ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 639
المشتركون
-224 ساعات
+37 أيام
+5630 أيام
أرشيف المشاركات
የወጣት ምድብ አገልግሎት ተጀመረ ከላይ የተዘረዘረውን ስም በማየት ከተመች ያስቀመጥነውን ሊንቅ በየምድባችሁ link እየተጫናችሁ ስለምድቡ መወያየት ትችላላችሁ
የወጣት ምድብ አገልግሎት ተጀመረ ከላይ የተዘረዘረውን ስም በማየት ከተመች ያስቀመጥነውን ሊንቅ በየምድባችሁ link እየተጫናችሁ ስለምድቡ መወያየት ትችላላችሁ

🔴ስንክሳር #የካቲት_30 #ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቀ_መለኮት አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሠላሳ በዚህች ዕለት የመጥምቁ ዮሐንስ የከበረች ራሱ ተገኘች። ይህም እንዲህ ነው ከሀዲ ኄሮድስ የከበረ ዮሐንስን ራሱን ይቆርጡት ዘንድ በአዘዘ ጊዜ በእሥር ቤት ራሱን ቆርጠው ወደ ኄሮድስ አቀረቧት እርሱም ለወገኖቹ በማሳየት በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ስለ አደረገው ሥራ እንደሚያዝን ገለጠላቸው የክቡር ዮሐንስንም ራስ በቤቱ ውስጥ አስቀራት። የፊተኛዪቱ ሚስቱ የንጉሥ አርጣ ልጅ ግን በአበረራት ጊዜ ወደ አባቷ መጥታ በፊቱ አለቀሰች ኄሮድስ በእርሷ ላይ ያደረገውን ሁሉ እርሷን አሳዶ የወንድሙን ሚስት ኄሮድያዳን እንዳገባ ነገረችው። በዚያንም ጊዜ ንጉሥ አርጣ ተቆጥቶ ተነሣ ሠራዊቱንም ሰብስቦ ወደ ገሊላ ዘመተ የገሊላንም ሀገሮች ሁሉ አጠፋ በእሳትም አቃጠለ። ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሣር ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ኄሮድስ በአባረራት በልጁ ምክንያት ንጉሥ አርጣ ይህን እንዳደረገም በአስረዱት ጊዜ ስለዚህ ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሣር ተቆጣ ኄሮድስንም ወደ ሮሜ ከተማ ወደርሱ አስቀረበው በእርሱም ምክንያት የሀገሮች ጥፋት በመደረጉና ታላቁን ነቢይም ስለ መግደሉ ከሹመቱ ሻረውና እንድልኩ ወደሚባል አገር አጋዘው በዚያም በክፉ አሟሟት ሞተ። የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ግን በኄሮድስ ቤት ተቀብራ ትኖር ነበር ከዚህም በኋላ ንጉሥ ጢባርዮስ ጭፍሮቹን ልኮ የኄሮድስን ቤት አስፈረሰ ጥሪቱን ሁሉ ወሰደ ለሚያየውም ሁሉ አርአያና ተረት ሆነ ያለ ጣሪያና ያለ ደጃፍ ቀርቷልና ነጋዴዎችም መነሃሪያ አድርገው ያድሩበት ነበር። በዚያንም ወራት በገንዘብ ድኆች በሃይማኖት ባለጸጎች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ እነርሱም ሊሰግዱ የከበረች የአርባ ቀን ጾምንም ሊጾሙ ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዙ ይህም ከብዙ ዘመን በኋላ ነው። ምሽትም በሆነ ጊዜ ምድረ በዳ በሆነ በኄሮድስ ቤት ውስጥ አደሩ ቅዱስ ዮሐንስም ከእርሳቸው ለአንዱ በሕልም ተገለጠለትና የከበረች ራሱ ያለችበትን ቦታ አስረዳው ወደቤቱም ተሸክሞ ይወስዳት ዘንድ አዘዘው በነቃም ጊዜ ራእይን እንዳየ ለባልንጀራው ነገረው። ቅዱስ ዮሐንስም ወደአመለከተው ወደዚያ ቦታ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ በቆፈሩም ጊዜ የሸክላ ዕቃ አግኝተው ከፈቷት ያን ጊዜ እጅግ የሚመስጥ በጎ መዓዛ ወጣ የቅዱስ ዮሐንስንም ራስ አገኙዋት ከእርሷም ተባረኩ ወደ ሸክላውም ዕቃ መለሱዋትና በፊት እንደ ነበረ አፉን ዘጉ ያም ሰው ከእርሱ ጋር ወደ ቤቱ ወሰዳት ታላቅ ክብርንም አከበራት ሁል ጊዜም የሚያበሩ መብራቶችን በፊቷ አኖረ። የዚያም ሰው ዕረፍቱ በቀረበ ጊዜ ለእኅቱ ነገራት እርሷ ቅድስና ስለአላት እርሱ ሲሠራው እንደነበረ ትሠራ ዘንድ አዘዛት እርሷም የምታከብራትና ሁል ጊዜ መብራትንም የምታበራ ሆነች። የቅዱስ ዮሐንስም ራስ ወደ አርዮሳዊ ሰው እስከ ደረሰች ድረስ ከአንዱ ሰው ወደ አንዱ ሰው የምትፋለስ ሆነች ይህም ሰው በከሀዲው አርዮስ እምነት ውስጥ እያለ የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ድንቆች ተአምራቶችን እንደምታደርግ ያስብ ነበር። የከበረ ዮሐንስም ከእርሱ የሚበልጥ ሰው በላዩ አስነሣበትና ከዚያ ቦታ አሳደደው ያም ቦታ አባ ቄርሎስ በኢየሩሳሌም ሀገር አባ አንያኖስ በሀገረ ኀምዳ ኤጲስቆጶስነት እስከ ተሾሙ ድረስ ፈጽሞ ሰው የማይኖርበት ምድረ በዳ ሆነ። ቅዱስ ዮሐንስም ለአባ አንያኖስ በሕልም ተገልጦ የከበረች ራሱ ያለችበትን ቦታ ነግሮ አመለከተው አባ አንያኖስም ሒዶ እንደ ዛሬው ግንቦት ሠላሳ ከዚያ አወጣት ይህም የካቲት ሠላሳ ቀን ከአገኙዋት በኋላ ዳግመኛ ያገኙበት ነው። እንዲህም የሚል አለ የከበረ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናገረ ይህም ኄሮድስ በአዘዘ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ በእሥር ቤት ሳለ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው በጻሕል አድርገው ወደ ኄሮድስ አመጡለት እርሱም ለኄሮድያዳ ልጅ ሰጣት እርሷም ለእናቷ ወስዳ ሰጠች። ይቺም የረከሰች አመንዝራ ልትዳስሣት በወደደች ጊዜ በወጭቱ ውስጥ ጠጒሩዋ ተዘርግቶ ወደ አየር በረረች በአየርም ሁና የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም እያለች የምትጮኽ ሆነች እንዲህም እያለች ዐሥራ አምስት ዓመት ኑራ በዓረቢያ ምድር ዐረፉ በዚያ ተቀበረች። ነጋድያንም በዚያ ቦታ የሚያድሩ ሆነ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ሁለት አማንያን ነጋዴዎች ወደዚያ ቦታ ደርሰው አደሩ ቅዱስ ዮሐንስም በሕልም ተገለጠላቸውና የከበረች ራሱን ያወጡ ዘንድ አዘዛቸው እነርሱም አወጡዋት ከእርሳቸውም ጋር ወደ ቤታቸው ወስደው ታላቅ ክብርን አከበሩዋት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም መለኮትን በአጠመቀ በከበረ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን፤ ልዩ የሆነች በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲት)

🔴 የሰንበት ት/ቤታችንን አገልግሎት ስለደገፉ እናመሰግናለን ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁን ከታች ያለውን link በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉን 👇👇 https://m.youtube.com/channel/U
🔴 የሰንበት ት/ቤታችንን አገልግሎት ስለደገፉ እናመሰግናለን ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁን ከታች ያለውን link በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉን 👇👇 https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ

መልአኩም እናታችንን ከቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም መልሶ ወደ ኢትዮጵያ ካመጣት በኋላ ዛሬ ገዳሟ ካለበት ቦታ ስትደርስ ከቦታዋ ላይ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ በቀስተ ደማና ተከቦ አይታ ‹‹ይህች ቦታ ምንታምር›› ብላ ጠራቻት፡፡ በመድኃኔዓለምም ትእዛዝ የቅድስት ኪዳነ ምሕረትን ቤተ ክርስቲያን በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታለች፡፡ ቦታዋ ዛሬም ድረስ ‹ምንታምር› እየተባለች የምትጠራ ሲሆን ቅድስት እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ የሠራቻት በስሚዛ (በሰንሰል) እንጨት፣ በአይጥ ሐረግ፣ በነጠላ ማገር አድርጋ የግድግዳ ቤተ መቅደስ በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታ በታኅሣሥ 16 ቀን በዕለተ እሁድ ቅዳሴ ቤቷን አክብራለች፡፡ በዚህም ጊዜ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤልና ቅዱስ መሲፋይል በክንፋቸው አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው በቦታዋ ላይ ቀላቅለውበታል፡፡ ጌታችንም ከብርሃን እናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ለፍቅርተ ክርስቶስ ተገልጦላት ቦታዋን ባርኮላት እስከዕለተ ምፅዓትም ድረስ እንደማትፈርስ ቃልኪዳን ገብቶላታል፡፡ ለምሳሌ በአንድ ወቅት ከባድ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ጫካውን ሁሉ ሲያቃጥል ከቤተክርስያኗ ላይ ግን ለምልክት ያህል ጫፏ ላይ ያለችውን የሰጎን እንቁላል ብቻ አቃጥሎ ቤተ መቅደሷን አልፎ ሄዶ ጫካውን ሁሉ አቃጥሏል፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በአንዲት ቀን ብቻ በተአምራት የሠራቻት ቤተ ክርስቲያኗ ተሠርታ ባለቀች ጊዜ ጌታችን ለእናታችን ተገልጦላታል፡፡ ጌታችንም በተገለጠላት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኗ በአራቱም አቅጣጫ ለጌታችን ሰግዳለች፡፡ ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያኗ በአራቱም አቅጣጫ ሆነው ሲመለከቷት በተቃራኒው አቅጣጫ እየሰገደች ትታያለች፡፡ በምሥራቅ አቅጣጫ ሆነው ቢያዩዋት ወደ ምዕራብ ሰግዳ ትታያለች፤ በምዕራብም ሆነው ቢያዩዋት ወደ ምሥራቅ ሰግዳ ትያለች፡፡ በሰሜን አስራቅ አቅጣጫ ሆነው ቢያዩዋት ወደ ደቡብ ሰግዳ ትታያለች፤ በደቡብም ሆነው ቢያዩዋት ወደ ሰሜን ሰግዳ ትያለች፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በተሰጣት ቃልኪዳን መሠረት በገዳሟም ውስጥ መርዘኛ እባብም ቢሆን ሰውን ወይም እንስሳትን ቢነድፍ መርዙ ምንም አይጎዳም፡፡ እንዲሁም ጌታችን ገዳሟን መናፍቃን ወይም ከሐዲያን እንደማይረግጧት ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ለምሳሌ የጣሊያን ጦር በሀገራችን የተለያዩ ገዳማትን እያጠፋ መነኮሳትን እየገደለ ከፍተኛ ጥፋት ባደረሰበት ወቅት ይህችንም ገዳም ለማጥፋትና መነኮሳቶቹንም ለመግደል መጥቶ ነበር፡፡ መነኮሳቶቹም ይህን ሰምተው ለሰማዕትነት ተዘጋጅተው ጠበቁ ነገር ግን የጦር አዛዡና ሠራዊቱ የገዳሟን ክልል አልፈው መግባት አልቻሉም፣ የገዳሟ ክልል ላይ ሲደርሱ በተአምራት እግራቸው ተሳስሮ መቆም መቀመጥ ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ የጦር አዛዡም ‹‹ክርስቶስ ከዚች ገዳም አለ›› ብሎ ሃምሳ ጠገራ ብር ሰጥቶ ወደመጣበት ተመልሷል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በዚህች ገዳም ላይ ለቅድስት እናታችን ድንቅ ድንቅ ቃልኪዳን ከሰጣት በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በየካቲት 29 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡ በሥጋዋም ላይ ታላቅ የብርሃን አምድ ተተክሎ የታየ ሲሆን እንደፀሐይም ከጠዋት እስከ ማታ ያበራ ነበር፡፡ በመካነ መቃብሯም ላይ እስከ አርባ ቀን ድረስ ብርሃን ተተክሎ ታይቷል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲትና #ከገድላት_አንደበት) https://t.me/finotebirhan12

🔴 ስንክሳር #የካቲት_29 የካቲት ሃያ ዘጠኝ በዚች ቀን ታላቋ ሐዋርያዊት እናታችን የእመ ምኡዝ #ቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ ዕረፍቷ ነው፣ የአርሞኒ ሀገር ኤጲስቆጶስ የከበረ #ቅዱስ_ቢላካርዮስ በሰማዕትነት ሞተ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ የካቲት ሃያ ዘጠኝ በዚች ቀን ታላቋ ሐዋርያዊት እናታችን የእመ ምኡዝ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት ዕረፍቷ ነው፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ወይም እመ-ምዑዝ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደራ ፎገራ አንበሳሜ በሚባለው ቦታ የአብርሃምና የሣራ ምግባር ካላቸው ከአባቷ ከላባ ከእናቷ ከወንጌላዊት ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን በታዘዘ መልአክ አብሳሪነት ተወለደች፡፡ በተወለደችም ጊዜ በእግሯ ቆማ ‹‹በማኅየዊ ቸርነትህ ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል›› ብላ አምላኳን አመስግናለች፡፡ ቤተሰቦቿ ያገኙዋት በስዕለት ሲሆን ስመ ክርስትናዋም ማርያም ጸዳለ ተባለ፡፡ ፍቅርተ ክርስቶስ የሚለው የቆብ (የምንኩስና) ስሟ ነው፡፡ ዕድሜዋ ለትምህርት እንደደረሰ እግዚአብሔር የላከው አንድ ደገኛ መነኩሴ ወደ እርሷ በመሄድ የዳዊትን መዝሙር፣ የብሉያትና የሐዲሳት መጻሕፍትንና የቤተክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ በሚገባ አስተምሯታል፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በነበረችበት ዘመን ዐፄ ሱስንዮስ ‹‹ሁለት ባሕርይ›› የሚለውን የረከሰ የሮማውያንን ሃይማኖት የአገራችን ሕዝዝ ሁሉ እንዲያምን በማወጁ ምክንያት በሀገራችን ከፍተኛ የሆነ የሃይማኖት ግጭት ስለተነሣና ከ8ሺህ በላይ ክርስቲያኖች በግፍ ተጨፍጭፈው ሲያልቁ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከእነ አቡነ ስምዖንና ከሌሎችም ቅዱሳንና ቅዱሳት ጋር ተሰልፋ ሰማዕትነትን ተቀብላ ለሃይማኖቷ መስክር ሆናለች፡፡ ባለቤቷ ዘርዐ ክርስቶስም በሰማዕትነት ዐርፎ ሰባት አክሊላት ወርደውለታል፡፡ ዐፄ ሱስንዮስ ለፖለቲካዊ ጥቅም ብሎ የረከሰች የሮማውያንን ሃይማኖት በአገራችን ላይ እንዳወጀ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ስምዖን ካህናትንና ክርስቲያን ልጆቻቸውን አነሳስተው እያስተማሩና እያጠነከሩ እያለ በጦር ተወግተው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ስምዖንም በሰማዕትነት ከማረፋቸው በፊት ግን እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን፣ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስን፣ ቅድስት አካለ ክርስቶስን፣ ቅድስት እመ ወተትንና ሌሎቹንም ቅዱሳንና ቅዱሳት አነሳስተው ባራ ሄደው ንጉሡን መክረውታል፣ ገሥጸውታል፡፡ ንጉሡ ግን ከፍተኛ ፖሊቲካዊ ጥቅም እንደሚያገኝ ሮማውያን ቃል ገብተውለት ስለነበር ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶ አብዝተው ቢመክሩትም ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይልቁንም ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን የሃይማኖቷን ጽናት ስላየ ሥጋዋ እየተቆረሰ መሬት ላይ እስኪወድቅ ድረስ በብረት በትር አጥብቆ ያስገርፋት ጀመር፡፡ በመጨረሻም ምድር እየሰወረቻት ለመግረፍ የማይመቻቸው ቢሆን ከሌሎቹ ሰማዕታት ጋር አንገቷን በሰይፍ አስቆርጦታል፡፡ በዚህም ጊዜ ፍጹም ጨለማ ሆኖ ምድርም ተነዋወጠች፡፡ ስምንት ሺህ አሥር ቅዱሳንም በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን አንገቷን በሰይፍ ቢቆርጧትና በሞት ብታርፍም ነገር ግን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ገነትንና ሲኦልን አሳይቶ 14 ቀን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ከተቀመጠች በኋላ እንደገና እንደተኛ ወይም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ከሞት አስነሥቶ ወደ ቦታዋ መለሳት፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ከሞት ካስነሣት በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ መናኒ ሆና በየገዳሙና በየአድባራቱ እየሔደች ዓለምን ስትዞር ያቀናቻቸው ብዙ ገዳማት አሉ፡፡ ለምሳሌ ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ በሆኑት በአባ ጉባ ተመሥርታ በግራኝ ወረራ ጠፍታ የነበረችውን ራማ ኪዳነምሕረት አንድነት ገዳምን አቅንታ የወንድና የሴት ገዳም ብላ ሥርዓት ሠርታለች፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም በመሄድ ላይ ሳለች በመንገድ ሰውን የሚበሉ ፍጡሮች ወደሚኖሩበት አካባቢ ስትደርስ 60 የሚሆኑ አገልጋዮቿን ለመብላት ይዘው ሳር ቅጠል እንዲበሉ በማድረግ ዐይናቸውን በጉጠት በማውጣት 4 ወራት በጨለማ ቤት ውስጥ ዘጉባቸው፡፡ ሰይጣንንም ያመልኩ ነበርና ከ4 ወራት በኋላም በዓል አድርገው ለመብላት ከእሳት ውስጥ ጨመሯቸው፣ ነገር ግን ጌታችን በቸርነቱ ጠብቋቸዋልና እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን ምንም አልሆኑም፡፡ ያንጊዜም ሰው በላዎቹ ‹‹እናንተ ሰዎች ምንድን ናችሁ?›› ብለው ጠየቋቸው። ቅድስት እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስም ክርስቲያን መሆናቸውንና እነርሱ የሥላሴ ሕንፃ የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው ብታስተምራቸው ‹‹ምን እንበላለን?›› አሏት፡፡ እርሷም ከራማ ኪዳነ ምሕረት ስትነሳ የእህል ዘርን ለአገልጋዮቿ አሰይዛ ስለነበር ከዚያ ስንዴ ወስዳ ዘራችው፡፡ ስንዴውም በአንድ ቀን ብቻ ተዘርቶ በቅሎ፣ ታጭዶ፣ ደርቆ፣ ተፈጭቶ ለምግብነት በቅቷል፡፡ ቅድስት እናታችንም ቀምሳ ስታቀምሳቸው እንደማር እንደወተት የሚጣፍጥ ሆኖላቸው በደስታ ተመግበውታል፡፡ ከዚያም እንደዚህ እያደረጉ እየሠሩ እንዲበሉ አስተምራ አስጠምቃቸው ስድስት አብያተ ክርስቲያናትን አሠርታላቸዋለች፡፡ ወንጌልን፣ ስንክሳርን፣ ሃይማኖተ አበውን፣ ግንዘትን፣ መዝሙረ ዳዊትን፣ አርጋኖንን ሁሉ በእጇ ጽፋ አስቀመጠችላቸው፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ምን ያህል የከበረች ‹‹ሐዋሪያዊት›› እንደሆነች ከዚህ ልብ ይሏል፡፡ የብርሃን እናቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ተገልጣላት በልጇ ምክንያት ስለደረሱባት ሀዘኖች አውርታላታለች፡፡ የፈለገችውንም እንድታደርግበት በእጇ ያለውን መስቀል ለፍቅርተ ክርስቶስ ሰጥታታለች፡፡ በዚህም መስቀል እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ባሕር ከፍላ ደቀ መዛሙርቶቿን አሻግራለች፡፡ የአባታችን የቅዱስ ኤዎስጣቴዎስን ገድል በማንበብና በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እርዳታ ባህሩን በአጽፏ ተሻግራ ወደ ሀገረ ናግራን ሄዳለች፡፡ እንዲሁም በበትረ መስቀሏም እንደ ዘርዐ ቡሩክ ከባሕር ውስጥ የሠጠሙ የደቀ መዛሙርቶቿን መጻሕፍት ምንም ሳይሆኑ ማውጣት ችላለች፡፡ እናታችን በሁሉም ሀገር እየዞረች ቅዱሳት መካናትን ትሳለም ነበር፡፡ በደብረ ዳሞም ሄዳ ‹‹ሴቶች መውጣት አይችሉም›› ቢሏት በሀዘን ስታለቅስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በሥውር ወስዶ ከዓምባው ላይ አውጥቶ ከቤተ መቅደሱ አድርሷታል፣ አቡነ አረጋዊም ተገልጸውላት ባርከዋታል፡፡ በዚያም ሥጋ ወደሙን በእጃቸው ተቀብላለች፡፡ እናታችን ወደ ኢየሩሳሌምም ሄዳ ቅዱሳት መካናትን እየተሳለመች ለ7 ዓመታት ቆይታለች፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዓምደ ብርሃን እየመራት ተመልሳ ወደ ሀገራችን መጥታ በድጋሚ ከሱስንዮስ ጋር ተሟግታለች፡፡ ሙታንንም እያስነሳች እንዲመሰክሩለት ብታደርግም እርሱ ግን ከጥፋቱና ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም፡፡ ነገር ግን እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ የተለያዩ ተአምራትን በማድረግ መልእክቷንም በንስር አሞራ አድርጋ እየላከች ትመክረው ነበር፡፡ በአንድም ወቅት በሀገራችን የእህል መታጣት ሆነና ቅድስት እናታችን ዘወትር እንደምታደርገው የኪዳምሕረትን ዝክር ልታደርግ ብላ ዝክሩን የምታደርግበት እህል አጣች፡፡ ደናግል ልጆቿንም ጠርታ ትንሽ ዱቄት እንዲያመጡላት ነግራቸው አመጡላት፡፡ በዚያችም ትንሽ ዱቄት ላይ ጸሎት አድርጋ ከጨረሰች በኋላ ‹ወደ ቦታው መልሱት› አለቻቸው፡፡ በማግስቱም እንስራው ጋኑ ሁሉ በዱቄት ተሞልቶ አግኝተውታል፡፡ ቅድስት እናታችንና ልጆቿም የየካቲት ኪዳነ ምሕረትን በዓል በታላቅ ደስታ አክብረዋል፡፡

🔴 ስንክሳር #የካቲት_28 #ቅዱስ_ቴዎድሮስ_ዘሮም አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሃያ ስምንት በዚች ዕለት በነገሥታት መክሲሞስና መክስምያኖስ ዘመን ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሰማዕትነት አረፈ። እርሱም ከእስያ አውራጃ አስጢር ከሚባል አገር ነው። ይህንንም ቅዱስ በነገሥታት ዘንድ አማልክትን በማምለክ እርሱ እንደማይስማማ ወነጀሉት በዚያንም ጊዜ አስጠርተው ለአማልክት ለምን አትሰግድም አሉት እርሱም እኔ ክርስቲያን ነኝ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አላመልክም ብሎ መለሰላቸው። የበርብዮስጦስ ልጅ ንጉሡም ለአማልክቶቼ ብትገዛ በጭፍራዎቼና በመኳንንቶቼ ሁሉ ላይ አለቃ አድርጌ እሾምሃለሁ ብዙ ወርቅና ብር የከበሩ ልብሶችንም እሰጥሃለሁ አለው ቅዱስ ቴዎድሮስም ወርቅህና ብርህ ለጥፋት ይሁንህ እኔስ በንጉሤ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ባለጸጋና አለቃ ነኝ አለው። ንጉሡም ለአምላክህ ልጅ አለውን አለው የከበረ ቴዎድሮስም አዎን ከመለኮቱ ባሕርይ የተገኘ ከእርሱ ጋር ዓለምን የፈጠረ በእውነት ልጅ አለው ብሎ መለሰለት ንጉሡም አምላክህን ብናውቀው ልናገኘው እንችላለን አለው ቅዱስ ቴዎድሮስም ወደርሱ ከተመለስክ እንደ እኔ ጭፍራ ትሆናለህ የተወደደ መሥዋዕትም ያደርግሃል አለው። ንጉሡም ነገር አታብዛ ብዙ ገንዘብ እሰጥህ ዘንድ ለአማልክቶቼ መሥዋዕትን አቅርብ እንጂ አለው የከበረ ቴዎድሮስም ንጉሡን ረገመው ጣዖታቱንም ሰደበ በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ተቆጣ። ልብሱንም እንዲገፉት በትምህርቱም ከአመኑ አሕዛብ ጋር በጨለማ ቤት ያሥሩት ዘንድ አዘዘ። የከበረ ቴዎድሮስም ጸለየ በሌሊትም ወጣ ዕንጨቶችንም ሰብስቦ ጣዖቶችን ሁሉ አመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጠላቸው እንዳይሰሙ በአገልጋዮቻቸው ላይ እግዚአብሔር ከባድ እንቅልፍ አሳድሮባቸዋልና። ለንጉሡም በነገሩት ጊዜ አጽንቶ አሠረውና ልዩ ልዩ በሆነ በጽኑ ሥቃይ አብዝቶ ያሠቃየው ዘንድ ለመኰንኑ ሰጠው መኰንኑም እንዲህ አለው ለንጉሥ ለምን አትታዘዘም ለአማልክቶችስ ለምን አትሠዋም የከበረ ቴዎድሮስም እኔስ ለረከሱ አማልክት አልሠዋም ለከሀዲ ንጉሥም አልታዘዝም ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ከወንበሩም ላይ ተነሥቶ እንደ ነብር ተወርውሮ አንገቱን አነቀውና የከበረ ቴዎድሮስን በምድር ላይ ጥሎ ፊቱን ጸፋው በእግሮቹም ረገጠው እግዚአብሔርም ትዕግስቱን አይቶ የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ላከለት መኰንኑንም ገድሎ ከምድር ዐዘቅት አሠጠመው ለከበረ ቴዎድሮስም በእስያ ሀገር ውስጥ እየተዘዋወረ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት እንዲአስተምር መንፈሳዊ ፀዓዳ ፈረስን ሰጠው። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ የከበረ ቴዎድሮስን ከነፈረሱ እንዲይዙት በትምህርቱም የአመኑትን ሁሉ እንዲገድሉ መቶ ፈረሰኞች ወታደሮቹን ላከ። ከሴቶችና ከልጆች በቀር ስድስት ሺህ አርባ ስምንት ሰውን ገደሉ። ሊይዙትም ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ በደረሱ ጊዜ ፈረሱ በላያቸው ተወረወረ ከአፉም እሳትን አውጥቶ አመድ እስኪሆኑ አቃጠላቸው ነገር ግን ሌሎች አግኝተው ያዙትና ወደ ንጉሥ ወሰዱት እርሱም ወደ እሥር ቤት እንዲአስገቡት እንዳይበላና እንዳይጠጣም ደጃፎችን እንዲዘጉበት አዘዘ። ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና ቃል ኪዳን ሰጠው በዚያንም ጊዜ ከእሥር ቤት አውጥተው ዘቅዝቀው ሰቀሉት ደሙም እንደ ውኃ እስቲፈስ ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ገረፉት ደሙ የነካቸውም ብዙ በሽተኞች ዳኑ ተአምራቱንም ያዩና የሰሙ በጌታችን አመኑ በዚያችም ቀን መቶ አርባ ስምንት ሰዎች ተገደሉ። እሊህን የተገደሉትንም ሰማዕታት ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ከእርሱ ጋር ጨመሩአቸው በዚያንም ጊዜ ነፋስ ነፈሰ መብረቅና ነጐድጓድም ሆነ እሳቱንም አቀዝቅዞት የከበረ ቴዎድሮስ ምንም ሳይነካው ከእሳት ውስጥ ወጣ። ከዚህም በኋላ ንጉሡ የሚያደርግበትን በአጣ ጊዜ ኃምሣ አራት ልጥር የሚመዝን ልጓም አምጥተው አፉን እንዲለጒሙት እግሮቹንና እጆቹንም በችንካር ቸንክረው ለአንበሳ እንዲጥሉት አዘዘ። አንበሳውም ዕንባውን እያንጠባጠበ እንደ ሰው አለቀሰለት እንጂ ምንም አልነካውም። ጌታችንም ተገለጠለትና ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ዕድል ፈንታውን ከርሱ ጋር በመንግሥተ ሰማያት ያደርግ ዘንድ ቃል ኪዳንን ሰጠው። ከዚህም በኋላ የሁለት መቶ ሰው ሸክም ዕንጨት መቶ ልጥር ባሩድ መቶ ልጥር የዶሮማር መቶ ልጥር ነሐስ አመጡ ከማንደጃውም ጨምረው እጅግ እስከሚግል አነደዱት ጸሎቱንም ከፈጸመ በኋላ ቅዱስ ቴዎድሮስን ወደ ነደደው እሳት ወረወሩት ምስክርነቱንም ፈጸመ የመላእክት አለቆች ሚካኤልና ገብርኤል ነፍሱን ተቀበሉ በሦስት አክሊላትም አቀዳጁት ሥጋውንም አውሳብያ የተባለች የመኰንኑ ሚስት ወሰደች ዋጋው ብዙ በሆነ ሽቱም ገነዘችውና ወደ ገላትያ ወሰደችው በዕብነ በረድ ሣጥንም አድርጋ በዚያ ቀበረችው ቤተ ክርስቲያንም ሠራችለት ከሥጋውም ታላላቆች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጹ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲት) https://t.me/finotebirhan12

🔴 ስንክሳር #የካቲት_27 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሃያ ሰባት በዚች ቀን የአንፆኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አንስጣስዮስ አረፈ፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ዓምደ_ሥላሴ እረፍታቸው ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አንስጣስዮስ_ሊቅ የካቲት ሃያ ሰባት በዚች ቀን በታላቁ ንጉስ በቈስጠንጢኖስ ዘመን የከበረ አባት የአንፆኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በአለም የመላ አንስጣስዮስ አረፈ። የከበሩ አባቶችም በኒቅያ ከተማ የአንድነት ስብሰባ በአደረጉ ጊዜ በዚህ ጉባኤ ከተሰበሰቡት ሊቃውንት አንዱ እርሱ ነው በዚህም ጉባኤ ተስማምተው አርዮስን ከባልንጀሮቹ ጋር አውግዘው ለይተውታል ባልንጀሮቹም የቂሳርያ አውሳቢዮስ የኒቆምድያ አውሳቢዮስና አርናሲስ ናቸው። እነዚህም በ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ታውቀዋል። እንዚህ የከበሩ አባቶች ስርአትን ሰርተው ወደ የሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ እነዚህ ከኤጲስቆጶስነት ሹመት የተሻሩት ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄዱ መስለው ወጡ ወደ አንፆኪያም ከተማ ገብተው ለአንዲት አመንዝራ ሴት ዘንድ ተሰበሰቡ ብዙ ገንዘብም ሊሰጣት ቃል ገቡላት ወደ ቤተክርስቲያን እንድትገባ ይህ አባት ከእርሷ ጋር እንዳመነዘረ የወለደችውም ልጅ የእርሱ እንደሆነ በዚህ ቅዱስ አባት አንስጦስዮስ ላይ ለካህናቱና ለህዝቡ እንድትናገር አስተማሩዋት። ህዝቡም እንዲህ አሏት አንቺ ሀሰተኛ ነሽ በዚህ ቅዱስ አባትም ላይ ሀሰትን ተናግረሻል በከበረ ወንጌል ካልማልሽ በቀር ቃልሽን አንቀበልም አሏት። እርሷም ስለገንዘብ ፍቅር በሀሰት ማለች። ከዚህም በኃላ ለንጉስ ነግረው ከመንበረ ሲመቱ ወደ አጥራኪያ ደሴት አሳደዱት በስደትም ሳለ በርሷ አረፈ። ነገር ግን ለእነዚህ ከሀዲያን ወዮላቸው የእግዚአብሄርን ልጅ ከመለኮቱ ባህርይ ለይተው ፍጡር ነው ብለውታልና ይህንንም ንፁህ አባት ሰይጣን አባታቸው እንዳስተማራቸው ከአመንዝራ ጋር አንድ ሆነው በተንኮል ከመንበረ ሲመቱ አውጥተውታልና። እግዚአብሄር ግን ቸል አላለም ይህን አባት ከአሳደዱት በኃላ ያቺ አመንዝራ ሴት ጭንቅ በሆነ ደዌ ተይዛ ብዙ ተሰቃየች ለሞትም ተቃረበች ያን ጊዜም ይህ ሁሉ የደረሰባት በከበረ ወንጌል በሀሰት ስለማለች እንድሆነ ተገነዘበች። በአንፆኪያም ሰዎች ሁሉ ፊት በደሏን አመነች እንዲህም አለቻቸው፦ ይህ ቅዱስ አንስጣስዮስ ከዝሙት ንፁህ ነው እነዚያ ከሀዲያን ብዙ ገንዘብ ሰጥተውኝ በእርሱ ላይ ሀሰትን እንድናገር በከበረ ወንጌልም በሀሰት እንድምል አደረጉኝ እንጂ። የአንፆኪያ አገር ሰዎችም ኃጢአቷን ማመኗን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ ካህናቱም በፀሎትና በቅዳሴ ጊዜ ስሙን የሚያነሱ ሆኑ ዩሀንስ አፈወርቅም አመሰገነው በመታሰቢያውም ቀን ስለ ውለታው የውዳሴ ድርሳን ጽፎለታል:: ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ጻድቁ_አቡነ_ዓምደ_ሥላሴ ዳግመኛም በዚህች ቀን አቡነ ዓምደ ሥላሴ እረፍታቸው ነው፡፡ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ሲሆን በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበሩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ የነበሩ ገዳማዊ መነኩሴ ናቸው፡፡ ጻድቁ ማኅበረ ሥላሴን ያቀኑ ታላቅ አባት ሲሆኑ በተለይም አንድ የሚታወቁበት ትልቅ ታሪክ አላቸው፡፡ እርሱም ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊካውያን ደግፈው 8ሺህ የሀገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን ባሳረዱ ጊዜ ንጉሡ ወዲያው ‹‹ኦርቶዶክስ ይርከስ ካቶሊክ ይንገስ›› ብሎ ያወጀበት ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ፡፡ እንደ አርዮስም ሆዱ አብጦ አንጀቱ ተልቶ ሊሞት ባለ ሰዓት አቡነ ዓምደ ሥላሴ አዘዞ ድረስ ሄደው ‹‹ፋሲል ይንገሥ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ትመለስ የሱስንዮስም ምላስ ይመለስ›› በማለት ተጎልጉሎ የወጣውን ምላሱን በመስቀላቸው ቢባርኩት ምላሱ ተመልሶለታል፡፡ ዐፄ ሱስንዮስ ግን ለካደበት ክህደት ቅጣቱ ነውና በመቅሰፍቱ ሳይድን በዚያው ታሞ ማቆ ማቆ ክፉ አሟሟት ሞቷል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የዐፄ ፋሲልን ሹመትና ሃይማኖትን በአዋጅ አጽንተው ተመልሰው ወደ ገዳማቸው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ገብተዋል፡፡ ዐፄ ፋሲልንም የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ግዛቱን ከሱዳን እስከ ጣቁሳ ድረስ እንዲሆን በአዋጅ ወስነው ሰጥተውት ነበር ነገር ግን ላይጠቀምበትና ላይጸና ነገር የደርግ መንግሥት የገዳሙን ሥርዓት ከማፍረሱም በላይ ርስት ጉልቱን ነጥቆ ወሰደበት፡፡ በደርቡሾች ወረራ ጊዜ እንግሊዞች አጋጣሚውን ተጠቅመው የአቡነ ዓምደ ሥላሴን ቅዱስ ገድል ዘርፈው ወስደውታል፡፡ ዛሬ በእንግሊዝ ሀገር ገድለ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ይገኛል፡፡ ጻድቁ የካቲት 27 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸው በዚያው በመሠረቱት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም በክብር ተቀምጧል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡ (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲተት እና #ከገድላት_አንደበት)

እደምን ዋላችሁ ነገ የካቲት 27በ10ሰአት ላይ የሰኔ ሚካኤል አጫብር ስለሚጀመር ሁላችንም ተሟልተን እንገኝ አዲስ ቃለ እግዚአብሔር ስለሆነ አስጠኚውም ስለሚመጣ በሰአቱ እንገኝ ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን።

#ቅድስት ቅድስት ማለት ‹የተለየች፣ የነጻች፣ የከበረች› ማለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ጾም የጀመረባት፣ ልዩ፤ የተቀደሰች፤ የከበረች፤ ልዩ፣ ንጹሕ፣ ክቡር በሚኾን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጾመች
#ቅድስት ቅድስት ማለት ‹የተለየች፣ የነጻች፣ የከበረች› ማለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ጾም የጀመረባት፣ ልዩ፤ የተቀደሰች፤ የከበረች፤ ልዩ፣ ንጹሕ፣ ክቡር በሚኾን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጾመች መኾኗን ያመላክታል፡፡ ይህች ጾም በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አራት የተገለጠችው የጌታችን ጾም ስትኾን፣ ስያሜዋና የዕለቷ የምስጋና ሥርዓትም የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ አምላካችን በገዳመ ቆሮንቶስ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት በጾመበት ጊዜያት እነዚህ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ ድል አድርጓል፡፡ ሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ የሚባሉትም፡- ትዕቢት፣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ናቸው፡፡ በእነዚህ ሦስት ኃጢአቶች ጌታችን በዲያሎስ በተፈተነ ጊዜ በትዕቢት ቢመጣበት በትሕትና፤ በስስት ቢመጣበት በትዕግሥት፤ በፍቅረ ንዋይ ቢመጣባት በጸሊዓ ንዋይ ጌታችን ዲያሎስን ድል አድርጎታል፡፡ ለእኛም እነዚህን ድል ለማድረግ የምንችልበትን ጥበብ – ጾምን ገልጦልናል ትዕቢት ያልተሰጠንን መሻት፣ ስስት አልጠግብ ባይነት ስግብግብ መኾን፣ ፍቅረ ንዋይ ለገንዘብ ሲሉ ፈጣሪን መካድ ነው፡፡ አንደ ክርስቲያን ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ ድል ካደረገ ሌሎችን ኃጣውእ በቀላሉ ድል ማድረግ ይቻለዋል፡፡

🔴 ስንክሳር #የካቲት_26 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት #ነቢይ_ሆሴዕ አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_ሳዶቅ በሰማእትነት አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ሆሴዕ_ነቢይ የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት ዖዝያ ይባል የነበረ እውነተኛ ነቢይ ሆሴእ አረፈ። ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገስታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህመ ዖዝያን ኢዮአታም አካዝ ህዝቅያስ ናቸው። በትንቢቱም ድንቆች ስራዎችን ተናገረ የእስራኤልንም ልጆች ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቁጣውን ከእርሳቸው እንደማይመልስ አስረዳቸው። እንዲህም አለ የእስራኤል ልጆች ቁጥራቸው እንደማይሰፈርና እንደማይቁጠር የባህር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም አለ። ስለ አህዛብም በእግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኞል። ዳግመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በከበረ ደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሳኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ።እሱ በመከራ ገርፎ ይድነናል እርሱም በመከራ አቁስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው ። በሶስትኛውም ቀን ድነን በሱ ፊት እንነሳለን እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ስልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነው ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ሳዶቅ በዚህችም እለት የከበሩ ሳዶቅና ከእርሱ ጋር የሆኑ ሁለት ሺህ ስምንት ሰዎች በሰማእትነት አረፉ። ይህንንም የከበረ ሳዶቅን ለፀሀይ ይሰግድ ዘንድ የፋርስ ንጉስ ብርህም ፈለገው ቅዱሱም ለፈጣሪዋ እንጂ ለዚች ለምትታይ ፀሀይ ልሰግድ ከእናቴ ማህፀን አልወጣሁም ብሎ መለሰለት። ብርህም ንጉስም መልሶ ለዚች ፀሀይ አምላክ አላትን አለው ቅዱስ ሳዶቅም አለሙን ሁሉ የፈጠረ ክርስቶስ አምላክ ነው አለው ።ንጉሱም የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የከበረ ሳዶቅም ቁሞ ወደ እግዚአብሄር ፀለየ ከዚህም በኃላ ራሱን ዘንበል አድርጎ ቆረጡት። ያን ጊዜ ከሰማይ ብርሀን በላዩ ወረደ ከዚያ ያሉትም ሁሉ አይተው እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ የምናምን ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ ንጉሱም ሁሉንም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማእትነት አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሁለት ሺህ ስምንት ነፍስ ናቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡ (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲት) https://t.me/finotebirhan12

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መጋቢት ፬ (4) ቀን ፲ወ፬ (2014) ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ቅዱ
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መጋቢት ፬ (4) ቀን ፲ወ፬ (2014) ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ። የካቲት ፳፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፬ ዓ.ም የቅዱስ አባታችን በረከት ይደርብን።

🌑#ዜና_እረፍት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰ
🌑#ዜና_እረፍት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም ይሆናል። የቅዱስ አባታችን በረከት ይደርብን። የካቲት ፳፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፬ ዓ.ም

🔴 ስንክሳር #የካቲት_25 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሃያ አምስት በዚች ቀን የከበሩ #ቅዱስ_አውሳንዮስ፣ #ቅዱስ_ፊልሞና ስሟ #ቅድስት_ሉቅያ ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ፣ የከበረ ሐዲስ #ቅዱስ_እንጦኒ (ረውሕ) በሰማዕትነት ሞተ፣ ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ የሆነ የከበረ አባት #ቅዱስ_አቡፋና አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞና_እና_ቅድስት_ሉቅያ_ድንግል የካቲት ሃያ አምስት በዚች ቀን የከበሩ አውሳንዮስና ፊልሞና ስሟ ሉቅያ የሚባል አንዲት ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ። እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ ሀገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተሰብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ። ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ። እሊህንም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው በቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በደንጊይ ወገሩት። የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖታቸው መታሰቢያ ተጽፎአል። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #የከበረ_ሐዲስ_እንጦኒ በዚችም ዕለት የከበረ ሐዲስ እንጦኒ በሰማዕትነት ሞተ ይህም ረውሕ የሚባል ነው። ይህም ከከበሩ ዐረቦች ወገን የቆሮስ ሰው የሆነ ብዙ ገንዘብ ያለው ነው በሰማዕታት አለቃ በቴዎድሮስ ገዳም አጠገብ በወንዝ ዳርቻ የሚኖር ነው ይህም ጐልማሳ አብያተ ክርስቲያናትን የሚቃወም ሁኖ ቅዱስ ቍርባንን በመስረቅ ኀብስቱን ይበላዋል የከበረ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ይጠጣል የመሠዊያውንም ልብስ ገፎ በእሳት ያቃጥለዋል በክርስቲያን ሃይማኖትም ላይ ይዘብታል። መኖሪያ ቤቱ ከከፍታ ቦታ ላይ ስለ ሆነ ካህናት ሲያገለግሉ ይታዩት ነበር። በአንዲትም ዕለት በቅዳሴ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ተከፍቶ አየ በፈረስም ተቀምጦ መጣ የቅዱስ ቴዎድሮስንም ሥዕል ተመልክቶ በፍላፃዎች ወጋው ። አንዲቱም ፍላፃ ተመልሳ መሐል እጁን ነደፈችው በጭንቅም ከእጁ ላይ መዘዛት ይህንንም ለማንም አልነገረም። በሌላዪቱም ዕለት በወንበሩ ላይ ተቀምጦ ሳለ መሥዋዕትን ተሸክመው ወደ መቅደስ ሲገቡ ካህናትን አያቸው በጻሕሉም ውስጥ ነጭ በግ ተኝቶ ከበላዩ ነጭ ርግብ ሲጋርደው በቅዳሴውም ፍጻሜ ያ በግ በየመለያያው የተከፋፈለ ሆኖ ካህናቱም ከተከፋፈለው ሥጋውን ሲቀበሉ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ሲቀበሉ አየ እጅግም አደነቀ። በልቡም የክርስቲያን ሃይማኖት እጅግ ድንቅ ነው በእውነትም የከበረ ክቡር ነው አለ። ዳግመኛም ያ በግ ተመልሶ እንደ ቀድሞው ኑሮው ሕያው ሁኖ አየ ከዚህም በኋላ ከመቀመጫው ወርዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ሔዶ ያየውን ሁሉ ለካህናቱ ነገራቸው እነርሱም ሰምተው ስለዚህ ድንቅ ሥራ ደስ አላቸው። በዚያችም ሌሊት ተግቶ ሲጸልይ ሊቅ ቴዎድሮስ ተገለጠለት እርሱም በፈረሱ ላይ ተቀምጦ ነበር እንዲህም አለው እነሆ በእኔ ላይ ሥዕሌን እስከ ወጋህ ድረስ ክፉ ሠራህ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሥጋ ላይም ዘበትክ አሁንም ከክህደትህ ተመልሰህ በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አለው ይህንም ብሎ ከእርሱ ተሠወረ። በማግሥቱም በፈረሱ ላይ ሁኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱም ገብቶ ከእርሱ የሆነውን ሁሉ ነገረው ሊቀ ጳጳሳቱም ሰምቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው እርሱንም በሕዝብ ፊት አጠምቅህ ዘንድ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ሒድ ጌታችን ክርስቶስም የሚያጠምቅህን ይሰጥሃል አለው። እርሱም ሰምቶ ወደ ዮርዳኖስ ሔዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገባ የሌሊቱም እኩሌታ ሲሆን የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ነጭ ሐር ግምጃ ለብሳ ተገለጠችለት ከእርሷም ጋር በንጹሕ ልብስ የተሸለመች ሴት ነበረች በእጅዋም ይዛ አነሳችውና አትዘን እኔ ካንተ ጋር እኖራለሁና አለችው። ሲነጋም ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ በሔደ ጊዜ ሁለት ገዳማውያን መነኰሳትን አገኛቸው እነርሱም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቁት። ስሙንም እንጦንስ ብለው ሰየሙት የምንኲስና ልብስ አሰኬማንም አልብሰው በሰላም አሰናበቱት ወደ ደማስቆም ሔዶ ወደ ቤቱ ገባ። ባልንጀሮቹና ወገኖቹም በአዩት ጊዜ የለበሰከው ምንድን ነው አሉት እኔ ክርስቲያን ነኝ አላቸው በዚያንም ጊዜ ይዘው በሜዳ ውስጥ እየጐተቱ ወደ መኰንኑ እስኪያደርሱት ይደበድቡት ነበር። መኰንኑም ወደ እሥር ቤት እንዲጨምሩት አዘዘ በታላቅ ሥቃይም ዐሥራ ሰባት ሌሊት በዚያ ኖረ እነሆ በላዩ ብርሃን ወረደ እንዲህም የሚል ቃል ሰማ እንጦንዮስ ሆይ አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና አትፍራ ብርሃንን የለበሱ ሁለት አረጋውያንም መጥተው በራሱ ላይ የብርሃን አክሊልን አኖሩ በነጋ ጊዜም ወደ አደባባይ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና በዕንጨት ላይ ሰቀሉት። በሌሊትም በላዩ ብርሃን ወረደ ጠባቆችም አይተው ከዕንጨት ላይ አወረዱት በጤግሮስም አቅራቢያ ቀበሩት ከመቃብሩም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡ (#ስንክሳር_ዘወርኀ_የካቲት) https://t.me/finotebirhan12