የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
إظهار المزيد2 631
المشتركون
+624 ساعات
+267 أيام
+4830 أيام
أرشيف المشاركات
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ቶማስ ቢተው ወንድም ስላረፈ ስርዓተ ቀብሩ ዛሬ ጥቅምት 05/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ላይ በገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ስለሚፈጸም የምትችሉ አባላት ቀብሩ ላይ እንድንገኝ ይሁን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው ከጃክሮስ ከፍ ብሎ የሚገኘው ሜታ ፋብሪካ አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የወንድማችንን ነፍስ ይማርልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር ጥቅምት 02/2017 ዓ.ም 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን
“ እርስ በእርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” በሚል ዐብይ ርዕስ በዛሬው እለት እሑድ መስከረም 26/2017ዓ.ም የተጠራው የነበረው የጠቅላላ ጉባኤ አባላት የውይይት መርሐ ግብር ተከናወነ። በጉባኤው ላይ ያለፈው ዓመት የ2016 ዓ.ም የነበረው የአገልግሎት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በጉባኤው ተሳታፊዎች በቀረበው ሪፖርተር ዙሪያ እና አሉ የሚሏቸውን ድክመቶች እና ጥንካሬዎች ሃሣባቸውን በመስጠት ጥያቄዎቻቸውም በማቅረብ በቀጣይ 2017 ዓ.ም የሚሰሩ ዓበይት ስራዎችን በማሳወቅ ሁሉም የአገልግሎቱ ተሳታፊዎች እንዲሆኑና በንቃት እናገለግል ዘንድ በበጎ መንፈስ ውይይት ተደርጎ ተጠናቋል።
ቅዱስ እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
+8
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን
“ እርስ በእርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” በሚል ዐብይ ርዕስ በዛሬው እለት እሑድ መስከረም 26/2017ዓ.ም የተጠራው የነበረው የጠቅላላ ጉባኤ አባላት የውይይት መርሐ ግብር ተከናወነ። በጉባኤው ላይ ያለፈው ዓመት የ2016 ዓ.ም የነበረው የአገልግሎት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በጉባኤው ተሳታፊዎች በቀረበው ሪፖርተር ዙሪያ እና አሉ የሚሏቸውን ድክመቶች እና ጥንካሬዎች ሃሣባቸውን በመስጠት ጥያቄዎቻቸውም በማቅረብ በቀጣይ 2017 ዓ.ም የሚሰሩ ዓበይት ስራዎችን በማሳወቅ ሁሉም የአገልግሎቱ ተሳታፊዎች እንዲሆኑና በንቃት እናገለግል ዘንድ በበጎ መንፈስ ውይይት ተደርጎ ተጠናቋል።
ቅዱስ እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
🌼🌼🌻🌻ወርሐ ጽጌ🌼🌼🌻🌻
ዘመነ ክረምትን አሳልፎ ዘመነ መጸውን የአበባው ወራት የሰጠን አምላክ ይክበር ይመስገን ዘመነ ክረምት መስከረም 25 ተጠናቀቀ። አሁን ዘመነ ጽጌ (ወርሐ ጽጌ) መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ይጠናቀቃል ፤ የጽጌ ጾም የፈቃድ ጾም ነው ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አይመደብምና ነገር ግን የእመቤታችንን ስደቷን እያሰቡ መጾም ትሩፋት ያሰጣል። «እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ፤ እናቱንና ሕፃኑን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው»
ዮሴፍም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በነቢይ ልጄን ከግብጽ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብጽ ሸሸ(ተሰደደ)
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ፤ ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትላ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር በግብጽ አውራጃዎች ተሰደደች በእነዚህ በስደቷ ወራት ወደ አስራት ሀገሯ ኢትዮጵያ መጥታ ነበር።ለዚህም በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ዘመነ ጽጌ ልዩ ቦታ ተሰጥቶት ከጅማሬው እስከ ፍጻሜው በማኅሌት እንዲሁም ፈቃዱ የሆነም በጾም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና የልጇ የወዳጇ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስደት ይታሰባል።
ከበረከቱ ያሳትፈን አሜን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ጠቅላላ ጉባኤ
⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
“ እርስ በእርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” ፩ኛ ተሰሎንቄ ፭፥፲፩
መንፈሳዊ ጥሪ ለፍኖተ ብርሃን አባላት በሙሉ
እግዚአብሔር በነፍስም በስጋም ያከበራችሁ ቅዱስ ሚካኤል ጠበቃና ሞገስ የሆናችሁ ዛሬ ቅድስት ቤተክርስቲያን ባለችበት ወቅታዊ ሁኔታ ና ሰንበት ትምህርት ቤታችን የትናንቱን የአገልግሎት እንቅስቃሴ ዛሬ አገልግሎቱ ያለበትን ሁኔታ እና ወደፊት መስራት ስለሚጠበቅብን ነገር ለመምከር ሁሉም የፍኖተ ብርሃን አባላት የፊታችን እሑድ በቀን 26/01/2017 ዓ.ም ከ11:00 ጀምሮ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ እንድትገኙ ፍኖተ ብርሃን ጠርታለች እናም የሰንበት ትምህርት ቤታችንን የጥሪ መልእክት የሰማችሁ ላልሰሙ ወንድም እህቶቻችን ጥሪውን በማዳረስ በጉባኤው ላይ እንድትገኙ በእናታችን በፍኖተ ብርሃን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።
ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የቅዳሜ መርሐግብር ቅዳሜ መስከረም 25/2017 ዓ.ም 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከራሽያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋራ ውይይት አካሔደ
___
ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከራሽያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋራ በትላንትናው እለት መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ጽሕፈት ቤት ውይይት አካሒዷል።
ውይይቱን የመሩት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ሲሆኑ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የራሽያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በጋራ ሰለሚሠሩበት ጉዳይ ውጤታማ ውይይት እንዳካሔዱ በሁለቱም ወገን ተገልጿል።
ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች "እየመጣ ባለው ፈጣን የግሎባላይዜሽን ዕድገት በዓለም ላይ ኢሞራላዊ ድርጊቶች እንደ ሥልጣኔ በመቆጠራቸው ባሕልንና ሃይማኖትን የሚያዳክሙ ሆነዋል። በመሆኑም ይህን የግሎባላይዜሽን አሉታዊ ተጽእኖ ወደ በጎ ዕድል መቀየር የሚቻለው በትምህርት ቤቶች በኩል በሚደረግ የሞራል ግንባታ ነው" በማለት የጋርዮሽ ውይይቱ ዋና ማጠንጠኛ አድርገውታል።
በሁለቱም ሀገሮች የሚኖሩ ሕዝቦች ባሕላቸውንና ሃይማኖታቸውን የሚጠብቁ በመሆናቸው ዩኒቨርሲቲዎቹ በመተጋገዝ በባሕል ጥበቃ፣ በሥነ ምግባር (Moral & Ethics) እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በተሐይ የነገ ሀገር ተረካቢ በሚሆኑት ወጣቶችን በማነጽ ረገድ አብረው ለመሥራት የሚያስችል ውይይት አድርገዋል።
የራሽያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች የሚቀጥለው ውይይት በራሽያ እንዲደረግ የጋበዙ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ በግብዣው እንዲገኙ ጥሪ አቅርበዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ በአገልግሎት መደራረብ ምክንያት የማይመቻቸው ቢሆን እንኳን በአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚደንቱ ፕ/ር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ የሚመራ ልዑክ ዩኒቨርሲቲያችንን ወክሎ ሊሳተፍ እንደሚችል ተጠቁሟል።
© የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሕዝብ ግንኙነት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ በያዝነው የ2017 ዓ.ም ለመማር የምትፈልጉ ካላችሁ የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ እስከ ጥቅምት 01/2017 ድረስ የሚያከናውን መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ስለገለጸ መስፈርቱን የምታሟሉና መማር የምትፈልጉ መመዝገብ ትችላላችሁ።
©መረጃውን ከቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ሕዝብ ግንኙነት አግኝተነዋል።
በእለቱ የእርስዎ በጠቅላላ ጉባኤው ላይ መገኘት ለቀጣዩ አገልግሎት ትልቅ አስተዋጽኦ (ድርሻ) አለውና እንዳይቀሩ በጉጉት እንጠብቃለን።
‛‛ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው’’
በሰንበት ት/ት ቤታችን መስከረም 26/2017 ዓ.ም በምናከናውነው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ቢቻል ሁላችንም ስንመጣ ሁለት ሁለት ደብተር ይዘን ብናመጣ የተማሪዎችን ችግር በመጠኑ መቅረፍ እንችላለን። የምትችሉ ፓኬጁን በመሸፈን አገልግሎቱን እንደግፍ።
እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን
የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል እያከናወነ ያለውን በጎ ስራ ለመደገፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ለሌሎች መረጃዎችም
0912 41 97 72
09 66 25 87 38
09 31 14 44 44 በመደወል ማነጋገር ይቻላል።
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
መስከረም 21
ብዙኃን ማርያም
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡
በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡
ጉባዔ_ኒቅያ
በ325ዓ.ም አርዮስ የሚባል መናፍቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአርዮስ ክህደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡
በዚህም መሠረት ከሚያዝያ 21 ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ 2348 (ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ዐርባ ስምንት) ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡
ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ (2348) መካከል (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ 318 ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት 318ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው /ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡
318ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም ፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "#ብዙኃን_ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡
2. ዕፀ መስቀል
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
1 ሳምንት ብቻ ቀረው
የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ
እሑድ መስከረም 26/2017ዓ.ም
ከምሽቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ
“ እርስ በእርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” ፩ኛ ተሰሎንቄ ፭፥፲፩
የዕለቱ የጉባኤው አጀንዳ
"የ2017ዓ.ም የአገልግሎት ዘመን ምክክር ስለ ማድረግ
💒በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
ጠቅላላ ጉባኤው ላይ በመገኘት መልዕክቱን የሰማችሁ ላልሰሙት ጥሪውን በማዳረስ የአባልነት ግዴታዎን ይወጡ ።
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የተከበራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በተከታታይ ቅዳሜ ምሽት የምናከናውነው የትምህርት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ማለትም መስከረም 18/2017 ዓ.ም በበዓላት መደራረብ ምክንያት የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን። ነገ መደበኛ መዝሙር ጥናት ይቀጥላል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
