ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 756
المشتركون
+124 ساعات
+97 أيام
+4330 أيام
أرشيف المشاركات
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ወርሐዊ የባለትዳር አባላት ጉባኤ እሑድ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም ከ5:00- 7:00 ጉባኤው በወር አንድ ቀን ብቻ የሚከናወን በመሆኑ በእለቱ ተ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን   ወርሐዊ የባለትዳር አባላት ጉባኤ እሑድ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም   ከ5:00- 7:00 ጉባኤው በወር አንድ ቀን ብቻ የሚከናወን በመሆኑ በእለቱ  ተገኝተው ቃለ እግዚአብሔርን ይመገቡ።             የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን የአብስራ አክሊሉ  አያት አርፈዋል ሥርዓተ ቀብራቸው ነገ ሐሙስ ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ይፈጸማል የምትችሉ አባላት በቀብሩ ላይ እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው ጭድ ተራ ወረድ ብሎ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። ነፍሳቸውን ይማርልን ።        የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን ዮዲት ገ/እግዚአብሔር አባት አርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል የምትችሉ አባላት መኖሪያ ቤታቸው አሸዋ ሜዳ አካባቢ በመሄድ ወይም በስልክ ቁጥር +251911124269 በመደወል  እንድናጽናናቸው ይሁን። የአባታችንን ነፍስ ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

''ትመስሊ ምሥራቀ፤ ወትወልዲ መብረቀ፤ ወታገምሪ ረቂቀ፡፡ ትመስሊ ፊደለ፤ ወትወልዲ ወንጌለ፤ ወታገምሪ ነበልባለ፡፡ ትመስሊ ጽጌ ረዳ፤ ወትወልዲ እንግዳ፤ ወታድኅኒ እሞተ ፍዳ … ሐረገ ወይን ሐረገ ወ
''ትመስሊ ምሥራቀ፤ ወትወልዲ መብረቀ፤ ወታገምሪ ረቂቀ፡፡ ትመስሊ ፊደለ፤ ወትወልዲ ወንጌለ፤ ወታገምሪ ነበልባለ፡፡ ትመስሊ ጽጌ ረዳ፤ ወትወልዲ እንግዳ፤ ወታድኅኒ እሞተ ፍዳ … ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ዐፀደ ወይን አንቲ ማርያም ''    ''በምሥራቀ ፀሐይ የምትመሰይው፤ እንደ መብረቅ ኃያል የሆነውን ጌታን የወለድሽ፤ ረቂቅ ምሥጢርን የምትችዪ፤ እንደ ፊደል ባለ ብዙ ዘር (ሆሄያት) የሆንሽ፤ ወንጌልን የወለድሽ፤ ነበልባለ እሳትን (ክርስቶስን) የተሸከምሽ፤ በጽጌ ረዳ አምሳል የምትመሰይው ቅድስት ማርያም ሆይ! የዓለሙን እንግዳ ፈጣሪን የወለድሽ፤ ከፍዳ ሞት የምታድኚ፤ የወይን ሐረግ የወይን ዐፀድ (ተክል) አንቺ ነሽ …''    ልመናዋ ክብሯ የልጅዋም ቸርነት ከሁላችንም ጋራ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር አሜን፡፡

''ትመስሊ ምሥራቀ፤ ወትወልዲ መብረቀ፤ ወታገምሪ ረቂቀ፡፡ ትመስሊ ፊደለ፤ ወትወልዲ ወንጌለ፤ ወታገምሪ ነበልባለ፡፡ ትመስሊ ጽጌ ረዳ፤ ወትወልዲ እንግዳ፤ ወታድኅኒ እሞተ ፍዳ … ሐረገ ወይን ሐረገ ወ
''ትመስሊ ምሥራቀ፤ ወትወልዲ መብረቀ፤ ወታገምሪ ረቂቀ፡፡ ትመስሊ ፊደለ፤ ወትወልዲ ወንጌለ፤ ወታገምሪ ነበልባለ፡፡ ትመስሊ ጽጌ ረዳ፤ ወትወልዲ እንግዳ፤ ወታድኅኒ እሞተ ፍዳ … ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ዐፀደ ወይን አንቲ ማርያም ''    ''በምሥራቀ ፀሐይ የምትመሰይው፤ እንደ መብረቅ ኃያል የሆነውን ጌታን የወለድሽ፤ ረቂቅ ምሥጢርን የምትችዪ፤ እንደ ፊደል ባለ ብዙ ዘር (ሆሄያት) የሆንሽ፤ ወንጌልን የወለድሽ፤ ነበልባለ እሳትን (ክርስቶስን) የተሸከምሽ፤ በጽጌ ረዳ አምሳል የምትመሰይው ቅድስት ማርያም ሆይ! የዓለሙን እንግዳ ፈጣሪን የወለድሽ፤ ከፍዳ ሞት የምታድኚ፤ የወይን ሐረግ የወይን ዐፀድ (ተክል) አንቺ ነሽ …''    ልመናዋ ክብሯ የልጅዋም ቸርነት ከሁላችንም ጋራ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር አሜን፡፡

''ትምህርተ ሃይማኖት '' ክፍል ሶስት በዲ/ን ሞገስ አብርሃም የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
''ትምህርተ ሃይማኖት ''           ክፍል ሶስት                 በዲ/ን ሞገስ አብርሃም የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  ዛሬ ቅዳሜ  ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ውድ የተከበራችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት እንዲሁም የአጥቢያችን ምዕመናን በሙሉ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯   በትላንትናው ዕለት ማለትም በ18/02/18 ዓ.ም በደብራችን የመንፈስ ቅዱስ ክብረ በዓልና በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ አላግባብ ጽሑፍና ማንም ባልፈቀደው መልኩ  ህግን በጣሰ መሠረት በደብራችን የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ/ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ   የትችት ጽሑፍ በሶሻል ሚዲያ ባስተላለፈው ዲ/ን  ከሳቴ ብርሃን ዙሪያ  እንደ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ ቤት መረጃ እያሰባሰብን እንዲሁም በግለሰቡ ላይ ማጣራት ያለብንን ጉዳዮች እየተከታተልን ሲሆን  ጽሁፉ ን እና ግላዊ ሃሳባቸውን ባስተላለፉት ግለሰብ ላይም የቤተ ክርስቲያኒቷ ህግ በሚያዘው  መሠረት የማጣራት እና እንዲጠየቅ የማድረግ ስራ ለመስራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እያደረግን መሆኑን ለክቡራን  አባላቶቻችን እና ወዳጆቻችን ለማሳሰብ እንወዳለን !!!     የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጽ/ቤት

'' ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ዘሠረጸ እም አብ ንስግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበ በነቢያት''     በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረጸ ከአብና ከወልድ ጋር በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን፤ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረው ነው። መንፈስ ቅዱስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ጰራቅሊጦስ:- ናዛዚ ፣ መጽንዒ፣ መስተፍሥሒ ፣ የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው። ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ''እናንተ  ግን  ከላይ ኃይል እስክትለብሱ  ድረስ  በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ'' ብሎ ለሐዋርያቱ በሰጣቸው ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሳ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ ድንገት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት መላው የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎችም በሁሉም ላይ አረፉባቸው በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በተለያዩ በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ ተናገሩ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጎለመሱ፤ ጥቡዓን ሆኑ፣ ፍርሃት ከውስጣቸው ተወግዶ መንፈሳዊ ድፍረት አግኝተዋል፤  ጽኑዓን ኾነዋል፤ ሰማያዊ ሀብት ዕውቀትና ጸጋን ታድለዋል። በዚህ ዕለት ሐዋርያት በተገለጠላቸው ቋንቋ ሲያስተምሩ ተቃዋሚ አይሁዳውያን  ''ጉሽ  ጠጅ  ጠጥተው  ሰክረው የሆነ ያልሆነውን ይቀባጥራሉ''  እያሉ ሐዋርያትን አሟቸው ቅዱስ ጴጥሮስም  ሰክረዋል  የምትሉ  እናንተ እንደምትሉት  አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ  ሰዓቱም ገና ጠዋት  ሦስት  ሰዓት  ነው    ይልቁኑ እናንተ በተንኮል ሰቅላችሁ የገደላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መሆኑን  በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ከክፋታቸው ተመልሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመኑ በዚያች ብቻ ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ተመልሰዋል ዕለቱም የቤተክርስቲያን የልደት ቀን ይባላል።   ከሶስቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ወር በገባ በ18 በዓሉ ሲሆን በአዲስ አበባ በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ዋና ደብሩ ሁልጊዜም በዓሉ ይታሰባል። ከዚያ በተጨማሪም በበዓለ ሃምሳ መንፈስቅዱስ የወረደበት ዕለት በታላቅ ድምቀት በየዓመቱ ይከበራል። ከሶስቱ አካላት አንዱ የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ጠብቆት አይለየን አሜን።