ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 381 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 582 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 381 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 09 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 38، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.91‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 370 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 449 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 25.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 381
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዱስ ያሬድ ዜማ በቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት የተጀመረበትን በማስመልከት፤ #ማክሰኞ_ታኅሣሥ_7/2012 ዓ.ም. #በደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ #ለመጀመሪያ_ጊዜ_ክብረ_በዓሉ_ታ
+3
ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዱስ ያሬድ ዜማ በቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት የተጀመረበትን በማስመልከት፤ #ማክሰኞ_ታኅሣሥ_7/2012 ዓ.ም. #በደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ #ለመጀመሪያ_ጊዜ_ክብረ_በዓሉ_ታቦቱ_ወጥቶ_ይከበራል_፡፡ አርአዮ ለሙሴ ግብራ ለደብተራ፤ ወተናገሮ በዓምደ ደመና፡፡ (አድራሻ፤ ጎተራ ከአጎና ሲኒማ ከ,ወደ መስቀል ፍላወር በሚወስደው መንገድ፡፡)

‹‹ነገረ ክርስቶስ በቅዱስ ያሬድ፡፡›› ታኅሣሥ 4/2012 ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት አዳራሽ፤ ከቀኑ በ7፡30፡፡
+2
‹‹ነገረ ክርስቶስ በቅዱስ ያሬድ፡፡›› ታኅሣሥ 4/2012 ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት አዳራሽ፤ ከቀኑ በ7፡30፡፡

#ኢየዐርብ_ፀሐይኪ_፤ #ወኢየሐልቅ_ወርኅኪ_፡፡ (ፀሐይሽ አትጠልቅም፥ ጨረቃሽ አይቋረጥም እግዚአብሔር የዘለዓለም ብርሃንሽ ሆናልና፤ የልቅሶሽም ወራት ታልቃለችና፡፡) ት.ኢሳ. ፷፥፳ (#እንዳይረሳ_የታ
+4
#ኢየዐርብ_ፀሐይኪ_፤ #ወኢየሐልቅ_ወርኅኪ_፡፡ (ፀሐይሽ አትጠልቅም፥ ጨረቃሽ አይቋረጥም እግዚአብሔር የዘለዓለም ብርሃንሽ ሆናልና፤ የልቅሶሽም ወራት ታልቃለችና፡፡) ት.ኢሳ. ፷፥፳ (#እንዳይረሳ_የታኅሣሥ_5ቱ #መርሐ_ግብራችን_በሚሊኒየም_አዳራሽ_)

#✤#የበኣታ_ማርያም_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ደብረ ኤረር በዓታ ወልደታ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብራሃ ወአጽብሃ የተመሠረተ፡፡ #ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ ዑርኤል ወበኣታ፤ ጎንደር ከተማ፤ ከ300ዓመ
+6
#✤#የበኣታ_ማርያም_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ደብረ ኤረር በዓታ ወልደታ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብራሃ ወአጽብሃ የተመሠረተ፡፡ #ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ ዑርኤል ወበኣታ፤ ጎንደር ከተማ፤ ከ300ዓመታት በፊት በጎንደር ዘመነ መንግሥት የተሠረተችና የታች ቤት አቋቋም ዋና ምስክር ጕባኤ ቤት፡፡ #ታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም ወስዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት፤ /አ.አ. መካነ አጽሙ ወተዝካረ ስሙ ለዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ፤ 1910ዓ.ም. በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለአባታቸው ምኒልክ መታሰቢያ የተሠራ/ #መቀሌ በኣታ ለማርያም #ባሕር ዳር በኣታ ለማርያም፤ #ጮቢ በኣታ ለማርያም ገዳም፤ ሸዋ #ሆሳዕና በኣታ ለማርያም፤ /በዛፍ ላይ ድንቅ ተአምር የሚታይበት/ #ጂንካ በኣታ ለማርያም፤ #ደብረ በአታ ለማርያም /ሂውስተን አሜሪካ/ ✤#የቅዱስ_ፋኑኤል_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ጋዥ ሜዳ ድሬ አክርሚት ፋኑኤል፤ /ሰሜን ሸዋ፥ ሃገረ ማርያም/ #አዲስ አበባ ካራ ቆሬ ቅዱስ ፋኑኤል ቤ.ክ. #አዲስ አበባ አያት ቅዱስ ፋኑኤል ✤#የአቡነ_ዜና_ማርቆስ_አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ምሁር ኢየሱስ ገዳም /ጉራጌ ሃገር/ #ደብረ ብሥራት /ሰሜን ሸዋ፥ እነዋሪ፥ ጅሩ/ …………. ሌሎችን በየአጥቢያችሁ ያሉትንና የምታውቋቸውን አብያተ ክርስቲያናት እናንተ ጨምሩበት...

#✤#በኣታ_ለማርያም፤ እመቤታችን አባትና እናቷ ኢያቄምና ሐና በስዕለት(ለቤተ መቅደስ ሊሰጡ ብፅዓት ገብተው) ያገኟት ናት፡፡ በአባት በእናቷ ቤትም ፫ ዓመት ተቀመጠች፤ ከእንግዲህ ወዲያማ ስእለት መብለት ይሆንብን የለምን ወስደን እንስጥ ብለው ይዘዋት ወደ ቤተ መቅደስ ሲሄዱ ዘካርያስም ሕዝቡን ሰብስቦ ጉባኤ አድርጎ ቆያቸው። **ከዚያውም ደርሰው እነሆ ተቀበሉን አሏቸው እነርሱም እንቀበላለን ብለው ቢያዩዋት ከፀሐይ ፯ እጅ አብርታ፥ ከመብረቅ ፯ እጅ አስፈርታ፥ ዕንቈ ባሕርይ መስላ ታየቻቸው፤ እነርሱም እኛ ይህችን የመሰለች ፍጡር ምን እናደርጋታለን? ምን እናበላታለን? ምን እንጋርድላታለን? ብለው ሲጨነቁ በዚህም መካከል እመቤታችንን እግዝእትነ ማርያም መንፈሳዊ ረኀብ ተነስቶባት ምርር ብላ አለቀሰች። ያን ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል በመሶበ ወርቅ ኅብስት ሰማያዊ፤ በብርሃን ጽዋዕ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው፡፡ ሕዝቡም ዘካርያስን አባታችን ይህ የወረደው ክብር ላንተ ነው የሚኾነውና ተነስተህ ታጥቀህ እጅ ነስተህ ሰግደህ ተቀበል አሉት፤ ዘካርያስም እሽ ብሎ እጅ ነስቶ ሰግዶ እቀበላለሁ ብሎ ሲጠጋ ወደ ሰማይ ራቀው፥ መጠቀው፡፡ ከሕዝቡም እያንዳንዱ እየተነሱ እንቀበላለን ብለው ቢያዩ ወደ ሰማይ ራቃቸው፥ መጠቃቸው፡፡ **ከዚህም በኋላ ዘካርያስ ሐናን ጠርቶ ለናንተ ለእንግዶች የወረደ ክብር እንደሆነ ሕፃኒቱን ይዘሽ ወደዚያ ፈቅ ብለሽ ተቀመጪ አላት፡፡ እርሷም ሕፃኒቱን ይዛ ወደዚያ ፈቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ መልአኩም ከራሳቸው ላይ ረቦ አልወርድም አለ፡፡ ***ሁለተኛም ዘካርያስ ሐናን ጠርቶ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ነገር የሚያውቅ የለም፤ ሕፃኒቱን ከዚያው ትተሽ አንቺ ወዲህ ነዪ አላት፤ እሽ ብላ ሕፃኒቱን እዚያው ትታ ወደነሱ ሄደች፡፡ ያን ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል ወርዶ ፩ ክንፉን ጋርዶ ፩ ክንፉን አጎናፅፎ ኅብስቱን አብልቷት፥ ወይኑን አጠጥቷት፤ እመቤቴ ሆይ መንገድ ባስመታሁሽ ማሪኝ ብሎ የብርሃን መሶብ፥ የብርሃን ጽዋ ይዞ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ **ሕዝቡም የምግቧማ ነገር ከተያዘ ከሰው ጋራ ምን ያጋፋታል፤ ቦታዋ ከቤተ መቅደስ ይሁን እንጂ ብለው ዙፋኑን ዘርግተው፥ ምንጣፏን አንጥፈው፥ መጋረጃውን ግራና ቀኝ ጋርደው ከቤተ መቅደስ አኖሯት፡፡ ***ይኸውም የተደረገው ታኅሣሥ ፫ ዕለት ነው፤ በአታ የሚለው ስያሜም የተሰጠው በዚሁ ነው፡፡ ‹‹አመ ፫ ለታኅሣሥ በኣታ›› እንዳለ መቅድመ ተአምር፡፡ በዚህም፤ #መቅደሲቱ_ወደ መቅደስ ገባች፤ #ቅድስቲቱ_ወደ ቅድስት ገባች፤ #ክብርቲቱ_ወደ ክብርት ቤቷ ገባች፤ #ልዩ_የሆነችው_ወደ ልዩ ሥፍራ ገባች፤ #ቅድስተ_ቅዱሳኗ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ገባች፤ #ንጽሕተ_ንጹሐኗ ወደ ንጽሕ አዳራሽ ገባች፤ #ቤተ_መቅደሷ ወደ ቤተ መቅደስ ገባች፡፡ ሊቃውንትም ‹‹መቅደስ ዘኢትትነሠት /የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ››/ እያሉ አመሠገኗት፡፡ **እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ኅብስት ሰማያዊ እየተመገበች፤ ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከመላእክት ጋራ እየተጫወተች 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች፡፡ ‹‹ከመዝ ነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ፤ ወመላእክት ያመጽኡ ወትረ ሲሳየኪ ከመዝ ነበርኪ ፲ተ ወ፪ተ ዓመተ እንዘ ትትናዘዚ እምኀበ መላእክት ወስቴኪኒ ስቴ ሕይወት ውእቱ። ወመብልዕኪኒ ኅብስት ሰማያዊ››። እንዳለ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ***ምግቧ ከየት የተገኘ ነው ቢሉ በገበሬ እጅ ያልተዘራ በቤተ ሰብእ እጅ ያልተሠራ በእግዚአብሔር እጅ የተፈጠረ ያማረ የተመረጠ ነው እንጂ ፡፡ ‹‹ኦ ድንግል አኮ ኅብስተ ምድራዌ ዘተሴሰይኪ፤ አላ ኅብስተ ሰማያዌ እም ሰማየ ሰማያት ዘበሰለ፡፡ ኦ ድንግል አኮ ስቴ ምድራዌ ዘሰተይኪ አላ ስቴ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘተቀድ›› (ድንንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለሽም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን እንጂ፡፡ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለሽም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጥን ነው እንጂ፡፡) /እንዳለ ሊቁ አባ ሕርያቆስ/። ***ስታድግም በንጽሕናና በቅድስና ነው፡፡ ‹‹ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና ኖርሽ እንጂ።›› /እንዳለ ሊቁ አባ ሕርያቆስ/ ***እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሳለች አይሁድ ብዙ የክፋት ምክር ይመክሩ ነበር። ከዚህም ውስጥ አንዱ መጥቁል ወደሚባል ጠንቋይ ሄደው ‹‹ፍታሕ ማዕከሌነ ኢያቄም ወሐና›› ብለው እመቤታችንን እንዲያጠፋ እጅ መንሻን ሰጡት፤ መጥቁልም በመካከል አይሁድ በኋላ ሁነው ነጋሪት እየጎሰሙ፥ እምቢልታ እየነፉ እመቤታችንን እግዝእትነ ማርያምን ለመግደል ለቤተ መቅደስ ፪ ምንዳፈ ሐፅ ሲቀራቸው፤ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ እዚያ ድረስ ያልተደረገና ያልተነገረ መብረቅ ነጎድጓድ ወርዶ አጋንንትንም፥ መጥቁልንም፥ አይሁድንም ቀጥቅጦ አጠፋቸው። እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም በማግሥቱ ወጥታ አይታ መጥቁል ሆይ እኔን አጠፋ ብለህ መጥተህ አንተ እንዲህ ሆንህ ካንተ መከራ መዓት ያወጣኝ አምላክ ይክበር ይመስገን ብላ ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ ከዚህ በኋላ በድኑ ለዝክረ ነገር የ፫ ቀን መንገድ እየሄደ ይሸት ጀመር። እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ‹‹ዮሰሜር፣ አድሜሽ፣ ድቸር፣ አዶናዊሮስ፣ ሰራሰቅሰሬል›› ብላ የአምላክ ኅቡዕ ስምን ብትደግም መሬት ተከፍቶ ዋጣቸው ከነሥጋቸውም ሲኦል ወረዱ፡፡ ከዚህ በኋላ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እጅግ ታፈረች የሚናገራት ጠፋ ‹‹ኦ ግርምት ድንግል›› /እንዳለ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም/። ✤#በዓለ_ሢመቱ_ለቅዱስ_ፋኑኤል_ሊቀ_መላእክት፤ #ሰዳዴ አጋንንት ነው፤ /ሄኖክ 10፥8፣ ድርሳን ዘፋኑኤል/ #መጋቤ ድንግል ነው፡፡/ተአምረ ማርያም/ #ማኅሌታዊ ነው፤ #በመንበረ መንግሥቱ ዙሪያ ከሚቆሙት ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው፡፡ /ሄኖክ 20፥39/ #በአራቱ የዓለም ማዕዘናት ሹም አንዱ ነው፡፡ #ለመልካም ነገሮች ከሚራዱ መላእክት አንዱ ነው /መዝ. 33፥7/ #ካህነ ንስሐ ነው /ሄኖክ 10፥5/ #ዐቃቤ ጻድቃን ነው፡፡ /2ኛ ነገ. 6፥14/ #ምስለ_አብያጺሁ_ከመ_አብ_እንዘ_ይሴስየኪ_መና፤ #ፋኑኤል_ጽጌ_ነድ_ዘይከይድ_ደመና፡፡ ✤#ኢትዮጵያዊው_አቡነ_ዜና_ማርቆስ_በዓለ_ዕረፍታቸው ነው፡፡ እኒህ ታላቅ አባት በምድረ ጉራጌ በሚገኘው በምሁር ኢየሱስ ገዳም 40 ዓመታትን ሱባኤ የገቡ፤ ምድረ ጉራጌን (ሙሉ ሸዋን ጨምሮ እስከ ደቡብ) እንዲሁም በሌሎችም የሃገራችን ክፍሎች ያስተማሩ፤ በርካታ ሊቃውንትን /አባ ጽጌ ድንልንና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታን ጨምሮ ሌሎችን ሊቃውንትም/ ያፈሩ ፈርጥ ሲኾኑ፤ በስተመጨረሻ በተአምራት የተሞላውን ታላቁን ገዳም ደብረ ብሥራትን (ጅሩ) መሥረተው በክብር አርፈዋል፡፡ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

፻፶፫ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ ታኅሣሥ ፫/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ በሰዐቱ ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በእለቱ ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮችና ውዳሴ ማርያም በዜማ ይካሄዳል ላልሰሙት ያሰሙ፤
፻፶፫ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ ታኅሣሥ ፫/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ በሰዐቱ ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በእለቱ ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮችና ውዳሴ ማርያም በዜማ ይካሄዳል ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

ዛሬ በሰንበት ት/ቤታችን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለመወያየት አስቸኳይ የጠቅላላ ጕባኤ ስብሰባ መጥራታችን ይታወሳል፡፡ በጠራነው ጥሪ መሠረት በርካታ አባላት በስብሰባው ላይ በሰዓቱ ስለተገኛችሁ በእግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ዛሬ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በተሰጠው መመሪያ መሠረት ከደብሩ ሰበካ ጕባኤ፣ ማኅበረ ካህናት፣ የልማት ኮሚቴ አባላትና ከአስተዳደር ሠራተኞች ጋር ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 12፡30 ሰዓት ሰፊ ውይይት በማድረግ ከታች በተያያዘው ቃለ ጕባኤ እንደተመለከተው የሰንበት ት/ቤቱ ጠቅላላ ጕባኤ ተሰብሰቦ ለሰንበት ት/ቤቱ አገልግሎት ምቹ የሆነ ቦታ እስኪሰጥ ድረስ አዳራሹን የአገልግሎት ክፍሎች እንደማይፈርሱ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ስለሆነም ሁሉም አባላት በቀጣይ በጉዳዩ ላይ ስብሰባ እስኪካሄድ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ እያሳሰብን ነገ በሚከናወነው የደብሩ ሁለገብ ሕንፃ የመሠረት ድንጋይ የመጣል መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ቅዱስነታቸውን እንድናጅብ መርሐ ግብሩን እንድንሳተፍ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡ የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራር፡፡

#ቅዱስ_ፊልሞና_ሐዋርያ_(_ጥዑመ_ቃል) ✤ከ72ቱ አርድእት አንዱ የኾነና 'ጥዑመ ቃል (አንደበቱ የሚጣፍጥ) በመባል የሚታወቅ ሲኾን፤ በዘመነ ሐዋርያት በጣም ልጅ በመሆኑ እየተሯሯጠ ለአበው ይታዘዝ ነበር፡፡ ከቅዱስ እንድርያስ ጋር ለስብከት ወጥቷል፤ ሃገረ ስብከቱም ልዳ ነበረች፤ እርሱ ሲያስተምርና ሲያነብብ ሰው ሁሉ በተመስጦ ይሰማው ነበር፤ አንዳንድ ቀን ደግሞ ወፎችና ርግቦች ያደምጡት ያዋሩትም ነበር፡፡ ሊገድሉት የመጡ ወታደሮች እንኳን በተደሞ መግደላቸውን ይረሱት ነበር፡፡ ይህ ታላቅ አርድእትና ሐዋርያ በዛሬው ዕለት ነው ያረፈው፡፡ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ፠•፠ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#ኅዳር_27_ #ያዕቆብ_ዘግሙድ_፤_የፋርሱ_ኰከብ፤ 42 አካላቱ ተቆራጠው ሰማዕት የኾነ፡፡ *ከክርስቲያን ቤተሰብ የተወለደው ቅዱስ፤ ሚስት አግብቶ በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ሠክራድ ጋር በጣም ይዋደዱና አማካሪውም ነበርና በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ሹም አድርጐ አስቀመጠው፤ በሒደትም ንጉሡ የሚለውን ሁሉ የሚፈጽም ሰው ሆነ፤ ንጉሡም "ለእሳትና ለፀሐይ ስገድ፤ እነሱንም አምልካቸው" ሲል ጠየቀው:: ያዕቆብም ገና በእምነት ያልጠነረ በመኾኑና ከንጉሡ ጋር ወዳጅ ስለነበረ ንጉሡን ለማስደሰት ብሎ የክርስትና እምነት የማይፈቀድወን ለሌሎች አማልክት (ለፀሐይ ሰገደ፤ እርሷንም አመለከ)፤ ክርስቲያኖቹ ይህንን ሲሰሙ እጅግ አዘኑ ይልቁኑ ደግሞ የቅርብ ወዳጆቹ የሆኑት እናቱ፥ እኅቱና ሚስቱ ይህንን ሲሰሙ እጅግ በማዘናቸው ደብዳቤ ጽፈው ተፈራርመው ላኩለት፤ የደብዳቤው ይዘት እንዲህ ይላል፤ "አንተ ክርስትናህን መካድህን ሰምተን አዘንን፤ በዚህም ምክንያት ከዚህ በኋላ በአካባቢህ መኖርን አንፈልግም፤ ከቅዱሳት መጻሕፍትም እየጠቀሱ፤ ለሞተልህ ለክርስቶስ ካልታመንሀ እኛ አንተን እንደ ልጅ፣ እንደ ወንድምና እንደ ባል ልናምንህ ይከብደናል፡፡››፤ ይህንን ደብዳቤ ልከውለት እነርሱ አካባቢውን ለቀቁ፤ ቅዱስ ያዕቆብ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደ ቤቱ ገብቶ ሲያነበው ደነገጠ፤ በዚህ ምድር ያሉት ዘመዶቹ ሚስቱ፣ እናቱና አንዲት እኅቱ ብቻ ናቸውና ውስጡ ተሸበረ፤ ተደፍቶም ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ *በመሸም ጊዜ ጸሎት ሲያደርግ ከንጉሡ ጋራ ያደረገውን ያልተገባ ቅርርብና ስህትት እግዚአብሔር ግልጽ ብሎ እንዲታየው አደረገ፤ እርሱም ‹‹ጌታ ሆይ፤ በምድር ካሉ የሥጋ ዘመዶቼ መለየት እንዲህ ካሸበረኝ፤ ካንተ ፍቅር መለየትማ እንደ ምን ይጨንቅ ይሆን፡፡ በሰማያዊ ዙፋንህ ፊትስ እንዴት ብዬ እቆማለሁ፡፡›› እያለ ሌሊቱን ሙሉ በእንባና በጸሎት አድሮ በጠዋት ንስሐ ገባ፡፡ ከዚህች እለት ጀምሮም ፍፁም በክርስቶስ ፍቅር ተጠመደ፤ ጾምና ጸሎትንም ወዳጆቹ አድርጐ ከንጉሡ እልፍኝና አደባባይ ቀረ፡፡ *ንጉሡም ይህንን በሰማ ጊዜ ጠርቶ ለምን እንዲህ አደረግክ ሲለው፤ ‹‹የፈጠረኝን ክርስቶስን ትቼ አንተን በባዕድ አምልኮ አስደስትህ ዘንድ የሚገባ አይደለም›› ሲል ተናገረው፤ ንጉሡም በብዙ ሽንገላ ሊያታልለው ቢሞክር እምቢ ስላለው ብዙ መከራን አደረሰበት ደሙ በመሬት ላይ እስኪንፈስ ድረስም አስገረፈው፣ አስደበደበው:፤ ጭንቅ መከራዎችንም አደረሰበት፡፡ **ቅዱሱ ግን በፍቅረ ክርስቶስ ጸና፤ በዚህ የተበሳጨው ንጉሡ በየቀኑ አካሉን እንዲቆራርጡት ግን ቶሎ እንዳይገሉት አዘዘ፡፡ ቀን በቀን እየገቡ ከአካሉ ይቆርጡ ጀመር፡፡ መሐል አካሉ (ወገቡና ራሱ) ብቻ እስኪቀሩ ድረስም ከጣቶቹ ተነስተው እጆቹን እስከ ክንዱ፤ እግሮቹን እስከ ታፋው ድረስ፤ ደረቱና አካሉ ግንድ እስኪመስል ድረስ ቆረጡ፤ ቅዱሱም እንዲህ እያለ በትጋት ይጸልይ ነበረ ‹‹የወይን ግንድ ሆይ፤ እኔን ቅርንጫፍህ አድርገኝ›› /ዮሐ. 15፥:5/ ይለው ነበር፤ ከአካሉ እየቆረጡ የጣሉትም ሲቆጠር 42 ሆነ:: 43ኛ ደግሞ የተረፈ ደረቱና አካሉ ነበርና፤ ተቆንጽሎ በቀረው ግማሽ አካሉ ‹‹አቤቱ ወደ አንተ የማነሳው አካል የልቀረልኝምና ነፍሴን ተቀበል›› እያለ ይጸልይ ነበር፤ ጌታችንም ተገልጾ ካረጋገው፣ ካጽናናውና ብዙ ቃልኪዳንን ከሰጠው በኋላ ከንጉሡ ጭፍሮች መካከል አንዱ መጥቶ አንገቱን በሰይፍ ቅረጠውና የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ኾነ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ታቅፎ ወደ ሰማይ አሳረገው፡፡ እናቱ፣ እኅቱና ሚስቱ ይህንን ሲሰሙ እያለቀሱና እየዘመሩ አካሉን ሰብስበው በክብር ቀበሩት፤ በደጋጎቹ ክርስቲያኖች በአኖሬዎስና በአርቃዴዎስ ዘመን ምዕመናን ውብ ቤተ ክርስቲያን ሰርተው በዚያ ሥጋውን በክብር አኖሩ፡፡ ✤#_አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት_ዘደብረ_ጽሙና_(_ዘገበርማ) **በምድረ አፋር(ለ14ዓመታት)፣ እንዲሁም በምድረ ሸዋና ጐጃም የሰበኩና ያስተማሩ አባት ናቸው፡፡ ከአባታቸው እንድርያስ (የአናዕርት ሃገረ ገዥ)ና ከእናታቸው እሌኒ፤ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወለዱና በዘመኑ ካሉ ዐበይት ጻድቃን አንዱ ናቸው፡፡ ገና በእናታቸው ማኅጸን ሳሉ አጋንንትን ያቃጥሉና ያጠፉም ነበር፡፡ *በዲቁናም ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመግባት እስከ ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ ደርሰዋል፤ ሥውራን የኾኑ ቅዱሳንም እየተገለጡ ምሥጢራትን ይነግሯቸው ነበር፡፡ ከስግደታቸው ብዛት የተነሣ የእጆቻቸው አጥንቶች እስከ መሠበር፥ ከቁመታቸውም ብዛት የተነሣ እግሮቻቸው እስከማበጥ ደርሰዋል፡፡ *ሲቀመጡና ሲሰግዱ የጌታችንን መከራ እንዲያስቡ፤ 8 ጦሮች ያሉበትን ሰንሰለት በአራቱ አቅጣጫ በወገባቸው ታጠቁ፡፡ ከልደት፣ ከጥምቀትና ከትንሣኤ በቀርም ከወገባቸው አይፈቱም ነበር፡፡ *ቅዱስ ሚካኤልም ዕፀ ገነት አምጥቶ ካሸተታቸው በኋላ ምድራዊን ነገር ለመቅመስ የሚጸየፉ ኾኑ፡፡ *ቅስናን እንዲሾሙ አበምኔቱ ሲጠይቃቸው እምቢ በማለታቸው ወደ ሊቀ ጳጳሱ መልእክት አድርሱልኝ ብለው በላኳቸው ጊዜ ጳጳሱ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ቅስናን ሹሟቸዋል፡፡ *ወደ ደብረ ጽሙና ጻድቁ አቡነ አትናቴዎስ መቃብር ሂደው በሚጸልዩበት ጊዜም ብርሃን ይወርድላቸው ነበር፤ እግራቸው በረገጠበት ቦታም ጸበል ፈልቆላቸው ቦታውን ላሳየቻቸው እግዚእ ክብራ ለተባለች ጻድቅት በጽዋ ሞልተው ሰጧት እርሷም መካን ለነበረችው አገልጋይ ብትሰጣት ልጅ ወለደች፤ ይህ ጠበላቸው እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ገቢረ ተዓምራትን እየሠራ በገዳማቸው ገኛል፡፡ መልአኩም ወደ በረሃ እንዲወርዱ በነገራቸው መሠረት ወደ ምድረ ሐጋይ በመሄድ ለ41ዓመታት በጽኑ ተጋድሎ ቆይተዋል፡፡ **ወደተለያዩ ገዳማት በመሄድም 40 ቀን (ከሰንበት ውጪ ሳምንቱን ሙሉ እያከፈሉ) ይጾሙና ይጸልዩ ነበር፡፡ ወደ ታላቁ ገዳም ወደ ዋልድባ ገብተው ሲወጡም ወደ ድባብ ገዳም ገዳም ሄደው 40ቀን ሲጾሙ ጌታችን ወዳልተጠመቁ ሄደው እንዲያስተምሩ አዝዟቸው አስተምረዋል፡፡ * ጻድቁ 3ት ነገሮችን እፈልጋለሁ፤ እነርሱም፤ ከሐሜት መራቅን፤ ክፉ ነገርን ከማየት መራቅን፤ ከንቱ ነገርን ከመስማት መራቅን፤ እያሉ ይናገሩ ነበር፡፡ *ሰማዕት እንዲኾኑም ይለምኑ ነበረ፤ እመቤታችንም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በመምጣት ‹‹የጳውሎስ አበባ፥ የጴጥሮስ ፍሬ፥ የልጄ ተክል›› የለመንከውን ታገኛለህና በርታ አለቻቸው፤ አርሳቸውም በነገረ ሠሪ ከንጉሡ ጋራ እንዲጣሉ አደረጓቸው፤ በንጉሡ ዘርዐያዕቆብና በሠራዊቶቻቸው ብዙ መከራን ተቀብለው በ71 ዓማታቸው በሰማዕትነት አረፉ፤ ከ14 ዓመት በኋላም በንጉሡ ዘርዐያዕቆብ ወንበር ልጁ በዕደ ማርያም በነገሠ ጊዜ ሥጋቸውን አፍልሶ በደብረ ጽሙና በክብር አሳረፈው፡፡ ጻድቁ በታላቁ ገዳማቸው በደብረ ጽሞናና በደብረ ሊባኖስ አጠገብ በሚገኘው በአጋት መድኀኔ ዓለም ክብረ በዓላቸው ይከበራል፡፡ ***ጻድቁ በተባሕትዎም ኾነ በትሩፋት እጅግ የተደነቁ አባት ነበሩ፡፡ ለአብነትም ያህል፤ * በትራቸው እንደ ሙሴ በትር ተዓምራትን ታደርግ ነበር፡፡ በብርሃን ሠረገላም ይጓጓዙ ነበር፡፡ * ክርስቶስን በመከራው ይመስሉት ዘንድ ዘወትር ይተጉ ነበር፤ *ሥጋ ወደሙ የተቀበለ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲያስመልሰው ተመልከተው ሁሉ ተጸይፎ ሲሸሽ እሳቸው ግን የፈጣሪን ሥጋና ደም በመመልከት ደስ እያላቸው እንደ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ተመግበውታል፤ በዚህ ጊዜም ጌታ ከሰማይ ወርዶ በግንባራቸው ላይ ፀሐይን ስሎባቸዋል፤ በዚህ ምክንያትም ፊታቸው ያበራ ነበር፡፡ *በገዳማቸው አንድ ዶሮ ለእንግዳ ሊያርዱት ሲሉ አፍ አውጥቶ ‹‹በአባ ተክለ ሐዋርያት ተማጽኛቹሃለሁ›› በማለቱ ትተውታል፡፡

#እጅግ_በጣም_አስቸኳይ_ጥሪ_፤ #ወአርአይከኒ_ፍኖተ_ሕይወት (#የሕይወትን_መንገድ_አሳየኸኝ_፡፡) መዝ. ፲፭፥፲፩ (ይህንን አስቸኳይ ጥሪ ላልሰሙ በስልካችሁ በመደወል፣ LIKE, SHARE በማድረግ በ
+1
#እጅግ_በጣም_አስቸኳይ_ጥሪ_፤ #ወአርአይከኒ_ፍኖተ_ሕይወት (#የሕይወትን_መንገድ_አሳየኸኝ_፡፡) መዝ. ፲፭፥፲፩ (ይህንን አስቸኳይ ጥሪ ላልሰሙ በስልካችሁ በመደወል፣ LIKE, SHARE በማድረግ በአስቸኳይ ጥሪውን አስተላልፉ!!)፤ #የሰንበት_ትምህርት_ቤታችንን_አዳራሽ_ተገቢና_በቂ_የሆነ_ተለዋጭ_ቦታ_ባልተሰጠበት_ሁኔታ_በልማት_ስም_ነገ_ቅዳሜ_የመሠረት_ድንጋይ_ሊጣልበትና_በቅርብ_ጊዜም_አዳራሻችንና_የክፍላት_ቢሮዎቻችንን_ሊያፈርሱብን_እንዲሁም_ሰንበት_ት/ቤታችን#መማሪያ_ቦታ_ላይኖረው_(#ሊበተን)#ስለሆነ፤ ዛሬ ዐርብ ኅዳር 26/2012 ዓ.ም.፤ ከምሽቱ 12 ሰዐት ላይ በሰ/ትቤታችን አዳራሽ እንድንገኝና ስለ ሰ/ትቤታችን የመማሪያ አዳራሽና የክፍላት ቢሮዎች ጉዳይ አንድንወስን፤ ሰ/ት/ቤታችን ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ #ከሰንበት ትቤታችን ምሥረታ እስከ አሁን ለ55 ዓመታት የሰ/ት/ቤታችን አሻራ ያረፈባችሁ በሙሉ፤ ፠ ነባር አባላት (በሰ/ት/ቤታችን ከምሥረታ እስከ አሁን ድረስ በተማሪነት፣ በአባልነትና በአገልጋይነት ላገለገላችሁ፤ በተለያዩ ሁኔታዎች /በሥራ፣ በትምህርት፣ በትዳር፣ በቤት ርቀት/ ለራቃችሁ ነባር አባላት፤ ፠ ነባር ተመራቂ ተማሪዎች፤ ፠ አገልጋይ ክፍል አባላት፤ ፠ ክፍል አገልጋይ አባላት፤ ፠ የተከታታይ ትምህርት (Course) /ለቀዳማይ፣ ካልዓይና ሣልሳይ/ ተማሪዎች፤ ፠ የታዳጊ ክፍል አባላትና ተማሪዎች፤ ፠ የመማክርት ጕባኤ አባላት፤ ፠ የወላጅ ኮሚቴ አመራሮችና የወላጅ ኮሚቴ አባላት፤ ፠ የባለትዳር ጕባኤ አባላት፤ ፠ የጕባኤ (ለረቡዕ የሕወይት ውይይት ጕባኤ፣ ለዐርብ ጕባኤ፣ …… ) ተሳታፊዎች፤ እንዲሁም፡፡ ፠፠፠ በጥቅሉ የሰ/ት/ቤታችን አሻራ በ50 ዓመታት ጕዞ ውስጥ ያረፈባችሁ በሙሉ፡፡ ዛሬ ዐርብ ኅዳር 26/2012 ዓ.ም. ከምሽቱ 12 ሰዐት ላይ እንድንገኝ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

መኳንንት፣ መሳፍንትና ነገሥታት የሰጡትን የገዳሙን ርስት ጉልት ማንም እንዳይነካ፤ **ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይገቡ (የአባቶች መነኰሳትና የባሕታውያን ብቻ መኖሪያ እንዲኾንና እኅቶች እንዳይቀላቀሉ በማሰብ) **መነኰስ ያልኾነ ማንም በሐይቅ ገዳም ቤትን እንዳይሠራ፡፡ ፠ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በሃገራችን አንጋፋና ቀደምት በኾነው ደብረ ዳሞ መካነ አእምሮ (University) የተማሩ እንደመኾናቸው፤ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሲመለሱም በሃገራችን በትምህርት መካነ አእምሮነቱ ዋናና ግንባር ቀደምቱን፤ በርካታ ሊቃውንትን ቅዱሳንን ያፈለቀውን የሐይቅ እስጢፋኖስ መካነ አእምሮ መሠረቱ፤ በዚህም የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን መሥራች ነው፤ ልጆቻቸውም ይህን ወርቃማ ዘመን አስቀጥለውታል፡፡ በቆብ የወለዷቸው ቅዱሳን ሊቃውንት ብዙ ቢኾኑም ለአብነት ያህል ዐበይቶቹ፤ ✤ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል (ምድረ ዐማራን፣ ሸዋንና ደቡብን፤ ምድረ ትግራይን ያስተማሩ፤ የአቡነ ተክለሃይማኖት የመጀመሪያ መምህር የኾኑ) ✤ አቡነ ተክለሃይማኖት (ሐዲስ ሐዋርያ ተብሎ የተሰየመ፤ በሐይቅ ከመመንኰሳቸው በፊት 7 ዓመታት፣ ከመነኰሱ በኋላ 3 ዓመታት ተቀምጠዋል) ✤ አባ ሕዝቅያስ (ከምድረ ወግዳ ይዞ እስከ ጎጃም ያስተማሩ) ✤ አባ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት (በጸበላቸው የእንጨት ቅርፊትን እንደ ደንጊያ መቁጠሪያ የሚያደርጉ፣ በድንጋይ ሠረገላ የሚጓጓዙ) ✤ እጨጌ አባ አሮን ዘደብረ ዳሪት (ከምድረ ዋድላ አንስቶ እስከ ዳውንት፤ ከበጌምድር እስከ ደምቢያ የሰበከ) ✤ አባ ገብረ ናዝራዊ ዘበለሳ (ምድረ ትግሬን ያስተማረ) ✤ አባ ኂሩተ አምላክ ዘዳጋ (እንደ መምህሩ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእስጢፋኖስ ስም በጣና ላይ የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳምን የመሠረተ፤ ምድረ ሳርክን ይዞ እስከ ጋዝጌ፤ መላዋን የአላፋና ጣቁሳ እና የአገው ምድርን ያስተማረ) ✤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ዘደብረ ባሕርይ) (የኢትዮጵያ መብራት)፤ አብዛኛዋን የኢትዮጵያ ምድር ያስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ከ40 በላይ በሚደርሱ ድርሳናቱ ያስጌጠ፡፡ ✤ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፡፡ ✤✤ እንዲሁም ንጉሡ ይኵኖ አምላክ (ከንግሥናው በፊት በልጅነቱ ያደገውና የተማረው ከጻድቁ ዘንድ ነው፡፡) ፠ ጻድቁ በአጠቃላይ 44 ዓመታትን ማለትም፤ * 20 ዓመት በይትባረክ ዘመነ መንግሥት * 15 ዓመት በይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት * 9 ዓመት በአግብዓ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የኖሩ ሲኾን፤ ለ44 ዓመታት በገዳም ቆይታቸው ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም፥ ለሰውነታቸውም(ለጎናቸውም) ምኝታን አላስለመዱትም፡፡ ‹‹እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ፤ መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ፡፡›› እንዲል፡፡ ጻድቁ በሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩም የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር፡፡ ** የማረፊያው እለት በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱና ሰዎች ተሰባሰቡ፤ በደብረ ነጐድጓድ ያደገውን ተክለ ኢየሱስን መምህር አድርጎ ሾመላቸው እነርሱንም ባርኳቸው፤ ኅዳር 26 በ1286ዓ.ም. በእለተ እሑድ ጧት ፀሐይ ስትወጣ ዐረፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም እንደሚገባ አድርገው በፍየል ሌጦ አድርገው ገንዘው በክብር ቀበሩት፡፡ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ፠•፠ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#ኅዳር_26_ #አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ፤ #_ከደብረ_ዳሞ_ቀጥሎ_በሃገራችን_ሁለተኛውን_መካነ_አእምሮ(#University)#የመሠረተ፤ #_በሃገራችን_ወርቃማ_ዘመን_ተብሎ_የሚታወቀውን_ዘመን_ፋና_ወግቶ_የጀመረ_ #_መጻሕፍትን በእጁ በመጻፍ ለትውልድ የታሪክ አሻራን ያሳረፈ #_የሐይቅ_እስጢፋኖስ_ገዳምን_ዳግመኛ_ያቀናና_ያስፋፋ፥ #በደብረ ዳሞ አስኬማ ዘመላእክትን የተማረ #እንደ እስጢፋኖስ ጸጋን ጽድቅንና ሞገስን የተመላ፥ በሥራው ፍጹም የኾነ፥ #የመጀመሪያውን_የዐቃቤ_ሰዐት_ማዕርግ_ያገኘ፡፡ #_ለቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል ፥ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ ፥ #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫና_ #ለሌሎችም_በርከካታ_ቅዱሳን_ወላዴ_አእላፍ_ቅዱሳን_የኾነ፡፡ * በበጌምድር ዳኅና(አሁን ስማዳ) ገብርኤል በተባለ ቦታ ከአባታቸው ዘክርስቶስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ነሐሴ 26 ሰኞ ተጸንሰው፤ ግንቦት 26/1205 ዓ.ም. ረቡዕ በቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ተወለዱ፡፡ ወንድሞቻቸው ገብረ ጽዮንና ስቡሕ አምላክ ይባላሉ፡፡ *እስከ 30 ዓመታቸው ድረስ በእናት አባታቸው ቤት እያገለገሉና ትምህርት እየቀሰሙ ቆዩ፤ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾላቸው ወደ 5ኛው የደብረ ዳሞ አበምኔት ዳግማዊ አቡነ ዮሐኒ ዘንድ እንዲሄዱ በራዕይ ነገራቸው፤ በመንገድም ሲሄዱም የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን አግኝተው ይምጻአ ምሕረት የሚባል ዲያቆንን አስከትለው ወደ ደብረ ዳሞ እንዲሄዱ መልአኩ ባዘዛቸው መሠረት ወደ ገዳሙ አቀኑ፡፡ *በደብረ ዳሞ ቆይታቸውም እህልን በመፍጨትና ለገዳሙ ንግድን (ሩቅ መንገድንና አስጨናቂ ኹኔታዎችን በማለፍ ) ይነግዱ ነበር፡፡ እንዲሁም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመጻፍ (በመገልበጥም) ትጉህ ጸሓፊ ናቸው፤ ይህ ይታወቅ ዘንድ በቅርብ የደብረ ዳሞ ዕቃ ቤት እስከተቃጠለበት ድረስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእጃቸው የጻፉት ወንጌል ይገኝ ነበር፡፡ *37ዓመት ሲኾናቸው ከአባ ዮሐኒ ሥርዐተ አስኬማ ዘመላእክትን ከተቀበሉ በኋላ መልአኩ ወደ ሐይቅ እንዲሄዱ በገለጻላቸው መሠረት በ1237 ዓ.ም. ወደ ሐይቅ በመምጣት በሐይቁ ዳር በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ.ክ. ለ6ወራት አገለገሉ፤ በዚሁ ደብር የሚገኘው ‹‹#ሔር_አምላክ_›› የተባለ ካህንም የጻድቁን ታሪካቸውን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ወደ ደሴቱ አስገባቸው፤ የአካባቢው ሕዝብም አገልግሎታቸውንና መንፈሳዊ ተጋድሏቸውን አይተው ንጉሡ ይትባረክ ዘንድ በመሄድ የገዳሙ አበምኔት እንዲያደርገው ጠየቁት እርሱም ሾመው፡፡ ጻድቁም ይህን ገዳም በዮዲት ጉዲት ከጠፋ ከ300 ዓመታት በኋላ ዳግም አቅንቶታል፡፡ *እርሳቸውም ደሴቲቷም ስለወደዷት ከገዳሟ ላለመውጣት፤ የባሕሩን ወደብም ላለመርገጥ ብፅዓት ገብተው 20 ዓመታት ያህል እንደኖሩ፤ አፄ ይኵኖ አምላክ እንደነገሠ ጻድቁ ወደ ንጉሡ እንዲመጡ ላከበቸው፤ እርሳቸው ግን ከሐየቁ እንደማይወጡ ብፅዓት እንዳለባቸው፤ ንጉሡ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ላኩበት፤ ንጉሡም በበቅሎ እስከ ጉልበቱ ድረስ ወደ ባሕሩ ገብቶ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ኂሩተ አምላክና ኀረየነ ክርስቶስ ከሚባሉ ደቀመዛሙርቶቹ ጋር በታንኳ (በጀልባ) መጥተው ተጨዋወቱ፤ ንጉሡም ምን ላደርግልህ ትወዳለህ ሲላቸው፤ * ገዳሟ የወንዶች ገዳም እንድትኾን ነው አሉት፤ ንጉሡም በቦታው ያሉትን ሴቶች ይህ ቦታ የወንዶች ገዳም ብቻ እንዲኾን ስለወሰንኩ የፈቀዳችሁ ከእኔ ጋር በከተማዬ መኖር አሊያ በፈቀዳችሁትና በመረጣችሁት ቦታ መኖር ትችላላችሁ የምትፈልጉትንም ኹሉ እሰጣችኋለሁ በማለት ሥርዐት አበጁለት፡፡ ደሴቲቱን ለቀው እየሄዱ ካሉት ሴቶች መካከልም አንዲቷ ምጧ ደርሶ ነበረና በደሴቱ ጫፍ ወለደች ቦታውም ‹‹#ምጥ_ገበታ_›› ተባለ፡፡ ዛሬ ክብረ በዓል የሚከበረው በዚሁ ምጥ ገበታ በተባለው ቦታ ነው፡፡ (ከምጥ ገበታ በስተምዕራብ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ፤ በስተሰሜን ምዕራብ መካነ አእምሮ (University)፤ በስተሰሜን የሴቶች ገዳም ይገኛል) * በንግግራቸው ሳሉም እባብና አለቅት በንጉሡን በቅሎ እግር ላይ ተጠመጠሙ፤ ጻድቁም መርዛማነት ያላቸው እንስሳት በዚህ ገዳም ሰውን እንዳይጎዱ አወገዟቸው፤ የደወልም ድምፅ ተሰማ ንጉሡም አሁን ስንት ሰዐት ነው የደወል ድምፁስ ምንድን ነው ብሎ ጻድቁን ጠየቀ፤ ጻድቁም ፱ኝ ሰዐት በመኾኑ ደወሉ ከገዳሙ የተደወለ መኾኑን ነገሩት ንጉሡም ለጻድቁ #የዐቃቤ_ሰዐት_ ማዕርግን ሰጣቸው (በአሁኔ ሰዐት ዐቃቤ ሰዐት የጠቅላይ ሚንስትሩ ዋና አማካሪ ከሚለው ጋር የተካከለ ነው)፡፡ (ምንም እንኳን እርሳቸው በሹመቱ ለመጠቀም ባይፈልጉም)፤ ከተከታያቸው ከአባ ዘኢየሱስ አንስቶ እስከ 16ኛው መጀመሪያ አጋማሽ ድረስ በሐይቅ መምህራን እጅ ቆይቷል፤ ኋላ የንጉሦች መናገሻ ከሸዋ ወደ ጎንደር ሲዛወር በቦታ ርቀት ምክንያት ይህ ሹመት በገጽ የሚሰጥ ሹመት ሁኗል፡፡) ✤ንጉሡ ይኵኖ አምላክ ለገዳሟ የሚከተለውን ሥርዐት ሠርተው መደ መናገሻቸው፤ ጻድቁም ወደ ደሴታቸው ተመለሱ፤

#የቤተክርስትያን_ጉዳይ_የእኔም_ጉዳይ_ነው_ #ስለ_ቤተክርስትያን_ዝም_አንልም፡፡ ፠# በልማት_ስም_(ካህናትን ደመወዝ እንጨምርልሃለን፣ ደብሩ በልማት ወደ ኋላ የቀረ ነው፣ …… በሚል) #ቤተ_ክርስቲያ
+1
#የቤተክርስትያን_ጉዳይ_የእኔም_ጉዳይ_ነው_ #ስለ_ቤተክርስትያን_ዝም_አንልም፡፡ ፠# በልማት_ስም_(ካህናትን ደመወዝ እንጨምርልሃለን፣ ደብሩ በልማት ወደ ኋላ የቀረ ነው፣ …… በሚል) #ቤተ_ክርስቲያንን_የንግድ_ማዕከል_የሚያደርጉና_ለማድረግ_የሚነሱ_አስተዳዳሪዎችንና_የአስተዳደር_አካላትን_እንቃወማለን፡፡ ፠ ቤተ ክርስቲያንሰ ትሰመይ ቤተ ጸሎት (ቤተ ክርስቲያን የጸሎት ቤት እንጂ መነገጃ አይደለችም)፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ያላዘዘው፤ በኢትዮጵያ መንግሥትም ቢሆን ቤተ ክርስቲያን የአምልኮ ቦታ እንጂ የንግድ ቦታ አይደለችም፡፡ #በአዲስ_አበባ_ደብረ_ሰላም_ቅዱስ_እስጢፋኖሰ_ቤተ_ክርስትያን_አስተዳዳሪው_እየፈጸሙት_ያለውን_፤ * የሃይማኖት ችግር፤ * ምዝበራ፤ * ዘረኝነት፤ * ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር ችግር፤ በልማት ስም ቅጽሩን መነገጃ ማድረግ (የጠበል ቤቱን አካባቢ ሳይቀር) ፠፠፠ ቤተ ክርስቲያን የምዕመናንንም ጭምር እንጂ የአስተዳዳሪና የካህናት ብቻ አይደለችም ብለው፤ ፠፠፠ ከሃገረ ስብከት እስከ ደብራት የተዘረጋው የሙስና ሰንሰለት ይበጠስ፤ ከ9 ወር በፊት ከደብሩ አስተዳዳሪነት ተነስተው የነበሩ አስተዳዳሪ አሁንም እያስተዳደሩ መሆኑን በመቃወም፤ ፠፠፠ የአጥቢያው ምዕመን ፣ የደብሩ ሰ/ት/ቤትና፣ የአጥቢያው ወጣቶች እንዲሁም የአዲስ አበባ ምዕመናን ይህን እኩይ ተግባር በመቃወም፤ ረቡዕ ኅዳር 24/2012 ዓ.ም. መልስ እንዲሰጣቸው (በፎቶ ላይ በምትመለከቱት መልኩ) ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤትና ለቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዳዩ በአስቸኳይ እንዲፈታለት አቅርቧል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤትና ቅዱስ ፓትርያርኩም ችግሩን እንደሚፈቱ ቃል ገብተውና ተወካዮቹን በመስቀል ባርከው አሰናብተዋል፡፡ ***ቸር ያሰማን፡፡

#ኅዳር_26_ #_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተማርያም፡፡ የአቡነ ሀብተ ማርያም ክብረ በዓል የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ ብሔረ ብፁዓን ደብረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ፡፡ ቡልጋ አቡነ ሀብተ ማርያም፡፡ ** አዲስ አበባ ቃሉ ተራራ አቡነ ሀብተ ማርያም፤ አስኮ (ከዊንጌት አጠገብ) ፠ በሽዋ (የራውዕይ /ቡልጋ/) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክ ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡ ፠ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መናኝ ነበረች፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠ ጻድቁ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ ይህንንም በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል፤ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ መንነዋል፤ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኰሱ በኋላም ብዙ ትርፋትንና ተጋድሎን ሠሩ፡፡ ለአብነትም፤ *ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ፤ *በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ፤ *በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ፤ *ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ነው፤ *በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ፤ *ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ፥ ክቡር ደሙን ይጠጣሉ፤ *በልባቸው ውስጥ በፍጹም ቂምን፥ መከፋትን አላሳደሩም፡፡ * ረአዬ ኅቡዓት በመባል ይታወቃሉ፡፡ * በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርኩት ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ * ‹‹#ጽድቅና_ትሩፋት_እንደ_ሀብተ_ማርያም፠›› ፠ ጌታችን ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔዱ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው፤ * ‹‹ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ፤ ስለ ምናኔህ፣ ስለ ተባረከ ምንኵስናህ፣ ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ፣ ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ፣ ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ፡፡›› * በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን፤ 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ፡፡ በስምህ የሚለምኑ፤ በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ ‹አማንየ በርእስየ› ብዬሃለሁ›› አላቸው፡፡ * ቅዱሳን መላእክትም ‹‹ሀብተ ማርያም ወንድማችን›› ሲሉ አቀፏቸው፡፡ ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው፡፡ ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ በዝማሬም ወሰዷት፡፡ ✤ ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ 1ኛ. #_መብረቅ፣ 2ኛ. #_ቸነፈር፣ 3ኛ. #_ረሃብ፣ 4ኛ. #_ወረርሽኝ፣ 5ኛ. #_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፠ በተሰጣቸው ቃል ኪዳንም ከላይ ያሉትን 5ት መቅሰፍቶች የሚያርቁ በመሆናቸው፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን በደብረ ሊባኖስ ገዳም እነዚህ 5ቱ መቅሰፍቶች እንዳይቀርቡ የሀብተማርያም ካህናት ከኅዳር 1-7(10) ማዕጠንት ያጥናሉ፤ ደብረ ሊባኖስ ገዳምም ለደብረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም 1ድ በሬ ስጦታን ያበረክታሉ፡፡ ፠ በዛሬው ዕለት በኅዳር 26 ባረፈ ጊዜ፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው፤ በዝማሬ ፥ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ፥ ከብርም የጠራ ፥ ከሁሉ የሚበልጥ ፥ የተመረጠ ፥ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) #_በዛሬዋ ዕለት #በናግራን ያሉ ክርስቲያኖች በ6ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት የኾኑበት ዕለትም ነው፡፡ ፠•፠ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ፠•፠ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፬፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋ
+1
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፬፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፶፫ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) ዐርብ ኅዳር ፳፮ ጀምሮ ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡