የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 357
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-97 أيام
+730 أيام
أرشيف المشاركات
+5
ባለስልጣኑ ለሰራተኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
(ታህሳስ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የባህሪ ግንባታና ትግበራ ክህሎትን አስመልክቶ 400 ለሚሆኑ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ከአመራር አካዳሚ ጋር በመሆን ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ባለስልጣኑ ባደረገው ሪፎርም ሂደቱን ጠብቆ ባደረገው የሰራተኞች ምደባ መሰረት ወደ ስራ ስንገባ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ወደስራ መግባት ስላለብንና ተቋማችንን የተሻለ ለማድረግ የተዘጋጀ ስልጠና በመሆኑ ስልጠናው ከራስ እውቀት ጋር ማዛመድ ያስፈልጋል፡፡በመሆኑም ስልጠናውን በጥብቅ ዲስፕሊን መከታተል ከሰራተኛው የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ ኢባ የአመራር አካዳሚ ም/ፕሬዝዳንትና የአመራር ልማት ዘርፍ ዋና ሃላፊ በመርሃ-ግብሩ እንደገለጹት ሀገር በተቋም ግንባታ ትገነባለች፡፡በመሆኑም መዋቅርን ከስትራቴጂ ጋር ማናበብና የሰው ሃይልን መመደብ ያስፈልጋል፡፡በመሆኑም በስልጠናው የሰልጣኞች እውቀት፣ ክህሎትና ባህሪን በማሳደግ በትክክል ራሳችንን ማወቅና ለተቋማችን የምንጠቅም መሆን አለብን፤ራሳችንንም ማሰተካከል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
እየተሰጠ ያለው ስልጠና ለቀጣይ ስድስት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
+3
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል አባላት በ2018 ቴ/ሙያ እውቅና ፍቃድ እድሳት የውጤት ትንተና እና በቴ/ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ላይ በተሰራ የጥናትና ምርምር ስራ ላይ ተወያዩ፡፡
(ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠቅላላ ካውንስል አባላት በ2018 ቴ/ሙያ እውቅና ፍቃድ እድሳት የውጤት ትንተና እና በቴ/ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ላይ በተሰራ የጥናትና ምርምር ስራ ላይ ተወያዩ፡፡
አቶ ቢንያም ፍቃዱ የባለስልጣኑ የቴ/ሙያ እውቅና ፍቃድ ቡድን መሪ የ2018 የእውቅና ፍቃድ እና እድሳት የተሰራላቸውን ኮሌጆች የውጤት ትንተና አቅርበዋል፡፡
እንዲሁም የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን መሪ አቶ በቃሉ ያየህ በትምህርት ምዘናና ምርምር ቡድን /በውስጥ አቅም የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አስመልክቶ የተሰራ ጥናት አቅርበዋል፡፡
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል ለውይይት በቀረቡት ስራዎች ላይ በመወያየት ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይ ለባለድርሻ አካላት የሚቀርብ ይሆናል፡፡
+4
ኢንስፔክሽን ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች የሚቀርብበትን ሁኔታ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው ተገለጸ፡፡
(ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራኒዮ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የቅድመ አንደኛ፣መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
አቶ አንዋር አብዲ የባለስልጣኑ የኮልፌ ቀራኒዮ ቅ/ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት ስርዓተ ትምህርቱን ተከትለው ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር የሚሰሩ ት/ቤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ገልጸው የአሰራር ጥሰት የታየባቸው ተቋማት ማስተካከያ በማያደርጉ የትምህርት ተቋማት ላይ በመመሪያው መሰረት የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስበዋል፡፡ እንዲሁም የትምህርት ተቋማት በተሰጣቸው ፈቃድ መሰረት የመማር ማስተማር ስራውን ማካሄድ እንደሚገባቸውም ተናግረዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀፍቱ ገ/ሚካኤል የ2018 ዓ.ም የቅድመ አንደኛ፣ መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ሪፖርት ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ከእቅድ አንጻር 100% መሳካቱን ገልጸው በ2018 ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተሰራላቸው ከቅድመ አንደኛ ደረጃ 155 ተቋማት፣አንደኛ እና መካከለኛ 87 በድምሩ 242 የትምህርት ተቋማት እንደተሰራላቸውና የትምህርት ቤት ማህበረሰብ በስርዓተ ትምህርት አተገባበር ዙሪያ በቂ ግንዛቤ መስጠት እንደሚገባም አቶ ሀፍቱ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ለተነሱ ሃሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች ከመድረኩ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
+4
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
(ታህሳስ 6 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ወንድሙ የአንድ ግለሰብ ታሪክ አካፈለው ከታሪኩ በመነሳት በህይወታችን ዉስጥ ለሚፈጠሩ ችግሮች ከስሜታዊነት በራቀ እንዲሁም ከብዙ አቅጣጫ መመልከት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ህይወት ትርጉም የሚኖረው ተረጋግተን ስናይ ብቻ ትክክለኛ ትርጉሙን መረዳት እንችላለን ብለዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ተቋሙ ሪፎርም ላይ መሆኑ እንደሚታወቅ ገልጸው ስራዎች የአሰራር ስርዓትን በተከተለ መልኩ በህግና መመሪያ መሰረት እየተሰሩ እንዳለ አስረድተው በሰራተኛው ላይ የሚፈጠሩ ስሜቶችን ሰራተኛው በተረጋጋ እና በጥሞና መገንዘብ ያለበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
+8
"ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ"
(ታህሳስ 2 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች "ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በዓለም ለ34ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ፆታዊ ጥቃት (ነጭ ሪቫን) ቀን በፓናል ውይይት አከበሩ፡፡
አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት በአሉን ስናከብር ሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ማህበራዊ፣ አካላዊ፣ስነ-ልቦናዊ ጥቃቶች ሊቆሙ ይገባል፤ይህን ጥቃት ለማስቆም ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማድረግ አለብን፡፡ ከዚህም ሌላ የሴቶችን ተጠቃሚነታቸውንና ተሳትፎአቸውን በሁሉም ዘርፍ ጎን ለጎን እኩል ማስኬድ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
ወ/ሮ ራሄል ሙሉጌታ ከአዲስ አበባ ሴቶች፣ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህጻናት መብት ድጋፍና ክብካቤ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ የመወያያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በዚህም ለትውልድ ግንባታ ሁላችንም ሚናችንን መወጣት እንዳለብን፣በሌሎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የኔም ጥቃትና ጉዳት ነው ብለን ጥቃትን መቃወም አለብን ብለዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተነሱ የተለያዩ ሀሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
አቶ መስፍን አበረ የቅ/ጽ/ቤቱ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ቅድመ አንደኛ ደረጃ 47 አንደኛና መካከለኛ ደረጃ 35 በድምሩ 82 ማለትም የእቅዳቸውን 100% የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተሰራቸው መሆኑን እንዲሁም መሻሻል የታየ መሆኑን ገልጸው የቁጥጥሩ አሰራርና አስፈላጊነት፣የትኩረት ነጥቦች፣ከቁጥጥሩ የሚጠበቁ ዉጤቶች፣ቁጥጥር የተደረገባቸው ተቋማት መረጃ ፣ የት/ት ተቋማት የስረዓተ-ትምህርት ጥሰቶች የትንተና ሪፖርት፣በቁጥጥሩ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች እና የተሰጡ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች በሰነዳቸው በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
አቶ ክፍሌ ዓለሙ የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እንደገለጽት ከቀረቡት ዝርዝር ትንተና ሰነዶች ያሉብንን ክፈተቶች በመለየት እንዲሁም የእቅዳችን አካል በማድርግ እና ለሚያጋጥሙ ችግሮች የመፍትሄ አካል በመሆን የተቋማቶችን ክፈተት መሙላት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አቶ ሲሳይ ተሰማ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የምንሰራው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ ነው ይህ ስራ ደግሞ ለነገ የሚተው አይደለም ዛሬ ከዛሬም አሁን ልንሰራው የሚገባ ስራ እንደመሆኑ ያሉትን ችግሮች እና ክፍተቶች ለማስተካከል ቁርጠኛ መሆን ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ተቋማቶች ሁሌም ተወዳዳሪ መሆን እንዳለባቸው ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም በመድረኩ ላይ ለተነሱ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
+4
የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት ዓመት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡
(ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ የግል ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ሰነድ ለባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡
የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ ዓለሙ እንደገለጽት ከእቅድ አንጻር ጥሩ ዉጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ ገልጸው ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተቋማትን ጥራት ለማረጋገጥ እና ጥሰቶችን ለማረም አስፈላጊ በመሆኑ በጥብቅ ክትትል እና ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም የአሰራር ጥሰት የታየባቸው እና ማስተካከያ በማያደርጉ ተቋማት ላይ በመመሪያው መሰረት እርምጃ እንደሚወስድም ጨምረው ተናግረዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የስነ-ምግባር እና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዋሲሁን ባይሳ በስነ-ምግባር እና በሙስና እንዲሁም በብልሹ አሰራር ላይ ግንዛቤ ፈጥረዋል፡፡
በመጨረሻም በመድረኩ ላይ ለተነሱ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ ዓለሙ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ አቶ ወንደሰን ጣፎ ምላሽ ሰጥተውበታል፡፡
+6
ቅ/ጽ/ቤቱ የአጫጭር የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የድንገተኛ ክትትልና ቁጥጥር ኢንስፔክሽን ውጤት ትንትና ግኝት ዙሪያ ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡
(ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት በአጫጭር የቴ/ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በተካሄደው ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
የ2018 ዓ.ም የአጫጭር ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ሰነድ ያቀረቡት የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ አቶ ወንደሰን ጣፎ የድንገተኛ ኢንፔክሽን ዓላማ ፣የትንተናውን አስፈላጊነት፣ያጋጠሙ ችግሮች እና የትኩረት ነጥቦችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡በተጨማሪም በሪፖርቱ እንደተገለጸው በድንገተኛ ኢንስፔክሽን ምዘና በቂርቆስ፣አራዳ እና ጉለሌ ክ/ከተማ አጠቃላይ 59 አጫጭር ማሰልጠኛ ተቋማት መታየታቸውን ገልጸዋል፡፡
+4
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
(ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
አቶ ዳባ ጉተታ የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን ባለሙያ "የችሎታ ዘርፎች" በሚል ርዕስ ላይ ያስተማሩ ሲሆን በተለይም ልዩ ችሎታ ያላቸውን ኢትዮጲያዊያን በተለይም በቋንቋ (ስነ-ልሳን)፣በሙዚቃ፣የስዕል እና ዕይታ ችሎታ፣የፈጠራ ስራዎችና አካላዊ እንቅስቃሴ፣በሂሳብና በሳይንስና ዘርፎች ላይ ኢትዮያዊያን ለአለም ያበረከቷቸውን አስተዋፅኦ በማንሳት አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ወደራሳችን መመልከት ተገቢ መሆኑን እንዲሁም ለሀገር በቀል እውቀት እውቅና መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
አቶ ከፈለኝ ከበደ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራት ማረጋጥ ቡድን መሪ እንዲሁም አቶ ጥላሁን ከበደ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ የትንተና ሰነዱን በተናጠል በየራሳቸው በ2ቱም መድረኮች ያቀረቡ ሲሆን የድንገተኛ ኢንስፔክሽን እቅድ አፈፃፀም፣ በት/ት እና ስልጠና ተቋማት የስርዓተ ትምህርት ይዘትና ትግበራ፣ አጠቃላይ በጥንካሬ የታዩ እና በዋናነት መሻሻል ያለባቸውና በጥሰት ወይንም በክፍተት የተለዩት ጉዳዮች በሚሉ ይዘቶች ላይ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በበጀት አመቱ 2018ዓ.ም በቅድመ አንደኛ ደረጃ 103 ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ 55 በድምሩ 158 ት/ቤቶች እንዲሁም 62 የቴክ/ሙያ ስልጠና ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተሰራላቸው መሆኑን ገልጸው ከእቅድ አንጻር ሲታይ ከእቅዱ በላይ ያሳኩ መሆኑንም ገልጸዋል::በተለይም በጥሰት ወይንም በክፍተት የተለዩት ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ነጥቦችን በማስቀመጥ ሰነዶችን አቅርበዋል፡፡
አቶ መስፍን ተ/ማሪያም የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ባስተላለፉት መልዕክት እየሰራን ያለነው ማህበረሰባችን አግባብነት ያለውና ጥራቱ የተጠበቀ የትምህርትና ስልጠና አገልግሎት በየደረጃውና በየእርከኑ በአግባቡ እያገኘ መሆኑን የማረጋጥ ስራ ላይ ነው፤ በመሆኑም ያለንበትን ሀላፊነትና ተግባር በአግባቡ ተረድተን የሀገራችንን አደራ በመወጣት እና መልካም ትውልድን በመገንባት ላይ ትኩረት ሊኖረን ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በጋራና ስንሰራ ለውጥ እናመጣለን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በተጨማሪም በበጀት አመቱ በተሰራላቸው ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተለያየ ጥሰቶች ተገኝቶባቸው የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ት/ቤቶች ብዛት 88 (55.6%) እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ብዛት 61 (98.4%) መሆኑን ገልጸው ከ2017ዓ.ም ጋር በንጽጽር ሲታይ በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ በመጨረሻም በመድረኩ ከነበሩት ተሳታፊ ት/ቤቶችና የማሰልጠኛ ተቋማት ባለቤቶችና አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው በዳይሬክቶሬቱ አመራሮች ምላሽ እና ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫዎችና እርምጃዎች በተመለከተ አቶ መስፍን ተ/ማሪያም የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በዝርዝር ነጥቦችን በማስቀመጥ እና ማጠቃለያ በመስጠት የውይይት መድረኮች ተጠናቀዋል፡፡
ምንጭ፡-የአቃቂ ቃሊቲ ቅ/ጽ/ቤት
+5
ቅ/ጽ/ቤቱ በ2018ዓ.ም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት እና የቴ/ሙያ ስልጠና ተቋማት ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አከናወነ፡፡
የምንሰራው ማህበረሰባችን አግባብነት ያለውና ጥራቱ የተጠበቀ የትምህርት ስልጠና አገልግሎት በየእርከኑ እያገኘ መሆኑን ለማረጋገጥ ስለሆነ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትጋትና በመቀናጀት ልንሰራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
(ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት የ2018 ዓ.ም የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ የግል ት/ቤቶች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማትን የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና በ2 የተለያዩ መድረኮች ለባለድርሻ አካላት አቀረበ::
+2
ባለስልጣኑ ከፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ በመጡ አባላት ክትትል ተደረገለት፡፡
(ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ በመጡ አባላት ክትትል ተደረገለት፡፡
በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ አዲስ ቴሌቭዥን አገልጋዩ በሚል ፕሮግራም ለቀረቡ ጥያቄዎች ለተሰጡት ምላሾች ስራው ምን ላይ እንደደረሰ ከፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ በመጡ የቡድን አባላት ክትትል የተደረገ ሲሆን የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ለተነሱት ጥያቄዎች ተለይተው ተይዘው የተፈቱና በመፈታት ላይ መሆኑን በዝርዝር አብራርተዋል፡፡
ከዚህም ሌላ የባለስልጣኑ አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ዳይሬክተሮች ለተነሱት ጥያቄዎች ማብራሪያ በመስጠት ሰነዶችንና መረጃዎችን አሳይተዋል፡፡
+4
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አለም አቀፍ የጸረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡
(ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ንፍስ ስልክ ላፍቶ ቅ/ጽ/ቤት”ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀንን የቅ/ጽቤቱ ሰራተኞችና አመራሮች እንዲሁም የዘጠኙ ቅ/ጽ/ቤት የስነምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክተሮች በተገኙበት ተከበረ፡፡
የባለስልጣኑ የስነምግባር እና ጸረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ አበበ ወንድሙ የስነ ምግባር እና የሙስና ምንነት እና የጸረ ሙስና ትግል ሁኔታ እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ሚናና አቅጣጫዎች እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ የሚያስረዳ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል፡፡
መልካም ስነምግባርን በመገንባት ሙስናን የማይሸከም ትውልድ መፈጠር እንዲሁም ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር በመዘርጋት ግልጽነት ፈትሀዊነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት አገልግሎት በተቋማችን በመዘርጋት የሀገር ጠላት የሆነውን ሙስናን በመዋጋት ሀላፊነታችንን እንወጣ በማለት አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም በመርሃ-ግብሩ ላይ ለተነሱ የተለያዩ ሀሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች ላይ የባለስልጣኑ እና የቅ/ጽ/ቤቶች የስነምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክተሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል፡፡
"አካል ጉዳተኝነትን የሚያሳትፍ ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል የአካል ጉዳተኞች ቀን ሲከበር ስለአካል ጉዳተኝነት ምንነት በጥልቀት ግንዛቤ ኖሮን ማንኛውም የሚሰሩ መሰረተ ልማቶች አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ በማድረግ ሊሰሩና የእኩል እድል ተሳትፎን በማረጋገጥ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ አካል ጉዳተኞች የሚያጋጥማቸውን ተግዳሮቶች በመረዳት እና መሰናክሎችን ለማሰወገድ በጋራ በመስራት ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን እንዲረጋገጥ ሃላፊነታችንን እንወጣ ሲሉ ከአዲስ አበባ ሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አቶ አሉላ ሲሳይ ለውይይት ያቀረቡትን ሰነድ አብራርተዋል፡፡
ዶክተር ደሳለኝ ጴጥሮስ የባስልጣኑ አማካሪ እንደገለጹት ሁለቱንም መርሃ-ግብሮች በጋራ ስናከብር በየዕለቱ ግንዛቤ በመውሰድ መማር አለብን ያሉ ሲሆን ኤች አይቪ ኤድስን አስመልክቶ ስርጭቱን ለመግታት የበኩላችንን ጥንቃቄ ማድረግና በአካባቢያችንም ያሉትን የማህበረሰብ ክፍሎች ማስተማር ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል አካል ጉዳተኝነት አስመልክቶ እንደገለጹት ያለምነውና ያሰብነው ግብ ላይ ለመድረስ አካል ጉዳተኝነት እንደማያግደን ገልጸው ዋናው አስተሳሰብ ነው ያሉ ሲሆን እኩል እድገትና ለውጥን ለማምጣት አካል ጉዳተኞችን በእኩል ደረጃ ማሳተፍ ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+6
ባለስልጣኑ የጸረ-ኤችአይቪ ኤድስ እና የአካል ጉዳተኞችን ቀን አስመልክቶ የፓናል ውይይት አደረገ፡፡
(ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጸረ-ኤችአይቪ ኤድስ እና የአካል ጉዳተኞችን ቀን አስመልክቶ የፓናል ውይይት አደረገ፡፡
"ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይቪ ኤድስ ምላሽን ዘላቂነት እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በዘንድሮ ዓመት የሚከበረውን የጸረ-ኤችአይቪ ቀን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አቶ አዲስኪዳን ተሰማ ለውይይት ባቀረቡት ሰነድ ወቅታዊ መረጃዎችን ያቀረቡ ሲሆን የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ ስርጭቱ እንደሃገር እየቀነሰ ቢመጣም እንደ አዲስ አበባ ግን ሰፊ በመሆኑ ራሳችንን እንጠብቅ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
