የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
إظهار المزيد2 610
المشتركون
+524 ساعات
+127 أيام
+3030 أيام
أرشيف المشاركات
+5
# ሰበር_ዜና
የወይራ ሠፈር ኆኅተ ገነት ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቀጠሎ ወደመ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኮሎፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የወይራ ሠፈር ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና መንበረ ብርሃን እጨጌ አቡነ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኝ ሲሆን ዛሬ ሌሊት በእሳት አደጋ ምክንያት የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
የቃጠሎው መነሻ የኤሌክትሪክ መስመር ችግር እንደሆነም የተገለጸ ሲሆን ከታቦቱ በስተቀር ሌሎች ንዋየተ ቅድሳት ሙሉ በሙሉ በአደጋው ምክንያት መውደማቸው ነው የተገለጸው።
ሊያገለግሉበት ሲሄዱ ቦታውን ያጡት ሊያስቀድሱበት የገሰገሱበት ቤተ ክርስቲያን በእሳት እንዳልሆነ ሆኖ ሲያዩት ልባቸው የከዳቸው ካህናትና ምእመናን በከፍተኛ ኀዘን ላይ እንደሚገኙም የደረሰን መረጃ ያለመክታል።
አቤቱ ማረን ይቅር በለን!
© የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
+9
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ ።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመቱ ዓመታዊ ታላቅ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ገ/ሥላሴ በላይ የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ ዋና አስተዳዳሪ፣ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው እና ሌሎችም የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት፣ የሰንበት ት/ት ቤት አገልጋዮችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ሰላም እብል ኪያከ መልዐከ፤
ሩኀሩኅ ልብ ለኵሉ እንተኢኮንከ ድሩከ
ሚካኤል ሊቅየ ለለዕቤለከ፤
ኅብአኒ በጽላሎትከ ነግሀ ወሠርከ፤
እስመ እምንዕስየ እፈርሕ ሀከከ።
ለሁሉ የምትራራ ጌታዬ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ እኔን ወዳጅህን በረድኤትህ ጥላ ከጧት እስከ ማታ ከክፉ ነገር ሁሉ ሠውረኝ ከልጅነቴ ጀምሮ ፀብንና ክርክርን እፈራለሁና።
ትንብልናሁ ወአስተብቊዖቱ ለቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት የሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።
“በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤..."
ትን ዳን. 12፥1
በነገው እለት ኅዳር 12 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል እርስዎም በክብረ በዓሉ ላይ እንዲገኙ የከበረ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!!
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን!!!
+6
🌹🌹🌹🌹🌹ሥርዐተ ማኅሌት
ዘኅዳር ቅዱስ ሚካኤል🌹🌹🌹🌹🌹
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የተከበራችሁ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ
ለማዕከላውያን (እድሜያቸው ከ13-18) ለሚሆኑ የዲጅታል ሰሌዳ መጽሔት በአዲስ መልክ ህዳር 12 ቀን ስለሚጀምር ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ቤተሰብ ይሁኑ ይከታተሉ🙏
https://t.me/+Czq3A7Y-zIwxNTk0
እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይባርክ።
+9
ጥቅምት 30/2018 በሚሊኒየም አዳራሽ ከነበረው የምርቃት መርሐግብር የሰንበት ት/ቤታችን ተመራቂዎች እና የመርሐ ግብሩ አቅራቢዎች በጥቂቱ ማስታወሻ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
