ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 406 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 570 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 189 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 406 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 76، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.12‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.38‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 871 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 446 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 23.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 406
المشتركون
+724 ساعات
+347 أيام
+7630 أيام
أرشيف المشاركات
20 ቀን ቀረው፤#ፍኖተ_ሕይወት_/#የሕይወት_ጕዞ/፤ #መጋቢት_15/2011ዓ.ም.፡፡ ወደ #ኵሉ_ወይን_ቅድስት_አርሴማ፡፡ **በብዙሃን ዘንድ ዜናው ያልተሰማው፤ 3ት ትላልቅና ሌሎችም ክፍሎች ያሉት፤ ብዙ ንዋያተ ቅድሳት የተገኙበትና በቁፋሮ የተገኘው ጥንታዊ ዋሻ ይጎበኛል፤ **ምክረ አበው በሊቃውንት መምህራን፣ ዝማሬ በዘማርያን ይቀርባል፡፡ **ከሰ/ትቤታችን ምሥረታ ጀምሮ የነበሩና አሁንም ያሉ አባላት በአንድነት የሚሳተፉበት ዐቢይ ጕዞ፡፡ **ለበለጠ መረጃ፤ 0977 30 17 18

ዛሬ የሊቀ መልአኩ ወርኀዊ የበዓል ውሎ በታላቁ ደብራችን ይህንን ይመስላል፡፡

፨፨የፌስቡክ/Facebook/ ((Add Friend)) ገጻችን ስለሞላ፤ የሚከተለውን የ‹‹LIKE›› ገጽ አድራሻችንን <<LIKE>> ያድርጉ ለሌላውም ያስተዋውቁ፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት) ወይም https://www.facebook.com/%E1%8B%A8%E1%89%80%E1%8C%A8%E1%8A%94-%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%88%B0%E1%88%8B%E1%88%9D-%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%8A%80%E1%8A%94%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%E1%8A%93-%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%89%B5%E1%8C%89%E1%88%83%E1%8A%95-%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5-%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%8A%A4%E1%88%8D-%E1%89%A4%E1%89%B0-%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8B%AB%E1%8A%95-%E1%8D%8D%E1%8A%96%E1%89%B0-%E1%88%95%E1%8B%AD%E1%8B%88%E1%89%B5-%E1%88%B0%E1%8A%95%E1%89%A0%E1%89%B5-%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%89%A4%E1%89%B5-1620932764891482/ ፨፨#በቴሌግራምም_ሊያገኙን_ከፈለጉ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት) ወይም https://t.me/medihanaelem

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፰_ #ዲያብሎስ_የሚፈራቸውና_የማይፈራቸው_ሰዎች አባ ጳውሊ፤ በውኑ ከአዳም ልጆች የምትፈራው አለን አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአዳም ልጆች የምፈራቸውም የማልፈራቸውም አሉ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ የምትፈራቸውና የማትፈራቸው እነማን እንደሆኑ ሳትዋሽ እውነቱን ትነግረኝ ዘንድ በአምላኬ ስም አምልሐለሁ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኩህ፡፡ #ስለ_እግዚአብሔር_ፍቅር_ብሎ_ሥጋውን_ለመከራ_የሚሰጠውን_ሰው_እፈራለሁ፡፡ ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብሎ ሥጋውን ለመከራ የማይሰጠውንና ከመከራ የሚሸሽውን አልፈራውም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ዳግመኛ አሁን ከነገርከኝ ሌላ ማንን ትፈራለህ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የቅዱሳንን ዐፅምና ዐፅማቸውን የሚጠብቁ #መላእክትን እፈራለሁ፡፡ ስለ ክርስቶስ ብለው መከራውን በመታገሥ ስለተጋደሉት ተጋድሎ ከእግዚአብሔር ዘንድ ታላቅ ክብር ተዘጋጅቶላቸዋልና፤ ቃል ኪዳንም ተቀብለዋልና፡፡ በቦታቸው እንዳንኖር መላእክት ይከለክሉናል፤ ያባርሩናል፡፡ ኃይላችንም ይደክማል፡፡ #እኛም በዚያ ቦታ የኃጢአት ፍርፋሪ እናገኝ ዘንድ ዘወትር ተግተን እንዋጋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ የተናገርከው እውነት ነው፡፡ በእውነት የቅዱሳንን ምግባርና ትሩፋት ስታዩ በእጅጉ የሚያስፈራችሁና የሚያስደነግጣችሁ አይደለምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ #ፍቅር፥ ቅን ኅሊናና ንጹሕ ልብን፥ ትሕትናን፥ ጾምን፥ ጸሎትን፥ ለመልካም ሥራ መትጋትን ስናይ እንፈራለን፡፡ ይበልጥኑም የድንግል ማርያም ልጅ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸውን #ጸሎት #አቡነ ዘበሰማያትን እንፈራለን አለ፡፡ አባ ጳውሊ፤ የማርያም ልጅ የምትለው ማንን ነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተን የፈጠረ እርሱ ነው አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በእውነት እርሱን ትፈራለህን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ ስሙን እየጠራህ አታቃጥለኝ፡፡ እንዴት አልፈራውም! እነሆ ኃይሌን አድክሟል፤ ብዙ ነፍሳትን አድኗል፤ ከእጄም ማርኳልና አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከነገርከኝ በዚህ ዓለም የምትፈሩት ሌላ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ እነማን ናቸው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የእርሱ ማደሪያ የሆኑና ደስ የሚያሰኙት ቅዱሳን ናቸው፡፡ ዳግመኛም #እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ሁሉ እንፈራለን፡፡ ዳግመኛም በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው የተናገሯትን #ጸሎተ ሃይማኖትን እንፈራለን፡፡ በውሃ ምንጭ፣ በባድማ፣ በመቃብር ቤት፣ በወንዝ ስንዘዋወር ወይም እኛ ባለንበት ቦታ ሁሉ #የጸሎተ ሃይማኖትን ጸሎት ስንሰማ እንደነግጣለን፡፡ ዳግመኛም አንዱ ወንድሙን እኔ በድያለሁና #ይቅር በለኝ የሚለውን የይቅርታ ቃል ስንሰማ ደንግጠን ከአጠገቡ እንርቃለን፡፡ ዳግመኛም ቅዱስ #መስቀልና የክርስቶስ #ሥጋና ደም፥ #ንጹሕ ጸሎት ካለበት ቦታ መቅረብ አይቻለንም እንሸሻለን አለው፡፡ (ማቴ.፮፥፲፬፤ ፲፰፥፴፭) #የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንን ሕዝቡን (በካህናት አንጻር)፤ ነገሥታት፥ መኳንንትና መሳፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፱.… ይቀጥላል ከነገ ወዲያ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፯_ #ለሰው በሚፈልገው ሰይጣናት ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ፤ የሰይጣናት አሳሳች መሆናቸው ለጥቂት ደጋጎች እንጂ (በመጨረሻ በሥራቸው) እንጂ ለሁሉ እንደማይታወቁ፤ በገዳም የሚኖሩትን በምን እንደሚዋጋቸውና እንደሚያሸነፉት፤ ከሰው ልጆች የሚፈራቸውና የማይፈራቸውን/ አባ ጳውሊ፤ ለሰው በምትሐት የምትታዩት በስንት አምሳል ነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ለማሳት እኛ በምንፈልገው መልክ እርያ፥ እባብ፥ ሴት፥ ወንድ፥ ወጣት፥ ሽማግሌ፥ ቀበሮ፥ ጦጣ፥ ዝንጀሮ መስለን መታየት እንችላለን፡፡ ከእኛ እያንዳንዳችን በድንግል ማርያምና በልጇ አምሳል፤ በብርሃን መልአክና በቀደሙ ቅዱሳንና ቀድሞ በሞቱ ሰዎች አምሳልም ቢሆን ሰው በሚፈልገው ሁሉ እንታያለን አለው፡፡ (ሙት ሳቢ የሚባሉትን ልብ ይለዋል)፤ "ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና፡፡ እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜያቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል፡፡" /፪ቆሮ.፲፩፥፲፬/ አባ ጳውሊ፤ እናንተ አሳቾች እንደሆናችሁ ለሰው በምን ትታወቃላችሁ? መጨረሻችሁስ እንዴት ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ ለጥቂት ደጋጎች ነው እንጂ ለሁሉ አንታወቅም፡፡ በመጨረሻ ሥራችን ግን እንታወቃለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ሥራህ ሁሉ ክፉ እንደሆነ ከአንተ ተረዳሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ እንደ አንተ ንጹሕ የሆነ ሁሉ በክፉ ሽታዬ ያውቀኛል፡፡ ኃጥአን ግን በሽታዬ ለይተው ሊያውቁኝ አይችሉም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ #አንተ ከክብርህ የተዋረድክ #እንደ አንተ ንጹሕ የሆነ በማለት በውዳሴ ከንቱና በትምክሕት ወጥመድ ጠልፈህ ልትጥለኝ ትፈልጋለህን? እግዚአብሔር የተመኘኸውን አይስጥህ ያሰብኸውንም አይፈጽምልህ፡፡ እኔስ ኃጢአተኛ ነኝ እንጂ ንጹሕና ጻድቅ አይደለሁም፡፡ ዕለተ ሞቴን አስባለሁ፡፡ በፊቴ የእግዚአብሔር ፍርድ አለ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ! ዳግመኛም ስለምጠይቅህ ነገር ምንም ከእኔ እንዳትሰውረኝ በስሙ አምልሐለሁ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ፡፡ እነሆ ከዚህ በፊት ተሰምቶ በማይታወቅ መከራ ተፈተንኩ፡፡ አንተ ክፉ ሽማግሌ በእኔ ላይ ከወዴት እንደሠለጠንክ አላወቅሁም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ እንዴት አድርገህ ነው በገዳም ከሚኖሩት ጋር የምትዋጋው አለው፡፡ ዲያብሎስም ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ በጠላቶቼ መካከል ሰውን የማጠምድበትን ሥራዬን ትገልጥብኝ ዘንድ ትወዳለህን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ሥራህን ብቻ የምገልጥ አይደለሁም ለሰው ጥቅም የሌለው የጥበብህንም ፍጻሜ ነው እንጅ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አስቀድመን መነኰሳትን የምንዋጋቸው በገዳሙ ቆይታ ላላቸውና በእድሜ በማዕረግ ለሚበልጧቸው ለአበ ማኅበሩ እሺ በጀ ብለው እንዳይታዘዙ፥ ምክራቸውን፣ ተግሣጻቸውን እንዳይቀበሉና እንዳይሰሙ፤ እኔ የምነግራቸውና የማሳስባቸውን ለአበው እንዳይነግሩ በማድረግ ነው፡፡ ዳግመኛም ጥርጣሬንና መሸበርን የልብ ድንጋጤን በላያቸው እናመጣባቸዋለን፡፡ በሐሰተኛ ሕልም እናስታቸዋለን፡፡ በዚህ ባያምኑና ቢያቸንፉን ብዙ የምኞት ፈተናን እናመጣባቸዋለን፡፡ ወርቅና ብር መውደድን የላመ የጣመ መብላት መጠጣትን እናመጣባቸዋለን፡፡ የማይጠቅም ዙረትን እንዲያበዙ እናደርጋቸዋለን፡፡ ሰውን የሚያጣሉና ነገር አመላላሾች እንዲሆኑ የአበውን ምክር እንዳይሰሙ ልቡናቸውን እናደነድነዋለን፡፡ በዚህ አኗኗራቸው በአንድ ቦታ እንዳይጸኑ በየጊዜው ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ እንዲዛወሩና ሥራን እንዳይወዱ ፤ ሌላ የደከመበትን እንዲመገቡ በአፋቸው እኛ ዓለምን ንቀናል እንዲሉ፤ ዓለም ግን ከደስታዋና ከፍላጎቷ ሁሉ ጋር በእነርሱ ላይ በዝታ እንድትታይና መንፈሳዊ ዕውቀትን ትዕግሥትን መረጋጋትን እንዲያጡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ሰይጣን፤ ከገዳማቸው በወጡ ጊዜ በነፍሳቸው ለገዳሙ አባት ሊገዙ ከገቡባት ከገዳማቸው ልቡናቸውን እናርቀዋለን፡፡ እኛ የዚህችን ዓለም ሥራ ስለምናሳምርላቸው በስም መነኮሳት ሲባሉ በገዳም መኖራቸውን ፈጽመው ይጠላሉ፡፡ በዚህ ፈትነናቸው ካቸነፉን ሌላ የሚፈተኑበት ምክንያት እናመጣባቸዋለን፡፡ ሌላው በሚሠራው ሥራ በመቅናትና በቂም አንዱ ለአንዱም መልካም ሥራ እንዳይሠራ እንቅፋት እንዲሆነው በማድረግ እንዋጋቸዋለን፡፡ በገዳሙ ውስጥ በሚሰሩት ሥራ ውዳሴ ከንቱን አብዝተው እንዲፈልጉና ራሳቸውን ከወንድሞቻቸው ከፍ እንዲያደርጉ፣ ከራሳቸው ሥራ በቀር የሌላውን እንዲነቅፉ እንዋጋቸዋለን፡፡ ኃላፊውን ዓለም መመኘትንና ሥጋዊ ትምክሕትን ዘወትር በልቡናቸው እናሳድርባቸዋለን፡፡ በዚህ ሁሉ የኃጢአት ወጥመድ ካቸነፉንም ተስፋ እንዲቆርጡ ክፉ ሐሳብን በእነርሱ ላይ ለማምጣት ዘወትር እንበረታለን፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር ዳግመኛ በላያቸው ላይ ጊንጡን እባቡን ቅማሉንና ቁንጫውን ትኋኑን የሚያሰቃዩአቸውን ሁሉ አራዊት እናስነሣባቸዋለን፡፡ ከምግባቸው ዘመሚቱን ትሉን ክፉውን ነገር ሁሉ እናስገባባቸዋለን፡፡ የእጅ ሥራ አዝመራቸውንና እንስሶቻቸውን በአራዊትና በአይጥ በአዕዋፍ በበሽታ በተቻለን ሁሉ እናጠፋባቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በዚህ በምትዋጋቸው መከራ ምን ትጠቀማለህ? እነርሱስ በምን ያቸንፉሃል አለው፡፡ ዲያብሎስም ፈጣሪያቸውን እንዳያመሰግኑ ተስፋ እንዲቆርጡና የዘለዓለም ሕይወትንም እንድናሳጣቸው ነው እንጂ የምንጠቀመው ጥቅም የለንም፡፡ ዲያብሎስ፤ በምን ያቸንፉሃል ስለምትለኝም ፤ በፍቅር፥ በመታዘዝና በትዕግሥት፤ በጾምና በጸሎት፤ ከቂም በቀል ንጹሕ በሆነ ልቡና፤ ባለመለያየት ወንድሞቻቸውን ፈጽሞ በመውደድ፤ ከዚህ ሁሉ ጋር ትሕትና ከመንፈሳዊ ሥራቸው ሁሉ ትበልጣለችና በፍጹም ሃይማኖት ትሕትናን ቢይዙ ያቸንፉናል፡፡ በመጨረሻም የክርስቶስን ሥጋና ደም በመቀበላቸው ያርቁናል ፤ ያቸንፉናል፡፡ #የክርስቶስ ሥጋና ደም የእኛን መርዝ ያጠፋል፡፡ እሾሃችንንም ይነቅላል ፤ ያቃጥላልና አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ የተነሳ ለሰው ወዮለት አለ፡፡ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጀመሪያ በራችሁን ይዝጋ ፤ ወጥመዳችሁን ያጥፋ ኃይላችሁም ያድክም አለው፡፡ ያን ጊዜ የተረገመ ዲያብሎስ አንተ ክፉ ሽማግሌ ከእንግዲህ ወዲህ ምንም ነገር አልነግርህም፡፡ ከአሁን በኋላ ከአንተ ዘንድ ወጥቼ እሄዳለሁ ብሎ ጮኸ፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከዚህ የሚበዛ ብዙ የምጠይቅህ አለኝና አንተ ርኩስ የክፉ ሥራ ምሥጢርህን ጨርሰህ ሳትነግረኝ ከእኔ ትሔድ ዘንድ ሥልጣን የለህም፡፡ #ዲያብሎስ የሚፈራቸውና የማይፈራቸው ሰዎች፤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፰.… ይቀጥላል ከነገ ወዲያ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

#አዋጅ_አዋጅ፤ #የምሥራች_የምሥራች፡፡ በ1 ወር ውስጥ 3 ዓይነ ሥውራን ዓይናቸው በርቷል (1ዱ ከጅማ አካባቢ የመጣ ነው)፤ መንቀሳቀስ የማይችል 1ድ ሰው ከበሽታው ተፈውሷል፡፡ ሲቈፈር መስቀል ተገኝቷል፡ በታላቁ ደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ስር የነበሩት 4ት ጠበሎችን ወደ 8 ከፍ የሚያደርጉ ተጨመሪ #4ት_ጠበሎች_ፈለቁ፡፡ ከቀጨኔ ወደ 19 ቀበሌ መሻገርያ ድልድዩ አጠገብ በታች በኩል ቀድሞም እንደ ጠበል የሚያገለግል ምንጭ ነበር፡፡ ታኅሣሥ 13/2011ዓ.ም. ግን በሦስት አቅጣጫ በብዛት መመንጨት ጀምሯል፤ አንዲት ዓይነ ሰሥውር እኅትንም ፈውሷል፡፡ (እንዚህ የኪዳነ ምሕረት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጠበሎች ናቸው፡፡) ከ1 ሳምንት በፊት የካቲት 3 ዕለት ደግሞ የእመቤታችን ማርያም ጠበል አዲስ ፈልቋል፡፡ **ቅዳሜ የካቲት 16/2011ዓ.ም. ይባረካል፡፡ (ቦታው ከሽሮ ሜዳ የቋስቋም ታቦት ማደሪያ ወደ ቀጨኔ መሻገሪያ 19 ድልድይ ጋር፡፡ ወይም ከቀጨኔ ከመስ (አዲስ ብርሐን ት/ቤት) ወደ 19 ቀበሌ መሻገሪያ ድልድይ ጋር) (ለማስታወስ ያክል፤ በደብራችን ሥር የሚገኙ የቀደሙት ጥንታውያን ጠበሎች፤ *የቅዱስ እግዚአብሔር አብ ጠበል(ከግቢ ውጭ) *የዮርዳኖስ ጠበል(ከግቢ ውጭ) *የቅዱስ ገብርኤል ጠበል (ከግቢ ውጭ) *የመድኀኔ ዓለም ጠበል (ግቢ ውስጥ)

በፎቶ ላይ ያሉት ቤተክርስቲያን፤ 1ኛ) #አዲስ አበባ እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም፡፡ ይህች ገዳም ታሪኳ ከታላቁ ገዳማችን ዋልድባ (ገዳመ ዋሊ) ለ2ኛ ጊዜ መሥፋፋት (መመሥረት ጋር) የተያያዘ ታሪክ ያላት ናት፡፡ ይኸውም የሸዋ አባቶች ወደ ዋልድባ በ485 ዓ.ም. በንጉሥ አልአሜዳ ዘመነ መንግሥት ባቀኑ ጊዜ የተሰባሰቡባት ቦታ ናት፡፡ እነዚህም አበው ከመኖሪያ ቀዬቸው (ቡልጋ/ምንጃር/) ሁለት ታቦታትን (ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ዘምሕረት አምባ፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ዘአብየ ገዳምን) ይዘው ነበር፤ በዚህች በተቀደች ቦታ ይዘዋት በመጡት ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ገዳመ ሐመረ ኖኅን መሥረተዋል፡፡ የመድኀኔዓለም ታቦትን ደግሞ በታላቁ ገዳም በዋልድባ አኑረዋል፡፡ ይህች ሐመረ ኖኅ፤ - በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተስፋፍታ ተቋቋመች፡፡ - በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተ ጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡ - በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ - አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ - አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ - በንግሥት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡ ይህች ቦታ ከታላቁ ገዳም ከዋልድባ ጋር አሁንም ግንኙነቷ እንደጠነከረ ነው፤ ከዋልድባ ያሉ አባቶች በተለያየ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ በዋነኛነት የሚያርፉባት ጥንተ ርስታቸውም ናት፡፡ ይህች ቦታ በርካት ቅዱሳን በኪደተ እግር የረገጧት እንደመኾኗ፤ ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ፤ የብዙ መነኮሳት መጠጊያ፤ የህሙማን መፈወሻ፤ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎችም አንዷ ናት፡፡ 2ኛ) #ደብረ_መድኀኒት_ዐቢየ_እግዚእ_ኪዳነ ምሕረት፤ . በሃገራችን ኢትዮጵያ የመጻሕፍተ ብሉያት አንድምታ ትርጓሜ ዋና ማስመስከሪያ መካነ አእምሮ (University) የኾነች፤ . ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዐቢየ እግዚእ በኪደተ እግር የረገጧት፤ . በአቋቋም በኩልም የላይ ቤት አብነት የኾነች፤ . የታላላቅ ሊቃውንት መፍለቂያና ታላላቅ ሊቃውንት ወንበር አርግተው፥ ጕባኤ አስፋፍተው ያስተማሩባትና በማስተማር ላይ ያሉባት ቦታ ናት፡፡ የምትገኘውም ጎንደር ከተማ ነው፡፡ 3ኛ) ኢየሩሳሌም ደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት፡፡ ሕንፃ ግንባታዋ፤ በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ተጀምራ በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የተጠናቀቀች፡፡ 4ኛ) አዲስ አበባ #ስዕል_ቤት_ኪዳነ_ምሕረት፤ በታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም ግቢ ውስጥ የምትገኝ፡፡ በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የተሠራች፡፡ 5ኛ) #ራማ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡

#ፍኖተ_ሕይወት_/#የሕይወት_ጕዞ/፤ 30 ቀን (1 ወር ቀረው)፤ #መጋቢት_15/2011ዓ.ም.፡፡ ወደ #ኵሉ_ወይን_ቅድስት_አርሴማ፡፡ **በብዙሃን ዘንድ ዜናው ያልተሰማው፤ 3ት ትላልቅና ሌሎችም ክፍሎች ያሉት፤ ብዙ ንዋያተ ቅድሳት የተገኙበትና በቁፋሮ የተገኘው ጥንታዊ ዋሻ ይጎበኛል፤ **ምክረ አበው በሊቃውንት መምህራን፣ ዝማሬ በዘማርያን ይቀርባል፡፡ **ከሰ/ትቤታችን ምሥረታ ጀምሮ የነበሩና አሁንም ያሉ አባላት በአንድነት የሚሳተፉበት ዐቢይ ጕዞ፡፡ **ለበለጠ መረጃ፤ 0977 30 17 18

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፮_ (#የሰይጣን_ኀይል_በምን_እንደሚደክም፤ #ሰው_በሰራው_ኀጢአት_ተጠያቂው_ራሱ_እንጂ_ሰይጣን_እንዳልሆነ፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_ፈጣሪያቸውን_እንዴት_ባለ_መንገድ_እንደሚያስክዳቸው፤ #አንድን_ኀጢአት_ያለፈን_ሰው_በሌላ_ኀጢአት_እንደሚፈትኑት፤ አባ ጳውሊ፤ ኃይላችሁ በምን ይደክማል? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ከፍቅር፥ ከትዕግሥት፥ ከጾም፥ ከጸሎት፥ ከመታዘዝ፥ ከትጋሃ ሌሊትና ከመሳሰሉት ትሩፋቶች ሁሉ ጋር ኃይላችን የሚደክመው #በትሕትና ነው አለው፡፡ እኛ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ጭንቅ የሆነ መከራ ከማምጣት ቸል አንልም አንቦዝንም፡፡ በሚቻለን ሁሉ እንፈትናቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ እንደምትለኝ ከሆነስ ሰዎች ምንም ኃጢአት የለባቸውም፡፡ ኃጢአትስ የሚሆንባችሁ የክፋትንና የርኵሰትን ሥራ በምታሠሯቸው በአንተና በወገኖችህ ላይ ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እኔ የንግድ ቤቱ ነኝ፡፡ በእኔ ዘንድም ብዙ የሚሸጡ የኃጢአት ዕቃዎች አሉኝ፡፡ የንግድ ቤቱንም በር እከፍታለሁ፡፡ ሁሉም እንደየፍላጎቱ የሚሻውን ይገዛል፡፡ ስለዚህ #ሰው ሁሉ በራሱ ፍላጎት የሚበድል ከሆነ እርሱ በሠራው ኃጢአት እኔ ስለ እርሱ አልጠየቅም፤ ኃጢአትም የለብኝም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምህ! የንግድ ቤትህ እንዳይከፈት እግዚአብሔር ይቅር አይበልህ፡፡ ፈጽመህም መሸጥ እንዳትችል የንግድ ቤትህ ይዘጋ፤ ይፍረስ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተ ክፉ ሽማግሌ ያለ በደሌ ስንት ጊዜ ትረግመኛለህ፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ከአንተ ጋር በመሆኔ ሃይሌን አደከምከኝ፤ ሰውነቴንም አሠቃየሃት፡፡ ስለዚህ እሄድ ዘንድ ተወኝ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ፈጣሪያቸውን እንዲክዱ የምታደርገው በምን መንገድ እንደሆነ እስኪ ዳግመኛ ንገረኝ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በዚህ ዓለም የማደርገውን ሁሉ ነገርሁህ፡፡ #መጀመሪያ ልጆች የወላጆቻቸውንና የአሳዳጊዎቻቸውን ምክር እንዳይሰሙ፣ ለቃላቸውም እንዳይታዘዙና ከእናንተ ይልቅ በእውቀት እኛ እንበልጣለን፣ እኛ እናውቃለን እንዲሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ##ዳግመኛም ወላጆቻቸውንና በዕድሜ የሚበልጧቸውን እንዲሳደቡ እናደርጋቸዋለን፡፡ /፪ጢሞ.፫:፪/፡፡ በዚህ ምክንያት የቤተሰብ ፍቅር እናሳጣቸዋለን፡፡ በሄዱበት ሁሉ እየተረገሙ ይኖራሉ፡፡ ###ከዚህ በኋላ በዝሙት፥ በክህደት፥ የምንዝር ጌጥን በመውደድ፥ በስካር፥ በስርቆት፥ ነፍስን በመግደል እንዲወድቁ እናደርጋቸዋለን፡፡ በመጨረሻም ተስፋ ቆርጠውና አእምሮ አጥተው ቊጥር የሌለው ኃጢአትን እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በዕድሜ ያረጀ ዘመኑም የተቃረበና ሥጋውም የደከመ ሽማግሌ ኃይሉ ይደክማልና በምን ትፈትኑታላችሁ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እኛ በሽማግሌዎች ብዙ ምክንያት እናገኛለን፡፡ ስንፍና እናመጣባቸዋለን፤ ጾምንና ጸሎትን እንከለክላቸዋለን፡፡ ዘመናቸውን እስኪረግሙና ራሳቸውን እስኪያጠፉ ድረስ የሚያደርስ ጭንቀትና ጥርጣሬን እናመጣባቸዋለን፡፡ ክፉ ሐሳብንና ገንዘብ መውደድንም እናመጣባቸዋለን፡፡ ተስፋ መቁረጥን ሰላም ማጣትን በውስጣቸው እናደርጋለን፡፡ ከልባቸው የኅሊና ጸሎትን፥ ከአንደበታቸው ምስጋናን እናጠፋባቸዋለን፡፡ ለልጆቻቸው፥ ለዘመዶቻቸው፥ ለሚረዷቸው፥ ለሚቀርቧቸው ሁሉ ሁከተኞች እንዲሆኑ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ዳግመኛ እንዲህ ብሎ ጠየቀው፤ አንተ የተረገምክ ከእናንተ እያንዳንዳችሁ ሰው ሁሉ በፍትወት ተማርኮ ኃጢአትን እንዲሠራ ለማድረግ ሁላችሁም የተሰለፋችሁ አይደለምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ ሁላችንም #ሰውን በኃጢአት ምኞት ተማርኮ እንዲወድቅ ለማድረግ የተሰለፍን ነን፡፡ ብዙዎችንም እናስታቸዋለን፤ በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዳግመኛም #ከአጠመድነው ወጥመዳችን አምልጦ የወጣውን ሰው በሌላ በታላቅ የኃጢአት ወጥመድ እንዲወድቅ አጥብቀን እንዋጋዋለን አለው፡፡ #ለሰው በሚፈልገው ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ፤ የሰይጣናት አሳሳች መሆናቸው ለጥቂት ደጋጎች እንጂ (በመጨረሻ በሥራቸው) እንጂ ለሁሉ እንደማይታወቁ፤ በገዳም የሚኖሩትን በምን እንደሚዋጋቸውና እንደሚያሸነፉት፤ ከሰው ልጆች የሚፈራቸውና የማይፈራቸውን .… ክፍል ፯.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

እንኳን ለእመቤታችን ኪዳነ ምሕረት ዓመታዊ ክብረ በዓል (ቃል ኪዳን ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤ ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ፡፡ (ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲዖልን ካየች በኋላ ስለኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች የካቲት አሥራ ስድስት ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡ ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም የሚያጠጡ(በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ) ፣ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘየካቲት_16፤ #በዓለ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡ በሃገራችን በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመው፤ የ3ት ዐበይት አድባራት አብነት ነው፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ) የላይ ቤት፤ የደብረ መድኀኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት 2ኛ) የታች ቤት አብነት፤ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ 3ኛ) የደፈጫ ኪዳነ ምሕረት አብነት ናቸው፡፡ እኛም ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ የዐቢየ እግዚእንና የበዓታን ይትበሃል አንድ ላይ በቅደም ተከተል አድረገን አዘጋጅተንላችኋል፤ የደፈጫ ከላይ ከተጠቀሱት ከ2ቱ በጥቂት ቀለም ብቻ የሚለይ በመኾኑ አላካተትነውም፡፡ ስለዚህ እንደ የደብራችሁ ይተበሃል የላይ ቤት ከኾነ ‹‹ዘዐቢየ እግዚእ›› የሚለውን፤ የታች ቤት ከኾነ ‹‹ዘበዓታ) የሚለውን እንድትጠቀሙ እናሳስባልን፡፡ መልካም ማኅሌት፡፡