Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
ከተማ አቀፍ የአንድ ማዕከል የጽዳት ንቅናቄ በቦሌ ክፍለ ከተማ ተካሄደ፡፡
በወረዳ 14 ጂቲዜድ ኮንዶሚኒየም በተካሄደው የጽዳት ንቅናቄ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙላት ተገኝ ባደረጉት ንግግር አካባቢን ማጽዳት ንጹህ ከተማና ሀገር ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህ ግብ መሳካት በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የአንድ ማዕከል የጽዳት ንቅናቄዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በከተማዋ በጽዳት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎች የከተማዋን ውበትና ንጽሕና በማስጠበቅ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ በጽዳት ዘርፍ በከተማ ደረጃ ግንባር ቀደም በመሆን ያሳየውን ስኬት በ2018 በጀት ዓመትም አጠናክሮ በማስቀጠል ኅብረተሰቡን ያሳተፈ ንቅናቄ በማድረግ ለላቀ ውጤት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
የቦሌ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ታደሰ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው ብሎኮችን በጽዳት ሞዴል ለማድረግ በሚደረገው የተቀናጀ እንቅስቃሴ የጽዳት ሥራን ከንቅናቄ ባለፈ ባሕል በማድረግ በኩል ተጨባጭ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በአንድ ማዕከል የጽዳት ንቅናቄ ነዋሪው ኅብረተሰብ፣ የጽዳት ሽርክና ማኅበራት እና ሌሎች ባለድርሻዎች በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ኃላፊው ገልጸው፣ ይህንን እንቅስቃሴ ለማጠናከር የወረዳና የክፍለ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቅንጅት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ በወረዳው ጽዳትን ባሕል ለማድረግ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጠናክሩ እንቅስቃሴዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ያመለከቱት የወረዳ 14 አስተዳደር ዋና አስፈጻሚ አቶ ማንደፍሮ ተመስገን፣ በወረዳው የአንድ ማዕከል የጽዳት ንቅናቄ መካሄዱ የተጀመረውን የጽዳት እንቅስቃሴ በሕዝብ የነቃ ተሳትፎ ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡
በንቅናቄው የክፍለ ከተማ እና የወረዳው አመራሮች፣ የጽዳት ሽርክና ማኅበራት፣ የጸጥታ አካላት እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ጥቅምት 22/2018
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ቆሻሻን በተገቢው መንገድ በማስወገድ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እንዲፈጠር እየሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ገለጸ።
ጽ/ቤቱ ከተማ አቀፍ በማህበረሰቡ የደረቅ ቆሻሻ ከምንጩ የመለየት ንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሄደ።
በፕሮግራሙ ላይ የጽዳት አምባሳደሮች፣ባለሙያዎች፣የሽርክና ማህበራት፣ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየ ዓለም እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን በማስተካከልና ከምንጩ በመለየት በቅብብሎሽ በማጓጓዝ የሚፈለገው ቦታ በማድረስ አካባቢያችንን በንጽህና በመያዝ ለመኖሪያ ምቹ እንድትሆን በመተባበር ልንሰራ የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሓዱሽ ሓጎስ በበኩላቸው የንቅናቄው ዓላማ ቆሻሻን በተገቢው መንገድ የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችንና የማይበሰብሱትን ከምንጩ በመለየት ጥቅማ ላይ እንዲውል ለማድረግና ደረቅ ቆሻሻ ከሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲዉሉ ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።
ደረቅ ቆሻሻን መልሶ ኡደት በማድረግ ይሰጠው ከነበረው አገልግሎት በሙሉ ወይም በከፊል ለሌላ አገልግሎት ማዋል በትኩረት ከተሰራበት የሀብት ምንጭ መሆኑን የገለጹት አቶ ኃዱሽ ደረቅ ቆሻሻን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚከናወነው ተግባር የተደራጁ የሽርክና ማህበራት፣ባለሙያዎች፣የጽዳት አምባሳደሮችና ህብረተሰቡ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ደረቅ ቆሻሻን ከምንጩ በመለየት መልሶ የመጠቀም ባህልን ልናሳድግ ይገባል ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አዲስ አበባ ከተማን ገጽታ የቀየሩ በርካታ የልማት ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸው ቆሻሻን በየቦታው ከመጣል ተቆጥበን ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል አካባቢያችን ለመኖሪያ ምቹ የተጀመሩ የልማት ስራዎችም ቀጣይ እንዲሆኑ መስራት የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
Lideta sub-city communication office
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ቆሻሻን በተገቢው መንገድ በማስወገድ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እንዲፈጠር እየሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ገለጸ።
ጽ/ቤቱ ከተማ አቀፍ በማህበረሰቡ የደረቅ ቆሻሻ ከምንጩ የመለየት ንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሄደ።
በፕሮግራሙ ላይ የጽዳት አምባሳደሮች፣ባለሙያዎች፣የሽርክና ማህበራት፣ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየ ዓለም እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን በማስተካከልና ከምንጩ በመለየት በቅብብሎሽ በማጓጓዝ የሚፈለገው ቦታ በማድረስ አካባቢያችንን በንጽህና በመያዝ ለመኖሪያ ምቹ እንድትሆን በመተባበር ልንሰራ የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሓዱሽ ሓጎስ በበኩላቸው የንቅናቄው ዓላማ ቆሻሻን በተገቢው መንገድ የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችንና የማይበሰብሱትን ከምንጩ በመለየት ጥቅማ ላይ እንዲውል ለማድረግና ደረቅ ቆሻሻ ከሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲዉሉ ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።
ደረቅ ቆሻሻን መልሶ ኡደት በማድረግ ይሰጠው ከነበረው አገልግሎት በሙሉ ወይም በከፊል ለሌላ አገልግሎት ማዋል በትኩረት ከተሰራበት የሀብት ምንጭ መሆኑን የገለጹት አቶ ኃዱሽ ደረቅ ቆሻሻን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚከናወነው ተግባር የተደራጁ የሽርክና ማህበራት፣ባለሙያዎች፣የጽዳት አምባሳደሮችና ህብረተሰቡ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ደረቅ ቆሻሻን ከምንጩ በመለየት መልሶ የመጠቀም ባህልን ልናሳድግ ይገባል ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አዲስ አበባ ከተማን ገጽታ የቀየሩ በርካታ የልማት ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸው ቆሻሻን በየቦታው ከመጣል ተቆጥበን ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል አካባቢያችን ለመኖሪያ ምቹ የተጀመሩ የልማት ስራዎችም ቀጣይ እንዲሆኑ መስራት የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
Lideta sub-city communication office
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በ1ኛ እና 2ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ስራዎች :-
342 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣
185 ኪ.ሜ የተሽከርካሪ መንገድ ፣
241 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣
101 የህፃናት መጫወቻዎች ፣
155 የስፓርት ማዘዉተሪያዎች ፣
153 ዘመናዊ ፓርኪንግ እና ተርሚናሎች ፣
210 የሕዝብ መፀዳጃዎች ፣ እንዲሁም
ዘመናዊ የመንገድ መብራቶች ፣ በርካታ የህዝብ መገልገያ እና መዝናኛ ቦታዎች ፣ የሕዝብ አገልግሎት መስጫ መሰረተ ልማቶች ፣ ተገንብተዉ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አቶ ሚሊዮን ማትዮስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ
ሆነዉ ተሹመዋል።
መልካም የስራ ዘመን!
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanagerአቶ ሚሊዮን ማትዮስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ
ሆነዉ ተሹመዋል።
መልካም የስራ ዘመን!
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በተቋማት የቅንጅታዊ አሰራር የማስፈፀሚያ ማኑዋል ላይ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት አስተባባሪነት የተቋማት የቅንጅታዊ አሰራር የማስፈፀሚያ ማኑዋል መሠረት በ2018 በጀት አመት በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በጋራ በዛሬው እለት የዉይይት መድረክ አከናውኗል።
በመድረኩም በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ በወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ እንደገለፁት የከተማችንን የአገልግሎት አሰጣጣችንን አሁን ከደረሰበት ጀረጃ ከፍ ለማድረግ እንዲሁም የሚከናወኑ ተግባራት በይበልጥ ተቀራርቦ በቅንጅት መስራት የህብረተሰቡን የአገልግሎት እርካታን ጥያቄ ለመመለስ ቅንጅታዊ አሰራርን ተግባራዊ ማድረግ ሚናው የጎላ ነዉ ሲሉ ገልጸዋል።
አክለዉም የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወጥ በሆነ መልኩ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት እንዲሁም ተቋማት የተሰጣቸውን ተልዕኮ ተግባራዊ ከማድረግ አነፃርና እንደ ከተማ የተደረሰበትን እድገት የሚመጥን አገልግሎት በይበልጥ ተደራሽ ለማድረግም ጭምር ስራዎችን ተቀናጅቶ በእቅድ መስራት ላይ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዉይይት መድረኩ በቀጣይ በቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት የተሚተገበሩ ተግባራት እንዲሁም ከተቋማት የሚጠበቁ አገልግሎት ምን መሆን እንዳለበት የሚያሳይ ሰነድ በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ በወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ቀርቦ ዉይትት የተካሄደበት ሲሆን በቀጣይ በ24/7 የስራ ባህል በማድረግ ወደ ተግባር መግባት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የዉስጥ ኦዲት የቁጥጥር ስርዓት ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ።
የአዲስ አበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የዉስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ለፅ/ቤቱ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች በዉስጥ የኦዲት የቁጥጥር ስርዓት ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬዉ እለት ተሰጥቷል።
በስልጠናዉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የዉስጥ ኦዲት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለም ጓዱ ስልጠናው የሚሰጡት አገልግሎት አሰራሮችን ግልፅ የሚያደርግ እንዲሁም በአሰራር ሂደት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ከመመለስ አንፃር ሚናዉ የጎላና ይበልጥ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ለስራ አስኪያጅ ፅ/ ቤት ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዉ የዉስጥ የቁጥጥር ስርዓት ከመተግበር፣የበጀትና ዝግጅት አስተዳደር፣የበጀት አመት ገቢና ወጪ እቅድ አንፃር፣የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት አዘገጃጀት፣የቅሬታ አፈታትና አተገባበር፣የግዥ እቅድ ከማዘጋጀት አንፃር ሰፊ አቅም የሚፈጥር እንዲሁም በቂ የሆነ ግንዛቤና አቅም ለመፍጠር የሚያስችል ነዉ ሲሉም የአዲሰ አበባ ከተማ ፋይንስ ቢሮ የአስተዳደር ኢኮኖሚ ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ እሸቱ ላቀዉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም በስልጠናው ላይ ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የመማክርት ጉባኤ ማቋቋምና ትግበራ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የመማክርት ጉባኤ የማቋቋም እና የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዘመናዊ ቀልጣፋ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ማለትም ከምክር ቤት አባላት፣ከተጠሪ ተቋማት፣ከሲቪክ ማህበራት፣ከሴክተር ተቋማት፣ከሽርክና ማህበራት፣ከእነዚህና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በዛሬው እለት የመማክርት ጉባኤ የማቋቋምና ግንዛቤ የማስጨበጥ መድረክ አከናውኗል።
በዚሁ መድረክ እንደተገለጸው ይህ ጉባኤ መቋቋሙ በተለይም በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ የሆነና የጎላ ፋይዳ እንደሚፈጥር ተገልጾ በተለይም የሚሰጡ አገልግሎቶችን ቀላል ፣ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እንዲሁም የህብረተሰቡን ቅሬታ ለመፍታት ከማስቻል አንፃር ጠቀሜታው የጎላ እንደሚሆን በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሠ ገልጸዋል።
አክለውም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን በመስራት አገልግሎቱን ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ ስፋፊ ስራ መሠራት መቻሉን አውስተው በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በተለይም ከብልሹ አሰራር፣ከመልካም አስተዳደር ችግር፣የሚነሱ ቅሬታዎችን በጋራ በመታገልና አዳጊ የሆነዉን የህብረተሰቡን የአገልግሎት ፍላጎት ከግምት ዉስጥ በማስገባት በጋራ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን እንዲሁም በቴክኖሎጂ የታገዘ የአገልግሎት አሰጣጥ በይበልጥ ለመዘርጋት እንዲሁም የህብረተሰቡን የእርካታ መጠን ከፍ ለማድረግ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቅረፍ የጉባኤዉ መቋቋም ሚናው የጎላ ነዉ ሲሉም የስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ መሳይ መርሻ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በዚሁ መድረክ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት የተካሄደ ሲሆን ለቀጣይ ሁለት አመታት የሚመሩ አካላትን በመምረጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
