ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 640
المشتركون
-224 ساعات
+87 أيام
+5630 أيام
أرشيف المشاركات
የሀዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤት አባላችን የሆነችው የገነት ፋንቱ እናት ስላረፉ የቻላችሁ መኖሪያ ቤታቸው በመሔድ እንድታጽናኗው ።    አድራሻቸው መንዲዳ ፊት ለፊት 47 ቀበሌ

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_16 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ ስድስት በዚች ቀን የእስራኤል መሳፍንት አንዱ #ቅዱስ_ጌዴዎን_ኃያል ዐረፈ፣ #የሙሴ_እኅት_ማርያም መታሰቢያዋ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጌዴዎን_ኃያል ታኅሣሥ ዐስራ ስድስት በዚች ቀን የእስራኤል መሳፍንት አንዱ ጌዴዎን ዐረፈ፡፡ ይህም ከነገደ ምናሴ የሆነ የአባቱ ስም ዮአስ ይባላል ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና ለእስራኤል ሾመው። የጠዖታትንም መሠዊያ እነሰዲያፈርስ ዛፎችንም እንዲቆርጥ አዘዘው መሠዊያም ለእግዚአብሔር ሠርቶ በዚያ በሰበረው ዕንጨት እንዲሠዋ አዘዘው ሁሉንም እንዳዘዘው አደረገ። እግዚአብሔር የላከው መልአክም ተመለከተው "እስራኤልን ከምድያም እጅ ታድናቸዋለህና ከሠራዊትህ ጋር ሒድ እነሆ ላክሁህ" አለው። ጌዴዎንም "አድናቸዋለሁ እንዳልክ እስራኤልን በእጄ ታድናቸው እንደሆነ እነሆ እኔ በአደባባይ የተባዘተ ፀምርን እዘረጋለሁ ጠል በምድር ላይ ሳይወርድ በፀምሩ ላይ ብቻ ቢወርድ አድናቸዋለሁ እንዳል እስራኤልን በእጄ እንድታድ ናቸው ያን ጊዜ አውቃለሁ" አለ እንዳለውም ሆነ። ጌዴዎንም በማግሥቱ ማልዶ ሒዶ ያንን ጨመቀው ከዚያ ፀምር አንድ መንቀል ሙሉ ውኃ ወጣ። ጌዴዎን እግዚአብሔርን "በቊጣህ አትቆጣኝ ዳግመኛ አንድ ጊዜ ልናገር በፀምር ላይ ብቻ ሳይወርድ ጠል በምድር ሁሉ ላይ ይውረድ" አለው። እግዚአብሔርም በዚያች ሌሊት እንዳለው አደረገ። ፀምሩ ብቻ ደረቅ ሁኖ ጠል በምድር ሁሉ ላይ ወረደ። ጌዴዎንንም የእግዚአብሔር መንፈስ ረድኤት አጸናው ነጋሪትንም መታ አብያዜርም በኋላው ሁኖ ደነፋ ወደ ነገደ ምናሴር፣ ወደ ነገደ ዛብሎን፣ ወደ ነገደ ንፍታሌምም መልክተኞችን ላከ ወጥተውም ተቀበሏቸው። ጌዴዎንም ከርሱ ጋር ያሉ ወገኖቹም ሁሉ ሔዱ አሮኤድ በሚባል አገርም ሰፈሩ የመሰድያምና የአማሌቅ ሠራዊትም በእንበሬም ቆላ መሠዊያ ቀኝ ሰፈሩ። እግዚአብሔርም ጌዴዎንን "እጃችን አዳነችን ብለው እንዳመኩብኝ የምድያምን ሰዎች በእጃቸው መጣል እንደማልችል ካንተ ጋር ያሉ ሕዝብ ብዙ ናቸው" እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው "ከእናንተ የሚፈራ የመመደነግጥ ሰው  ከሕዝቡ ተለይቶ ይመለስ" ብለህ ለሕዝቡ ንገራቸው። ሕዝቡም ከገለዓድ ተመለሱ ከሕዝቡም ሁለት እልፍ ከሁለት ሽህ ተመልሰው እልፍ ሰዎች ቀሩ። እግዚአብሔር ጌዴዎንን "ገና ብዙ ሕዝብ አሉ ወደ ውኃ አውርደህ በዚያ ፈትናቸው እኔ ይሒዱ የምልህ ሰዎች እነርሳቸው ካንተ ጋር ይሒዱ" አለው ሕዝቡንም ወደ ውኃ አወረዳቸው። እግዚአብሔር ጌዴዎንን "ውሻ በምላሱ ጠለፍ ጠለፍ አድርጎ እንዲጠጣ ከውኃው ጠለፍ ጠለፍ አድርጎ የሚጠጣውን ሁሉ ለብቻው አቁመው ውኃን ይጠጣ ዘንድ በጉልበቱ የተንበረከከውንም ሁሉ ለብቻው አቁመው" አለው። በምላሳቸው ጠለፍ ጠለፍ አድርገው የጠጡ ሰዎች ቊጥራቸው ሦስት መቶ ሆነ የቀሩት ሕዝብ ግን ውኃን ይጠጡ ዘንድ በጉልበታቸው ተንበረከኩ። እግዚአብሔርም ጌዴዎንን "እንደዚህ በእጃቸው ውኃን በጠጡት በእነዚህ ሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ የምድያምን ሰዎች ወደ ቤታቸው ይመለሱ" አለው። በዚያችም ሌሊት እሊህ ሦስት መቶ ሰዎች መለከትን ነፉ "ይህ የእግዚአብሔር ኃይልና የጌዴዎን ጦር ነው" ብለው ጮኹ። የምድያምም ሰዎች የመለከቱን ድምፅ በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔር በልባቸው ፍርሀትን አሳድሮባቸው ደንግጠው ሸሹ እግዚአብሔርም ያንዱን ሰይፍ ወዳንዱ ወደ ጓደኛው መለሰ በሠራዊቶቻቸው ሁሉ እርስበርስ መተላለቅ ሆነ መኳንንቶቻቸውን ኄሬብንና ዜብን ነገሥቶቻቸው ዛብሄልንና ስልማናንም ገደሏቸው ከምድያምም ሠራዊት ፈረሰኞችና ጦረኞችን አንድ መቶ ሁለት ሽህ ገደሉ። ከዚህም በኋላ የምድያም ሰዎች በእስራኤል ፊት ተዋረዱ ዳግመኛም ራሳቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም በጌዴዎንም ዘመን ምድር አርባ ዘመን ዐረፈች። ከዚህም በኋላ በዚች ቀን ታኅሣሥ16 በሰላም በፍቅር ዐረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ማርያም_እህተ_ሙሴ ዳግመኛም በዚህች ቀን የሙሴ እኅት ማርያም መታሰቢያዋ ነው፡፡ ይህች እናት የሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴና የሊቀ ካህናቱ ቅዱስ አሮን ትልቅ እህት ስትሆን ወላጆቿ እንበረምና ዮካብድ ይባላሉ:: እሥራኤል ከግብጽ ባርነት እንዲወጡ የእርሷን ያህል አስተዋጽኦ ያደረገች ሴት የለችም:: ከመነሻውም ቅዱስ ሙሴን የጠበቀች: በሕግ በሥርዓት እንዲያድግ ከእናቱ ጋር ያገናኘች: ወገኖቿ ከግብጽ ሲወጡም ሴቶችን የመራች እናት ናት:: ወንድሞቿን ሙሴንና አሮንንም ታገለገላቸው ነበር:: በተለይ እግዚአብሔር ባሕረ ኤርትራን የብስ ሲያደርጋት ከበሮን አንስታ "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር" ብላ ፈጣሪዋን አመስግናለች:: (ዘጸ. 15:20) አንድ ጊዜም "ኢትዮዽያዊቷን ሲፓራን ለምን አገባህ" በሚል ስለ ተናገረችው እግዚአብሔር ተቆጥቶ በለምጽ መቷታል:: (ዘኁ. 12:1) ቆይቶም በቅዱሱ ምልጃ ምሯታል:: ማርያም በመንገድ ሳሉ: ወደ ርስት ሳይደርሱ ዐርፋ ተቀብራለች:: (ዘኁ. 20:1) ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

በዚህች እለት በአንዲት ምሰሶ ላይ ወጥተው ከዚያ ሳይወርዱ በላይዋ ላይ ሆነው ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደሉ 45 ዓመት የኖሩት አቡነ ሉቃስ ዘዓምድ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይኸውም ሀገሩ ፋርስ ሲሆን በመቶ የንጉሡ ጭፍራ ላይ መኰንን ሆኖ ተሹሞ ነበር፡፡ በኋላም ሹመቱን ትቶ ገዳም ገብቶ መነኮሰ፡፡ በምሥራቅ ካሉ ገዳማት ውስጥ በአንዱ ገብቶ ብዙ ዘመን ሲጋደል ኖረ፡፡ ልብሱንም የብረት ልብስ በማድረግ እስከ 6 ቀን የሚጾም ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ ከዓምድ ላይ ወጥቶ በዚያ ላይ ሦስት ዓመት ለጸሎት ቆመ፡፡ የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከዚያ ዓምድ ላይ እንዲወርድ ነግሮት በብርሃን መስቀል እየመራው ወስዶ አንድ ገዳም አደረሰው፡፡ በዚያም ብዙ ተአምራት እያደረገ ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ሉቃስ አርምሞ ያዘ፡፡ ከቶ እንዳይናገርም በአፉ ውስጥ ድንጋይ ነክሶ ያዘ፡፡ አሁንም መልአኩ ወደ ቍስጥንጥንያ ዳርቻ ቦታ ይዞት እየመራ ወስዶት በዚያም አንዲት ምሰሶ ላይ ወጥቶ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ በላይዋ ላይ 45 ዓመት ኖረ፡፡ በዚያም አስደናቂ ተአምራትን እያደረገ ብዙዎችን በመፈወስና ወንጌልን በማስተማር ብዙ ደከመ፡፡ ታኅሣሥ 15 ቀን ካረፈ በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱና ካህናቱ መጥተው በክብር ወደ ቍስጥንጥንያ ከተማ ወሰዱት፡፡ በዚህም ጊዜ በድውያን ላይ ታላቅ ፈውስ ሆነ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞    #የእኔ_ቢጤው_አባ_ቆራይ በዚህች እለት ጻዱቁ አባ ቆራይ ዕረፍታቸው ነው፡፡ እጅና እግር የሌላቸውና የእኔ ቢጤ የነበሩት ጽድቃቸውን ማንም ሳያውቅባቸው የኖሩት አባ ቆራይ ጻድቅ መሆናቸው ካረፉ በኋላ ነው የታወቀው፡፡ ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ ቅዱሱ በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት በትግራይ ተንቤን አውራጃ አዲ ራእሶት-የራሶች (የታላላቅ ሰዎች አገር) በሚባለው ቦታ የእግርና የእጅ ጣቶች የሌሏቸው አባ ቆራይ ወንበር በምትመስል ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ተገለጡ፡፡ አንድ የአካባቢው ሰው በመንገድ ሲያልፍ አባ ቆራይ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ጸሎት ሲያደርጉ አያቸውና በሁኔታው ተገርሞ ወደ እርሳቸው ጠጋ ብሎ ስማቸውንና የመጡበትን አገር ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም "ስሜ አባ ቆራይ ይባላል፣ አገር ግን የለኝም" አሉት፡፡ እርሱም "እባክዎን ወደ መንደር እንሂድና የጸሎትና ቤት ሠርተንልዎት በዚያ ይቀመጡ" አላቸው፡፡ አባ ቆራይ ግን "ማረፊያዬ ይህቺ ናት፣ ከዚህች ሥፍራ አልነሣም" አሉት፡፡ አባ ቆራይም በዚያው እንደተቀመጡ ዝናቸው በሁሉ ዘንድ ተሰማና ሰዎች መጥተው በተቀመጡበት ድንጋይ ዙሪያ ጎጆ ቀለሱላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ መንደርተኞቹ በየተራ በምግብ ሊረዷቸው ዕጣ ተጣጥለው ወደየቤታቸወ ሄዱ፡፡ በመጀመሪያ ተራ የደረሰው ሰው ከአንድ ሰዓት በኋላ ምግብ ይዞ ቢመለስ የአባ ቆራይ ጎጆ በብርሃን ተሞልታ አገኘ፡፡ ወደ ጎጆዋም ሲጠጋ ነበልባሉ እየፈጀው አላስቀርበው አለ፡፡ እርሱም በድንጋጤ ወደ መንደሩ ተመልሶ ለአካባቢው ሰው ነግሮ ሁሉም ተሰብስበው መጡ፡፡ መንደርተኛውም ካህናትን ይዘው ብዙ የምሕላ ጸሎትና እግዚኦታ ካደረሱ በኋላ እግዚአብሔር ወደ ጎጆዋ እንዲገቡ ፈቀደላቸውና ገቡ፡፡ ነገር ግን አባ ቆራይን በሕይወት አላገኟቸውም፡፡ አስክሬናቸውን ብርሃን ከቦት አገኙት፡፡ ከአስክሬናቸው አጠገብ "የአባ ቆራይን አስክሬን ከዚህች ጎጆ ውስጥ እንድትቀብሩት፤ ወደ ሌላ ቦታ ወይም ቤተ ክርስቲያን ወስደን እንቀብራለን ብላችሁ እንዳታስቡ፡፡ ነገሩን በድፍረት ብትፈጽሙት በሀገሩ ላይ እግዚአብሔርን ቁጣ ታመጣላችሁ" የሚል ትእዛዝ በብራና ተጽፎ ተገኘ፡፡ በዚሁ ትእዛዝ መሠረት የአሀሩ ሕዝብ ተሰብስቦ አባ ቆራይን ታኅሣሥ 15 ቀን እዚያው ቀበሯቸው፡፡ ከጥቂት ዘመናት በኋላ ባልና ሚስት የሆኑ ሰዎች መቆምም ሆነ መራመድ የማይችል ድውይ ልጃቸውን ይዘው ወደ ጸበል ሲሄዱ መሸባቸውና በአካባቢው ማደሪያ ሲፈልጉ የአባ ቆራይ ጎጆ ክፍት ሆኖ ታያቸውና ልጃቸውን ይዘው ሄደው ገቡ፡፡ ድውይ ልጃቸውን በአባ ቆራይ መቃብር ላይ ቢያስተኙት የኤልሳዕን አጥንት እንደነካውና ፈጥኖ እንደተነሣው ሙት ይህ ድውይ ልጅም በአባ ቆራይ መቃብር ላይ እንዳረፈ ወዲያው አፈፍ ብሎ በመነሣት እንደ እንቦሳ ጥጃ መዝለል ጀመረ፡፡ ወላጆቹም እልልታቸውን አቀለጡት፡፡ ወላጆቹም በነጋ ጊዜ ወደ መንደርተኛው ሄደው የተደረገላቸውን ተአምር ተናገሩ፡፡ ከዚያም ጊዜ ጀምሮ የአባ ቆራይ በዓል በአካባቢውና አጎራባች ቦታዎች ሁሉ ዘንድ መከበር ጀመረ፡፡ የዕረፍታቸውም በዓል ታኅሣሥ 15 ቀን ሆነ፡፡ አባ ቆራይ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ለይተው እንደ ቅዱስ አልዓዛር (ሉቃ. 16፡19-35) ለዚህ ዓለም ውዳቂ መስለው ለታላቅ ክብር የበቁ ጻድቅ አባት ናቸው፡፡ ዛሬም ልብሳቸውንና አካላቸውን ብቻ እያየን የምንንቃቸው ሰዎች እንደ አባ ቆራይ ያሉ ቅዱሳን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከልዑል እግዚአብሔር በቀር ማንም ማንንም የሚያውቅ የለም፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_15 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ አምስት በዚህች እለት #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘአርማንያ ዕረፍታቸው ነው፣ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ #አቡነ_ኤዎስጣቴዎስ_ከፋሌ_ባህር ልደታቸው ነው፣ #የቅዱስ_አቡነ_ሉቃስ_ዘዓምድ ዕረፍታቸው ነው፣ የእኔ ቢጤ የነበሩትና ጽድቃቸውን ማንም ሳያውቅባቸው የኖሩት #የአባ_ቆራይ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘአርማንያ ታኅሣሥ ዐስራ አምስት በዚህች እለት የአርማንያ አገር ኤጲስቆጶስ አባ ጎርጎርዮስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ የንጉሡን ትእዛዝ ስመተላለፋና ለአማልክት አልሠዋም ስላለ የአርማንያ ንጉሥ ድርጣድስ አሠቃይቶ ጥልቅ ወደ ሆነ ደረቅ ጒድጓድ ውስጥ ጨመረው በዚያ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበር አንዲቷን አሮጊትም ሁል ጊዜ ምግቡን እነሰድታመጣለት አደረጋት ሕያው እንደሆነም የሚያውቅ የለም። ንጉሥ ድርጣድስም ቅድስት አርሴማን ለማግባት ሽቶ ነበርና በእርሷ ምክንያት ደናግሎችን ገደላቸው። የእሊህ ደናግልም ሥጋቸው በተራራ ላይ እንደ ወደቀ ነበር ንጉሡም ስለ ገደላቸው ደናግል ይልቁንም ውበቷንና ደም ግባቷን እያሰበ ስለ ቅድስት አርሴማ አብዝቶ የሚያዝንና የሚጸጸት ሆነ። ከዚህም በኋላ ወገኖቹ ለመኑት እንዲህም አሉት አውሬ ታድን ዘንድ በፈረስ ተቀመጥና ወደ ዱር እንውጣ የልብህም ኀዘን ይወገድልሃል። በዚያንም ጊዜ አውሬ ለማደን በፈረሱ ተቀምጦ ወደ ዱር ወጣ። የሚነክስ ሆነ ወገኖቹንም ነከሳቸው እግዚአብሔርም መልኩን ለውጦ እንደ እሪያ አደረገው ያገኘውን ሁሉ የሚነክሰ ሆነ። እንዲሁም ከቤተ መንግሥት ሰዎች በብዙዎቹ ላይ ሰይጣን አደረባቸው ታላቅ ድንጋጤም ሆነ ይህም ሁሉ የሆነ ስለ ቅዱሳት ደናግልና ስለ ቅድስት አርሴማ ነው። የንጉሡ እኅት ግን "ጎርጎርዮስን ከጒድጓድ ካላስወጣችሁት ድኅነት የላችሁም" የሚላት ሰው በራእይ አየች ይህንንም ለወገኖቿ ነገረች እርሱ አስቀድሞ በጒድጓድ ውስጥ የሞተ ስለ መሳላቸው ደነገጡ። በዚያንም ጊዜ ወደ ጒድጓድ ሔዱ በሕይወት እንዳለም ያወቁ ዘንድ ወደ ጒድጓዱ ውስጥ ገመዶችን አወረዱና ገመዶቹን እንዲይዝ ወደርሱ ጮኹ እርሱም ገመዶችን ያዘ ስበው አወጡት አጥበውም ንጹሕ ልብስን አለበሱት በበቅሎም አስቀምጠው ወደ ቤተ መንግሥት አደረሱት። በዚያንም ጊዜ በሰማዕትነት ስለሞቱ ደናግል ሥጋ ጠየቀ እነርሱም የደናግሉ ሥጋቸው ወዳለበት መርተው አደረሱት የዱር አራዊትና አዕዋፍ ሳይበሏቸው በደኅና አገኛቸው ያማሩ ቦታዎችን አዘጋጅተው በውስጣቸው ያኖሩዋቸው ዘንድ አዘዘ እንዳዘዛቸውም አደረጉ። ከዚህም በኋላ ንጉሡን ያድነው ዘንድ ሕዝቡ ለመኑት ንጉሡም ወዳለበት ዱር አደረሱት እርሱም "ከክፉ ሥራህ ትመለሳለህን? ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታምናለህን?" አለው። እሪያ የሆነውም ንጉሥ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አድርጎ አመለከተ በዚያንም ጊዜ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ጸለየ ከንጉሡም ላይ በእሪያ አምሳል ሰይጣንን አስወጣው። የንጉሡም አእምሮውና መልኩ እንደ ቀድሞው ተመለሰለት ነገር ግን ዳግመኛ እንዳይታበይ ከእግሩ ላይ የእሪያ ጥፍር አስቀረ ፈጣሪውም ተገዢ ይሆን ዘንድ  ዳግመኛም የቤተ መንግሥት ሰዎችን ሁሉንም አዳናቸው ከላያቸውም አጋንትን አስወጥቶ ሰደዳቸው። ከዚህም በኋላ የአርማንያን ሰዎች ሁሉንም ሰበሰባቸውና ሥርዓትን ሠራላቸው ስምንት ቀንም እንዲጾሙ አዘዛቸው እንዳዘዛቸውም አደረጉ የእግዚአብሔርንም ሕግ እያስተማራቸው ኖረ። ዳግመኛም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆኑን አስተማራቸው ታላቆችም ታናናሾችም ትምህርቱን ተቀበሉት ለአርማንያ ሰዎች ሃይማኖትን የመቀበላቸው ምክንያት ይህ ነው። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቃቸው ዘንድ ቅዱስ ጎርጎርዮስን ለመኑት እርሱም "እኔ ካህን ስለአልሆንኩ አይገባኝም ነገር ግን የሚያጠምቃችሁን ካህን ይልክላችሁ ዘንድ ወደሮሜ ሊቀ ጳጳሳት መልክተኞችን ላኩ" አላቸው። በዚያንም ጊዜ ከርሱ ጋር ወደ ንጉሥ አኖሬዎስና ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ መልክተኞችን ልከው የአርማንያ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሱ አስረዱአቸው ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱም ሰምተው ደስ አላቸው ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ለአርማንያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ይሆን ዘንድ ቅዱስ ጎርጎርዮስን ሾመው ወደ አርማንያን ንጉሥ ወደ ድርጣድስም በክብር ላከው። ቅዱስ ጎርጎርዮስም ተሹሞ ወደ አርማንያ አገር በደረሰ ጊዜ በመምጣቱ ደስ ተሰኙበት እርሱም የአርማንያን ሰዎች ሁሉንም አጠመቃቸው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው ሃይማኖንትም ከአጸናቸውና መልካም ጉዞንም ከፈጸመ በኋላ ታኅሣሥ15 ቀን በሰላም በፍቅር ዐረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ኤዎስጣቴዎስ_ከፋሌ_ባህር ዳግመኛም በዚህች ዕለት አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር የተሻገሩት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ልደታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ አባታቸው ክርስቶስ ሞዐ ሲሆን እናታቸው ስነ ሕይወት ይባላሉ፡፡ ደጋግ የሆኑ ወላጆቻቸው በሃይማኖትና በምግባር ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ በአደጉም ጊዜ ከአባ ዘካርያስ እጅ መነኮሱ፡፡ ታላላቅ ቅዱሳን እስኪያደንቋቸው ድረስ በጽኑ ተጋደሎ ሲኖሩ ጌታችን ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር ተገልጦላቸው በንፍሐት መንፈስ ቅዱስን አሳደረባቸው፡፡ ‹‹ከእናትህ ማኅፀን የመረጥኩህ ወዳጄ ኤዎስጣቴዎስ ሆይ ለብዙዎች ወንጌልን ትሰብክ ዘንድ ከኢትዮጵያ እስከ አርማንያ ድረስ መምህር አደረግሁህ፡፡ አንተን የሰማ እኔን ሰማ፣ አንተንም ያልሰማ እኔን ያልሰማ ነው›› ካለቸው በኋላ ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ፡፡ አባታችን ቅስናን ከተሸሾሙ በኋላ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ እነ አቡነ አብሳዲን ጨምሮ ብዙዎችንም አመንኩሰው ደቀ መዛሙርቶቻቸው አደረጓቸው፡፡ እጅግ አስገራሚ ተአምራትን በማድረግ ለብዙ ሕሙማን መድኃኒት ሆኗቸው፡፡ ልጆቻቸውን ሰብስበው ከመናፍቃን ጋር በፍጹም እንዳይቀላቀሉ በመምከር አቡነ አብሳዲን ሾመውላቸው ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ ቅዱሳት ቦታዎችን ተሳለሙ፡፡ በመንገዳቸውም የክርስቶስን ወንጌል እየሰበኩ ብዙዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሷቸው፡፡ ወደ አርማንያም ሄደው ወደ ኢያሪኮ ባሕር በደረሱ ጊዜ መርከበኞችን እንዲያሳፍሯቸው ቢለምኗቸው እምቢ አሏቸው፡፡ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ግን አጽፋቸውን በባሕሩ ላይ ዘርግተው በስመ ሥላሴ አማትበው አጽፋቸውን እንደመርከብ አድርገው ልጆቻቸውን ይዘው ባሕሩን ተሻገሩ፡፡ ልጆቻቸውን ‹‹ልጆቼ በልባችሁ ቂምንና ሽንገላን እንዳታኖሩ ተጠበቁ፣ ለእኔ ግን ከእናንተ አንዱ እንደሚጠፋ ይመስላኛል›› አሏቸው፡፡ ይህንንም እንዳሉ ከመካከላቸው አንዱ የቂም በቀል መከማቻ ነበርና ወዲያው ሰጠመ፡፡ አባታችን አርማንያ ደርሰው ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር ቡራኬን ከተሰጣጡ በኋላ ማስተማር ጀመሩ፡፡ የአርማንያ ሰዎች ሁሉም በሃይማኖት አንድ እስኪሆኑ ድረስ ታላላቅ ተአምራትን እያደረጉ አስተምረው አጠመቋቸው፡፡ አባታችን ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታችን ተገልጦላቸው ታላቅ ቃልኪዳን ከሰጣቸው በኋላ መስከረም 18 ቀን ዐርፈው ሊቀ ጳጳሳቱና ካህናቱ በታላቅ ክብር ገንዘው በሰማዕቱ በቅዱስ መርምህናም ቤተ ክርስቲያን ቀብረዋቸዋል፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ሉቃስ_ዘዓምድ

አስወግደ ከፊቱም ብርሃን ገናናነት የተነሣ ሊያዩት አልተቻላቸውም። እኛ ቊርባንን ከተቀበልን በኋላ ቆረበ ከነገሥታት ልጆች ወገንም እንደሆነ ተጠራጠርን መብልንም በአቀረብንለት ጊዜ ከእኛ አልተቀበለም ነገር ግን ሰይጣን በእነርሱ ከሚያስትባቸው ሴቶችን ከማየት እንርቅ ዘንድ መከረን። ሮማዊ የሆነ አንድ ደግ ጻድቅ አረጋዊ መነኵስ ነበር እርሱም "አባቴ ያዕቆብ ሆይ ይቺ ከነገሥታት ልጆች ውስጥ የሆነች ሴት ናት ስለዚህም እንዳትታወቅ ፊቷን ከሰው ትሠውራለች" አለኝ። ከዚህም በኋላ ሥራዋን ከእኔ ሳትሠውር እንድትነግረኝ በክርስቶስ ስም አምላት ዘንድ ወደርሷ ሔድሁ። ግን አላገኘኋትም ከአምስት ወርም በኋላ ከንጉሥ አባቷ ዘንድ የተላኩ ብዙ ሰዎች እርሷን እየፈለጉ መጡ። እነርሱም ቤተሶቦቿ ከተኙ በኋኋ በሌሊት እንደወጣች እነርሱም እርሷን ሲፈልጉ ዐሥራ ሁለት ዓመት እንደሆናቸው ሥራዋን ነገሩን። ከዚህም በኋላ መጻተኞች ሰዎች በዚች ቀን እንዳረፈች ነገሩን። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ በጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_14 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ አራት በዚህች እለት #ቅዱስ_መርምህናም እና እኅቱ #ቅድስት_ሣራ በሰማዕትነት ዐረፉ፣ መኑፍ ከሚባል አገር #ቅዱስ_ስምዖን በሰማዕትነት ዐረፈ፣ #የቅድስት_ነሳሒት ለዕረፍቷ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱሳን_መርምህናምና_እኅቱ_ሣራ ታኅሣሥ ዐስራ አራት በዚህች እለት ቅዱሳን መርምህናምና እኅቱ ሣራ አርባ አገልጋዩቹ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ የዚህም ቅዱስ አባት የአቶር ንጉሥ የተቀረጹ ስማቸው ቤል አጵሎን የሚባሉ ጣዖታትን የሚያመልክ ነው እናቱ ግን ክርስቲያን ናት። ይህም ቅዱስ መርምህናም ወደ ዱር ሒዶ አራዊትን ያድን ዘንድ እንዲፈቅድለት አባቱን ለመነው በፈቀደለትም ጊዜ ወደ እናቱ ሒዶ "አራዊትን ለማደን ወደ በረሀ እሔዳለሁ" አላት እናቱም "የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላይህ በረከትን ያሳድር" አለችው። ከዚህም በኋላ ከአርባ ፈረሰኞች አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሔደ መቅሉብ ወደሚባል ተራራም ደርሶ በዚያ አደረ። በሌሊትም የእግዚአብሔር መልአክ ጠራው እንዲህም አለው "መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ላይ ውጣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል" ሲነጋም ወደ ተራራው ወጣ እንደ በግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን አገኘው መርምህናም በአየው ጊዜ ፈራ ቅዱስ አባ ማቴዎስ "ልጄ ሆይ ወደ እኔ ቅረብ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረቱ የሆንኩ እንዳንተ ሰው ነኝ" አለው። መርምህናምም "ከአባቴ አማልክቶች በቀር አምላክ አለን?" አለው አባ ማቴዎስም የክርስትና ሃይማኖትን ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክርስቶስን ህልውና በተለየ አካሉ ሰው መሆኑንና መከራ ተቀብሎ መሞቱን መነሣቱን ወደ ሰማይ ማረጉንም የፍርድ ቀንም እንዳ ለጻድቃን በጎ ዋጋ ለኃጢአተኞች ቅጣት እንዳለ አስተማረው። መርምህናምም "ከራስዋ እስከ እግርዋ ለምጽ የያዛት እኅት አለችኝ የአምላክህን ስም ጠርተህ በጸሎትህ ብታድናት እኔ አምንበታለሁ" አለው አባ ማቴዎስም "እኔ አድናታለሁ ና በአንድነት እንውረድ" አለው ከተራራው በወረዱ ጊዜ አባ ማቴዎስን በመንገድ ትቶ ቅዱስ መርምህናም ወደ እናቱ ሒዶ ሁሉን ነገራት እኅቱንም በሥውር ወደ አባ ማቴዎስ ወሰዳት አባ ማቴዎስም ወደ እግዚአብሔር ጸለየና ምድሪቱን አመሳቅሎ መታት በዚያን ጊዜ ውኃ መንጭቶ እንደ ባሕር ሆነ ወደ ባሕሩም አውርዶ እጁን በራሳቸው ላይ አድርጎ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው አሽከሮቹን አርባ ሰዎችንም ሥጋውንና ደሙንም አቀበላቸው ወዲያውኑ ሣራ ከለምጽዋ ነጻች። ከዚህም በኋላ አባ ማቴዎስ ስለ ከበረ ስሙ በላያቸው የሚመጣውን መከራ በሚቀበሉ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን እንዲጸኑ መከራቸው ከዚህም በኋላ በላያቸው ጸለየና በፍቅ አንድነት አሰናበታቸው። ቅዱስ መርምህናምም በመጣ ጊዜ ወደ እናቱ ቤት ገባ ወደ አባቱ ወይም ወደ አማልክቶቹ አልሔደም አባቱም ሰምቶ ተቆጣ ወደ አማልክቶቹ ቤትም እንዲጠሩት አዘዘ ቅዱስ መርምህናም ግን ከእኅቱና ከሠራዊቱ ጋር ስሟ ቅሳር ወደ ምትባል ተራራ ሒዶ ከላይ ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ። አባቱም በሰማ ጊዜ ከልብሰ መንግሥትና ከዘውድ ጋር መኳንንቱን "የመንግሥቴን ሥልጣን ተረከብ ብሎሃል" እንዲሉት ላካቸው እርሱ ግን በቊጣ ተመለከታቸውና "እኔ ክብር ይግባውና የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ የማይጠፋ መንግሥት እሻለሁ" አላቸው። የአቶር ንጉሥ አባቱም በዚያን ጊዜ ተቆጣ ልቡ ፈርቶ ይመለስ ዘንድ አገልጋዮቹን በፊቱ እንዲገድሏቸው ካልተመለሰ ግን እርሱንም እኅቱንም እንዲገድሉ አዘዘ። ቅዱስ መርምህናምም ሰምቶ የተመኘውን ይሰጠው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ "ጸሎትህን ሰማሁ ልብህ የወደደውንም ሰጠሁህ" የሚል ቃል ከሰማይ መጣ። ከዚህም በኋላ የቅዱሳኑን ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጡና ከጒድጓድ ውስጥ ጣሏቸው ሥጋቸውንም ያቃጥሉ ዘንድ ብዙ ዕንጨቶችን ሰበሰቡ ግን አላገኙአቸውም እግዚአብሔር ሠውሮዋቸዋልና። ወዲያውኑ ንውጽውጽታ ሆነ ፀሐይም ጨለመ ወታደሮችም ፈርተው ሸሹ ሰይጣንም በአቶር ንጉሥ በሰናክሬም ላይ አድሮ አሳበደው እንደእሪያም ጮኸ የቅዱስ መርምህናምም እናት አይታ ወደ አባ ማቴዎስ ልካ አስመጣችውና የንጉሡን ነገር ነገረችው እርሱም በዘይት ላይ ጸልዮ ቀባው ሰይጣንም በእሪያ አምሳል ከርሱ ወጣ። በዚንም ጊዜ ንጉሥ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ከቤተ ሰቦቹና በሚገዛው አገር ካሉ ሰዎች ሁሉ ጋር ተጠመቀ። ከዚህም በኋላ አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ ገንዘብንም ለድኆችና ለችግረኞች እንዲበትኑ አዘዘ ሁሉንም እንዳዘዛቸው አደረጉ። የቅዱስ መርምህናምም እናት ከከበሩ ደንጊያዎች አርባ ሣጥኖችን አሠራች የልጅዋ ጭፍራ የነበሩ የእነዚያን አርባ ሰማዕታት አጥንቶቻቸውን አሰብስባ በየአንዳንዱ ሣጥን ጨመረቻቸው ለልጆቿም ብርሌ ከሚመስል ዕንቊ ሁለት ሣጥን አሠርታ በውስጣቸው አድርጋ በሠራችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖረቻቸው ከሥጋቸውም ታላላቅ የሆኑ ቊጥር የሌላቸው ተአምራት ተገለጡ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ስምዖን ዳግመኛም በዚህች እለት መኑፍ ከሚባል አገር ቅዱስ ስምዖን በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ እርሱም በእስላሞች ዘመን ከመሳፍንቶቻቸው ከአንዱ ጋር ተከራከረና ቅዱስ ስምዖን ረትቶ አሳፈረው ያም እስላም ወደ መሳፍንቱ አለቃ ሒዶ "ይህ ስምዖን የእስላሞች ሃይማኖት ያቃልላል" ብሎ ወነጀለው ስለዚህም ይዘው በጽኑዕ ሥቃይ አሠቃዩት ከዚያም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ነሳሒት በዚህች ዕለት የውሲም ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ ስርሷ የተናገረላት የሮሜ ንጉሥ ልጅ ቅድስት ነሳሒት ዐረፈች፡፡ እንዲህም አለ በአንዲት ዕለት አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያለሁ የገዳሙን ደጅ ሰው ሲያንኳኳ ሰማሁ ተነሥቼም ወደ በሩ ሔድኩ ያረጀ ዓጽፍ የለበሰ ፊቱንም የተሸፋፈነ ሰው አየሁ "ከወዴት መጣህ? ወዴትስ ትሔዳለህ?" አልሁት። "ከአባ መቃርዮስ ገዳም መጣሁ በዚች ሌሊት ከዚህ ገዳም አድሬ ቊርባንን መቀበል እሻለሁ" አለኝ። ያን ጊዜ ቀዳሚት ሰንበት ነበረች እኔም "ፊትህን ካላሳየኸኝ አልከፋትልህም" አልሁት እርሱም "ፊቴን ማየት አትሻ ፊቴ በኃጢአቴ የጨለመ ነውና ፊቴንም ለሚያይ የከፋች ሥራዬ ትታየዋለች" አለኝ። በከለከልኩትም ጊዜ ወደ ዱር ሊመለስ ወደደ እኔም ተርቦ ወይም ተጠምቶ እንደሆነ ብዬ በልቤ አሰብኩ ስለዚህም ከፈትኩለትና ወደ ማደሪያዬ አስገባሁት መብልንም አመጣሁለት እርሱም "ከነገ ከቊርባን በኋላ በቀር እኔ አልበላም" በማለት እምቢ አለኝ። ከዚህም በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገባና በጨለማ ቦታ ቆመ ከዚያ ያሉ መነኰሳትም እስከ አደነቁ ድረስ የዳዊትን መዝሙር ሲያነብ ድምፁን እንደ መላእክት ድምፅ ሁኖ ሰማሁት በነጋም ጊዜ በእግሮቹ ላይ ተቀመጠ ምንም ምን ማንበብ አልሻም። እኛ ግን ይጸልይልን ዘንድ ልንለምነው ቀረብን እርሱም "አባቴቼ ሆይ በበደሌ ብዛት ፊቴን ያጨለምኩ ስሆን ስለ እናንተ እንዴት እጸልያለሁ" አለን። ቊርባንንም በምናሳርግ ጊዜ በእግሩ ቁሞ የቅዱስ ጳውሎስን መልእክት፣ የሐዋርያትንም መልእክትና የሐዋርያትን ሥራ ማንበብ ጀምረ በአራተኛም ጊዜ በመሠዊያው ፊት ቁሞ የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ማንበብ ጀመረ በፊቱም ላይ የተከናነበውን ልብስ

ሀዘን የወንድማችን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል አባት ስላረፉ ነገ ኮዬፈጬ ወረዳ ጋር ብሎክ 194 ቀብር ቦታው ዘነብወርቅ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን 5:00 ስለሆነ የምንችል እንገኝ።

የወንድማችን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል አባት ስላረፉ ነገ ኮዬፈጬ ወረዳ ጋር ብሎክ 194 ቀብር ቦታው ዘነብወርቅ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን 5:00 ስለሆነ የምንችል እንገኝ ።

የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት በተለያየ ጊዜ ከሰ/ት/ቤቱ ንብረት /ዕቃ/ ዩኒፎርምን ጨምሮ  የወሰዳችሁ  በእጃችሁ ካለ ንብረቱን ወደ ሒሣብ ክፍልና ንብረት አስተዳደር እንድታስገቡ/ተመላሽ/ እንድታደርጉ በአምላከ ሚካኤል ስም እንጠይቃለን።

ዳግመኛም በዚህች እለት ታላቁ አባት አባ መቃርስ ገዳማዊ ዓመታዊ የዕርገታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይኸኛው መቃርስ ዕረፍቱ መጋቢት 27 ከሚውለው ከታላቁ መቃርስ ይለያል፡፡ በመቃርስ ስም የሚጠሩ ከ8 በላይ ሌሎች ቅዱሳንም አሉ፡፡ ታኅሣሥ 13 ቀን የዕርገቱ በዓል የሆነው መቃርስ ግን ቆቅ ይመገብ የነበረው መቃርስ ነው፡፡ እርሱም በልጅነቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እየተማረ አደገ፡፡ የዓለምን ከንቱነት ተመልክቶ ዳግመኛም የኃጥአንንና የጻቃንን ዋጋቸውን አይቶ ወደ ገዳም ገብቶ መነኮሰ፡፡ ከመነኮሰም በኋላ የ10 ቀን መንገድ ተጉዞ ኩዕንትና ቆቆች ውኃም ካለበት ተራራ ላይ ደረሰ፡፡ እንዲህም አለ፡- ‹‹ለምግቤ ኩዕንትን ወደ መልቀም ብሰማራ የስግደቴና የጸሎቴ ሥራ ይቋረጣል፣ በዚህም ተራራ ላይ ብቸኛ ነኝና ሰብስቦ የሚያስገባልኝ የለም፡፡ ሥጋ አትብላ ያለውስ የባልንጀራችንን ሥጋ በሐሜት የምንበላውን አይደለምን? ሌላ ምግብ እንደሌለኝ ፈጣሪዬ ያውቃል›› ብሎ ከዚያች ዕለት ወዲህ ለምግቡ ቆቅ የሚያጠምድ ሆኖ በእግዚአብሔር ፈቃድ በየቀኑ አንድ አንድ ቆቅ የሚያዙለት ሆነ፡፡ በየቀኑም አንድ አንድ ቆቅ እየተመገበ ውኃ እየጠጣ ፈጣሪውን እያመሰገነ በታላቅ ተጋድሎ ሆኖ የሰውን ፊት ሳያይና ከማንም ጋር ሳይነጋገር ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ ከቍስጥንጥንያ ከተማ የመጣ አንድ መነኩሴ ዋሻ ሲፈልግ አባ መቃርስ ደግሞ ቆቅ ሲያጠምድ አየውና ለሐሜት ቸኩሎ ወደ ቍስጥንጥንያ ተመልሶ ሄዶ ለሊቀ ጳጳሳቱ ‹‹ቆቅ እያጠመደ ሥጋ የሚበላ መነኩሴ አገኘሁ፣ እርሱም በሕዝብ ዘንድ ሊያስነቅፈን ነው›› ብሎ ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ከአንድ ሌላ መነኩሴ ጋር ድጋሚ እንዲያረጋግጡ ላካቸው፡፡ እነርሱም ገና ከበዓቱ ሳይደርሱ አባ መቃርስ ቆቅ ሊያጠምድ ሄደና ያለወትሮው በአንዲት ወጥመድ ሦስት ቆቆችን ተያዙለት፡፡ ሌላ ጊዜ በቀን አንድ ብቻ ነበር የሚያዝለት ዛሬ ግን እግዚአብሔርም ለሚመጡት እንግዶችም ጭምር ሲያዘጋጅላቸው ነው ያለወትሮው ዛሬ ሦስት ሆነው የተያዙለት፡፡ አባ መቃርስም ሁለቱን መነኮሳት ሲያያቸው ሁለቱ ተጨማሪ ሆነው የተያዙለት ቆቆች የእንግዶቹ መሆናቸውን ዐውቆ ጌታችንን አመሰገነው፡፡ እነርሱ ግን ማዕድ ሠርቶ እስካቀረበላቸው ድረስ በመቃርስ ላይ ይጠቋቆሙበት ነበር፡፡ አባ መቃርስም ምግብን አዘጋጅቶ ሲጨርስ የራሱን ድርሻ አንዷን ቆቅ አስቀርቶ ሁለቱን ለእንግዶቹ አቀረበላቸው፡፡ እርሱ በልቶ ጨርሶ ቀና ሲል እንግዶቹ መነኮሳት እንዳልበሉ ተመለከተና ‹‹አባቶቼ ለምን አልበላችሁም?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እኛ መነኮሳት ስለሆንን ሥጋ አንበላም ትኅርምትም አለን›› አሉት፡፡ አባ መቃርስም ‹‹እሺ ተውት›› አላቸውና እነዚያን አብስሎ በገበታ ላይ ለምግብነት ያቀረባቸውን ሁለት ቆቆች ሦስት ጊዜ በእስትንፋሱ እፍ ቢልባቸው ሕይወት ዘርተው በረሩና ወደ ጫካ ሄዱ፡፡ እነዚያ መነኮሳትም እጅግ ደንግጠው ‹‹ማረን ይቅር በለን፣ ቅዱሱን የእግዚአብሔር ሰው በከንቱ አምተንሃል›› ብለው እግሩ ሥር ሲወድቁ ‹‹እግዚአብሔር የሁላችንን በደል ይቅር ይበለን›› አላቸው፡፡ ሁለቱ መነኮሳት ወደ ቍስጥንጥንያ ተመልሰው ለሊቀ ጳጳሳቱና ለሕዝቡ ያዩትን ነገር መሰከሩ፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም እጅግ ተደንቆ ወደ ንጉሡ ደብዳቤ ጽፎ ‹‹በምድራችን ጻድቅ ሰው ተገኝቷልና አንተም ና ሄደን በረከቱን እንቀበል›› ብሎ መልእክት ላከበት፡፡ ንጉሡም እሺ ብሎ ከሠራዊቱ ጋር ተነሥቶ ከካህናቱ ጋር ወደ አባ መቃርስ ዘንድ ሄዱ፡፡ ወደ ገዳሙም በቀረቡ ጊዜ አባ መቃርስን ወደ ብሔረ ሕያዋን ያደርሰው ዘንድ መልአክ አንሥቶ በክንፎቹ ተሸክሞት ሲያርግ አዩት፡፡ እነርሱም ‹‹የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ባርከን፣ የምንድንበትንም አንዲት ቃል ንገረን›› አሉት፡፡ አባ መቃርስም ‹‹ከሐሜትና ከነገር ሥራ አንደበታችሁ ይከልከል፤ ካህን ብዙ ባይማር ትዕቢትና መታጀር ባልመጣበት ነበር፣ መነኩሴም ትኅርምት ባያበዛ ባልተመካም ነበር፡፡ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ እግዚአብሔር አድሮባችሁ ይኑር›› አላቸው፡፡ ይህንንም ከተናገራቸውና ከባረካቸው በኋላ ከዐይናቸው ተሰወረ፡፡ ይህም ዕርገቱ ታኅሣሥ 13 ቀን የተፈጸመ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_አብራኮስ_ገዳማዊ ዳግመኛም በዚህች ቀን መነኮስ አቡነ አብራኮስ ገዳማዊ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ዕድሜው 20 ዓመት በሆነው ጊዜ የዚህን ዓለም ኃላፊነት ተረድቶ የነፍሱን ድኅነት ሽቶ መንኩሶ ገዳም ገባ፡፡ በዚያም በታላቅ ተጋድሎ ሲኖር ሰይጣን በቅናት ተነሳስቶበት ብዙ ፈተናዎችን አመጣበት ነገር ግን ቅዱስ አብራኮስ ጽኑ በሆነው መንፈሳዊ ተጋድሎው ሰይጣንን ድልነሣው፡፡ ሰይጣንም በተደጋጋሚ መሸነፉን አይቶ የፈተናውን ዓይነት ለወጥ አድርጎ በሰንፍና ሊጥለው ፈለገ፡፡ እናም ሰይጣን በግልጽ ፊት ለፊት ተገልጦ ቅዱስ አብራኮስን ‹‹እነሆ ከዚህ ዕድሜህ ሌላ 50 ዓመት ቀረህ›› አለው፡፡ ቅዱስ አብራኮስም ሰይጣን በስንፍና ሊጥለው ያመጣበት ፈተና መሆኑን ዐውቆ በተራው ሰይጣን ላይ ተራቀቀበት፡፡ እንዲህም አለው፡- ‹‹አሁንስ ልቤን አሳንከው፣ እኔ ሌላ መቶ ዓመት እኖር ዘንድ ስላሰብኩ ቸል ብያለሁ ነገር ግን አንተ እንዳልከው 50 ዓመት ከሆነ የምኖረው ከቀድሞው እጅግ አብዝቼ እጋደል ዘንድ ይገባኛል›› አለው፡፡ ሰይጣንም ይህን ጊዜ አፍሮ ከእርሱ ሸሸ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አብራኮስ ጽኑ የሆነ ተጋድሎውን በገድል መጠመዱን አብዝቶ ከ70 ዓመት ተጋድሎው በኋላ በሰላም ዐረፈ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_በጽንፍርዮስ_ሰማዕት በዚህች እለት የሰማዕት ቅዱስ በጽንፍርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ አባት ዓለምን ንቆ በመመንኮስ በታላቅ ተጋድሎ ይኖር ነበር፡፡ የሚያገለግለውም በምስር አገር በወንዝ ዳር ባለች በሊቀ መላእክት በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለቀናች ተዋሕዶ ሃይማኖቱም ከእስላሞች መሳፍንት ጋር ተከራከረ፡፡ የጌታችንም የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነቱን ገለጠላቸው፡፡ እስላሞችም ባፈሩ ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጡ፡፡ ከዚህም በኋላ እስላሞች አባ በጽንፍርዮስን ይዘው በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ በመጨረሻ ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን መልእክት አና ጻድቃን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_13 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ ሦስት በዚህች ቀን #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱና ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፣ ታላቁ አባት #አባ_መቃርስ_ገዳማዊ ዓመታዊ የዕርገታቸው መታሰቢያ ነው፣ መነኮስ #አቡነ_አብራኮስ_ገዳማዊ ዕረፍታቸው ነው፣ የሰማዕት #ቅዱስ_በጽንፍርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል ታኅሣሥ ዐስራ ሦስት በዚህች ቀን በዚህች ዕለት ፈታሄ ማህጸን ሊቀ መልአክት ቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱና ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፡፡ ሰማያውያን ከሆኑ ከመላአክት አለቆች ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ 3ተኛ ነው፡፡ "ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ” እንዲል፡፡ ጦቢት 12፡15፡፡ ሩፋኤል የሚለው የስሙ ትርጓሜ ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል መልአከ የሰላምና የጤና መልአክ ይባላል፡፡ በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ሆነ ቁስል ይፈወስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” መጽሐፈ ሄኖክ 6፡3፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የሰው ልጆች ከተያዙበት የኀጢአት ቁስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የማይለይ መልአክ ነው፡፡ “በበሽታ ሁሉ ላይ በሰው ልጆችም ቁስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡” በማለት ሄኖክ ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል፡፡ ሄኖክ 10፡13፡፡ ለሴቶች ረዳታቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ በማኅፀን ላለ ችግርና ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም፡፡ ሕፃኑ ዐርባ ቀን ሞልቶት በማሕፀን እያለ ማለትም በሥላሴ አርአያ መልኩ መሳል ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል አይለየውም፡፡ በመውለጃቸው ቀን ሴቶች ከሚደርስባቸው ጭንቀትና ሕመም ስሙን ጠርተው ይማጸኑታል፡፡ ፈታሔ ማኅፀን ነውና ቅዱስ ሩፋኤልም ጭንቀታቸውን ያቀላል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነት ያለን ረቂቅ ርኩስ መንፈስ ያውቃል፡፡ አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ጭን ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሠቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል ጦቢት 3፡8-17፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው አለው” ሄኖክ 3፡5-7፡፡ በዚህ መሠረት ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሄኖክ 2፡18፡፡ ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠብቃቸው እግዚአብሔር እንዳዘዘዉ የሚከፍታቸዉ የሚዘረጋቸዉ ይህ ታላቅ መልአክ ነዉ፡፡ የምህረትና የረድኤት መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ከሥራዎቹ አንፃር በተለያየ ስም ይጠራል፡፡ "ፈታሄ ማህጸን" ይባላል-እናቶች ሲወልዱ ምጥ እንዳይበዛባቸዉ የሚራዳ መልአክ ስለሆነ አያሌ ክርስቲያኖች ማርገዛቸዉን ካወቁ ጀምሮ ድርሳኑን በማንበብ መልኩን በመድገም ጠበሉን በመጠጣት ሰዉነታቸዉን በመቀባት ይለምኑታል፡፡ እንደ እምነታቸዉ ጽናት ይደረገላቸዋል፡፡ ዳግመኛም "ዐቃቤ ኖኀቱ ለአምላክ" ይባላል-ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠበቅ ስለሆነ ነው፡፡ ዳግመኛም "መራሔ ፍኖት" ይባላል-ጦቢትን በቀና መንገድ መርቶታልና ነው፡፡ እንዲሁም "መላከ ክብካብ" ይባላል-ጦቢያና ሣራን ያጋባ ጋብቻቸዉን የባረከ በመሆኑ ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያደረገው ተዓምር ይህ ነው፡፡ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዓል እስኪፈፀም ድረስ በከበረ ሊቀ ጳጳስ አባ ቴዎፍሎስ ዘመን በምድረ ግብጽ ውስጥ ከእስክንድርያ ውጭ በታናፀች አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ ይህች ቤተ ክርስቲያን ከአሳ አንበሪ ላይ የታነፀች ነበር፡፡ ነገር ግን በወደቡ አጠገብ ከነበረ ግዙፍ አንበሪ ጀርባ ላይ መታነጿን ቀድሞ ያነጿት ሰዎች ቢሆኑ ከካህናትም ቢኾን ያወቀ አልነበረም፡፡ ያ አንበሪም የቤተክርስቲያኑ ህንጻ በከበደው ጊዜ ፈጽሞ ተንቀሳቀሰ፡፡ ከአሸዋማው መሬት ላይ በባህሩ ዳርቻ የታነፀች ይህች ቤተ ክርስቲያንም ከመሰረቷ አናወጻት፡፡ ያን ጊዜ ትልቁም ትንሹም ወንዱም፣ ሴቶችም፣ የተሾሙ ዲያቆናት፣ ካህናት፣ ሕዝቡም ሁሉ ደነገጡ ታወኩ፡፡ አሣ አንበሪው ግን መንቀሳቀሱን አልተወም፡፡ በመንቀሳቀሱም የቤተ ክርስያኗ ሕንፃ እኩሌታ ይሰነጠቅ ዘንድ ጀመረ፣ ምድርን ተናወፀች፣ ንጉስና፣ ሊቀ ጳጳሳቱም፣ ካህናቱም፣ ዲያቆናቱም፣ ህዝቡም፣ ሁሉም ካሉበት በባህሩ ወደብ ከተሰራች ከዚህች ቤተ ክርስቲያን መናወጥ የተነሳ ፍርሃት መንቀጥቀጥ በላያቸው ወረደ፡፡ ያ አንበሪ ግን በባህሩ ውስጥ ወደፊት መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ቤተ ክርስቲያኗም በጀርባው ላይ ነበረች፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ የሉትም ሁሉ ያ አሳ አንበሪ ወደ ባሕሩ ውስጥ ሊያሰጥመን ነው ሲሉ አሠቡ፡፡ ያን ጊዜም በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ስዕል ፊት በጽኑ አለቀሱ፡፡ በአንድ ቃልም "ገናናው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ ርዳታህ ፈጥኖ ይደርስልን ዘንድ በቅድስት ቤተክርስቲያን ወደተሰበሰብን ወዳጆችህ ተመልከት" እያሉ ይጸልዩ ጀመር፡፡ ያንጊዜም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ከሰማይ ወርዶ ያችን ቤተክርስቲያን በብሩሃት ክንፎቹ እንደደመና ጋረዳት፡፡ በእጁ በተያዘ የብርሃን በትረ መስቀሉ ያን ኣሣ አንበሪ ወገቶ "በኢየሱስ ክርስቶስ ሃይል ከቦታህ ሳትንቀሳቀስ እስከትውልድ ፍፃሜ ዘመን ለዘለአለም ትኖር ዘንድ አዝዝሃለሁ" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ሊቀመላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያኗን ከነመዓዘኗ ከግርግዳዎቿ ከመሠዊያዋ በውስጧ ተተክለው ካሉት ሁሉ ጋር ከጀርባው ላይ እያለች ያንን አሳ አንበሪ ወግቶ በያዘበት ብርሃናዊ በትረ መስቀሉ ወደቀድሞው የባሕሩ ወደብ ጎተተው፡፡ ያንጊዜም ግንቡ ቦታውን ሳይለቅ እርስ በእርሱ ተጣበቀ፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አሣ አንበሪውን በቀድሞ ሥፍራው ያቺን ቤተክርስቲያን በቀደመ መሠረቷ ላይ አጽንቷቸዋልና፡፡ ሊቀመላእክት ቅዱስ ሩፋኤልም አዳኝ የሆነ የጌታው የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ጠርቶ ከሞት እንዳዳናቸው ሁሉም አስተዋሉ፡፡ በድንቅ ተዓምራቱ የዳኑ ንጉሡና ሕዝቡም ሁሉ በሊቀመላእክቱ ቅዱስ ሩፋኤል ላይ አድሮ ድንቅ ተዓምራቱን ስለገለጸላቸው የቅዱስ ሩፋኤልን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ የዚህች ቤተክርስቲያን ታሪክም በዓለም ሁሉ በየአውራጃዎቹም ተሰማ፡፡ የቅርብም የሩቅም ሰዎች ሁሉ ተሰብስበው ታላቁ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የለመኑትን ሁሉ ያደርግላቸው ዘንድ የነገሩትን ያማልዳቸው ዘንድ በውስጧ ይጸልያሉ፡፡ በዚችም ቤተክርስትያን ብዙ ውስጥ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተደረጉ፡፡ ታኅሣሥ 13 ቀንም ተአምራቶቹ ከተፈጸመባቸው ዕለታት አንዷ ናት፡፡ ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ተከናውኗል፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_መቃርስ_ገዳማዊ

ዳግመኛም በዚህች እለት ታላቁ አባት አባ መቃርስ ገዳማዊ ዓመታዊ የዕርገታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይኸኛው መቃርስ ዕረፍቱ መጋቢት 27 ከሚውለው ከታላቁ መቃርስ ይለያል፡፡ በመቃርስ ስም የሚጠሩ ከ8 በላይ ሌሎች ቅዱሳንም አሉ፡፡ ታኅሣሥ 13 ቀን የዕርገቱ በዓል የሆነው መቃርስ ግን ቆቅ ይመገብ የነበረው መቃርስ ነው፡፡ እርሱም በልጅነቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እየተማረ አደገ፡፡ የዓለምን ከንቱነት ተመልክቶ ዳግመኛም የኃጥአንንና የጻቃንን ዋጋቸውን አይቶ ወደ ገዳም ገብቶ መነኮሰ፡፡ ከመነኮሰም በኋላ የ10 ቀን መንገድ ተጉዞ ኩዕንትና ቆቆች ውኃም ካለበት ተራራ ላይ ደረሰ፡፡ እንዲህም አለ፡- ‹‹ለምግቤ ኩዕንትን ወደ መልቀም ብሰማራ የስግደቴና የጸሎቴ ሥራ ይቋረጣል፣ በዚህም ተራራ ላይ ብቸኛ ነኝና ሰብስቦ የሚያስገባልኝ የለም፡፡ ሥጋ አትብላ ያለውስ የባልንጀራችንን ሥጋ በሐሜት የምንበላውን አይደለምን? ሌላ ምግብ እንደሌለኝ ፈጣሪዬ ያውቃል›› ብሎ ከዚያች ዕለት ወዲህ ለምግቡ ቆቅ የሚያጠምድ ሆኖ በእግዚአብሔር ፈቃድ በየቀኑ አንድ አንድ ቆቅ የሚያዙለት ሆነ፡፡ በየቀኑም አንድ አንድ ቆቅ እየተመገበ ውኃ እየጠጣ ፈጣሪውን እያመሰገነ በታላቅ ተጋድሎ ሆኖ የሰውን ፊት ሳያይና ከማንም ጋር ሳይነጋገር ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ ከቍስጥንጥንያ ከተማ የመጣ አንድ መነኩሴ ዋሻ ሲፈልግ አባ መቃርስ ደግሞ ቆቅ ሲያጠምድ አየውና ለሐሜት ቸኩሎ ወደ ቍስጥንጥንያ ተመልሶ ሄዶ ለሊቀ ጳጳሳቱ ‹‹ቆቅ እያጠመደ ሥጋ የሚበላ መነኩሴ አገኘሁ፣ እርሱም በሕዝብ ዘንድ ሊያስነቅፈን ነው›› ብሎ ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ከአንድ ሌላ መነኩሴ ጋር ድጋሚ እንዲያረጋግጡ ላካቸው፡፡ እነርሱም ገና ከበዓቱ ሳይደርሱ አባ መቃርስ ቆቅ ሊያጠምድ ሄደና ያለወትሮው በአንዲት ወጥመድ ሦስት ቆቆችን ተያዙለት፡፡ ሌላ ጊዜ በቀን አንድ ብቻ ነበር የሚያዝለት ዛሬ ግን እግዚአብሔርም ለሚመጡት እንግዶችም ጭምር ሲያዘጋጅላቸው ነው ያለወትሮው ዛሬ ሦስት ሆነው የተያዙለት፡፡ አባ መቃርስም ሁለቱን መነኮሳት ሲያያቸው ሁለቱ ተጨማሪ ሆነው የተያዙለት ቆቆች የእንግዶቹ መሆናቸውን ዐውቆ ጌታችንን አመሰገነው፡፡ እነርሱ ግን ማዕድ ሠርቶ እስካቀረበላቸው ድረስ በመቃርስ ላይ ይጠቋቆሙበት ነበር፡፡ አባ መቃርስም ምግብን አዘጋጅቶ ሲጨርስ የራሱን ድርሻ አንዷን ቆቅ አስቀርቶ ሁለቱን ለእንግዶቹ አቀረበላቸው፡፡ እርሱ በልቶ ጨርሶ ቀና ሲል እንግዶቹ መነኮሳት እንዳልበሉ ተመለከተና ‹‹አባቶቼ ለምን አልበላችሁም?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እኛ መነኮሳት ስለሆንን ሥጋ አንበላም ትኅርምትም አለን›› አሉት፡፡ አባ መቃርስም ‹‹እሺ ተውት›› አላቸውና እነዚያን አብስሎ በገበታ ላይ ለምግብነት ያቀረባቸውን ሁለት ቆቆች ሦስት ጊዜ በእስትንፋሱ እፍ ቢልባቸው ሕይወት ዘርተው በረሩና ወደ ጫካ ሄዱ፡፡ እነዚያ መነኮሳትም እጅግ ደንግጠው ‹‹ማረን ይቅር በለን፣ ቅዱሱን የእግዚአብሔር ሰው በከንቱ አምተንሃል›› ብለው እግሩ ሥር ሲወድቁ ‹‹እግዚአብሔር የሁላችንን በደል ይቅር ይበለን›› አላቸው፡፡ ሁለቱ መነኮሳት ወደ ቍስጥንጥንያ ተመልሰው ለሊቀ ጳጳሳቱና ለሕዝቡ ያዩትን ነገር መሰከሩ፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም እጅግ ተደንቆ ወደ ንጉሡ ደብዳቤ ጽፎ ‹‹በምድራችን ጻድቅ ሰው ተገኝቷልና አንተም ና ሄደን በረከቱን እንቀበል›› ብሎ መልእክት ላከበት፡፡ ንጉሡም እሺ ብሎ ከሠራዊቱ ጋር ተነሥቶ ከካህናቱ ጋር ወደ አባ መቃርስ ዘንድ ሄዱ፡፡ ወደ ገዳሙም በቀረቡ ጊዜ አባ መቃርስን ወደ ብሔረ ሕያዋን ያደርሰው ዘንድ መልአክ አንሥቶ በክንፎቹ ተሸክሞት ሲያርግ አዩት፡፡ እነርሱም ‹‹የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ባርከን፣ የምንድንበትንም አንዲት ቃል ንገረን›› አሉት፡፡ አባ መቃርስም ‹‹ከሐሜትና ከነገር ሥራ አንደበታችሁ ይከልከል፤ ካህን ብዙ ባይማር ትዕቢትና መታጀር ባልመጣበት ነበር፣ መነኩሴም ትኅርምት ባያበዛ ባልተመካም ነበር፡፡ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ እግዚአብሔር አድሮባችሁ ይኑር›› አላቸው፡፡ ይህንንም ከተናገራቸውና ከባረካቸው በኋላ ከዐይናቸው ተሰወረ፡፡ ይህም ዕርገቱ ታኅሣሥ 13 ቀን የተፈጸመ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_አብራኮስ_ገዳማዊ ዳግመኛም በዚህች ቀን መነኮስ አቡነ አብራኮስ ገዳማዊ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ዕድሜው 20 ዓመት በሆነው ጊዜ የዚህን ዓለም ኃላፊነት ተረድቶ የነፍሱን ድኅነት ሽቶ መንኩሶ ገዳም ገባ፡፡ በዚያም በታላቅ ተጋድሎ ሲኖር ሰይጣን በቅናት ተነሳስቶበት ብዙ ፈተናዎችን አመጣበት ነገር ግን ቅዱስ አብራኮስ ጽኑ በሆነው መንፈሳዊ ተጋድሎው ሰይጣንን ድልነሣው፡፡ ሰይጣንም በተደጋጋሚ መሸነፉን አይቶ የፈተናውን ዓይነት ለወጥ አድርጎ በሰንፍና ሊጥለው ፈለገ፡፡ እናም ሰይጣን በግልጽ ፊት ለፊት ተገልጦ ቅዱስ አብራኮስን ‹‹እነሆ ከዚህ ዕድሜህ ሌላ 50 ዓመት ቀረህ›› አለው፡፡ ቅዱስ አብራኮስም ሰይጣን በስንፍና ሊጥለው ያመጣበት ፈተና መሆኑን ዐውቆ በተራው ሰይጣን ላይ ተራቀቀበት፡፡ እንዲህም አለው፡- ‹‹አሁንስ ልቤን አሳንከው፣ እኔ ሌላ መቶ ዓመት እኖር ዘንድ ስላሰብኩ ቸል ብያለሁ ነገር ግን አንተ እንዳልከው 50 ዓመት ከሆነ የምኖረው ከቀድሞው እጅግ አብዝቼ እጋደል ዘንድ ይገባኛል›› አለው፡፡ ሰይጣንም ይህን ጊዜ አፍሮ ከእርሱ ሸሸ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አብራኮስ ጽኑ የሆነ ተጋድሎውን በገድል መጠመዱን አብዝቶ ከ70 ዓመት ተጋድሎው በኋላ በሰላም ዐረፈ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_በጽንፍርዮስ_ሰማዕት በዚህች እለት የሰማዕት ቅዱስ በጽንፍርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ አባት ዓለምን ንቆ በመመንኮስ በታላቅ ተጋድሎ ይኖር ነበር፡፡ የሚያገለግለውም በምስር አገር በወንዝ ዳር ባለች በሊቀ መላእክት በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለቀናች ተዋሕዶ ሃይማኖቱም ከእስላሞች መሳፍንት ጋር ተከራከረ፡፡ የጌታችንም የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነቱን ገለጠላቸው፡፡ እስላሞችም ባፈሩ ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጡ፡፡ ከዚህም በኋላ እስላሞች አባ በጽንፍርዮስን ይዘው በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ በመጨረሻ ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን መልእክት አና ጻድቃን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_13 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ ሦስት በዚህች ቀን #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱና ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፣ ታላቁ አባት #አባ_መቃርስ_ገዳማዊ ዓመታዊ የዕርገታቸው መታሰቢያ ነው፣ መነኮስ #አቡነ_አብራኮስ_ገዳማዊ ዕረፍታቸው ነው፣ የሰማዕት #ቅዱስ_በጽንፍርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል ታኅሣሥ ዐስራ ሦስት በዚህች ቀን በዚህች ዕለት ፈታሄ ማህጸን ሊቀ መልአክት ቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱና ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፡፡ ሰማያውያን ከሆኑ ከመላአክት አለቆች ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ 3ተኛ ነው፡፡ "ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ” እንዲል፡፡ ጦቢት 12፡15፡፡ ሩፋኤል የሚለው የስሙ ትርጓሜ ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል መልአከ የሰላምና የጤና መልአክ ይባላል፡፡ በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ሆነ ቁስል ይፈወስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” መጽሐፈ ሄኖክ 6፡3፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የሰው ልጆች ከተያዙበት የኀጢአት ቁስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የማይለይ መልአክ ነው፡፡ “በበሽታ ሁሉ ላይ በሰው ልጆችም ቁስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡” በማለት ሄኖክ ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል፡፡ ሄኖክ 10፡13፡፡ ለሴቶች ረዳታቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ በማኅፀን ላለ ችግርና ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም፡፡ ሕፃኑ ዐርባ ቀን ሞልቶት በማሕፀን እያለ ማለትም በሥላሴ አርአያ መልኩ መሳል ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል አይለየውም፡፡ በመውለጃቸው ቀን ሴቶች ከሚደርስባቸው ጭንቀትና ሕመም ስሙን ጠርተው ይማጸኑታል፡፡ ፈታሔ ማኅፀን ነውና ቅዱስ ሩፋኤልም ጭንቀታቸውን ያቀላል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነት ያለን ረቂቅ ርኩስ መንፈስ ያውቃል፡፡ አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ጭን ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሠቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል ጦቢት 3፡8-17፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው አለው” ሄኖክ 3፡5-7፡፡ በዚህ መሠረት ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሄኖክ 2፡18፡፡ ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠብቃቸው እግዚአብሔር እንዳዘዘዉ የሚከፍታቸዉ የሚዘረጋቸዉ ይህ ታላቅ መልአክ ነዉ፡፡ የምህረትና የረድኤት መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ከሥራዎቹ አንፃር በተለያየ ስም ይጠራል፡፡ "ፈታሄ ማህጸን" ይባላል-እናቶች ሲወልዱ ምጥ እንዳይበዛባቸዉ የሚራዳ መልአክ ስለሆነ አያሌ ክርስቲያኖች ማርገዛቸዉን ካወቁ ጀምሮ ድርሳኑን በማንበብ መልኩን በመድገም ጠበሉን በመጠጣት ሰዉነታቸዉን በመቀባት ይለምኑታል፡፡ እንደ እምነታቸዉ ጽናት ይደረገላቸዋል፡፡ ዳግመኛም "ዐቃቤ ኖኀቱ ለአምላክ" ይባላል-ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠበቅ ስለሆነ ነው፡፡ ዳግመኛም "መራሔ ፍኖት" ይባላል-ጦቢትን በቀና መንገድ መርቶታልና ነው፡፡ እንዲሁም "መላከ ክብካብ" ይባላል-ጦቢያና ሣራን ያጋባ ጋብቻቸዉን የባረከ በመሆኑ ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያደረገው ተዓምር ይህ ነው፡፡ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዓል እስኪፈፀም ድረስ በከበረ ሊቀ ጳጳስ አባ ቴዎፍሎስ ዘመን በምድረ ግብጽ ውስጥ ከእስክንድርያ ውጭ በታናፀች አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ ይህች ቤተ ክርስቲያን ከአሳ አንበሪ ላይ የታነፀች ነበር፡፡ ነገር ግን በወደቡ አጠገብ ከነበረ ግዙፍ አንበሪ ጀርባ ላይ መታነጿን ቀድሞ ያነጿት ሰዎች ቢሆኑ ከካህናትም ቢኾን ያወቀ አልነበረም፡፡ ያ አንበሪም የቤተክርስቲያኑ ህንጻ በከበደው ጊዜ ፈጽሞ ተንቀሳቀሰ፡፡ ከአሸዋማው መሬት ላይ በባህሩ ዳርቻ የታነፀች ይህች ቤተ ክርስቲያንም ከመሰረቷ አናወጻት፡፡ ያን ጊዜ ትልቁም ትንሹም ወንዱም፣ ሴቶችም፣ የተሾሙ ዲያቆናት፣ ካህናት፣ ሕዝቡም ሁሉ ደነገጡ ታወኩ፡፡ አሣ አንበሪው ግን መንቀሳቀሱን አልተወም፡፡ በመንቀሳቀሱም የቤተ ክርስያኗ ሕንፃ እኩሌታ ይሰነጠቅ ዘንድ ጀመረ፣ ምድርን ተናወፀች፣ ንጉስና፣ ሊቀ ጳጳሳቱም፣ ካህናቱም፣ ዲያቆናቱም፣ ህዝቡም፣ ሁሉም ካሉበት በባህሩ ወደብ ከተሰራች ከዚህች ቤተ ክርስቲያን መናወጥ የተነሳ ፍርሃት መንቀጥቀጥ በላያቸው ወረደ፡፡ ያ አንበሪ ግን በባህሩ ውስጥ ወደፊት መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ቤተ ክርስቲያኗም በጀርባው ላይ ነበረች፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ የሉትም ሁሉ ያ አሳ አንበሪ ወደ ባሕሩ ውስጥ ሊያሰጥመን ነው ሲሉ አሠቡ፡፡ ያን ጊዜም በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ስዕል ፊት በጽኑ አለቀሱ፡፡ በአንድ ቃልም "ገናናው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ ርዳታህ ፈጥኖ ይደርስልን ዘንድ በቅድስት ቤተክርስቲያን ወደተሰበሰብን ወዳጆችህ ተመልከት" እያሉ ይጸልዩ ጀመር፡፡ ያንጊዜም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ከሰማይ ወርዶ ያችን ቤተክርስቲያን በብሩሃት ክንፎቹ እንደደመና ጋረዳት፡፡ በእጁ በተያዘ የብርሃን በትረ መስቀሉ ያን ኣሣ አንበሪ ወገቶ "በኢየሱስ ክርስቶስ ሃይል ከቦታህ ሳትንቀሳቀስ እስከትውልድ ፍፃሜ ዘመን ለዘለአለም ትኖር ዘንድ አዝዝሃለሁ" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ሊቀመላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያኗን ከነመዓዘኗ ከግርግዳዎቿ ከመሠዊያዋ በውስጧ ተተክለው ካሉት ሁሉ ጋር ከጀርባው ላይ እያለች ያንን አሳ አንበሪ ወግቶ በያዘበት ብርሃናዊ በትረ መስቀሉ ወደቀድሞው የባሕሩ ወደብ ጎተተው፡፡ ያንጊዜም ግንቡ ቦታውን ሳይለቅ እርስ በእርሱ ተጣበቀ፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አሣ አንበሪውን በቀድሞ ሥፍራው ያቺን ቤተክርስቲያን በቀደመ መሠረቷ ላይ አጽንቷቸዋልና፡፡ ሊቀመላእክት ቅዱስ ሩፋኤልም አዳኝ የሆነ የጌታው የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ጠርቶ ከሞት እንዳዳናቸው ሁሉም አስተዋሉ፡፡ በድንቅ ተዓምራቱ የዳኑ ንጉሡና ሕዝቡም ሁሉ በሊቀመላእክቱ ቅዱስ ሩፋኤል ላይ አድሮ ድንቅ ተዓምራቱን ስለገለጸላቸው የቅዱስ ሩፋኤልን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ የዚህች ቤተክርስቲያን ታሪክም በዓለም ሁሉ በየአውራጃዎቹም ተሰማ፡፡ የቅርብም የሩቅም ሰዎች ሁሉ ተሰብስበው ታላቁ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የለመኑትን ሁሉ ያደርግላቸው ዘንድ የነገሩትን ያማልዳቸው ዘንድ በውስጧ ይጸልያሉ፡፡ በዚችም ቤተክርስትያን ብዙ ውስጥ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተደረጉ፡፡ ታኅሣሥ 13 ቀንም ተአምራቶቹ ከተፈጸመባቸው ዕለታት አንዷ ናት፡፡ ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ተከናውኗል፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_መቃርስ_ገዳማዊ

ያመጣለት ነበር፡፡ አባታችንም ከገዳም ወጥቶ መሄድ በፈለገ ጊዜ አንበሶችን እንደ ፈረስና በቅሎ ይጋልባቸዋል፣ መጻሕፍቶቹንም ይጭንባቸዋል፤ መንታ የወለደች አንበሳም ብትኖር ልጆቿን እየታቀፈ በየተራ ያጠባቸው ነበር፡፡ ወደ ደብረ ዋሊም በሄደ ጊዜ ጌታችን ተገልጦለት በዕለቱ የእመቤታችን በዓል ስለነበር እንዲቀድስ ነግሮት ከሰማይ ኅብስትና ጽዋ መጥቶለት ቅዱሳን ሐዋርያት በቀኝ በግራ እየተራዱት ሲቀድስ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ ኅብስቱንና ጽዋውን ጋርዶታል፡፡ ጌታችንም ቦታዋንና በዚያ ያሉትን መነኮሳት ሁሉ ልጆቹ ይሆኑ ዘንድ አስራት አድርጎ ሰጠው፡፡ ዋልድባ የተመሠረተው በቀደምት ጥንታዊያን አበው ቢሆንም አባ ሳሙኤል ሲገቡበት ምድረ በዳ ሆኖ ጠፍቶ ቋያ በቅሎበት የወባ ትንኞች መፈልፈያ ሆኖ ነበር፡፡ አባታችን ግን የተበታተኑትን መነኮሳት ሰብስበው ዋልድባን እንደገና አደራጅተውና አድሰው አቀኑት፡፡ የተባሕትዎ ኑሮንም አጠናከሩበትና ገዳሙን የመናንያን አበው መሰብሰቢያ አደረጉት፡፡ አባታችን ዋልድባን እንደ ሞሰብ አንስተው አስባርከዋታል፡፡ አባ ሳሙኤል ጊዜው ደርሶ ከማረፉ በፊት ቅዱስ ሚካኤል ነሐሴ 16 ቀን ወደ ገነት ነጥቆ ወስዶ ከዕረፍቱ በኋላ ከልጆቹ ጋር የሚኖርበትን ሥፍራ አሳይቶታል፡፡ በገነት ያሉ ቅዱሳንን ሁሉ ካሳየው በኋላ በእግዚአብሔርም ዙፋን ፊት ቀርቦ ምስጋናና ቃልኪዳንን ተቀብሎ ወደ በዓቱ ተመልሶ ታኅሣሥ 12 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፎ ነፍሱን ጌታችን በእጆቹ ተቀብሏታል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ የገባላቸው ልዩ ቃልኪዳን፡- ‹‹መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ወደ ገነት ነጥቆ ወስዶ በዚያ ያሉ ቅዱሳንን ሁሉ መኖሪያቸውንና ክብራቸውን አሳየኝ፡፡ ‹እነሆ የተጋድሎህን ሥራ ፈጽመሃልና አንተም ወደተዘጋጀችልህ ትመጣ ዘንድ ጊዜህ ቀርቧል› ብሎ ጌታዬ የሰጠኝን መኖሪያዬን አሳየኝ፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ልዑል ዙፋን ወደ አርያም አደረሰኝ፡፡ በዚያም በክብሩ ዙፋን በአባቱ ቀኝ ተቀምጦ ተወዳጅ ወልድን አየሁት፡፡ በዚያም እመቤታችን ማርያምን ከተወዳጅ ልጁዋ ቀኝ አየኋት፡፡ የብዙ ብዙ ቅዱሳን መላእክትና ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ በየወገናቸው ‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የክብር ምስጋና ሰማያትንና ምድርን መላ› እያሉ በፊቱ ይዘምሩ ያመሰግኑ ነበር፡እኔም በአምላኬ ፊት ሰገድኩ፡፡ ተወዳጅ ወልድም ተናገረኝ፣ እንዲህም አለኝ፡- ‹ወዳጄ ሳሙኤል ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፣ ደስ ይበልህ፡፡ በጥቂቱ የታመንህ ባሪያዬ ሆይ በብዙ እሾምሃለሁ፡፡ እኔን በመውደድ ብዙ ደክመሃልና የመስቀሌንም መከራ በመሸከም እኔን መስለሃልና እኔም በመንግሥቴ መልካም የሆነውን የድካምህን ዋጋ እሰጥሃለሁ፡፡ እነሆ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የተካከለ መቀመጫህንና አክሊልህን አዘጋጀሁልህ፣ ዕድል ዕጣህም ከአሥራ ሁለቱ ቅዱሳን ሐዋርያቶቼ ጋር ነው፡፡ አፅምህ በተቀበረበት፣ የገድልህ መጽሐፍ በተነበበት፣ መታሰቢያህ በተደረገበት፣ ሥፍራ ሁሉ ምሕረትና ድኅነት ይሁን፡፡ በጸሎትህ የሚታመነውን፣ መታሰቢያህን የሚያደርገውን ሁሉ ለአንተ አሥራት ሰጥቼሃለሁ፡፡ ስለ እኔ የተቀበልከውን ድካም ሁሉ ዛሬ ያገኘኸውን የአንዲት ቀን የደስታ ልክ አይሆንም፡፡›› ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሰማዕታቱ_ቅዱስ_አንቂጦስ_እና_ቅዱ_ፎጢኖስ ዳግመኛም በዚህች ቀን ወንድማማቾቹ ቅዱሳን አንቂጦስ እና ቅዱስ ፎጢኖስ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ መእመናንን የሚያሠቃይባቸውን የማሠቃያ መሣሪያዎች ለሕዝቡ እያሳየ ሲያስፈራራ የጸኑንም ሲገድል ቅዱስ አንቂጦስ በሕዝቡ መሐል ቆመና ንጉሡን ስለከንቱ እምነቱ ዘለፈው፡፡ ንጉሡም ይዞ ብዙ ካሠቃየው በኋላ በሕዝቡ ፊት ለተራበ አንበሳ ሰጠው፡፡ ነገር ግን አንበሳው ቅዱስ አንቂጦስን ፊቱን አሻስቶ ሲተወው በማየቱ ንጉሡ ሰይፉን መዞ ሊሰይፈው ሊሄድ ሲል መንቀሳቀስ ተሳነው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰውነትን ቆራርጦ ወደሚጥል መንኮራኩር ውስጥ ከተተው ነገር ግን ሰማዕቱን ጌታችን ፍጹም ጤነኛ አድርጎ አስነሣው፡፡ ንጉሡ ዳግመኛ ቅዱስ አንቂጦስ እርሳስ ካፈሉበት ትልቅ ጋን ውስጥ ቢጨምረውም የታዘ መልአክ ከጋኑ ውስጥ ነጥቆ አውጥቶ በንጉሡ ፊት አቆመው፡፡ ይህን ጊዜም ወንድሙ ፎጢኖስን አንጢቆስን አቅፎ ካሳመው በኋላ ንጉሡን ‹‹አንተ ከዳተኛና ጎስቋላ ንጉሥ ወንድሜን ታሸንፈው ዘንድ አይቻልህም አምላኩ ይጠብቀዋልና›› አለው፡፡ ንጉሡም የሚያደርግባቸውን ነገር እስኪያስብ ድረስ ቅዱሳኑን ወንድማማቾቹን እጅና እግራቸውን አሳሥሮ ወህኒ ቤት ጨመራቸው፡፡ በማግሥቱም አውጥቶ ሰውነታቸውን ጥፍር ባለው ብረት ሰነጣጠቃቸው፡፡ ወደ አደባባይም አውጥቶ በድንጋይ አስወገራቸው፡፡ ከብዙ ግርፋትም በኋላ በቁስላቸው ላይ ጨው ጨምሮ ካሠቃያቸው በኋላ እሳት ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ነገር ግን አሁንም እሳቱ እንደቀዝቃዛ ጠል ሆነላቸው፡፡ ንጉሡም ይህን ባየ ጊዜ ነበልባሉ ከፍ ብሎ እስኪታይ ድረስ እሳት አስነድዶ ከዚያ ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ቅዱሳኑም ከእሳቱ ውስጥ ሆነው በመስቀል ምልክት አማትበው ረጅም ጸሎት ካደረጉ በኋላ ቅድስት ነፍሳቸውን ለእግዘኢብሔር አሳልፈው ሰጡ፡፡ የሥጋቸውም በድን ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት ድረስ ከእሳቱ ፍሕም ላይ ነበር ነገር ግን የራሳቸው ፀጉር እንኳን አልተቃጠለችም ነበር፡፡ ምእመናንም ቅዱስ ሥጋቸውን ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ አስደናቂ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_12 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ ሁለት #የአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ዐረፉ፣ #ቅዱሳን_አንቂጦስ እና #ቅዱስ_ፎጢኖስ በሰማዕትነት ዐረፉ፣ #ዳግማዊ_ቂርቆስ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልጅ ብሔረ ብፁዓን የገባበት ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ታኅሣሥ ዐስራ ሁለት በዚህች ዕለት ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ ቅዱስን መንበር ያጠኑ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ዋሊ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ የተወለዱት በአክሱም ጽዮን ነው፡፡ ነገዳቸው የአክሱም ገበዝ ከነበረው ከጌድዮን ነው፡፡ የአባታቸው እስጢፋኖስና እናታቸው አመተ ማርያም ምግባር ሃይማኖታቸው የቀና ትሩፋት ተጋድሏቸው የሰመረ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ገና በ12 ዓመቱ ማይ ሹም በተባለው ባሕር ገብቶ ሲጸልይ ባሕሩ በብርሃን ተከቦ ይታይ ነበር፡፡ ከባሕሩም ወጥቶ ወደ ቤተክርስቲያን ገብቶ እያለቀሰና እያዘነ ሲጸልይ ካህናቱ ‹‹ይህ ሕፃን የእኛ ኃጢአት እየታየው? ወይስ ምን ኃጢአት ኖሮበት ነው እንዲህ የሚያዝነውና የሚያለቅሰው?›› እያሉ ያደንቁና ይገረሙ ነበር፡፡ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ እናቱ አመተ ማርያም ቤተሰቧንና ቤት ንብረቷን ትታ ከመነኮሰች በኋላ እርሱም ካልመነኮስኩ በማለት አባቱ እስጢፋኖስን ቢለምነውም እምቢ ስላለው በራሱ ፈቃድ ከአንድ ሽማግሌ ጋር ወደ አባ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ደብረ በንኰል ገብቶ መነኮሰ፡፡ በዚያም ነፍሱን ‹‹ነፍሴ ሆይ! እነሆ ለክርስቶስ ታጨሽ፣ የቅዱሳንን ቀንበር እንሆ ተሸከምሽ፣ የመላእክትን ንጽሕና ትጠብቂ ዘንድ ዛሬ በእግዚአብሔርና በቅዱሳኑ ሁሉ ፊት ቃልኪዳን ገባሽ፣ ቃልኪዳንሽን ብትጠብቂ መላእክት ይደሰቱብሻል፣ ባትጠብቂ ግን አጋንንት ይዘባበቱብሻል…›› እያለ ብዙ መከራን በራሱ ላይ በማብዛት ሰባት ዓመት በዚያች ገዳም ኖረ፡፡ እህልም አይቀምስም ነበር ይልቁንም የሚሰጡትን እንጀራ ለሕጻናትና ለውሾች እየሰጠ አሠር ይመገብ ነበር፡፡ ዳግመኛም በሌላ ጊዜ ቅጠልን እየቀቀለ እስከ አምስት ቀን ከድኖ ያስቀምጠዋል፣ እስከሚተላም ድረስ ይጠብቀውና ያን ይመገባል፡፡ ኩስይ የምትባል ከሣር ሁሉ የምትመርን ሣር ምግቡ አደረገ፡፡ በኋላም አባቱም ልጁን ሳሙኤልን ተከትሎ ወደ እርሱ መጥቶ በአባ እጅ መነኮሰ፡፡ ለአባቱም መምህር ሆኖት እያገለገለው ያስተምረው ነበር፡፡ በሌላም ጊዜ 17 ዓመት ከተቀመጠባት ወይና በምትባል ቦታ ሲኖር ከውኃ በቀር ምንም ሳይቀምስ 12 ዓመት ተቀምጧል፡፡ ለ50 ዓመትም ያህል ሣር፣ ቅጠል፣ የዛፍ ሥርና ፍሬን እነዚህንና የመሳሰሉትን እየበላ ኖረ እንጂ እህል የሚባል አልበላም፡፡ ወጥቶም ወደ ዋሻ እየገባ ብዙ ጊዜ 40 ቀንና 40 ሌሊት በጾም በጸሎት እየኖረ እንቅልፍም እንዳያሸንፈው እስከሚነጋ ድረስ ሳይቆም ሳይተኛ እንደቆመ በጽኑ ተጋድሎ ተቀመጠ፡፡ ትልቅ ጉድጓድ ቆፍሮ በውስጡ እየገባ ሳይቀመጥ ሳይተኛ ሰውነቱ እንደ እንጨት እስኪደርቅ ድረስ በጾም በጸሎት በእጅጉ ይተጋ ነበር፣ በዚህም ወቅት ጌታችን ተገልጦለት ሰውነቱን በሙሉ ምራቁን ስለቀባለትና አውራ ጣቱን ስላጠባው ከዚህ ጊዜ በኋላ ርሀብና ጥሙ ጠፍቶለት ሰውነቱም ታድሶለታል፡፡ ዳግመኛም በአፉም ድንጋይ ጎርሶ፣ እግሩንም ታስሮና ማቅ ለብሶ ወደ ባሕር እየገባ ይጸልይ ነበር፡፡ አባታችን አባ ሳሙኤል በሕይወተ ሥጋ ሳለ እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን አድርጓል፡፡ እንደሙሴ ባሕርን የከፈለበት ጊዜ አለ፤ በልዑልም ዙፋን ፊት እየቀረበ ከቅዱሳን መላእክት ጋር የሚያመሰግንበት ጊዜ አለ፣ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይም ጋር ሆኖ የሚያጥንበት ጊዜ አለ፤ በሰማያዊት ኢየሩሳሌምም ሆኖ ከእነ ቅዱስ ጴጥሮስና ከሁሉ ቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ጋር በአንድ ላይ ማዕድ የሚቀርብበት ጊዜ አለ፤ በእጆቹ የያዛቸው መጻሕፍቶቹ ምንም ሳይርሱ ትልቅ ወንዝን በውስጡ እያቋረጠ የሚሻገርበት ጊዜ አለ፤ እመቤታችንንም ሲያመሰግናት ከምድር ወደ ላይ አንድ ክንድ ያህል ከፍ የሚልበት ጊዜ አለ፤ በቤትም ውስጥ ሆኖ ምስጋናዋን ሲጀምር የቤቱ መሠረት እየተናወጠ ዝናብ እንደያዘ ደመና ቤቱ ከምድር ከፍ ብሎ የሚቆምበት ጊዜ አለ፤ መንፈስ ቅዱስም በብርሃን ክንፍ እየወሰደው ወደተለያዩ ገዳማት ያደርሰውና ሥጋ ወደሙን እንዲቀበል ያደርገው ነበር፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም የሁልጊዜ ጠባቂው ነውና በሁሉ ነገር ይራዳውና እንደ ጓደኛም ያማክረው ነበር፡፡ በአንዲት ዕለትም በጎዳና ሲጓዝ ወንዝ መልቶበት አገኘው፡፡ አባታችንም መጻሕፍቶቻቸውንና እሳት በእጃቸው እንደያዙ በወንዙ ውስጥ ለውስጥ ውኃውን አቋርጠው ሲሻገሩ መጻሕፍቶቻቸው አልራሱም በእጃቸው የነበረው እሳትም አልጠፋም ነበር፡፡ አባታችን ሊያስቀድሱ ወደ በተ መቅደስ በሚገቡ ጊዜ ሰማያዊ ኅብስትና ጽዋ ይወርድላቸው ነበር፡፡ የእመቤታችንንም ውዳሴዋን ሲደግሙ ክንድ ከስንዝር ያህል ከምድር ከፍ ይሉ ነበር፡፡ እመቤታችንም እየተገለጠች ንጹሕ ዕጣንንና የሚያበራ እንቁን ሰጥታቸዋለች፡፡ ቅዱስ አባታችን ለክቡር ሥጋ ወደሙ እጅግ ትልቅ ክብር አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያን አስቀድሰው ሁሉም ሥጋ ወደሙን ተቀብለው ወደ ቤታቸው ሲወጡ ከአራቱ መነኮሳት ውስጥ አንዱ አስታወከ፣ በቤተክርስቲያንም ዳርቻ ተፋው፡፡ ያዩትም ሁሉ ደንግጠው ቆሙ፡፡ የእግዚአብሔር ሰው ብፁዕ ሳሙኤል ግን ሁሉንም በአፉ ተቀበለው፣ በምላሱም መሬቱን ላሰው፡፡ ይህን ጊዜ ከሰማይም ‹ሳሙኤል ሳሙኤል› የሚልን ድምጽ ሰማና ወደላይ ባንጋጠጠ ጊዜ ሰባቱ ሰማያት ተከፍተው አየ፡፡ ከላይ ያለው ያ ቃልም መለሰ፡- ‹በሰው ፊት እንዳመሰገንኸኝና ፈጽሞም እንዳከበርከኝ የባልንጀራህን ትውኪያ ትቀበል ዘንድ እንዳላፈርህ እኔም እንዲሁ አከብርሃለሁ፤ በሰማያት ባለው በአባቴም ፊት በመላእክት ማኅበር አመሰግንሃለሁ› አለው፡፡›› ሌሎቹም ቅዱሳን እነ አቡነ ተክለሐዋርያትም እንዲሁ ለሥጋ ወደሙ ክብር ሲሉ የቆረበ ሰው ሲያስመልሰው የዚያን ሰው ትውኪያ ይጠጡት እንደነበር በቅዱስ ገድላቸው ላይ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን ለክርስቶስ ያላቸው ክብር እስከዚህ ድረስ ነው፡፡ አንድ ቀን አባታችን በገዳም ውስጥ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይጎበኘው ዘንድ ወደ እርሱ መጣ፡፡ ከእርሱም ጋር ተቀምጦ ‹ወዳጄ ሆይ! ሰላምታ ይገባሃል፡፡ አንተ ግን ከትንሽነትህ ጀምሮ አገለገልኸኝ፣ ምን አደርግልህ ዘንድ ትወዳለህ?› አለው፡፡ ትሑት ሳሙኤልም ‹የነፍሴ ወዳጅ ጌታዬና አለቃዬ ሆይ! መልካም ሀብት ሁሉ ከአንተ ዘንድ ነውና ምሕረትህንና ብሩህ ፊትህን ታሳየኝ ዘንድ እሻለሁ› አለ፡፡ ጌታችንም ‹አገልጋዬ ወዳጄ ሆይ! የፈለግኸውን እሰጥሃለሁ፣ ዳግመኛም ያልፈለግኸውንም እጨምርልሃለሁ› አለው፡፡ አባ ሳሙኤልም ‹ጌታዬ ሆይ! አንዲት ልመናን እለምንሃለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ኃጢአቴን አይ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ የሌላውን ኃጢአት ግን አታሳየኝ› አለው፡፡ አባ ሳሙኤልን የዱር አራዊትም ሁሉ ይገዙለት ነበር፡፡ ታላቅ የሆነ ዘንዶ፣ ነብር፣ ጅብ፣ ቶራህ፣ ዝሆን፣ አንበሳና ሌሎችም የዱር አራዊት ሁሉ እየመጡ እግሩን እየላሱት ወደ ቦታቸው ይመለሱ ነበር፡፡ አንበሶቹንም እሾህም በወጋቸውና እግራቸው መግል በያዘ ጊዜ በመርፌ እያነቆረ ያድናቸው ነበር፡፡ ስንጥርም ሲወጋቸው ወደ እርሱ እየመጡ ያሳዩትና ያወጣላቸው ነበር፡፡ አንበሳም አጋዘንን ገድሎ ሲበላ ሲያየው ‹‹አንዴ ዞር በልልኝ ቆዳዋን ለልብሴ እፈልገዋለሁ›› ባለው ጊዜ ይለቅለት ነበር፡፡ እንዲሁም አንበሳው ለአባታችን ምግብም ትሆነው ዘንድ ጅግራን እየያዘ በሕይወት ሳለች

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ገላውዴዎስን አስጠርቶ የአባቱን ሹመት እንደሚሾመው ቃል ከገባለት በኋላ ለጣዖቱ እንዲሠዋ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስ ግን በድፍረት ጣዖቱንና ንጉሡን ሰደባቸው፡፡ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ኅርማኖስ የተባለው ባለሟሉ ‹‹እንደ ልጄ ፊቅጦር ዐመፀኛ ነውና ወደ እስክንድርያ ልከነው በዚያ እንዲገድሉት እናድርግ›› ብሎ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስን መከረው፡፡ አሠቃይተው እንዲገድሉትም ከደብዳቤ ጋር አድርገው ወደ እንዴናው ሀገር ገዥ ወደ ጨካኙ አርያኖስ ላኩት፡፡ አርያኖስም ቅዱስ ገላውዴዎስን ባየው ጊዜ ደንግጦ በክብር ተቀበለው፡፡ እጅ ነሥቶም ከሳመው በኋላ ‹‹ጌታዬ ስለምን የንጉሡን ትእዛዝ ትተላለፋለህ?›› እያለ መከረው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስም ‹‹ንጉሡ ያዘዘህን ትእዛዝ ልትፈጽም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላኩም›› አለው፡፡ መኮንኑም እስኪቆጣ ድረስ ብዙ ጊዜ እያባበለው ተነጋገሩ፡፡ ከዚህም በኋላ አርያኖስ እጅግ ተቆጣና በያዘው ጦር ወግቶ ቅዱሱን ገደለው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ምእመናንም የመከራው ዘመን እስኪፈጸም ቅዱስ ሥጋውን ወስደው ከቅዱስ ፊቅጦር ጋር በሣጥን አኖሩት፡፡ የቅዱስ ፊቅጦርም እናት ቅድስት ሶፍያ ወደ እንዴና ሀገር መጥታ የሁለቱን ቅዱሳን ሥጋቸውን ወደ አንጾኪያ ወስዳ በክብር አኖረችው፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት አና ጻድቃን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ_11 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስራ አንድ በዚህች ዕለት ታላቁ አባት #ቅዱስ_አባ_በኪሞስ ዐረፈ፣ ታላቁ ሰማዕት #ቅዱስ_ገላውዲዮስ ልደቱ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ታላቁ_አባት_ቅዱስ_አባ_በኪሞስ ታኅሣሥ ዐስራ አንድ በዚህች ዕለት ታላቁ አባት ቅዱስ አባ በኪሞስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ መጺል ከምትባል አውራጃ የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ እርሱም የአባቱን በጎች የሚጠብቅ እረኛ ነበር፡፡ ዕድሜውም 12 ዓመት በሆነው ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ በሰው አምሳል ተገለጠለትና ‹‹በአንድነት ሄደን እንመነኩስ ዘንድ ትሻለህ?›› አለው፡፡ በኪሞስም በዚህ ደስ ተሰኝቶ ሁሉቱም ተስማምተው አብረው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገቡ፡፡ በዚያም ሦስት አረጋውያን መነኮሳት አገኙና አባ በኪሞስ ከእነርሱ ጋር 24 ዓመታትን ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ በኪሞስ ከዚያ ተነሥቶ የሦስት ቀን ጎዳና ተጓዘና ሩቅ ወደሆነ በረሃ ሄደ፡፡ በዚያም ሰይጣናት በእሪያዎችና በዘንዶዎች አምሳል ሆነው መጡበት፡፡ ሊነክሱትም አፋቸውን ከፍተው በከበቡት ጊዜ እርሱ ግን የአጋንንት ሥራ መሆኑን ዐውቆ በእግዚብሔር ኃይል እፍቢልባቸው እንደትቢያ ተበተኑ፡፡ እርሱም ወንዝ አግኝቶ ሰባት ሰባት ቀን እየጾመ በዚያ ሦስት ዓመት ኖረ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ ላይ በእጁ ቴምር በተአምራት መልቶ ስለሚገኝ እርሱን ይመገባል፡፡ ቅዱሱም በሌሊት ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ በቀንም እንዲሁ ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልያል፡፡ ከዚህም በኋላ 40 40 ቀን እየጾመ 24 ዓመታትን በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡ አርባውም ቀን ሲፈጸም አንድ ጊዜ ይመገባል፡፡ ከዚህም በኋላ ቆዳው ከአንጥንቱ እስኪጣበቅ ድረስ አንድ ጊዜ እስከ ሰማንያ ቀን ጾመ፡፡ በዚህም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ አባ በኪሞስ የሚበላውንና የሚጠጣውን ሰማያዊ የሕይወት ምግብና መጠጥ አምጥቶ መገበው፡፡ ያንንም መልአክ ያመጣለትን ምግባ መጠጥ አባ በኪሞስ እስካረፈበት ጊዜ ድረስ ብዙ ዓመታት ሲመገበው ኖረ፡፡ በአንደኛውም ቀን በሌሊት ጌታችን ለአባ በኪሞስ ተገልጦለት ወደ አገሩ እንዲመለስ ነገረው፡፡ እርሱም ወደ ሀገሩ ተመልሶ በዚያች ትንሽ በዓት አበጅቶ መኖር ሲጅር ብዙዎች ወደ እርሱ መጥተው ፈውስን የሚያገኙ ሆኑ፡፡ እርሱም ጣዕም ባለው አንደበቱ ወንጌልን እያስተማራቸው ድውያንንም ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ በአንዲት ዕለትም የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ በኪሞስን ነጥቆ ወስዶ ወደ ኤፍራጥስ ምድር አደረሰው፡፡ የዚያች አገር ሰዎች ሕግን በመተላለፍ ከእውነተኛ ሃይማኖት ወጥተው ነበርና፡፡ አባ በኪሞስም አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖትና ወደ በጎ ምግባር መለሳቸውና ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በአንዲት ዕለትም ሸጦ የዕለት ምግቡን ያገኝ ዘንድ አገልግሎችን ተሸክሞ ወደ ከተማ ሲሄድ በጎዳና ላይ ደክሞት አገልግሎቹን አስቀምጦ ያርፍ ዘንድ ተቀመጠ፡፡ ወዲያውም ከአገልግሎቹ ጋር የእግዚአብሔር ኃይል ተሸክሞ ወስዶ ከሚሸጥበት ቦታ አደረሰው፡፡ በአንደኛውም ቀን ታላቁ አባት አባ ሲኖዳ ከፍተኛ የዕንቁ ባሕርይ ምሰሶ በራእይ አየና ‹‹ይህ ታላቅ ግሩም የሆነ ምሰሶ ምንድነው?›› ብሎ ደነገጠ፡፡ የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና ‹‹ይህ አባ በኪሞስ ነው›› አለው፡፡ አባ ሲኖዳም አባ በኪሞስን ያገኘው ዘንድ ወደ እርሱ አገር በእግሩ ተጓዘ፡፡ ከዚያም በፊት ከቶ አላየውም ነበር፡፡ ሄዶም ባገኘው ጊዜ ሁለቱ ቅዱሳን ሰላምታ ተሰጣጡና የእግዚአብሔርን ነገር እየተነጋገሩ አብረው እየጸለዩ ጥቂት ቀን ቆዩ፡፡ በአንዲት ዕለት አብረው ሲጓዙ አንድን የሞተ ሰው ራስ ቅል አገኙና አባ ሲኖዳ በበትሩ ነቅነቅ አደረገውና ‹‹ምውት ሆይ! ያየኸውን ትነግረን ዘንድ በጌታችን ስም ተነሥ›› አለው፡፡ ወዲውም ነፍሱ ወደ ዐፅሙ ተመልሳ ሥጋ ለብሶ ተነሣና ሰገደላቸው፡፡ በሲኦል ያየውንም ሁሉ በዝርዝር ነገራቸው፡፡ በየወገናቸው በሲኦል ውስጥ የሚሠቃዩትንና እርሱም የማያምን አረማዊ መሆኑን ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ክብር ይግባውና በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያመኑ ትእዛዙን ግን ያልጠበቁ በአሕዛብ ሥራባ በአረማውያን ርኩሰት የኖሩ በሲኦል ከእኛ በታች የሚኖሩ ክርስቲያኖች አሉ›› ብሎ ነገራቸው፡፡ ቅዱሳኑም ‹‹በል ተመልሰህ ተኛ›› አሉትና እንቀድሞው ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ሲኖዳ አባ በኪሞስን ተሰናብቶ ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡ አባ በኪሞስም የዕረፍቱ ጊዜ ሲደርስ አገልጋዩን ጠርቶ የሥጋውን መቅበሪያ ቦታ አሳየው፡፡ ወዲያውም በሆድ ዝማ ሕመም ጥቂት ታመመና፡፡ ቅዱሳንም ከተለያየ ቦታ በአንድነት ወደእርሱ ሲመጡ በመንፈስ ተመለከተ፡፡ቅዱሱ 58 ዓመት በገዳም በምንኩስና ሥራ ተጠምዶ ኖሮ በሰባ ዓመቱ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም በዝማሬ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አሳረጓት፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ታላቁ_ሰማዕት_ቅዱስ_ገላውዲዮስ ዳግመኛም በዚህች ዕለት ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ገላውዲዮስ ልደቱ ነው፡፡ ገላውዴዎስ ማለት ‹‹ዕንቈ ጳዝዮን›› ማለት ነው፡፡ የመላእክት አርአያ ያለቅ ቅዱስ ገላውዴዎስ አባቱ አብጥልዎስ የሮሙ ንጉሥ የኑማርያኖስ ወንድም ነው፡፡ አባቱን የአንጾኪያ ሰዎች እጅግ ይመኩበትና ይወዱት ነበር፡፡ በሕይወት እያለም በጦርነት ድል ሲያደርግ የሚያሳይ ሥዕሉን በከተማው ላይ አሠርተው ያከብሩት ነበር፡፡ ልጁ ቅዱስ ገላውዴዎስ ግን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እየተማረ አደገ፡፡ የሮሙ ንጉሥም ዜናውን ሰምቶ ሊያየው ወደደና ልጁን እንዲልክለት መልእክት ላከ፡፡ ሄዶ ሲያየውም ንጉሡ ከነሠራዊቱ ወጥቶ በክብር ተቀበለው፡፡ ጣዖት አምላኪ የሆኑ የቁዝና የሌሎችም ሀገሮችን ቅዱስ ገላውዴዎስ ድል እያደረጋቸው ጣዖቶቻቸውንም ይሰባብርባቸው ነበር፡፡ ወደ አንጾኪያም በተመለሰ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታችንን ክዶ ጣዖት ማምለክ መጀመሩን ባየ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ከቅዱስ ፊቅጦርም ጋር ሆነው የመጻሕፍትን ቃል ዕለት ዕለት ያነቡ ነበር፡፡ ሁለቱም ስለ ጌታችን ክብር ሰማዕት ሆነው ደማቸውን ያፈሱ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ ሰይጣንም በሽማግሌ አምሳል ተገልጡ ያዘነላቸው በመምስል ‹‹ልጆቼ ሆይ መልካም ጎልማሶች ናችሁ፣ የነገሥታት ልጆችም ናችሁ፣ እኔ ስለ እናንተ አዝንላችኋለሁ ስለዚህም ከንጉሡ ጋር ተስማምታችሁ አማልክቶቹን እያጠናቸሁ ትእዛዙንም እየፈጸማችሁ ኑሩ፡፡ ነገር ግን ክርስቶስን በቤታችሁ አምልኩት ይህ ዲዮቅልጥያኖስ ግን እጅግ ጨካኝና ኃይለኝ ነው›› እያለ መከራቸው፡፡ እግዚአብሔርንም ይህን የሚናገራቸው ሰይጣን መሆኑን ገለጸላቸውና ‹‹አንተ የሐሰት አባት ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ሀሳብ ትቃረናለህ›› ብለው በገሠጹት ጊዜ መልኩን ለውጦ ጥቁር ባሪያ ሆነ፡፡ ‹‹እነሆ ከንጉሡ ጋር አጣልቼ ደማችሁን እንዲፈስ አደርገዋለሁ›› ብሎ ወደ ከሃዲው ንጉሥ ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ሄዶ ‹‹ፊቅጦርንና ገላውዴዎስን ካልገደልካቸው በአንተ ላይ ይነሱብሃል፣ አንተንም ገድለው መንግሥትህን ይወስዳሉ፣ እነርሱም የመንግሥት ልጆች መሆናቸውን ዕወቅ›› አለው፡፡

የቁርባኑም ሥርዓት ከተፈጸመ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ ከአቡነ ሳዊሮስ ቡራኬ ተቀበሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አባታችን አቡነ ሳዊሮስ ከአንደኛው ገዳም ወደ አንደኛው ገዳም አንድ ተራ መነኩሴ መስለው በስውር እየተዘዋወሩ በየሄዱበትም ምእመናንን እያጠነከሩ በእጆቻቸውም ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ሲያገለግሉ ኖሩ፡፡ በመጨረሻም ስካ ወደሚባል አገር ሄደው ስሙ ዶራታዎስ ከሚባል ደግ ምእመን ባለጸጋ ሰው ዘንድ ተቀምጠው ሳለ ጌታችን በእጆቻቸው ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረገ፡፡ በመጨረሻም በዚህች ስካ በምትባል አገር የካቲት 14 ቀን እስካረፉ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ሁሉንም አስተማሯቸው፡፡ በኋላም ታኅሣሥ 10 ቀን ምእመናን ቅዱስ ሥጋቸውን ዝጋግ ወደምትባል ገዳም አፍልሰውታል፡፡ ጥቅምት 2 ቀን ደግሞ አባታችን ተሰደው ወደ ግብፅ አገር የመጡበት ዕለት ነው፡፡ ከእስክንድርያ ውጭ ወደሆነቸ ደብረ ዝጋግ ገዳም ቅዱስ ሥጋቸው በፈለሰበት ወቅት እንዲህ ሆነ፡- ቅዱስ ሳዊሮስ ስሓ በምትባል አገር አምላክም በሚወድ ደገኛ ክርስቲያን ባለጸጋ ስሙ ዱራታዎስ በሚባል ሰው ዘንድ ባረፉ ጊዜ ከምእመናን ሰዎች ጋር ወደ በመርከብ አሳፍሮ ላከው፡፡ ወደ ደቡባዊ ባሕረ ቅርጣስ በደረሱ ጊዜ ግን መርከባቸውን ማንቀሳስ ፈጽሞ አልተቻላቸውም፡፡ ከዚያም ወደ ደብረ ዝጋግ አድርሰው ያ ባለጸጋ ዱራታዎስ በሠራለት ቦታ ውስጥ አኖሩት፡፡ በግብጽ አገርም ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችን ከሥጋቸው ገለጠ፡፡ ቅዱሱ በሕይወት ሳሉ የወለቀች አንዲት ጥርሳቸውን አንዱ መነኮስ አግኝቶ በጨርቅ ጠቅልሎ በገዳሙ አስቀምጧት ነበርና እርሷም ለሕሙማን ሁሉ ፈውስን የምትሰጥ ሆነች፡፡ እነርሱም ወደ እስክንድርያ ያመጧትና በሕሙማን ላይ ሲያኖሯት ሕሙማኑ ፈጥነው ይድናሉ፡፡ እግዚአብሔርም ቅዱስ ሳዊሮስን በሕይወታቸው ካሉበት ጊዜ ይልቅ በሞት ካረፉ በኋላ እጅግ ከፍ ከፍ አድርጓቸዋል፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_ኒቆላዎስ ዳግመኛም በዚህች ቀን ቅዱስ አባት አባ ኒቆላዎስ አረፈ፡፡ አባቱ ኤጲፋንዮስ እናቱ ዮና ይባላሉ፡፡ እርሱም ሜራ በምትባል አገር እጅግ ባለጸጎች ሆነው የሚኖሩ ደጋግ ሰዎች ናቸው፡፡ እጅግ ባለጸጎች ቢሆኑም ልጅ ስላልነበራቸው እያዘኑ እግዚአብሔርን በመለመን ብዙ ዘመን ኖሩ፡፡ የመውለጃ ጊዜአቸውም ባለፈ ጊዜ ስለ ልጅ መለመናቸውን አቆሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በመጨረሻ ዘመናቸው የተባረከ ይህን ኒቆላዎስን ሰጣቸው፡፡ እግዚአብሔርም በልጃቸው ላይ የጽቅን ሥራ ገለጠ፡፡ ልጁ ገና እንደተወለደ ተነሥቶ በእግሮቹ ቆሞ በሰዎች መካከል ለሁለት ሰዓት ያህል ቆመ፡፡ ይህም ለመንደሳዊ ሥራ የተነሣ ቅዱስ መሆኑን ያጠይቃል፡፡ በሕፃንነቱም የሐዋርያትን ትምህርት ፈጽሞ ረቡንና ዓርብን በመጾም እስከ ዘጠኝ ሰዓት የእናቱን ጡት አይጠባም ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ወላጆቹ ለመምህር ሰጥተውት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ ተማረ፡፡ ወደ ገዳምም ገብቶ ማንም እንደ እርሱ ሊሠራው የማይችለውን ጽኑ ገድል ተጋደለ፡፡ ዘጠኝ ዓመትም በሆነው ጊዜ ቅስና ተሾመና ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ማድረግ ጀመረና ሕመምተኞችን ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ አንድ ባለጸጋ በሀገሩ ነበር፡፡ እርሱም የዕለት እራት እስኪያጣ ድረስ ፈጽሞ ድኃ ሆነ፡፡ አራት ሴት ልጆችም ነበሩትና እነርሱን ስለድኅነቱ የሚያገባቸው ጠፋ፡፡ ባለጸጋ የነበረውም ሰው የዝሙት ሙት ሠርቶ በዚያ ልጆቹ እያመነዘሩ በዝሙት ዋጋ ይኖሩ ዘንድ ይህንን የረከሰ ሀሳብ ሰይጣን አሳሰበው፡፡ እግዚአብሔር ግን የዚያን ባለጸጋ የነበረ ሰው ክፉ ሀሳብ ለአባ ኒቆላዎስ ገለጠለት፡፡ አባ ኒቆላዎስም ከአባቱ ገንዘብ ላይ መቶ የወርቅ ዲናር ወስዶ በሌሊት ማንም ሳያየው ወደዚያ ባለጸጋ ወደነበረው ሰው ቤት ሄዶ በበሩ ሥር አስቀምጦለት ተመለሰ፡፡ ባለጸጋ የነበረውም ሰው ወርቁን ወስዶ እጅግ ደስ ብሎት ታላቂቱን ልጁን አጋባት፡፡ አሁንም ለ2ኛ ጊዜ አባ ኒቆላዎስ መቶ የወርቅ ዲናር አስቀመጠለትና ሰውየውም ሌላኛዋን ታላቅ ልጁን ዳራት፡፡ አባ ኒቆላዎስም ለ3ኛ ጊዜ እንዲሁ አደረገ፡፡ ባለጸጋውም በስተመጨረሻ ‹‹ይህን የሚያደርግልኝ የእግዚአብሔርን ሰው ማየት አለብኝ›› ብሎ ቁጭ ብሎ እያደረ በሌሊት የሚመጣውን መጠበቅ ጀመረ፡፡ አባ ኒቆላዎስም ለ4ኛ ጊዜ ወርቁን ሲያኖርለት አገኘውና ወድቆ ሰገደለት፡፡ ‹‹ከገንዘብና በኃጢአት ከመውደቅ አድነኸኛልና ዋጋህ ፍጹም ነው›› ብሎ አመሰገነው፡፡ አባ ኒቆላዎስ በአካባቢው ባለው ዛፍ ላይ አድረው በሰውየው ላይ መከራ ያመጡበትን አጋንንት አባረራቸው፡፡ በዚያ የነበሩ ሕመምተኞችንም አዳናቸው፡፡ ዳግመኛም ጥቂት እንጀራን አበርክቶ ብዙ ሕዝቦችን አጠገባቸው፡፡ እጅግ የበዛ ትራፊም ተመልሶ ተነሣ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ኒቆላዎስ ኤጲስቆጶስነት ከመሾሙ አስቀድሞ የክህነት ልብስንና ብርሃንን የለበሰ ሰው በዙፋን ላይ ተቀምጦ በራእይ አየና ‹‹ይህንን የክህነት ልብስ ለብሰህ በዙፋኑ ተቀመጥ›› የሚል ድምጽ ሰማ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜም እመቤታችን ተገልጣለት የክህነትን ልብስ ስትሰጠው ጌታችንም የከበረች ወንጌልን ሲሰጠው አየ፡፡ ከዚህም በኋላ የሜራ አገር ኤጲስቆጶስ በሞት ባረፈ ጊዜ የታዘዘ መልአክ ለሮሜው አገር ሊቀ ጳጳስ ተገለጠለትና ስለ አባ ኒቆላዎስ መልኩንና ስሙን በዝርዝር ነገረው፡፡ እርሱም ለሕዝቡ ሁሉ ነገራቸው አባ ኒቆላዎስን ወስደው በሜራ አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ አምለኮ ጣዖትን በግዛቱ ሁሉ ሲያውጅና የክርስቲያኖችን ደም እንደውኃ ሲያፈስ አባ ኒቆላዎስ ደግሞ ክርስቲያኖችን ያስተምራቸውና በሃይማኖት ያጸናቸው ነበር፡፡ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ አባ ኒቆላዎስን ይዞ እጅግ ብዙ አሠቃየው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ከመከራው ሁሉ እያዳነው ከቁስሉም ይፈውሰው ነበር፡፡ ንጉሡም እጅግ ቢያሠቃየውም ቅዱሱ ደግሞ መልሶ ጤነኛ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በዚህም ማሠቃየት ቢሰለቸው ወደ እሥር ቤት ጨመረው፡፡ እግዚአብሔርም ዲየቅልጥያኖስን አጥፍቶት ጻደቁን ቆስጠንጢኖስን እስካነገሰው ድረስ አባ ኒቆላዎስ በእሥር ቤት ብዙ ዓመታት ኖረ፡፡ ቆስጠንጢኖስም የታሰሩትን ቅዱሳን ሁሉ በፈታቸው ጊዜ አባ ኒቆላዎስ ከእሥር ወጥቶ ወደ መንበረ ጵጵስናው ተመለሰ፡፡ ሕዝቡንም ስለቀናች ሃይማኖት አስተማራቸው፡፡ ሃይማኖታቸው የቀና እጅግ የከበሩ 318 ቅዱሳን በአርዮስ ጉዳይ በተሰበሰቡ ጊዜ ይህ ቅዱስ አባት አባ ኒቆላዎስ ከእነርሱ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እርሱም ከሌሎቹ ቅዱሳን ጋር ሆኖ አርዮስን አሳዶ የቀናች ሃይማኖትን ደነገገልን፣ ሥርዓትን ሠራልን፡፡ እርሱም ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ታኅሣሥ 10 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐስር በዚህች ዕለት የአንጾኪያው ሊቅ #ቅዱስ_አባት_አቡነ_ሳዊሮስ ፍልሠተ ሥጋው ነው፣ #ቅዱስ_አባት_አባ_ኒቆላዎስ አረፈ፣ #አባ_ጥዋሽ ዕረፍቱ ነው፣ የከበረች #ቅድስት_ሱርስት ዐረፈች፣ ቅዱሳን ሰማዕታት #ቅዱስ_ተላስስና_ቅዱስ_አልዓዛር በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባት_አቡነ_ሳዊሮስ ታኅሣሥ ዐስር በዚህች ዕለት እጅግ የከበሩ አቡነ ሳዊሮስ የፍልሥተ ሥጋቸው ሆነ፡፡ እርሳቸውም በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ቤተ ክርስቲያንን እንደፋና አብርተውላት በዓለም መድረክ አንድ ያደረጓት ናቸው፡፡ (የዕረፍታቸውን ዕለት የካቲት ዓሥራ አራትን ይመለከቷል፡፡) እጅግ ክቡር የሆኑት የአንጾኪያው ታላቁ አባት የአቡነ ሳዊሮስ ትውልዳቸው ከሮሜ ሀገር ሲሆን አባታቸው ሳዊሮስ የሚባሉ ኤጲስ ቆጶስ ናቸው፡፡ አባታቸው ሳዊሮስ ስለ ንስጥሮስ የከፋ ክህደት በኤፌሶን ከተማ ጉባኤ በተደረገ ጊዜ ከሁለት መቶው እጅግ ከከበሩት ሊቃውንት ቅዱሳን አባቶች ጋር ተሰብስበው ሃይማኖትን አቅንተዋል፡፡ ንስጥሮስንም በቃላቸው ትምህርትና የተለያዩ ተአምራትን እያሳዩ አስተምረው ሊያሳምኑት ቢሞክሩ ሰይጣን በልቡ ስላደረ ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም ነበርና ቤተ ክርስቲያንን እንዳያውክ ምእመናንም በክህደት በመርዙ እንዳይበክል ብለው ቅዱሳኑ በኅብረት አውግዘው ለዩት፡፡ ታላቁ አቡነ ሳዊሮስም ለጉባኤው በኤፌሶን ከተማ እንደመጡ ‹‹ከአንተ የሚወለድ ልጅህ ስሙም እንደ ስምህ ሳዊሮስ ተብሎ የሚጠራ ልጅህ የቀናች ሃይማኖትን ያጸናታል›› የሚል ታላቅ ራእይን ተመለከቱ፡፡ ይህም ታላቁ አቡነ ሳዊሮስ ባረፉ ጊዜ ልጃቸውን ሳዊሮስ ብለው ጠሩት፡፡ እርሱም ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆኑትን የጥበብና የፍልስፍና ትምህርቶቸን በሙሉ ጠንቅቆ ተማረ፡፡ በአንዲት ዕለትም ከመምህሩ ዘንድ ወጥቶ በመንገድ ሲጓዝ በዋሻ ውስጥ የሚኖርና ራሱን እስረኛ ያደረገ አንድ ታላቅ ጻድቅ ሰው አገኘ፡፡ ያም ጻድቅ ሰው ሳዊሮስን ‹‹የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን መምህራቸው የሆንክ ሳዊሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው›› አለው፡፡ ያም ጻድቅ ሰው ሳዊሮስን ከነጭራሹ ሳያውቀው በስሙ ስለጠራውና የሚደረግለትንም ከመሆኑ አስቀድሞ ትንቢት በመናገሩ በጣም ተደነቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ሳዊሮስ የትሩፋት ሥራዎችን መሥራት ጀመረ፡፡ ወደ አቡነ ሮማኖስ ገዳም ገብቶ መነኮሰና በጾም በጸሎት በእጅጉ ይተጋ ጀመር፡፡ በገዳሙም ጽኑ በሆነ በመንፈሳዊ ተጋድሎ እየበረታ ሲሄድ ዜናው በሁሉ ዘንድ መሰማት ጀመረ፡፡ የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት በሞት ባረፉ ጊዜ የከበሩ ሊቃውንት ኤጲስቆጶሳት በአንድ ሀሳብ ሆነው ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው አቡነ ሳዊሮስን የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ይሾሙት ዘንድ ወደዱ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም ያለ ፈቃዱ በግድ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት፡፡ በአቡነ ሳዊሮስ በሹመታቸው ዘመን እስከ ዓለም ዳርቻ ያለች ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆኑላት፡፡ የመለኮት ነገር የሚናገሩት ድርሰቶቻው እጅግ ድንቅ ናቸው፡፡ በየሀገሩ ወዳሚገኙ መናፍቃን ከሃድያን ትምህርታቸው በሚደርስ ጊዜ ሁለት አፍ እንዳለው ስለታም ሰይፍ ሥራቸውን ይበጥሳልና፡፡ የአቡነ ሳዊሮስን ትምህርታቸውን የሰማ መናፍቅ በውስጡ ያደረበት የጥርጥር መንፈስ መድረሻ ያጣል፡፡ አቡነ ሳዊሮስ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ቤተ ክርስቲያንን እንደፋና አብርተውላት በዓለም መድረክ አንድ አድርገዋታል፡፡ አቡነ ሳዊሮስ በቀናው ተጋድሎአቸው ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ከመናፍቃን ተኩላዎች በመጠበቅ ሲተጉ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደጉና አማኙ ንጉሥ ሞቶ በእርሱ ፈንታ ስሙ ዮስጥያኖስ የሚባል መናፍቅ ነገሠ፡፡ ይህም ከሃዲ ንጉሥ ዮስጥያኖስ ‹‹በውሾቸ ጉባኤ›› የተወሰነውን የኬልቄዶንን ሃይማኖት የሚያምን መናፍቅ ከሃዲ ነው፡፡ ንግሥቲቱ ሚስቱ ቴዎድራ ግን ሃይማኖቷ የቀና ምግባሯ ያማረ ነው፡፡ አቡነ ሳዊሮስ በጣም ትወዳቸውና ታከብራቸው ነበር፡፡ ይህም ከሃዲ ንጉሥ አቡነ ሳዊሮስን ወደ ረከሰች ሃይማኖቱ ያስገባቸው ዘንድ ግድ አላቸው፡፡ በብዙ ማስፋራራትና ቁጣ ሊያስገድዳቸው ቢሞክርም አቡነ ሳዊሮስ ግን ቁጣውንና ማስፈራራቱን አልፈሩም፡፡ ንጉሡም አስገድዶ ወደረከሰች ሃይማኖቱ ሊያስገባቸው እንዳልቻለ ባየ ጊዜ አቡነ ሳዊሮስን በስውር ሊገድላቸው ፈለገ፡፡ ንግሥቲቱም ከሃዲው ንጉሡ ባሏ አቡነ ሳዊሮስን በሥውር ሊገድላቸው እንደሆነ ስትሰማ አባን ከአንጾኪያ አገር ወጥተው በመሄድ ራሳቸውን እንዲያድኑ ነገረቻቸው፡፡ አቡነ ሳዊሮስ ግን መሸሽ አልፈለጉምና ‹‹ክብር ይግባውና ስለ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመሞት የተዘጋጀሁ ነኝ›› ብለው ለንግሥቲቱ መለሱላት፡፡ ነገር ግን ብዙ ምእመናንና ንግሥቲቱ አጥብቀው ስለለመኗቸው ጻደቁ ወጥተው ወደ ግብፅ አገር ተሰደዱ፡፡ ከምእመናንም አብረዋቸው የተሰደዱ አሉ፡፡ ከሃዲውም ንጉሥ አቡነ ሳዊሮስን በስውር ሊገድላቸው አስቦ ይዘው እንዲያመጧቸው ወታደሮቹን ላካቸው ነገር ግን አላገኟቸውም፡፡ አቡነ ሳዊሮስን ጌታችን ስለሰወራቸው የንጉሡ ጭፍሮች ሊያገኟቸው አልቻሉም፡፡ እሳቸው በጭፍሮቹ አጠገብ እየተጓዙ ጭፍሮቹ ግን አያዩአቸውም ነበር፡፡ ጭፍሮቹም በፍለጋ ሲጓዙ ከአቡነ ሳዊሮስ ጋር በአንድ ቦታ የሚያድሩበት ጊዜም አለ ነገር ፈጽሞ አላዩአቸውም፡፡ እግዚአብሔር አቡነ ሳዊሮስን ለምእመናን ጥቅም ሲል አሁን እንዲሞቱ አልፈቀደም ነበርና ጭፍሮቹም ፈልገው ባጧቸው ጊዜ ወደ ንጉሣቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡ አቡነ ሳዊሮስም ግብፅ አገር ከደረሱ በኋላ ከአንደኛው ገዳም ወደ አንደኛው ገዳም አንድ ተራ መነኩሴ መስለው በስውር የሚዘዋወሩ ሆኑ፡፡ በየሄዱበትም በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ምእመናንን የሚያጠነክሩ ሆኑ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ በአንዲት ዕለት አባታችን ወደ አስቄጥስ ገዳም በደረሱ ጊዜ በመጻተኛ መነኩሴ አምሳል ወደ አቡነ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ገቡ፡፡ በዚያም ቄሱ ዕጣንንና ቁርባንን ሊያሳርግ ጀመረና እንደ ሥርዓቱ እየዞረ አጠነ፡፡ ሐዋርያት የጻፏቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትና መልዕክቶቻውን የከበረ ወንጌልንም ካነበቡ በኋላ ቄሱ እጆቹን ታጥቦ ማኅፈዱን በገለጠው ጊዜ በጻሕሉ ውስጥ የቁርባኑን ኅብስት አላገኘውም፡፡ ደንግጦም መሪር ልቅሶን አለቀሰ፡፡ ከዚያም ወደ ሕዝቡ ተመልሶ ‹‹ወንድሞቼ እነሆ የቁርባኑ ኅብስት ተሰውሮ በጻሕሉ ውስጥ አላገኘሁትምና ይህ የሆነው በእኔ ኃጢአት ወይም በእናንተ ኃጢአት እንደሆነ ዐላወቅሁም›› አላቸው፡፡ ያንጊዜም የእግዚአብሔር መልአክ ለቄሱ ተልጦለት ‹‹ይህ የሆነው በአንተ ኃጢአት ወይም በሕዝቡ ኃጢአት አይደለም ነገር ግን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ እያለ መሥዋዕትን ለማሳረግ በመድፈርህ ነው›› አለው፡፡ ቄሱም በጣም ደንግጦ መልአኩን ‹‹ጌታዬ ሆይ! ሊቀ ጳጳሳት መኖሩን ዐላወቅሁም›› አለው፡፡ መልአኩም ተራ የመነኩሴ ልብስ ለብሰው ወደቆሙት ወደ አባ ሳዊሮስ አመለከተው፡፡ ቄሱም ወደ አቡነ ሳዊሮስ ሄዶ ከእግራቸው በታች ሰገደና ቡራኬ ተቀበለ፡፡ አባታችንም የጀመረውን ቅዳሴውን እንዲፈጽም ቄሱን አዘዙት፡፡ እርሳቸውንም በታላቅ ክብር ወደ ቤተ መቅደሱ አስገቧቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቄሱ ወደ መሠዊያው በወጣ ጊዜ ተሰውሮበት የነበረውን የቁርባኑን ኅብስት በጻሕሉ ውስጥ መልሶ አገኘው፡፡ በዚህም ካህናቱና ሕዝቡም ሁሉ ምስጉን የሆነ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡