመኾኑ ቅዳሴ ቤቷ የተከበረው ግን ጥር 30 ቀን 1957 ዓ.ም ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ፣ እቴጌ መነን፣ የታላቋ ብሪታንያ ንግሥት ግርማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥና ልዑል ፊልፕ በተገኙበት ቢሆንም) ቅዳሴ ቤት የተከበረበት በመሆኑ፡፡ #ታቦተ_ጽዮንና #ጽዮን_ድንግል_ማርያም_፤ ፠ ታቦተ ጽዮንን፤ ሌዋውያን ከበዋት ውዳሴ፥ ዝማሬ ያቀርቡላት እንደነበረው፤ ✤ ዛሬም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ካህናትና ምእመናን ከሩቅ እና ከቅርብ ተሰብስበው በማኅሌት፥ በዝማሬ፥ በቅዳሴና በውዳሴ ያከብሯታል፡፡ ፠ ታቦተ ጽዮን በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ የኖረች ፥ የዮርዳኖስን ባሕር የከፈለች /ኢያሱ 3÷14-17/ ፥ ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች /ኢያሱ 6÷1-21/ ፥ ዳጎን የተባለ የፍልስTጤማውያንን ጣዖት የቈራረጠች /1ኛ ሳሙ. 5÷1-5/ ፥ በድፍረት ሊነካ የሞከረውን ኦዛን የቀሰፈች /1ኛ ሳሙ. 6÷6/ ፥ በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች /2ሳሙ 6÷12/ ፥ ዳዊት የዘመረላት /2ሳሙ 6÷14/ ፥ ጠቢቡ ሰሎሞን በቤተ መቅደስ በክብር ያኖራት /1ኛ ነገ፣ 8÷1/ ፥ የእግዚአብሔር የክብር መገለጫ ናት፡፡ ✤ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያምም ንጽሐ ጠባይዕ ሳያድፍባትና የቅድስና ባሕርይ ሳይጎድፍባት፤ (በማየት፣ በመስማት፣ በመዳሰሰ፣ በማሽተት አንዳችም እድፍ ጉድፍ ሳያገኛት) በንጽሕናና (በኀልዮ፣ በነቢብ፣ በገቢር) በቅድስና ጸንታ በኀጢአት ሳትለወጥ ኖራለች፡፡ /ውዳሴ ማርያም፣ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም፤ አንቀጸ ብርሃን፣ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ/ እንዲሁም ‹‹ምክንያታዊ ነውር ኃጢአት የሌለብሽ የኀጢአት ሸታ ያልደረሰብሽ ንጽሕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና ክብርት በልዕልና አንቺ ነሽ» ብሏታል ጠቢቡ ሰሎሞን /መሓ. 4÷7/ ፠ ታቦተ ጽዮን በከበረ ወርቅ እንደተሸለመች ✤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በንጽሐ ሥጋ፣ በንጽሐ ነፍስ እና በንጽሐ ልቡና የተሸለመች ያጌጠች ናት፡፡ ፠ ታቦተ ጽዮን የቃለ እግዚአብሔር ማደሪያ እንደሆነች፤ ✤ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያምም ለአካላዊ ቃል ለእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያ ኾናለች፡፡ «ድንግል ማርያም ሆይ ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አምላክ ለእርሱ ማደሪያ ሆንሽ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀንሸ ቻልሽው ተሸከምሽው ሰማይና ምድር የማይወስኑትን ለመወሰን የታመንሽ አንቺ ነሽ» /ውዳሴ ማርያም፣ ቅዱስ ኤፍሬም/ ……… **** በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቃል ኪዳኑ ታቦት መካከል ጥልቅ የሆነ ምሥጢራዊ ትምህርት አለ፡፡ /ዘፀ. 25÷9-20/፡፡ ይህንንም በተመለከተ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል ምሥጢሩን ከምሥጢር አመሳጥሮ፤ እንደ ሸማ አንከባሎ፥ እንደ ወርቅ ከብልሎ እንዲህ አስቀምጥታል፤ «ታቦተ አምላከ እስራኤል ጽዮን ዘነገደት ምድረ ኢሎፍሊ፤ ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ፡፡ አመ ነገደት ቊስቋመ በኀይለ ወልዳ ከሃሊ፤ ወድቁ አማልክተ ግብፅ መናብርተ ሰይጣን ሐባሊ፤ ወተኀጉሉ ኲሎሙ ዘቦሙ አስጋሊ፡፡ ወደ ኢሎፍሊ ምድር ተማርካ የሔደች የእስራኤል አምላክ የቃል ኪዳኑ ታቦተ ጽዮን የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው፡፡ ድንግል ማርያምም ሁሉን ማድረግ ከሚችለው ከልጇ ጋር ግብፅ ወደሚባል ሀገር በሔደች ጊዜ የሐሰተኛ ሰይጣን ዙፋኖች የሆኑ የግብፅ ጣዖታት ፈረሱ ጠንቋይ አስጠንቋይ ያላቸው ሁሉ ዐፈሩ» /ኢሳ 19÷1፣ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል/ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #የኅዳር_ጽዮን_ወረቦችን_በዚህ_በቴሌግራም_አድራሻችን_ያገኛሉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#ለኅዳር_ጽዮን_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ (የሰ/ትቤታችን አባላት፣ 30 የሚጠጉ የሰ/ትቤት ተዋካዮች፣ የአጥቢያችን ምዕመናንና ሕዝበ ክርስቲያንን በአንድነት የሚያሳትፍ ጕዞ) ፠የጕዞ ቀናት፤ ቅዳ
+2
#ለኅዳር_ጽዮን_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ (የሰ/ትቤታችን አባላት፣ 30 የሚጠጉ የሰ/ትቤት ተዋካዮች፣ የአጥቢያችን ምዕመናንና ሕዝበ ክርስቲያንን በአንድነት የሚያሳትፍ ጕዞ) ፠የጕዞ ቀናት፤ ቅዳሜና እኁድ (ከኅዳር 20-21) 2012 ዓ.ም. ፠ለመመዝገብ፤ የሰ/ትቤታችን ልማት ክፍል፣ ትምህርት ክፍል ወይም መዝሙርና ኪነ ጥበባት ክፍል እንዲሁም በ0910 61 72 58 ወይም 0902 50 39 54 ብለው ይደውሉ፡፡ ፠የጕዞ ዋጋ፤ 250 ብር (ምግብን ጨምሮ) ፠የመመዝገቢያ ቀናት፤ እስከ ኅዳር 19/2012 ዓ.ም. /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

፨፨፨ #በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤ ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ
+3
፨፨፨ #በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤ ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን ታቦቷ የመጣው) ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም (በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ተመሠረተች) ✣ዝዋይ ደብረ ጽዮን ማርያም (ደቡብ ሸዋ) ✣ሳዶቅ አምባ ማርያም (በ1670 ዓ.ም. በአባ ሳዶቅ የተመሠረተች ፥ ሰሜን ተራሮች) ✣እንፍራንዝ ደብረ ጽዮን ማርያም (ጥንታዊዋ ደብር) ✣ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም (በወርቅና በዕንቊ ተደርጋ በራስ ውቤ የታነጸች፤ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠባት፤ ስሜን፣ ራስ ደጀን አጠገብ) ✣ ደብረ ጽዮን ማርያም (ነቀምት) ✣ ደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም (ባሕርዳር) ✣ አርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ማርያም ✣ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ማርያም (እንግሊዝ ፥ ለንደን) በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

፨፨፨ #በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤
+8
፨፨፨ #በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤

✣✣✣ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች የጾም ምግብ ይዘጋጅልን በማለታቸው፣ ነጠላ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲሔዱና እንዲመለሱ በመጠየቃቸው፤ ተማሪዎችን እንዳይማሩ ቀሰቀሳችሁ ተብለው አምስት ተማሪዎች እንደተባረሩ፤ ከ20 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ለመባረር ስማቸው ተዘርዝሮ መያዙን ተማሪዎች ገለጡ። ✣✣✣ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተማሪዎች በሃይማኖታቸው ምክንያት በተደጋጋሚ ችግር ያጋጥማቸዋል፤ ለምሳሌ ያህልም ከዓመት በፊት አንድ ተማሪ ትልቅ መስቀል አደረግህ ተብሎ ተባርዋል።

የዓለም ኹሉ መምህር የኾነው #ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ባረፈ በ35 ዓመቱ (በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን) በዛሬዋ ዕለት ኅዳር 17 ሥጋው ፈልሶ በቊስጥንጥንያ በክብር ያረፈበት ነው፤ የቅዱሱ ሥጋውም ቀና ብሎ ሕዝቡን ባርኳል፡፡ ✣✣✣ስለ ቀዳማዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዳግማዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ) እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡፡ ✤አፈ ዕንቊ ✤አፈ ጳዝዮን ፤(/ስለ እመቤታችን ፍቅር/ የወር አበባ ያላትን ሴት አንቀጸ ሥጋ ለመሳም ያላፈረ) ✤አፈ ባሕርይ (በድርስቶቹ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስጌጣት) ✤አፈ መዐር ✤አፈ ሦከር (በቃሉ ጣፋጭነት ምእመናንን የሚያለመልማቸው) ✤አፈ አፈው /ሽቱ/ (በትምህርቱ መዐዛ የምሥጢር በጎችን ደስ የሚያሰኛቸው) ✤አፈ ርኄ ✤አፈ ሰይፍ (በውግዘቱ ሥልጣን ከሀዲዎችን የሚቆርጥ) ✤አፈ መጥባሕት ✤የማይነዋወጥ ዐምድ ✤የማይፈርስ መሠረት ✤ከሞገዶች መነሣት የተነሣ የማይሰበር መርከብ ✤በሃይማኖት ባሕር ውስጥ የሚዋኝ ዋናተኛ ✤የማይፈርስ ግንብ ✤በጠላት ፊት የሚፀና አዳራሽ /መጽሐፈ ምሥጢር፣ ዘጌና ምንባብ/ በተጨማሪም፤ በሚከተሉት ስሞችም ይጠራል፡፡ ፨አፈ ወርቅ /የእመቤታችን ስዕል አፍ አውጥታ ነው ዮሐንስ አፈወርቅ ብላ የሰየመችው/ ፨አፈ በረከት ፨ልሳነ ወርቅ ፨የዓለም ሁሉ መምህር ፨ርዕሰ ሊቃውንት ፨ዐምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ) ፨ሐዲስ ዳንኤል ፨ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው ሊቀ ጳጳሳት) ፨መምህር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ ፨ጥዑመ ቃል ~~ ምስጋና ለአምላካችን ይሁንና ንስጥሮስ በምፍቅናው የአንዲት ሴትን ኀፍረት ሥጋ ገልጦ እግዚአብሔር ወልድ በዚህ ማሕፀን ተፀንሶ አልተወለድም ብሎ በሕዝቡ ፊት ተናገረ፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም፤ * ‹‹እኔ እግዚአብሔር .. በዚህ ሥጋ ከሴት እንደተወለደ አምናለሁ፤ * እኔ እግዚአብሔር በመዋለጃ ማኅፀን እንደተወሰነ አምናለሁ፤ * እኔ እግዚአብሔር በድንግልና ወተት እንዳደገ፣ በሕፃናትም ሥርዐት ሕፃናትን እንደመሰላቸው፣ ከብቻዋ ከኀጢአትም በቀር የሰውን ሕግ ሁሉ እንደፈጸመ አምናለሁ፡፡›› ብሎ የዚህችን ሴት ኀፍረተ ሥጋ ስለ እመቤታችን ፍቅር ብሎ ሳመ፤ ከእመቤታችን ሥዕል አንደበትም ከዚህ በኋላ ስምህ ዮሐንስ ብቻ ሳይኾን ‹‹ዮሐንስ አፈወርቅ›› ይሁን ብላ ሰይመችው፤ አርሱም ‹‹እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ ወእዌድሰኪ … ›› ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የሚነበበውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት፡፡ *በ347 ዓ.ም. በሶርያ ዋና ከተማ በአንጾኪያ ሲኾን የተወለደው፤ አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ አትናስያ ይባላሉ፡፡ *ገና የ15 ዓመት ሕፃን ሳለ በሕፃንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) በሙሉ ተምሮ ተመልሷል፤ በዚህም በመንፈሳዊውም ኾነ በዘመናዊው ይፍልስፍና ይህ ቀረህ የማይባል ሊቅ ኾነ፡፡ *ቅዱሱ በ16 ዓመቱ ኃብትና ንብረቱን ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ፤ በበርሃ ሳለም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጥተው፤ ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሰጡት፡፡ የመጻሕፍት ድርሰት ተገለጹለት፤ በዚህም ቅዱስ በትጋትና በንቃት እጆቹ ታመው በክር አስሮ እስኪጽፍ ድረስ ዐሥር ሺህ የሚደርሱ ድርሳናትን መልዕክታትንና ትርጓሜያትን ጻፈ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ፤ በቅድስናው ወደውታልና የቊስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት፡፡ በሚያስተምርበት ጊዜም ከጣዕመ ትምህርቱ የተነሣ ሕዝቡ ተመስጠውና ተደመው ይሰሙት ነበር፤ ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር፡፡ በሠርጓ ቀን በሞት ሊወስዳት የመጣውን መልከአከ ሞት ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ ገዝቶ 10 ዓመት አቁሞታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ.ም. አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ:: /ምንጭ፤ መጽሐፈ ምሥጢር፣ ማኅሌተ ጽጌ፣ ተአምረ ማርያም፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱና ትምህርቱ በዲ.ን. ያረጋል አበጋዝ፣ የቃል ትምህርት፣ የዲ.ን. ዮርዳኖስ መጽሐፈ ገጽ፣ በእንተ ምክንያተ ሐውልታት በገብረእግዚአብሔር ኪደ/ ✤✤ #በአንበሳ ላይ የምትጫነው ኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዕረፍቷ ነው፡፡ * በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ ኢትዮዽያ ደዋሮና ፈጠጋር አካባቢ ሲኾን የተወለደችው፤ አባቷ ባሕር አሰግድና እናቷ ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ፡፡ * በወግ በማዕረግ ባል አገባች፤ ግን ወዲያው አፄ ያዕቆብ ገደሉባት፤ ወላጆቿም ግድ ብለው ስዕለ ክርስቶስ የተባለ የሱስንዮስን የጦር መሪ አጋቧት 24 ዓመት እስኪኾናት ድረስም 3ት ልጆችን ወለደች፡፡ አፄ ሱስንዮስ ካቶሊክ በኾነ ጊዜ ባሏ ወደ ንጉሡ እምነት ወደ ካቶሊክነት ገባ፡፡ ልጆቿም እግዚአብሔርን የማያስደስቱ ከኾነ በሞት ውሰዳቸው ብላ ለፈጣሪ በመንገሯ ሦስቱም ልጇቿ ሞቱ፤ ባሏም ክዶ ወደ ካቶሊክነት ስለገባ ተለይታው ወደ ጣና ገዳማትና ወደ ታላቁ ገዳም ዋልድባ ገብታ ብዙ ተጋደለች፡፡ * ንጉሡንም በካቶሊክ እምነቱ ከሌሎች ቅዱሳን ጋራ ኾና ስለተቃወመችው 2 ጊዜ ወደ በርሃ አግዟታል፤ ወደ ጉሙዝ ባጋዛት ወቅት ወደ እሳት ውስጥ ቢከታትም እሳቱ ሳያቃጥላት ወጥታለች፡፡ * ፋሲል ነግሶ ሃይማኖት ተመልሶ ሃገር ሲረጋጋ ወደ ምጽሌ ከዚያም ወደ መንዞ መጥታ 7ት ገዳማትን አቅንታለች፡፡ ከ700 በላይ ለሚኾኑ መነኰሳትና መነኰሳይያት እመ ምኔት ኾናም አስተዳድራለች፡፡ ምግቧም የመረረ ቅጠልና ኮሶ ነበረ፡፡ በስተመጨረሻም የሬማ መድኀኔ ዓለምን አቅንታ በተወለደች በ50 ዓመቷ ብዙ ቃል ኪዳንን ተቀብላ በ1630ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ዐርፋ በዚሁ ገዳም በክብር አርፋለች፤ በበዓለ ዕረፈቷም የብርሃን ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ታይቷል፡፡ ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ ሰማዕትም ጻድቅም ናት፡፡ /ምንጭ ገድለ ወለተ ጴጥሮስ፣ የዲ.ን ዮርዳኖስ መጽሐፈ ገጽ/ (ጽሑፎቹን ከቃል ትምህርት፣ ከመጻሕፍትና ከመጽሐፈ ገጽ አውጣትቶ ለጻፈልን ወንድማችን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ የዳግማዊ ዮሐንስ አፈወርቅ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ)ና የቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ረድኤት በረከታቸው ይደርበት፡፡) እኛንም አንባቢዎቹን በረከታቸው ትድረሰን፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ HYPERLINK "https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/" የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ HYPERLINK "https://t.me/medihanaelem" https://t.me/medihanaelem

ለ 2ት ዓለም ሰዎች ትምህርት የሚሆኑ፤ ታሪካቸው እጅጉን ከመሚሰጠውና በስንክሳር ላይ ከተጻፉት መካከል አንዱ ዛሬ ኅዳር 16 በዓለ ዕረፍታቸው የሆነው የመነኰስ #አባ_ዳንኤል_ገዳማዊና_ጻድቁ_ንጉሥ_አኖሬዎስ_ናቸው፡፡ ፠ #አባ_ዳንኤል_፤ የተባለው ጻድቅ፣ ታላቅ ገድለኛ ሲኾን እንጀራን ዓሣንም ቢሆን ማርንም ዘይትንም ቢሆን ከብቻው ቅጠል በቀር ሳይቀምስ አርባ ዓመት ተኩል በአስቄጥስ ገዳም ኖረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ መነኰሳትን የሚፈትን የመመካት ጾር መጣበት። ይህ ፈተና አንድ ጊዜ ታላቁን ቅዱስ አባ መቃርስን በፈተነው ጊዜ ሰውን የሚወድ ቸሩ አምላካችን አባ መቃርስን ወደ ከተማ እንዲኼድና የወንድማማች ሚስቶችን ኹነው ልጆቻቸውን እያሳደጉ በከተማ ከሚኖሩት ኹለት ገድለኛ እናቶች እንዲማርና ጾሩ እንዲጠፋለት አድርጓል። አሁንም ይህ ታላቅ ቅዱስ አባ ዳንኤል የመጣበትን ጾር ቢመለከት መልአከ እግዚአብሔር ተገለጠና ወንድሜ፣ ቸሩ አምላካችን ክርስቶስ እንዲህ ያለውን የመመካት ከትሕትናና ከፍቅር በቀር አይወድምና ተው አለው። አባ ዳንኤልም ጌታዬ ይህን እንድተውና ጦሩም እንዲጠፋልኝ ከኔ የሚበልጥ ጻድቅ አሳየኝ አለው፡፡ መልአኩም በሮሜ የነገሠ ንጉሥ ኹኖ ሳለ ነገር ግን በገድሉ ጽኑዕ ታጋይ ተጋዳይ መነኰስ የሆነውን #የጻድቁን_አኖሬዎስን_ ነገር ነገረው። አባ ዳንኤልም ይህን ሲሰማ በምድር ላይ ተደፋና በራሱ ላይ አመድ ነስንሶ አለቀሰ፤ በኋላም ይህን ገድለኛ ንጉሥ ሊያየው ወደደና ጸለየ። ብርህት ደመናም መጣችለትና ተጭኖ ወደ ሮሜው ንጉሥ ዘንድ ኼደ። እንደደረሰም አገልጋዩን ጠርቶ እባክህ ወንድሜ ንጉሡን ማግኘት እሻለሁና የሚያገናኘኝን መኰንን አገናኘኝ አለው። እርሱም እኔ ባስገባህስ አትገባምን? አለው። እግዚአብሔር ይባርክህ ልጄ አስገባኝ አለው። አባቴ ሆይ ግን ምድራዊ የሆነ ሟች ፈራሽ ንጉሥን ስለምን ማየትን ወደድህ አለው፣ እርሱም ቸሩ ጌታዬ ስላዘዘኝ እንጂ ነው አለው። በኋላም ቆየን ለጌታዬ የሚሻውን ገዝቼ ልምጣ ብሎ ወጣና ጥቂት ጨው አምባሻና እና መጻጻ ገዝቶ መጣ። ይህንም ይዞ አብማሻ ጨው መጻጻና የጎመን ቅጠልም ገዝቶ ወደ ጌታው ወደ ንጉሡ እና ወደ ንጉሡ መምህር አባ አውሎጊስ ዘንድ ገባ፣ አባ ዳንኤልንም በውጭ ተወው። ንጉሡም ረዳቱን አንተ አላዋቂ ነህን? ስለምን አባ ዳንኤልን በአፍአ ተውኸው አለውና ከመምህሩ ከአውሎጊስ ጋራ ወጣ። ለአባ ዳንኤልም ሰገዱለት። ሰላምታም ተሰጣጥተው ወደ ቤተ መንግሥት አስገቡትና በአንድነት ተቀመጡ። ዘጠኝ ሰዓትም በሆነ ጊዜ ለማዕድ ሲሰየሙ አባ ዳንኤል እንዳይታመም ፈርቶ ጌቶቼ እንጀራን ባለመብላቴ በእኔ ላይ አታጒረምርሙ፣ እንዳልታመም ፈርቼ ነው አላቸው። ጸሎትንም ጸለዩ፣ ከዚህም በኋላ ንጉሥ አኖሬዎስ አባ ዳንኤልን ስለአመጣጡ መረመረው፣ አባ ዳንኤልም የሚቻልህስ ከሆነ ከንጉሡ ዘንድ አስገባኝ፣ በጌታ ክርስቶስ ትእዛዝ መጥቻለህይና አለው፣ ነገ አስገባሃለሁ አለው። በማግስቱም አኖሬዎስ ዐይን የሚበዘብዝ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ በዙፋኑ ላይ ተቀመጠ፣ አባ ዳንኤልንም አስገቡት በአየውም ጊዜ ፈርቶ ተንቀጠቀጠ፣ ረዳቱም መፍራቱን አይቶ ወደ ማደሪያው መለሰው። ንጉሡም ችሎቱን ሲጨርስ ልብሰ መንግሥቱን ጨርሶ ልብሰ ምንኲስናውን ለብሶ ወደ አባ ዳንኤል መጣ፣ እርሱም ወንድሜ ሆይ በልቤ ያለውን ነግሬው ወደ ቦታዬ እመለስ ዘንድ ወደ ንጉሡ ለምን አላስገባኸኝም አለው። አኖሬዎስም አባቴ ሆይ አልገ አልገባህምን? ለዚህች ምድር ንጉሥ ብለው የሰየሙኝ እኔ ነኝ አለው፣ አባ ዳንኤልን በሰማ ጊዜ ከእግሩ በታች ሰገደለትና አኗኗሩን ሁሉ ይነግረ ዘንድ በጌታችን ስም አማጸነው። አኖሬዎስም በጅግ ሥራው ፈክሞ ከሚያገኘው በቀር (ይህም ሰሌን መታታት ነው) ሳይበላ ሳይለብስ አርባ ዓመታት እንደሆነው፣ የሚተርፈውንም ለድኆች እንደሚሸጥ ምግቡም እንጀራና ጨው ቅጠል መጻጻም እንደሆነ፣ የማንንም ገንዘብ ለመቀማት እንዳልደፈረ ድንግልናውንም መጠበቁን ነገረው። አባ ዳንኤልም ከእግሩ በታች ሰገደለትና አባቴ በአንተ ላይ ስለተመካሁ ይቅር በለኝ አለው። ከዚህም በኋላ አባ ዳንኤል ፈጽሞ እያዘነ ወደ ቦታው ተመለሰ። ከኹለት ወራትም በኋላ ጻድቁ ንጉሥ አኖሬዎስ ከመምህሩ ተማክሮ መንግስቱን ጥሎ ወደ አባ ዳንኤል ኼደ። መልአከ እግዚአብሔርም ተሸክሚ አደረሰው። እነርሱም በአንድነት ሲጋደሉ በፍቅር ኑረው በዚህች ቅድስት እለት በአንድነት አረፉ። እንዲሁም መምህሩ አውሎጊስና ረዳቱ በዚያች ዕለት በአንድነት አረፉ። አባ ጽጌ ድንግልም በማኅሌተ ጽጌ እንዲህ ሲል አውስቷቸዋል፡፡ እንበይነ አውሎጊስ ለዳንኤል አመ አርአዮ ስቅለተ፤ ከመ እገሪሁ ሰዓምኪ ወሰአልኪዮ ምሕረተ፡፡ ለተአምረ ሣህል ወልድኪ በእንተ ፍቅረ ሰብእ ዘሞተ፤ እንዘ ታዘክሪዮ ድንግል ይምሐረኒ ሊተ፤ ከናፍሪሁ ጽጌ አንኂ ስዕመተ፡፡

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን #ፍኖተ_ሕይወት_የንዋያተ_ቅድሳት_መሸጫ_ ፠ ቅዱሳት መጻሕፍት ፠ ዕጣን፣ ጧፍ፣ ሻማ፣ ዘቢብ፣ ….. ፠ ንዋያተ ቅድሳት (ጥላ፣ መጎናጸፊያ፣ መስቀል፣
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን #ፍኖተ_ሕይወት_የንዋያተ_ቅድሳት_መሸጫ_ ፠ ቅዱሳት መጻሕፍት ፠ ዕጣን፣ ጧፍ፣ ሻማ፣ ዘቢብ፣ ….. ፠ ንዋያተ ቅድሳት (ጥላ፣ መጎናጸፊያ፣ መስቀል፣ …….) ፠፠ እንዲሁም ሌሎችንም በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ፡፡ አድራሻ፤ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ በዋናው በር አጠገብ፡፡