የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
إظهار المزيد2 636
المشتركون
+124 ساعات
+167 أيام
+5630 أيام
أرشيف المشاركات
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_11
#ቅድስት_ታኦድራ_ገዳማዊት
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ዐሥራ አንድ በዚች ዕለት የከበረችና የነጻች እመሜኔት ታዖድራ አረፈች። ይቺም ቅድስት ከእስክንድርያ አገር ከታላላቆች ባለጸጎች ወገን ናት። ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው። እነርሱም ዋጋው ብዙ በሆነ በወርቅና በብር ያጌጡ የከበሩ ልብሶችን አሠሩለት ከእርስዋ በቀር ልጅ ስለሌላቸው ሊአጋቡአት እነርሱ ያስባሉና።
እርሷ ግን የምንኲስና ልብስ ለብሳ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ልትጋደል ትወዳለች መከራ መስቀሉንም ልትሸከም ትወድ ነበር የዚህን የኃላፊውን ሠርግ አልፈለገችም። ከዚህም በኃላ የወላጆቿን ዕቃ ገንዘብ ወስዳ ለሚሸጥላት ሰጠችው ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተች በቀረውም ከእስክንድርያ ውጭ በስተምዕራብ አብያተ ክርስቲያናትን አነፀች።
ወደ እስክንድያው ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ አትናቴዎስም ሔዳ ራሷን ተላጭታ ከእርሱ ዘንድ መነኰሰች። ከደናግል ገዳማትም ወደ አንዱ ገብታ በገድልም ተጸምዳ ጽነዕ ገድልን ተጋደለች አምላካዊ ራእይንም ታይ ዘንድ ተገባት መላእክትን ታያለችና የሰይጣናትንም ሥራቸውን ለይታ ታውቃለችና ለሠሩ የታሰቡትን የምታውቅበትና የምትፈትንበት እውቀት ተሰጣት።
ቅዱስ አትናቴዎስም በእርሷ ፈጽሞ ደስ ይለው ነበር ወደርሱም ይጠራታል እርሱም ሊጎበኛት ወደርሷ ይሔዳል ኀሳቧንም ትገልጥለታለች እርሱም የጠላት ደያብሎስን ወጥመዱንና ምትሐቱን ያስገነዝባታል። ከመንበረ ሢመቱ ከእስክንድርያ በአሳደዱትም ጊዜ ብዙዎች ድርሳናትን ጽፎ ላከላት።
ይቺም ቅድስት እጅግ እስከአረጀች ድረስ ኖረች በመንፈሳዊ ተጋድሎም የጸናች ናት እርስዋ ከአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ተምራለችና። እሊህም እለ እስክንድሮስ አትናቴዎስ ጴጥሮስ ጢሞቴዎስና ተዎፍሎስ ናቸው።
እንዲህም ብለው ጠየቋት ሰው ተርታ ነገር ቢናገር ዝም በል ሊሉት ወይም እንዳይሰሙት ጆሮአቸውን መክደን ይገባልን እንዲህም ብላ መለሰች ምንም ምን ሊሉት አይገባም ነገሩ ደስ እንዳላቸው ሆነው ዝም ይበሉ እንጂ ሰው ማዕዱን በፊትህ ቢያኖር በላይዋም በጎ የሆነና ብላሽ የሆነ ምግብ ቢያኖር ይህን ብላሹን ከእኔ ዘንድ አርቀው አልሻውም ልትለው አይቻልህም መጥፎውን ትተህ ከምትፈቅደው ትበላለህ እንጂ ያለ ትሕትና ያለ ጾምና ጸሎት ሰይጣንን ድል የሚነሣው የለም።
መላ ዕድሜዋም መቶ ዓመት ሆኖዋት በሰላም።
ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_10
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ዐሥር በዚች ቀን ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ ልደታቸው ነው፣ የታላቁ አባት የአባ ዕብሎ ረድእ #ቅዱስ_ይስሐቅ አረፈ፣ ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ገብርኤል አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ
ሚያዝያ ዐሥር በዚህች ቀን ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ ልደታቸው ነው፡፡ ሀገራቸው ትግራይ ቆየጻ ከተባለው ቦታ ነው፡፡
አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኮሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ይህ ጻድቅ በተለየ ሁኔታ በሊቅነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ መነኮሳት ነበሯቸው፡፡ 120 የሐረግ ሥዕላት ያሉት ትርጓሜ ወንጌል በ4 ዓምድ አድርገው በብራና ላይ ጽፈው እንደ አይሁድ 70ው ሊቃውንት እሳቸውም 70 እውቅ የሀገራችንን ሊቃውንት ሰብስበው እጅግ ትልቁን ትርጓሜ ወንጌል በጉባኤ አስወስነዋል፡፡
በጉባኤውም ካስወሰኑ በኋላ ወስደው ከሙታን መቃብር ላይ ቢጥሉት 211 ሙታን ተነሥተው ነአምን በአምላከ ጻድቃን ወሰማዕታት በጸሎተ ሳሙኤል ተንሣዕነ ብለው መስክረዋል። ወንጌላቸውንም በሊቃውንት ሲያጽፉ ቀለሙን ቅዱሳን መላእክት ያመጡላቸው ነበር፡፡
ጻድቁ ባረፉ ጊዜ 5 ነብሮች መጥተው መቃብራቸውን ቆፍረው ቀብረዋቸዋል፡፡ ትልቁ ገዳማቸው በትግራይ ክፍለ ሀገር እንዳ ሥላሴ ቆሪሮ ወረዳ ውስጥ ይገኛል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ይስሐቅ
ዳግመኛም በዚህች ቀን የታላቅ አባት የአባ ዕብሎ ረድእ ቅዱስ ይስሐቅ አረፈ። ይህም ቅዱስ ይህን ዓለም ተድላ ደስታውን ምቾቱን ጣዕሙን ትቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥቶ መነኰሰ ። ለአባ ዕብሎም ረድእ ሁኖ ሃያ አምስት ዓመት ሲያገለግለው ኖረ።
ሥጋውም እሰኪደርቅ ድረስ ጹኑዕ ተጋድሎን ተጋደለ ። ከሰውነቱም ሥጋዊ ፍላጎትን ሁሉ አጠፋ ባሕርዩ ቀንቶለት ኖረ በጸሎትና በቅዳሴም ጊዜ ጸጥታን አጸና ። የቍርባን ቅዳሴ ጸሎትም እስኪፈጸም ሁለት እጆቹ የኋሊት ታሥረው ራሱን አዘንብሎ እያለቀሰ ይቆማል።
ከቅዳሴም በሚወጣ ጊዜ በዚያች ዕለት ከሰው ወገን ከማንም ጋራ አይገናኝም በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ከአንተ ጋራ መነጋገር ከሚፈልግ ሰው ጋራ ለምን አትነጋገርም ብለው በጠየቁት ጊዜ እንደሚገባ ለሁሉ ጊዜ አለው ብሎ መለሰ ።
ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ በረከት ከርሱ ሊቀበሉና በጸሎቱም ሊማጻኑ መነኰሳት ወደርሱ ተሰበሰቡ። ከሰው ለምን ትሸሻለህ ብለው ጠየቁት እርሱም ከሰይጣን እንጂ ከሰው የምሸሽ አይደለም አንድ ሰው መብራት እያበራ በነፋስ ውስጥ ቢቆም መብራቱ የሚጠፋ አይደለምን? እንዲሁ እኛም በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ልባችን ብሩህ ሁኖ ሳለ ከሰው ጋራ ተገናኝተን እርስበርሳችን በተነጋገርን ጊዜ ልባችን ይጨልማል ብሎ መለሰ።
ይህም አባት መልካም ገድሉን ፈጽሞ በገድሉም እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው ጊዜ ጌታችንም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ድካም ሊአሳርፈው ወደደ። ጥቂትም ታሞ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ገብርኤል
በዚችም ዕለት ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል አረፈ። ይህም ቅዱስ የምስር አገር አለቆች ከሆኑት ከልጆቻቸው ውስጥ ነው። በግብጽ ባለች በቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያንም ዲቁና ተሾመ ዐዋቂና ጥበበኛም ስለሆነ ጸሐፊ ሁኖ ብዙዎችን መጽሕፍቶች ጻፈ የሚበዙትንም በዐረብና በቅብጥ ቋንቋ ተረጐመ። ከመሆኑ በፊት ሁሉን አይቶ በመንፈስ ቅዱስ የሚናገር የእግዚአብሔር ጸጋ በላዩ ያደረች ሶርያዊ አባ ዮሴፍ የሚባል አንድ አረጋዊ ሰው ነበረ።
አረጋውያን መነኰሳትና ኤጲስቆጶሳት ወደርሱ ተሰብስበው ለዚች ለከበረች የሊቀ ጵጵስና ሹመት ማን እንደሚሻል ይገልጥላቸውና ይነግራቸው ዘንድ ለመኑት።
እርሱም የታሮይክ ልጅ አንድ ሰው አለ ብሎ መለሰላቸው ምልክቱንም አመለከታቸው መነኰሳቱና ኤጲስቆጶሳቱም በዚህ ወደው ተስማሙ ከዓመተ ሰማዕታትም በስምንት መቶ ዓመት የካቲት ሃያ አንድ ቀን ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
ወደ አስቄጥስ ገዳምም በሔደ ጊዜ መታመንን ጨመረ ይቺም በባስልዮስ ቅዳሴ ፍጻሜ ከመለኮቱ ጋር አንድ ሆነ የምትል ናት። መለኮቱ ከትስብእቱ ተጨመረ ብሎ እንዲህ እንዳያስብ መነኰሳቱ ስለፈሩ እኛስ ልማዳችን እንዲህ አይደለም አሉት። ከብዙ ምርምርም በኋላ ይች ቃል ከሚከተላት ያለ መለያየት ያለ መጨመርና ያለ መደባለቅ ከሚለው ጋራ ተሰራች በበጎ አቀባበልም ተቀብለዋት እስከዚች ቀን ጻንታ ኖረች።
በሹመቱ ወራትም ብዙዎች በጎ ሥራዎች ተሠሩ ሙታንን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዳይቀብሩዋቸው በውግዘት ከለከለ ሁለተኛም ዕቁባቶችን በእነርሱ ዘንድ ያኖሩትን አውጥተው እንዲሰዱ አወገዘ ።
ይህም አባት ስለሙታን ርስትና ስለሌሎች ሥራዎች የሕግና የሥርዓት መጽሐፍን ደረሰ፡፡ ከቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትም ብዙዎችን ተረጐመ፡፡ በዘመኑም ኃምሳ ሦስት ኤጲስቆጶሳትንና ብዙ ካህናትን ሾመ፤ ነገረ ግን ከእርሳቸው አንድ አላድ እንኳ አልተቀበለም።
የግብጽ ንጉሥም በግፍ ከእርሱ ገንዘብ ሽቶ አሠቃየው እንዲጠባበቁትም ሰላዮችን በላዮ አኖረ። ጸሐፊዎችና ሹሞች ከሕዝቡም ታላላቆች ከሕዝቡም ሆነ ከአብያተ ክርስቲያናት ወይም ከገባሬዎች ምንም ምን እንዳልወሰደ በአወቁ ጊዜ ስለዚህ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ሰብስበው ስለርሱ ለንጉሡ ሰጡት ።
የዕረፍቱም ጊዜ ሲቀርብ እግዚአብሔርም ትሩፋቱንና ጽድቁን ለሰው ሊገልጽ ወደደ ጥቂትም ታመመ ብዙ ካህናትና መነኰሳትም ወደ ርሱ እንደ መጡ በሌሊት ራእይ አየ። እነርሱም ወንጌሎችን መስቀሎችንና ማዕጠንቶችን በእጆቻቸው ይዘዋል። እንዲህም አሉት እኛ ልንጐበኝህ መጣን ከዓመትም ፍጻሜ በኋላ ወደአንተ ተመልሰን መጥተን ከእኛ ጋራ እንወስድሃለን ። በነቃም ጊዜ ከእርሱ ዘንድ ላሉ መነኰሳትና ኤጲስቆጶሳት ለካህናትም እንዴት እንዳየ ነገራቸው ከደዌውም ዳነ።
ከዓመት ፍጻሜም በኋላ ጥቂት ታመመ አስቀድመው ወደርሱ መጥተው የነበሩትን ካህናትና መነኰሳት ደግሞ አያቸው፤ ሰላምታም ሰጡት ። ከእንርሱም ጋራ ደስ አለው በዚያን ጊዜም ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጥቶ በሰላም አረፈ፡፡ በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ዓሥራ አራት ዓመት ከኖረ በኋላ ነው።
ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን እመቤት ወርቁ ወላጅ እናት ስላረፉ ቀብር ዛሬ በ ሚያዝያ 09/2015 ከቀኑ 5:00 ሰዓት ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ቀብር መገኘት የምትችሉ እድንትገኙ ይሁን መኖሪያ ቤታቸው ደቀመሐሪ አካባቢ ተገኝተን እንድናጽናናቸው ይሁን። የእናታችንን ነፍስ ይማርልን።
ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-
#ሰኞ
#ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
#ማክሰኞ
#ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
#ረቡዕ
#አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
#ሐሙስ
#አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
#አርብ
#ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
#ቅዳሜ
ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
#እሁድ
#ዳግም_ትንሳኤ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡https://t.me/finotebirhan12
ከዚህም በኃላ እየአንዳንዱ ወደ በረሀ ይበተናሉ አንዱም አንዱ ባልንጀራውን ያየ እንደሆነ እንዳያየው ወደ ሌላ ቦታ ይሄዳል። ቅዱስ ዘሲማስም በየአመቱ ከሳቸው ጋራ ወጥቶ በበረሀው ውስጥ ይዘዋወራል የሚፅናናበትንም ይገልጥለት ዘንድ እግዚአብሄርን ይለምነው ነበር፡፡ ሲዘዋወርም በበረሀ የምትኖር ግብፃዊት ማርያምን አገኘ ከእርሷም በልጅነቷ ወራት በእርሷ ላይ እንዴት እንደሆነና በበረሀም የሆነውን ኑሮዋን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ተረዳ።
ከዚህ በኃላም በሁለተኛው አመት ስጋውንና ደሙን ያመጣላት ዘንድ ፈለገች እንዳለችውም አደረገላት። ለዚህም ፃድቅ ብሄረ ብፁአን ይገባ ዘንድ ተገባው እርሱም ገድላቸውን ፃፈ ስራቸውንና ፅድቃቸውን ገለጠ። ዘጠና ሶስት የሚሆን መላ እድሜው በተፈፀመለት ጊዜ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ስንትዩ
በዚህችም ቀን በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት በአባ ስንትዩ እጅ ታላቅ ምልክት ታየ። ይኸውም የከበረች የጌታን ፆም ከመነኰሳት ጋራ ይፆም ዘንድ ወደ አስቄጥስ ወደ አባ መቃርስ ገዳም ወጣ።
ሰሙነ ህማማትም በሆነ ጊዜ ገዳማቱንና አድባራቱን ሊዘርፉና ሊማርኩ የአረብ እስላሞች ተሰበሰቡ። በቤተ ክርስቲያኒቱ በስተምስራቅ ሰዎችንም ይገድሉ ዘንድ ሰይፎቻቸውን መዝዘው በእጆቻቸውም ይዘው በአለት ላይ ቆሙ።
ኤጲስቆጶሳትና መነኰሳትም ወደ አባ ስንትዩ ተሰብስበው ከአረብ እስላሞች እንዴት እንደሆነ ነግረው ከዚያ ገለል እንዲል ለመኑት። የከበረ አባ ስንትዩም ጌታችን የደቀ መዛሙርቱን እግራቸውን አጥቦ አዲስ ስርአት የሰራበት የፋሲካ ፍስህ በአል ሳይፈፀም እኔ ከዚህ አልለይም አላቸው።
እነዚህ እስላሞችም እየደነፉ ጩኸታቸው ተጨመረ። አባ ስንትዩም የወገኖቹን ድንጋፄ በአየ ጊዜ በላዩ የመስቀል ምልክት ያለበት በትሩን ይዞ ከእግዚአብሄር ወገኖች ጋራ ብሞት ይሻለኛል እያለ ወደ እነርሱ ሊወጣ ተነሣ።
ኤጲስቆጶሳቱም እንዳይወጣ ያዙት። እርሱ ግን ልባቸውን በማፅናናት አረጋጋቸውና ወደ አረብ እስላሞች ወጣ። እስላሞችም መስቀል ያለበትን በትር በእጁ ይዞ በአዩት ጊዜ ብዙ ሰራዊት እንዳሳደዳቸው ሆነው ወደ ኃላቸው ተመልሰው ሸሹ። ከዚያችም እለት ወዲህ ወደ ቅዱሳት መካናት እስላሞች አልተመለሱም።
ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_9
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ #አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ እረፍታቸው ነው፣ የከበረ #ቀሲስ_ዘሲማስ አረፈ፣ በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #በአባ_ስንትዩ እጅ ታላቅ ምልክት ታየ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ
ሚያዝያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ እረፍታቸው ነው። አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ እናቱ ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል፡፡ የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን፣ ድርሳናትንም ጠንቅቀው ዐውቀዋል፡፡
በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባሕሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተዋል፡፡ ለ3 ዓመታት ያህል በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት ለአባቶች መነኮሳት ምግብ የሚሆናቸው ዓሣ ከባህር ውስጥ በማውጣት አገልግለዋል፡፡
አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ከጾሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከሠሩ በኋላ ዕለቱን ስንዴ ዘርተው፣ ወይን ተክለው፣ ጽድን ወይራንና ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል፡፡ ስንዴውን ለመሥዋዕት ወይኑን ለቍርባን በተአምራት አድርሰዋል፡፡
አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አቆማቸው፡፡ ጌታንም በቅዱሳኑ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ መልአኩን ‹‹ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ ኢየሩሳሌም አድርሰው›› ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል፡፡
አባታችን ሁሉንም የኢትዮጵያን ቅዱሳት ገዳማትን ተዘዋውሮ ሲጎበኙ በሕይወተ ሥጋ የሌሉት የየገዳማቱ ቅዱሳን ሁሉ በአካል ይገለጡላቸው ነበር፡፡ ጎጃም ውስጥ እያስተማሩ፣ እያጠመቁ፣ የታመሙትን እየፈወሱ፣ የዕውራንን ዐይን እያበሩና ሙታንን እያሥነሱ ብዙ ካገለገሉ በኋላ ለዘጠኝ ዓመታት በባሕር ውስጥ ገብተው ቁልቁል ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ጸልየው የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጌታችን መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ሁሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ ሆይ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ምሬልሃለሁ ከዚህች ባሕር ውጣ›› በማለት በሞት የሚያርፉበትን ቦታ ነግሯቸዋል፡፡
ጻድቁ ወደ ደብረ አሰጋጅ በሚሄዱበት ጊዜ ጸሐይ ልትገባ ስትል ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አውግዤሻለሁ ለመስፍን ኢያሱ በገባኦን እንደቆምሽ አሁንም ቀጥ ብለሽ ቁሚ›› ብለው ገዝተው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም ደብረ አሰጋጅ ሲደርሱ ፀሐይ አፍ አውጥታ ‹‹አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ እገባ ዘንድ ፍታኝ›› ስትላቸው ‹‹እግዚአብሔር ይፍታሽ›› ባሏት ጊዜ ጠልቃለች፡፡ ጻድቁ ሌላው በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ በአምላክ ልቡና የሚገኝ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ልቡና የሚገኝ፣ በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ መልክአ መድኃኔዓለም ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው፤ እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣሉ፡፡
ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡ በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት ይደግማሉ፡፡ ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡ እያንዳንዱን የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም የሆነች ጸሎት ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡ ጻድቁ ታኅሣሥ 8 ቀን ተወልው ሚያዝያ 9 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዘሲማስ_ገዳማዊ
በዚህች ቀን የከበረ ቀሲስ ዘሲማስ አረፈ። ይህም ፃድቅ ከፍልስጥኤም ሰዎች ወገን ነው። ወላጆቹም ደጋጎች ክርስቲያኖች ናቸው ይህንን ፃድቅ በወለዱት ጊዜ አምስት አመት አሳደጉት። ከዚያም የቤተክርስቲያን ትምህርትን የሀይማኖትንም ምስጢር ህግና ስርአትንም እያስተማረ እንዲያሳድገው ለአንድ ሽማግሌ መምህር ሰጡት።
ያ ሽማግሌም ተቀበሎ ልጁ አደረገው ትምህርቱንም ሁሉ አምላካዊ ጥበብ ሀይማኖትንም አስተምሮ አመነኰሰው ዲቁናም አሾመው በበጎ ስራም አደገ ትሩፋት መስራትንም አበዛ እግዚአብሄርንም ሁልጊዜ ያመሰግነዋል በቀንና በሌሊትም መፃህፍትን ያነባል። ስራ ሲሰራ ሲበላም ቢሆን ሁል ጊዜ ከአፉ ምስጋናዎችን አያቋርጥም።በዚያ ገዳም አርባ አምስት አመት በተፈፀመለት ጊዜ ቅስና ተሾመ ተጋድሎውንም ጨመረ።
ከዚህ በኃላም እየተጋደለና አገልግሎት በመጨመር በቅስና ሹመት አስራ ሶስት አመት ሲሆነው በዘመኑ ካሉ ተጋዳዮች ሁሉ እርሱ በገድሉ ከፍ ከፍ እንዳለ ተቃራኒ ጠላት ዲያብሎስ በልቡ ክፉ ሀሳብ አሳደረበት በልቡም ከበጎ ስራ እኔ ያልሰራሁት የቀረኝ አለን ይል ጀመር።
ነገር ግን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልተወውም መልአኩን ልኮ በዮርዳኖስ ወንዝ አቅራቢያ ወደ አለ ገዳም ይሄድ ዘንድ እንጂ። ያን ጊዜም ተነስቶ ሄዶ ወደዚያ ገዳም ደረሰ በገድላቸው ፍፁማን የሆኑ እውነተኞች አገራውያንን አገኘ እርሱ ከእርሳቸው እንደሚያንስ አወቀ እርሱ በአለም ውስጥ ነው የኖረውና ስለዚህ ከእርሱ ይሻላሉ።
በዚያ ገዳም ከሳቸው ጋር ኖረ ብዙ ዘመናትም አብሮአቸው ሲጋደል ኖረ። ለዚያ ገዳም መነኰሳትም ልማድ አላቸው ታላቁ ፆም በደረሰ ጊዜ የመጀመሪያውን አንድ ሱባኤ በአንድነት ይፆማሉ በቅድስት እሑድ ስጋውንና ደሙን ይቀበላሉ በማግስቱም ሰኞ ጥዋት ሀያ ስድስተኛ መዝሙር እግዚአብሄር ብርሀነ ረድኤቱን ሰጥቶ ያድነኛል የሚያስፈራኝ ምንድነው የሚለውን እሰከ መጨረሻው እየዘመሩ ይወጣሉ በሚወጡም ጊዜ ወደ በሩ ተሰብስበው በአንድነት ፀልየው እርስ በርሳቸው ሰላምታ ይሰጣጣሉ የገደሙ አበ ምኔትም ይባርካቸዋል።
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ቤተክርስቲያንን ለማግባት መከራውን ጥሎሽ እና ድግስ ያደረገ ሙሽራ የበረከታችን መሐላ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለቤተክርስቲያን ደስታ ሲል መከራን ታገሰ ! መከራችን ምን ያኽል ሊያስገርፍ ሊያሰቃይ እና ሊበረታ እንደሚችል በክርስቶስ ላይ በሚደርሰው መከራ ታየ ፤የሰውን ተፈጥሮ ያስጨነቀውን እና ያሸነፈውን መከራ ክርስቶስ ፊት ለፊት ተገናኘው !የኃጢአት መከራ እና የሞት ሽታ ክርስቶስን ምንም ማድረግ አለመቻሉ እየተሸነፈ ስለመጣ ብዙ መከራዎችን እያከታተለ በማምጣቱ ታይቷል፤ ኃጢአት የጠራው ሞትም በክርስቶስ መከራ አመካኝቶ ወደ ክርስቶስ ሰውነት መጠጋት አቅቶታል !የመቃብር ጠባቂዎች ኃይል ትንሳኤውን ትንሳኤ የተስፋ መሟሸሽንና ሞትን የማሸነፍ በዓል ነው፤ በእለተ አርብ በጦር ጉልበታቸው የሚተማመኑ ሮማውያንና ሁሉን እናውቃለን በሚሉ ፈሪሳውያን የሀሰት ክስና ፍርድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መዋሉን ተከትሎ ፀሐይ የጨለመችበት፣ ጨረቃ ደም የለበሰችበት፣ ከዋክብት የረገፉበት እና ሞት የነገሰበት እንዲሁም ብዙዎች ተስፋ የቆረጡበት እለት ነበር፡፡ የጌታ ትንሳኤ በመከራና በጨለማ ውስጥም ሆነው ኃቅንና እውነትን ወግነው ለቆሙትና በጽናት ለጠበቁት ግን ከጨለመችው ፀሐይ ባሻገር አማናዊ ብርሃን፣ ደም ከለበሰችው ጨረቃ ባሻገር በደሙ የሚድኑ የሰው ልጆች መኖራቸውን፣ ከረገፉ ከዋክብት ባሻገር በሞቱ ሞትን ድል የሚነሳ አምላክ መኖሩን ያዩበት የድል እለት ነው፡፡ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ !!መልካም የትንሳኤ በዓል !!
አቶ ካሳሁን እሸቱ
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
እንደ ፍኖተ ብርሃን ልጅነታችን ለኛ የበራውን ብርሃን ለወገኖቻችን ይዳረስ ዘንድ እኛም ከመንገዳችን እንዳንነዋወጥ በአገልግሎታችን መትጋት ይገባናል። መከሩ እጅግ ብዙ ነው ሰራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው እንዳለን ቅዱስ ወንጌል የመከሩን መብዛት የሰራተኞችን ( የአገልጋዮች) ጥቂትነት በመረዳትና በመዋቀር እየተሰራ ባለው ቤተክርስቲያን የሌለው ትውልድ ትውልድ የሌላት ቤተ ክርስቲያን ለመፍጠር ህፃናቱን ወጣቱን ቢቻል መናፍቅ ማድለግ ካልተሳካ የቤተ ክርስቲያን ጠላት ማድረግ ካልሆነም ባለበት ማምከን እየተተገበረብን መሆኑን ማሳያ ማቅረብ አያሻንም እናታችን ፍኖተ ብርሃን ከዚህ ትውልድን የማዳን ተጋድሎ ውስጥ ትገኛለች ለኛ የበራውን ብርሃን ለሌሎች እንድናበራ እንተጋገዝ ብዙ አባላት ያለን ብዙ የሚጎድለን ነንና በትንሳኤው ዳግም ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ በበራልን ብርሃን እንተያይ።
“” እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሰን አደረሳችሁ “”
መ/ ር ተስፋዬ ተሾመ
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
‹‹ ሌሊቱም አልፎአል ቀኑም ቀርቦአል እንግዲህ የጨለማን ሥራ ከእኛ እናርቅ
የብርሃንንም ጋሻጦር እንልበስ በቀን እንደሚሆን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ……… .››› ሮሜ 13÷12
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው የሰውን ልጅ ጨለማ ከተባለው የሰይጣን የግዞት ዘመን ከጨለማ ኃጢያት ጨለማ ከተባሉት ሥጋዊ ፍትወታት ከመንገዳችን ለማስወገድ ጨለማ የሚገብረንን የሞት ደብዳቤ ለመደምሰስና የብርሃን ጋሻ ጦር እንድንለብስና በብርሃን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ ዘንድ ነው
ይኸው በሞቱ ሞታችን ተሻረልን በትንሳኤው ብርሃን ጨለማችን ተወገደ በብርሃን እንድንመላለስ ( ፍኖተ ብርሃንን) የብርሃን መንገድን አበጀልን ስለሆነም የጨለማን ስራ አስወግደን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ በዘመናችን ብርሃኑን ለመጋረድ የብርሃኗን ማህደር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከልዑል እግዚአብሔር የተሰጠችንን አንዲቷን ሃይማኖት መንትያና እኩያ ያላት በማስመሰል ትውልዱን በድንግዝግዝ እንዲጓዝ ታላቅ ውጊያ እንደተከፈተብን በነነዌ ሰሞን የነበረውን ማስታወስ በቂ ምስክር ነው።
እንደ ፍኖተ ብርሃን ልጅነታችን ለኛ የበራውን ብርሃን ለወገኖቻችን ይዳረስ ዘንድ እኛም ከመንገዳችን እንዳንነዋወጥ በአገልግሎታችን መትጋት ይገባናል። መከሩ እጅግ ብዙ ነው ሰራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው እንዳለን ቅዱስ ወንጌል የመከሩን መብዛት የሰራተኞችን ( የአገልጋዮች) ጥቂትነት በመረዳትና በመዋቀር እየተሰራ ባለው ቤተክርስቲያን የሌለው ትውልድ ትውልድ የሌላት ቤተ ክርስቲያን ለመፍጠር ህፃናቱን ወጣቱን ቢቻል መናፍቅ ማድለግ ካልተሳካ የቤተ ክርስቲያን ጠላት ማድረግ ካልሆነም ባለበት ማምከን እየተተገበረብን መሆኑን ማሳያ ማቅረብ አያሻንም እናታችን ፍኖተ ብርሃን ከዚህ ትውልድን የማዳን ተጋድሎ ውስጥ ትገኛለች ለኛ የበራውን ብርሃን ለሌሎች እንድናበራ እንተጋገዝ ብዙ አባላት ያለን ብዙ የሚጎድለን ነንና በትንሳኤው ዳግም ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ በበራልን ብርሃን እንተያይ።
“ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሰን አደረሳችሁ “
መ/ ር ተስፋዬ ተሾመ
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ቤተክርስቲያንን ለማግባት መከራውን ጥሎሽ እና ድግስ ያደረገ ሙሽራ የበረከታችን መሐላ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለቤተክርስቲያን ደስታ ሲል መከራን ታገሰ ! መከራችን ምን ያኽል ሊያስገርፍ ሊያሰቃይ እና ሊበረታ እንደሚችል በክርስቶስ ላይ በሚደርሰው መከራ ታየ ፤የሰውን ተፈጥሮ ያስጨነቀውን እና ያሸነፈውን መከራ ክርስቶስ ፊት ለፊት ተገናኘው !የኃጢአት መከራ እና የሞት ሽታ ክርስቶስን ምንም ማድረግ አለመቻሉ እየተሸነፈ ስለመጣ ብዙ መከራዎችን እያከታተለ በማምጣቱ ታይቷል፤ ኃጢአት የጠራው ሞትም በክርስቶስ መከራ አመካኝቶ ወደ ክርስቶስ ሰውነት መጠጋት አቅቶታል !የመቃብር ጠባቂዎች ኃይል ትንሳኤውን ትንሳኤ የተስፋ መሟሸሽንና ሞትን የማሸነፍ በዓል ነው፤ በእለተ አርብ በጦር ጉልበታቸው የሚተማመኑ ሮማውያንና ሁሉን እናውቃለን በሚሉ ፈሪሳውያን የሀሰት ክስና ፍርድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መዋሉን ተከትሎ ፀሐይ የጨለመችበት፣ ጨረቃ ደም የለበሰችበት፣ ከዋክብት የረገፉበት እና ሞት የነገሰበት እንዲሁም ብዙዎች ተስፋ የቆረጡበት እለት ነበር፡፡ የጌታ ትንሳኤ በመከራና በጨለማ ውስጥም ሆነው ኃቅንና እውነትን ወግነው ለቆሙትና በጽናት ለጠበቁት ግን ከጨለመችው ፀሐይ ባሻገር አማናዊ ብርሃን፣ ደም ከለበሰችው ጨረቃ ባሻገር በደሙ የሚድኑ የሰው ልጆች መኖራቸውን፣ ከረገፉ ከዋክብት ባሻገር በሞቱ ሞትን ድል የሚነሳ አምላክ መኖሩን ያዩበት የድል እለት ነው፡፡ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ !!መልካም የትንሳኤ በዓል !!
አቶ ካሳሁን እሸቱ
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
https://www.google.com/imgres?imgurl=https%3A%2F%2Flookaside.fbsbx.com%2Flookaside%2Fcrawler%2Fmedia%2F%3Fmedia_id%3D921718315066276&tbnid=TBLWIJnPoYKjfM&vet=1&imgrefurl=https%3A%2F%2Fm.facebook.com%2Fsmeotctt%2Fphotos%2Fmelkam-tinsae-happy-resurrection-day-brothers-and-sisters-christ-is-risen%2F921718315066276%2F&docid=s_6NYWuURVARWM&w=212&h=238&hl=en-US&source=sh%2Fx%2Fim
ክብርት እመቤታችን በተፀነሰች ጊዜ ብዙ ተአምራት ተደርጓል፡፡ የሃናን ማሕፀን እየዳሰሱ፡- ብዙ እውራን አይተዋል፣ ድውያን ተፈውሰዋል፣ ምውታን ተነሥተዋል፡፡ ይህንን የተመለከቱ አይሁድ ቅዱስ ኢያቄምን እና ቅድስት ሐናን በድንጋይ ወግረው በእሳት አቃጥለው ሊገድሏቸው በጠላትነት ሲነሡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሊባኖስ ወደ ሚባል ተራራ ይዟቸው ወጣ፡፡ በዚያ ሳሉ በግንቦት 1 ቀን ከፀሐይ 7 እጅ የምታበራ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በመኀልይ በም.4፥8 ላይ እንደተናገረ “ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ነይ…. ከአንበሶች ጉድጓድ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች፡፡” እንዳለ ይህ ትንቢት ተፈጸመ በተወለደች በ8ኛው ቀን ስሟን “ማርያም” ብለው አወጡላት ፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእናቷ ማኅፀን እያለች አያሌ ተአምራትን በማድረጓ፥ ለቅዱስ ኢያቄምና ለቅድስት ሐና ከባድ ፈተና ሆኖባቸው ነበር።የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ሰይጣን አይሁድን በምቀኝነት አስነ ሣባቸው። የምቀኝነት ምንጩ ደግሞ ክፉ ልቡና ነው፤ ማር፡፯፥፳፪። የሰው ልጅ መንፈሳዊነቱን ትቶ ፍጹም ሥጋዊ ሲሆን ምቀኝነት ይሰለጥንበታል። ገላ፡፭፥፳፩። ፈቃደ ሥጋው ገዝቶት በክፋትና ነት የሚኖር ሰው ደግሞ ለማንም ፍቅር ሊኖረው አይችልም። ገላ፡፫፥፫። ሰይጣን አዳምን እና ሔዋንን ያሳሳተው በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፫፥፩። ቃየል አቤልን የገደለው በምቀኝነት ነው። ዘፍ ፬፥፰። ዔሳው ወንድሙን ያዕቆብን ለመግደል የዛተው በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፳ ፯፥፵፩። የያዕቆብ ልጆች ወንድማቸውን ዮሴፍን፡- “እንግደለውና በአንድ ጉድጓድ ውስጥ እንጣለው፤” ያሉት፥ በኋላም በሮቤል በጎ ምክር አሳባቸውን ለውጠው ለእስማኤላውያን ነጋዴዎች የሸጡት በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፴፯፥፳፣፳፰። ሄሮድስ፡- ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ያሳደደው፥ በዚህም ምክንያት አሥራ አራት እልፍ ሕፃናትን ያሳረደው በምቀኝነት ነው። ማቴ፡፪፥፲፮። አይሁድ ኢየሱስ ክርስቶስን እጆቹን እና እግሮቹን በቅንዋተ መስቀል ቸንክረው የገደሉት በምቀኝነት ነው። ማር፡፲፭፥፳፬።
ምቀኝነት የባህርያቸው እስከሚያስመስልባቸው የደረሱ አይሁድ፥ በማኅፀነ ሐና ባለች ፅንስ ምክንያት የሚደረጉት ልዩ ልዩ ተአምራት አላስደሰታቸውም። ተሰብስበውም፡- “ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? ሐና ፀንሳ ሳለች በማኅፀንዋ ታድናለችና፥ የእስራኤልን መንግሥት አጥፍታ በእኛ ላይ ልትነግሥ አይደለምን?” ተባባሉ።
ይኸውም፡- “ከአሁን ቀደም ከእነዚህ ወገን የሆኑት ዳዊት ሰሎሞን፥ አርባ፣ አርባ ዓመት ገዝተውን ነበር፥ ከእነዚህ የሚወለደው ደግሞ ምን ያደርገን ይሆን?” ብለው ነው። ሀገር ያወቀውን፥ ፀሐይ የሞቀውን ምቀኝነታቸውን በሃይማኖት ለመሸፈን፡- “በሙሴ ሕግ መሠረት በድንጋይ ቀጥቅጠን እንግደላቸው፤” ብለው በሌሉበት ሞት ፈረዱባቸው። ይህ የሙሴ ሕግ የሚጠቀሰው ለአመንዝሮች እንጂ፥ ትዳራቸውን አክብረው፥ ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው፥ በጾም በጸሎት ተወስነው በቅድስና ለሚኖሩ፥ ለቅዱስ ኢያቄምና ለቅድስት ሐና አልነበረም። ዘሌ፡፳፥፲፣ዘዳ፡፳፪፥፳፬።
መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜ፥ የመፀነሷን ነገር አስቀድሞ በሕልም ነግሮአቸው የነበረ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል፥ እያዩት ከሰማይ ወርዶ፥ “በዘመድ የከበራችሁ ኢያቄምና ሐና ሆይ፥ ተነሡ፤” አላቸውና ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው።
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ኢያቄምን እና ቅድስት ሐናን ወደ ሊባኖስ ተራራ የወሰዳቸው ያለ ምክንያት አይደለም። “ወዳጄ ሆይ፥ ሁለንተናሽ ውብ ነው፤ (ጥንተ አብሶ የተባለ የአዳም ኃጢአት ያላረፈብሽ ንጽሕተ ንጹሐን ነሽ፤) ነውር የለብሽም። (የአዳም ኃጢአት የለብሽም)።
እኅቴ ሙሽራ ሆይ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፤” ተብሎ ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም የተነገረው ቃለ ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው። መኃ፡፬፥፯። ሊባኖስ፡- ከገሊላ በስተ ሰሜን እና ከፊንቄ በስተ ምሥራቅ የሚገኝ ተራራማ ሀገር ነው። ዘዳ፡፩፥፯። በዝግባ ዛፍ የተሞላ ተራራ ነው፥ ንጉሡ ሰሎሞን ለቤተ መቅደሱ ሥራ ያስፈለገውን የዝግባ እንጨት ያስመጣው ከዚያ ነበር። ፩ኛ፡ነገ፡፬፥፴፫፤ ፭፥፮። ምሳሌነቱ ጥሩ ነው፥ ከሊባኖስ የተገኘ ዝግባ ለአግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆነ ሁሉ፥ በሊባኖስ የተወለደች ድንግል ማርያምም ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሆና ተገኝታለች። አንድም የሊባኖስ ዝግባ ለቅዱሳን ምሳሌ ነው፤ የዚያ ፍሬው እንዲበዛለት፥ እነርሱ ደግሞ ጸጋና ክብር ይበዛላቸዋል። መዝ፡፺፩፥፲፪።
ቅድስት ሐና የፅንስዋ ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ ግንቦት አንድ ቀን፥ ከፀሐይ ይልቅ የምታበራ ሴት ልጅ ወለደች። ቅዱስ ኢያቄምም እመቤታችንን ስለሰጠው እግዚአብሔርን ካመሰገነ በኃላ በልቡናው ደስ ብሎት መሥዋዕት አቅርቧል፡፡ እመቤታችንንም ጡት ካስጣሏት በኃላ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ተሸክመው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው አስገቧት፡፡ ጻድቁ ኢያቄምም ጥቂት ዘመን ኑሮ በዚኽች ዕለት በሰላም ዐረፎ ወደሚወደው እግዚአብሔር ሔደ፡፡
የአባታችን የቅዱስ ኢያቄም ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!https://t.me/finotebirhan12
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
‹‹ ሌሊቱም አልፎአል ቀኑም ቀርቦአል እንግዲህ የጨለማን ሥራ ከእኛ እናርቅ
የብርሃንንም ጋሻጦር እንልበስ በቀን እንደሚሆን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ……… .››› ሮሜ 13÷12
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው የሰውን ልጅ ጨለማ ከተባለው የሰይጣን የግዞት ዘመን ከጨለማ ኃጢያት ጨለማ ከተባሉት ሥጋዊ ፍትወታት ከመንገዳችን ለማስወገድ ጨለማ የሚገብረንን የሞት ደብዳቤ ለመደምሰስና የብርሃን ጋሻ ጦር እንድንለብስና በብርሃን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ ዘንድ ነው
ይኸው በሞቱ ሞታችን ተሻረልን በትንሳኤው ብርሃን ጨለማችን ተወገደ በብርሃን እንድንመላለስ ( ፍኖተ ብርሃንን) የብርሃን መንገድን አበጀልን ስለሆነም የጨለማን ስራ አስወግደን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ በዘመናችን ብርሃኑን ለመጋረድ የብርሃኗን ማህደር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከልዑል እግዚአብሔር የተሰጠችንን አንዲቷን ሃይማኖት መንትያና እኩያ ያላት በማስመሰል ትውልዱን በድንግዝግዝ እንዲጓዝ ታላቅ ውጊያ እንደተከፈተብን በነነዌ ሰሞን የነበረውን ማስታወስ በቂ ምስክር ነው።
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
‹‹ ሌሊቱም አልፎአል ቀኑም ቀርቦአል እንግዲህ የጨለማን ሥራ ከእኛ እናርቅ
የብርሃንንም ጋሻጦር እንልበስ በቀን እንደሚሆን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ……… .››› ሮሜ 13÷12
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው የሰውን ልጅ ጨለማ ከተባለው የሰይጣን የግዞት ዘመን ከጨለማ ኃጢያት ጨለማ ከተባሉት ሥጋዊ ፍትወታት ከመንገዳችን ለማስወገድ ጨለማ የሚገብረንን የሞት ደብዳቤ ለመደምሰስና የብርሃን ጋሻ ጦር እንድንለብስና በብርሃን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ ዘንድ ነው
ይኸው በሞቱ ሞታችን ተሻረልን በትንሳኤው ብርሃን ጨለማችን ተወገደ በብርሃን እንድንመላለስ ( ፍኖተ ብርሃንን) የብርሃን መንገድን አበጀልን ስለሆነም የጨለማን ስራ አስወግደን በጽድቅ ሥራ እንመላለስ በዘመናችን ብርሃኑን ለመጋረድ የብርሃኗን ማህደር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከልዑል እግዚአብሔር የተሰጠችንን አንዲቷን ሃይማኖት መንትያና እኩያ ያላት በማስመሰል ትውልዱን በድንግዝግዝ እንዲጓዝ ታላቅ ውጊያ እንደተከፈተብን በነነዌ ሰሞን የነበረውን ማስታወስ በቂ ምስክር ነው።
እንደ ፍኖተ ብርሃን ልጅነታችን ለኛ የበራውን ብርሃን ለወገኖቻችን ይዳረስ ዘንድ እኛም ከመንገዳችን እንዳንነዋወጥ በአገልግሎታችን መትጋት ይገባናል። መከሩ እጅግ ብዙ ነው ሰራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው እንዳለን ቅዱስ ወንጌል የመከሩን መብዛት የሰራተኞችን ( የአገልጋዮች) ጥቂትነት በመረዳትና በመዋቀር እየተሰራ ባለው ቤተክርስቲያን የሌለው ትውልድ ትውልድ የሌላት ቤተ ክርስቲያን ለመፍጠር ህፃናቱን ወጣቱን ቢቻል መናፍቅ ማድለግ ካልተሳካ የቤተ ክርስቲያን ጠላት ማድረግ ካልሆነም ባለበት ማምከን እየተተገበረብን መሆኑን ማሳያ ማቅረብ አያሻንም እናታችን ፍኖተ ብርሃን ከዚህ ትውልድን የማዳን ተጋድሎ ውስጥ ትገኛለች ለኛ የበራውን ብርሃን ለሌሎች እንድናበራ እንተጋገዝ ብዙ አባላት ያለን ብዙ የሚጎድለን ነንና በትንሳኤው ዳግም ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ በበራልን ብርሃን እንተያይ።
“ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሰን አደረሳችሁ “
መ/ ር ተስፋዬ ተሾመ
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
ክብርት እመቤታችን በተፀነሰች ጊዜ ብዙ ተአምራት ተደርጓል፡፡ የሃናን ማሕፀን እየዳሰሱ፡- ብዙ እውራን አይተዋል፣ ድውያን ተፈውሰዋል፣ ምውታን ተነሥተዋል፡፡ ይህንን የተመለከቱ አይሁድ ቅዱስ ኢያቄምን እና ቅድስት ሐናን በድንጋይ ወግረው በእሳት አቃጥለው ሊገድሏቸው በጠላትነት ሲነሡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሊባኖስ ወደ ሚባል ተራራ ይዟቸው ወጣ፡፡ በዚያ ሳሉ በግንቦት 1 ቀን ከፀሐይ 7 እጅ የምታበራ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በመኀልይ በም.4፥8 ላይ እንደተናገረ “ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ነይ…. ከአንበሶች ጉድጓድ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች፡፡” እንዳለ ይህ ትንቢት ተፈጸመ በተወለደች በ8ኛው ቀን ስሟን “ማርያም” ብለው አወጡላት ፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእናቷ ማኅፀን እያለች አያሌ ተአምራትን በማድረጓ፥ ለቅዱስ ኢያቄምና ለቅድስት ሐና ከባድ ፈተና ሆኖባቸው ነበር።የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ሰይጣን አይሁድን በምቀኝነት አስነ ሣባቸው። የምቀኝነት ምንጩ ደግሞ ክፉ ልቡና ነው፤ ማር፡፯፥፳፪። የሰው ልጅ መንፈሳዊነቱን ትቶ ፍጹም ሥጋዊ ሲሆን ምቀኝነት ይሰለጥንበታል። ገላ፡፭፥፳፩። ፈቃደ ሥጋው ገዝቶት በክፋትና ነት የሚኖር ሰው ደግሞ ለማንም ፍቅር ሊኖረው አይችልም። ገላ፡፫፥፫። ሰይጣን አዳምን እና ሔዋንን ያሳሳተው በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፫፥፩። ቃየል አቤልን የገደለው በምቀኝነት ነው። ዘፍ ፬፥፰። ዔሳው ወንድሙን ያዕቆብን ለመግደል የዛተው በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፳ ፯፥፵፩። የያዕቆብ ልጆች ወንድማቸውን ዮሴፍን፡- “እንግደለውና በአንድ ጉድጓድ ውስጥ እንጣለው፤” ያሉት፥ በኋላም በሮቤል በጎ ምክር አሳባቸውን ለውጠው ለእስማኤላውያን ነጋዴዎች የሸጡት በምቀኝነት ነው። ዘፍ፡፴፯፥፳፣፳፰። ሄሮድስ፡- ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ያሳደደው፥ በዚህም ምክንያት አሥራ አራት እልፍ ሕፃናትን ያሳረደው በምቀኝነት ነው። ማቴ፡፪፥፲፮። አይሁድ ኢየሱስ ክርስቶስን እጆቹን እና እግሮቹን በቅንዋተ መስቀል ቸንክረው የገደሉት በምቀኝነት ነው። ማር፡፲፭፥፳፬።
ምቀኝነት የባህርያቸው እስከሚያስመስልባቸው የደረሱ አይሁድ፥ በማኅፀነ ሐና ባለች ፅንስ ምክንያት የሚደረጉት ልዩ ልዩ ተአምራት አላስደሰታቸውም። ተሰብስበውም፡- “ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? ሐና ፀንሳ ሳለች በማኅፀንዋ ታድናለችና፥ የእስራኤልን መንግሥት አጥፍታ በእኛ ላይ ልትነግሥ አይደለምን?” ተባባሉ።
ይኸውም፡- “ከአሁን ቀደም ከእነዚህ ወገን የሆኑት ዳዊት ሰሎሞን፥ አርባ፣ አርባ ዓመት ገዝተውን ነበር፥ ከእነዚህ የሚወለደው ደግሞ ምን ያደርገን ይሆን?” ብለው ነው። ሀገር ያወቀውን፥ ፀሐይ የሞቀውን ምቀኝነታቸውን በሃይማኖት ለመሸፈን፡- “በሙሴ ሕግ መሠረት በድንጋይ ቀጥቅጠን እንግደላቸው፤” ብለው በሌሉበት ሞት ፈረዱባቸው። ይህ የሙሴ ሕግ የሚጠቀሰው ለአመንዝሮች እንጂ፥ ትዳራቸውን አክብረው፥ ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው፥ በጾም በጸሎት ተወስነው በቅድስና ለሚኖሩ፥ ለቅዱስ ኢያቄምና ለቅድስት ሐና አልነበረም። ዘሌ፡፳፥፲፣ዘዳ፡፳፪፥፳፬።
መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜ፥ የመፀነሷን ነገር አስቀድሞ በሕልም ነግሮአቸው የነበረ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል፥ እያዩት ከሰማይ ወርዶ፥ “በዘመድ የከበራችሁ ኢያቄምና ሐና ሆይ፥ ተነሡ፤” አላቸውና ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው።
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ኢያቄምን እና ቅድስት ሐናን ወደ ሊባኖስ ተራራ የወሰዳቸው ያለ ምክንያት አይደለም። “ወዳጄ ሆይ፥ ሁለንተናሽ ውብ ነው፤ (ጥንተ አብሶ የተባለ የአዳም ኃጢአት ያላረፈብሽ ንጽሕተ ንጹሐን ነሽ፤) ነውር የለብሽም። (የአዳም ኃጢአት የለብሽም)።
እኅቴ ሙሽራ ሆይ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፤” ተብሎ ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም የተነገረው ቃለ ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው። መኃ፡፬፥፯። ሊባኖስ፡- ከገሊላ በስተ ሰሜን እና ከፊንቄ በስተ ምሥራቅ የሚገኝ ተራራማ ሀገር ነው። ዘዳ፡፩፥፯። በዝግባ ዛፍ የተሞላ ተራራ ነው፥ ንጉሡ ሰሎሞን ለቤተ መቅደሱ ሥራ ያስፈለገውን የዝግባ እንጨት ያስመጣው ከዚያ ነበር። ፩ኛ፡ነገ፡፬፥፴፫፤ ፭፥፮። ምሳሌነቱ ጥሩ ነው፥ ከሊባኖስ የተገኘ ዝግባ ለአግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆነ ሁሉ፥ በሊባኖስ የተወለደች ድንግል ማርያምም ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሆና ተገኝታለች። አንድም የሊባኖስ ዝግባ ለቅዱሳን ምሳሌ ነው፤ የዚያ ፍሬው እንዲበዛለት፥ እነርሱ ደግሞ ጸጋና ክብር ይበዛላቸዋል። መዝ፡፺፩፥፲፪።
ቅድስት ሐና የፅንስዋ ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ ግንቦት አንድ ቀን፥ ከፀሐይ ይልቅ የምታበራ ሴት ልጅ ወለደች። ቅዱስ ኢያቄምም እመቤታችንን ስለሰጠው እግዚአብሔርን ካመሰገነ በኃላ በልቡናው ደስ ብሎት መሥዋዕት አቅርቧል፡፡ እመቤታችንንም ጡት ካስጣሏት በኃላ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ተሸክመው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው አስገቧት፡፡ ጻድቁ ኢያቄምም ጥቂት ዘመን ኑሮ በዚኽች ዕለት በሰላም ዐረፎ ወደሚወደው እግዚአብሔር ሔደ፡፡
የአባታችን የቅዱስ ኢያቄም ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ሚያዝያ_7
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
#ቅዱስ_ኢያቄም
ሚያዝያ ሰባት በዚች ቀን የእመቤታችን አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም አባትዋ ጽድቅ ኢያቄም አረፈ። ይህም ጻድቅ በሦስት ስሞች ይጠራል እንርሱም ኢያቄም ዮናኪር ሳዶቅ ናቸው እርሱም ከይሁዳ ነገድ ከዳዊት ዘር ነው።
ይህም የአልዓዛር የኤልዩድ ልጅ ኢያቄም በትውልድ ሐረግ እስከ ሰሎሞንና እስከ ንጉሥ ዳዊት የሚደርስ ነው ። ይኸውም በዙፋኑ የሚቀመጥና ለዘላለሙ በእስራኤል ዘሥጋ በእስራኤል ዘነፍስ ነግሦ የሚኖር ከዘሩ ሊሰጠው ጌታ የማለለት ነው።
ሚስቱ ሐናም መካን ሆነች ሁለቱም ወደ እግዚአብሔር አዘ ውትረው ይጸልዩና ይማልዱ ነበር። እግዚአብሔርም ልመናውቸውን ተቀበሎ ይችን ጣፋጭ የሆነች መልካም ፍሬን ዓለሙን ሁሉ ከረኃበ ነፍስ ያዳነች ሰጣቸው።
መሪር የሆነ ተገዢነትንም ከሁሉ በእርስዋ አስወገደ። ለዚህም ጻድቅ ኢያቄም ለክብር ባለቤት ክርስቶስ አያት መሆን ተገባው ድንቅ ስለ ሆነ ሥጋዊው ከልጁ ስለመወለዱ ነው።
እግዚአብሔርም በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ ደስ በአሰኘው ጊዜ በልቡናው ደስ ብሎት መስዋዕቱን አቀረበ። ከላዩም ከወገኖቹም ልጆች ኀፍረትን አስወገደ።
አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጡት ከአስተዋት በኋላ ለእግዚአብሔር እንደተሳሉ ተሸክመው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወስደው አስገቡአት። ጻድቅ ኢያቄም ጥቂት ዘመን ኑሮ በሰላም አረፈ። (ስንክሳር ዘወርኀ ሚያዝያ)
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
አባታችን ቅዱስ ኢያቄም (ከገድላት አንደበት-የተወሰደ)
ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ደጋግ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሄርም በሰውም ዘንድ የተመሰከረለላቸው ባለጸጎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን መካን ስለነበሩ የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውም፡፡
አንድ ቀን ጴጥርቃ ቴክታን እንዲህ አላት፡- ‹‹እኅቴ ሆይ! ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን? ልጅ የለን የሚወርሰን አንቺም መካን ነሽ፣ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ወንድሜ ሆይ! አምላከ እስራኤል ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ›› ብላ ብታሰናብተው ‹‹እንደዚህ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬም እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቃል›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም፣ ትላንትና ማታ በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማኅፀኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ፣ ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ›› አለችው፡፡ እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሄዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፡፡ ያም ህልም ፈቺ ‹‹እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል በሳህሉ መግቧአችኋል፣ 7 አንስት ጥጆች መውለዳችሁ 7 ሴቶች ልጆችና የልጅ ልጆች ትወልዳላችሁ፣ ከቤታችሁ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ፤ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም›› አለው፡፡ እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ለሚስቱ ነገራት፡፡ እርሷም ‹‹እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል!›› ብላ ዝም አለች፡፡ ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ስሟንም ሔሜን ብለው አወጡላት፤ ሔሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ባል አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች፣ በስምንተኛ ቀኗም ዴርዲ ብለው ስም አወጡላት፡፡ ዴርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደችና ቶና አለቻት፣ ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት፣ ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት፣ ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሔርሜላ አለቻት፣ ሔርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የወለደቻትን ቅድስት ሐናን ወለደች፡፡
ይኽችም ቅድስት ሐና በሥርዓት አድጋ ለአእምሮ ስትበቃና አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፡፡ እነርሱም እጅግ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡ መብዓ ይዘው ለሊቀ ካህኑ ሲሰጡት ሊቀ ካህኑም እንኳ ሳይቀር ‹‹እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ ያለውን ሕግ በእናንተ ላይ እንዳይፈጸም አድርጎ ልጅ የከለከላችሁ ኃጢአተኛ ብትሆኑ ነውና መብዓችሁን አልቀበልም›› ብሎ በእጅጉ አሳዝኗቸዋል። በሊቀ ካህኑ እያዘኑና እየተከዙ ሲመለሱ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ዛፍ ሥር ተቀመጠው ሳለ እርግቦች ጫጩቶቻቸውን ሲያጫውቱ ተመልክተው ‹‹ለእነዚህ ወፎች እንኳ ልጆችን የሰጠህ አምላክ ለእኛስ መች ይሆን ልጅ የምትሰጠን?›› ብለው እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡
ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው ‹‹አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ውኃ ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን›› ብለው ስዕለት ገቡ፡፡ ዘካርያስም ‹‹እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስዕለታችሁን ይቀበልላችሁ የልቦናችሁን ሀሳብ ይፈጽምላችሁ›› ብሎ አሳረገላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅድስት ሐናና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩስ እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም ‹‹ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› አላት፡፡ ‹‹ወፍ›› የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው፤ ‹‹ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› ማለቱ የኢያቄምን (የሰውን) ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው ዕወቅ ሲል ነው፡፡ ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባሕርይው ምልአቱ ስፍሃቱ ርቀቱ ልእልናው ናቸው፡፡ ቅድስት ሐናም ‹‹እኔም ደግሞ አየሁ እንጂ›› አለችው፡፡ ‹‹ምን አየሽ?›› ቢላት ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ›› አለችው፡፡ ‹‹ርግብ›› የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፣ ነጭነቱ ንጽህናዋ ቅድስናዋ ድንግልናዋ ነው፡፡ ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ›› ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መፀነሷን ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው፡፡ እነርሱም እንዲህ ያለ ራእይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም ይልቁንም ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ‹‹‹ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉአት› ብሎ ያበሰረ አምላክ ለእኛስ ይልክልን የለምን!›› ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ ሰባት ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ‹‹ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁና ዛሬ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ ብሎሏችኋል ጌታ›› ብሎ መልአኩ ለሐና ነገራት፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ተፀነሰች፡፡
#ቀዳም_ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ)
የዐቢይ ጾም የመጨረሻዋ ቅዳሜ ብዙ ስያሜዎች አሏት፦
#ቀዳም_ሥዑር
በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡ የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
# ለምለም_ቅዳሜ
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቄጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡ በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
(የቄጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡)
#ቅዱስ_ቅዳሜ
ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
