ar
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
የብልፅግና ፓርቲ ዓመታዊ ስልጠናውን ማካሄድ ጀመረ የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠናውን ማካሄድ ጀምሯል። ስልጠናው "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለሚቀጥሉት 10 ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል። ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት ነው። በስልጠናው ከ2000 በላይ ከፌዴራልና ከክልል የተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ይሳተፋሉ። ከስልጠናው በተጓዳኝ የተግባር የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች የሚካሄድ ይሆናል።

በቅርቡ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት ፉሪ የኮሪደር ልማት ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አከባቢ ነዋሪዎች አንደበት !… See more

የአዲስ አበባ አሁናዊ የጥዋት መልክ !

ባለስልጣኑ ወንዞችንና የወንዝ ዳርቻዎችን የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 1.6 ሚሊዮን ብር ቅጣት ጣለ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም ***************** የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ወንዞችና የወንዝ ዳርቻዎች ላይ ብክለት ሲፈጽሙ የነበሩ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ባለስልጣኑ በጠቅላላው 1,600,000 (አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ) ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት መጣሉን ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የከተማዋን ጽዳት፣ ጤናማ አካባቢና ወንዞች ለታለመላቸው ልማት እንዲውሉ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። በተለይ በየካ ክፍለ ከተማ፣ ሦስት የከብት እርባታ ተቋማት የከብት እዳሪን በቀጥታ ወደ ወንዝ በመልቀቅ ወንዙን በእጅጉ በመበከል ተቀጥተዋል። እነዚህ ሦስቱም ማህበራት እያንዳንዳቸው 300,000 ብር በድምሩ 900,000 ብር ቅጣት ተጥሎባቸዋል። በተመሳሳይ በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ ላይም ቅጣት ተጥሏል። ዩኒቨርሲቲው ወደ ወንዝና መንገድ ላይ ከፍተኛ ብክለት በመፍጠር በ400,000 ብር ተቀጥቷል። እንዲሁም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 የሚገኘው ኢትዮቤስት ሪልስቴት የተሰኘው ተቋም ፈሳሽ ቆሻሻን ከወንዝ ጋር በማገናኘት ወንዞችንና ወንዝ ዳርቻዎችን በማበከሉ 300,000 ሺህ ብር ተቀጥቷል። የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ ይህን እርምጃ ለመውሰድ የቻለው ወንዞችን ለከተማ ልማትና ለነዋሪዎች ጤናማ ኑሮ ማስቀጠል በሚል ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሆን ባለስልጣኑ በቀጣይም ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ለታለመላቸው ልማት እንዲውሉ የሚያደርገውን የደንብ ማስከበር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ለዚህ ስኬት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ፣ ባለስልጣኑ ማንኛውንም የደንብ መተላለፍ የሚመለከት መረጃ ወይም ጥቆማ በነፃ ስልክ ቁጥር 9995 እንዲሰጥ ጥሪውን አቅርቧል። የከተማዋን ፅዳት የማስጠበቅና የብክለትን የመከላከል ጥረት የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን ባለስልጣኑ አሳስቧል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የገጠር ሽግግርን ለማረጋገጥ አንዱ መንገድ የእርሻ ማሽነሪዎችን ማበራከት ነው ።

አዲስ አበባ እንደ ስሟ ዉብ አበባ ሁናለች! ቃልን በተግባር ያሳየችው አዲስ አበባ የምሽት ገፅታ

"ለዛሬዉ ትዉልድ ብቻ ሳይሆን ለቀሪዉ ትዉልድ የሚተላለፍ ዘመኑን የዋጀ ሁሉን አካታች የልማት ስራ መርቀን እንካችሁ ብለናልና በተገቢዉ ልንጠቀምበት ይገባል፡፡! ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከንቲባዋ ሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት ፉሪ የኮሪደር ልማትን በመረቁበት ወቅት እንደተናገሩት ፡፡ ይህ ኮሪደር ልማት በአዲሳ አበባ እስከዛሬ ከተጀመሩት የኮሪደር ስራዎች 11ኛዉ፤በሁለተኛዉ ዙር ከጀመርናቸዉ ዉስጥ 6ኛዉ የሆነና በርካታ የከተማ መልሶ ማልማት ስራዎችን በፍትሃዊነት በዉስጡ ያካተተ ነዉ ብለዋል ከንቲባዋ፡፡ ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ ረጅሙና ሰፊዉ የኮሪደር ልማት ስራ ሲሆን 16 .5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለዉና 589 ሄክታር የሚሸፍን ነዉ ። 33 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን በስፋትም ከ5 እስከ 8 ሜትር የእግረኛ እና 13.5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የሳይክል መንገድ ያለዉ እና ማህበረሰቡ ቋሚ እና ዘላቂ የስራ እድል እንዲያገኝ ወደ 1100 ሱቆች ተገንብተዉ በጉልት ሲነግዱ የነበሩ ወገኖቻችን በእነዚህ የፀዱ ሱቆች እንዲነግዱ መደረጉ ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ወጣቶች ለስፖርት ያላቸዉ ፍቅር የተለየ መሆኑን የገለፁት ከንቲባ አዳነች አቤቤ 20 የስፖርት ሜዳዎች ተገንብተዉ የህብረተሰቡን ፍላጎትና ጥያቁ መመለስ የተቻለበት እና ተጨማሪ 20 የህፃናት መጫወቻ ሜዳዎች ተዘጋጅተዉ ለአገልግሎት ከፍት መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡ 40 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ያካተተዉ ይህ የኮሪደር ልማት 5.2 ኪሎ ሜትር የሚሆን የወንዝ ዳርቻ ልማትም ተሰርቶ ህብረተሰቡን ከጤና ጠንቅ ነፃ እዲሆኑ የሚያስችል ነዉ ተብሏል፡፡ ከተማን ከተማ የሚያሰኙ የከተማ ስታንዳርድ የሚጠይቃቸዉን ሁሉ የተካተተበትን፤በርካታ ጎስቋላ ገፅታዎች አበባ መስለዉ እና ፍክት ብለዉ የተሰሩበትን፤ለዛሬዉ ትዉልድ ብቻ ሳይሆን ለቀሪዉ ትዉልድ የሚተላለፍ ዘመኑን የዋጀ ሁሉን አካታች የልማት ስራ መርቀን እንካችሁ ብለናልና በተገቢዉ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም የመስራት ባህላችንን የበለጠ አጠናክረን በቀጣይ ህዝባችን የሚጠይቃቸዉን ሌሎች ስራዎችን እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ እንደምንሰራ እርግጠኞች ነን በማለት ከልማቱ ጎን አብረዉ ለነበሩ አካላት ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡

ዛሬ በምስራቅ ሸዋ ዞን የነበረን ጉብኝት በክረምት የስንዴ ምርት ሥራዎች የተገኘውን ውጤት የምርት አሰባሰቡን በመመልከት ለመገምገም እና የበጋ ስንዴ ሥራ ማስጀመር ላይ ያተኮረ ነበር። በዚያው አካባቢ የሙዝ፣ ፓፓያ እና አሳ ክለስተር ሥራዎችንም ተመልክተናል። ነባሩ ባሕላዊ የግብርና ዘዴ አሁንም ያለ ቢሆንም በሰፊው ለማረስ የሚያስችለው ሜካናይዜሽን እያደገ በመሄዱ የአካባቢውን የግብርና ብቁነት እና ምርታማነት እያሳደገ ይገኛል። ወደኋላ መለስ ብለን የነበረውን አሰራር ስንገመግም እነዚህን መሰል ዘመናዊ ዘዴዎችን ከብዙ አመታት በፊት እንደ ሀገር ጀምረን ቢሆን ኖሮ የግብርና ምርታችን በከፍተኛ ደረጃ የተለየ ይሆን እንደነበር እንረዳለን። ዛሬ ከአመት ወደ አመት እየጨመረ የሚሄድ ምርታማነት እየተመለከትን እንገኛለን። ለማደግ ምንም አይነት የውጭ ድጋፍ አይመጣም። እውነተኛውን የሀገራችን ለውጥ የሚመራው የራሳችን ጽናት፣ ፈጠራ እና የሥራ ትጋት ነው። Daawwannaan har'a Godina Shawaa Bahaatti goone sassaabbii min'aanii, homisha qonna qamadii gannaatiin argame ilaaluun gamaaggamuufi hojii qonnaa qamadii bonaa eegalchiisuu irratti kan xiyyeeffate ture. Naannawaadhuma sanatti kilaasterii hojiilee muuzii, paappaayyeefi qurxummii ilaalleerra. Malli qonnaa aadaa duraanii ammas kan jiru yoo ta'u, mekaanaayizeeshiniin bal'inaan qotuuf dandeessisu guddachaa dhufuusaatiin gahumsaafi homishtummaa qonna naannichaa guddisuurratti argama. Hojimaata duraan ture duubatti deebinee yoo gamaaggamnu maloonni ammayyaa akkasii akka biyyaatti utuu waggoota hedduu dura eegalleerra ta'ee homishni qonnaa keenyaa haala guddaadhaan adda kan ta'u akka ture hubanna. Har'a homishtummaa waggaa waggaatti dabalaa deemu argaa jirra. Guddachuudhaaf deeggarsi alaa kamiyyuu hin dhufu. Jijjiirama biyya keenyaa isa dhugaa kan hoogganu kutannoo, kalqaafi cimina hojii mataa keenyaati. Our visit today to East Shewa zone focused on reviewing the rainy season wheat harvest and launching the summer wheat production activities. In the same area, we also assessed the progress of the banana, papaya, and fish clusters. Although traditional farming methods still exist, the growing adoption of mechanization in the area is significantly enhancing agricultural efficiency and productivity. Reflecting on the past, had we embraced such modern approaches many years ago, our agricultural output would have been vastly different. Today, we are already witnessing remarkable year-to-year improvements in productivity. Ultimately, no external help is coming. It is our own dedication, innovation, and hard work that will drive the true transformation of our nation.

ዛሬ በምስራቅ ሸዋ ዞን የነበረን ጉብኝት በክረምት የስንዴ ምርት ሥራዎች የተገኘውን ውጤት የምርት አሰባሰቡን በመመልከት ለመገምገም እና የበጋ ስንዴ ሥራ ማስጀመር ላይ ያተኮረ ነበር። በዚያው አካባቢ የሙዝ፣ ፓፓያ እና አሳ ክለስተር ሥራዎችንም ተመልክተናል። ነባሩ ባሕላዊ የግብርና ዘዴ አሁንም ያለ ቢሆንም በሰፊው ለማረስ የሚያስችለው ሜካናይዜሽን እያደገ በመሄዱ የአካባቢውን የግብርና ብቁነት እና ምርታማነት እያሳደገ ይገኛል። ወደኋላ መለስ ብለን የነበረውን አሰራር ስንገመግም እነዚህን መሰል ዘመናዊ ዘዴዎችን ከብዙ አመታት በፊት እንደ ሀገር ጀምረን ቢሆን ኖሮ የግብርና ምርታችን በከፍተኛ ደረጃ የተለየ ይሆን እንደነበር እንረዳለን። ዛሬ ከአመት ወደ አመት እየጨመረ የሚሄድ ምርታማነት እየተመለከትን እንገኛለን። ለማደግ ምንም አይነት የውጭ ድጋፍ አይመጣም። እውነተኛውን የሀገራችን ለውጥ የሚመራው የራሳችን ጽናት፣ ፈጠራ እና የሥራ ትጋት ነው። Daawwannaan har'a Godina Shawaa Bahaatti goone sassaabbii min'aanii, homisha qonna qamadii gannaatiin argame ilaaluun gamaaggamuufi hojii qonnaa qamadii bonaa eegalchiisuu irratti kan xiyyeeffate ture. Naannawaadhuma sanatti kilaasterii hojiilee muuzii, paappaayyeefi qurxummii ilaalleerra. Malli qonnaa aadaa duraanii ammas kan jiru yoo ta'u, mekaanaayizeeshiniin bal'inaan qotuuf dandeessisu guddachaa dhufuusaatiin gahumsaafi homishtummaa qonna naannichaa guddisuurratti argama. Hojimaata duraan ture duubatti deebinee yoo gamaaggamnu maloonni ammayyaa akkasii akka biyyaatti utuu waggoota hedduu dura eegalleerra ta'ee homishni qonnaa keenyaa haala guddaadhaan adda kan ta'u akka ture hubanna. Har'a homishtummaa waggaa waggaatti dabalaa deemu argaa jirra. Guddachuudhaaf deeggarsi alaa kamiyyuu hin dhufu. Jijjiirama biyya keenyaa isa dhugaa kan hoogganu kutannoo, kalqaafi cimina hojii mataa keenyaati. Our visit today to East Shewa zone focused on reviewing the rainy season wheat harvest and launching the summer wheat production activities. In the same area, we also assessed the progress of the banana, papaya, and fish clusters. Although traditional farming methods still exist, the growing adoption of mechanization in the area is significantly enhancing agricultural efficiency and productivity. Reflecting on the past, had we embraced such modern approaches many years ago, our agricultural output would have been vastly different. Today, we are already witnessing remarkable year-to-year improvements in productivity. Ultimately, no external help is coming. It is our own dedication, innovation, and hard work that will drive the true transformation of our nation. You're commenting as Etsegenet Tesfahun.

አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል! እውቀትን ሰብስቡ፣ ክህሎትን አዳብሩ፣ ለአገር የሚበጅ ዜጋ ሁኑ። ሁሌም እንኮራባቸኃለን ! ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

ዛሬ በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ500 በላይ ውጤት ካስመዘገቡ 1321 ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት ላመጡ 336 ተማሪዎች እውቅና ሰጥተን አበረታተናል። በ2016 የትምህት ዘመን የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ ያለፋት 21.3 በመቶ ሲሆኑ በ2017 ወደ 31 በመቶ አድጓል፤ እንዲሁም እንደ ሀገር 100 ፐርሰንት ካሳለፉ 50 ትምህርት ቤቶች መካከል 17ቱ በከተማ አስተዳደራችን ስር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ናቸው። በተጨማሪም ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ መቻላቸው የስራችን ውጤታማነት ማሳያ ነው። በተለይም ዛሬ የማበረታቻ ሽልማት ከሰጠናቸው መካከል አይነ ስውራን እና መስማት የተሳናቸው ተማሪዎቻችን ለገጠማቸው የአካል ጉዳት ፈተና እጅ ሳይሰጡ ላስመዘገቡት ከፍተኛ ውጤት ትልቅ ክብር አለኝ ። የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ውድ ተማሪዎቻችን በዩኒቨርሲቲዎቹ የሚኖራችሁ ቆይታ የበለጠ እውቀት የምትቀስሙበት፣ ለአገር ለወገን የሚጠቅም ክህሎት ይዛችሁ የምትወጡበት እንዲሆን እመኛለሁ። ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ Har'a bara barnootaa 2017 qormaata dabriinsa kutaa 12ffaa barattoota qabxii 500 ol galmeessan 1321 keessaa qabxii olaanaa kanneen fidan barattoota 336f beekamtii laannee jajjabeessineerra. Bara barnootaa 2016 barattoota qormaata kutaa 12ffaa fudhatan keessaa kan dabran dhibbeentaa 21.3 yemmoo ta'an,kuni bara 2017tti gara dhibbeentaa 31.3 guddateera. Akkasumas akka biyyaatti manneen barnootaa 100% dabarsan 50 keessaa 17 manneen barnootaa bulchiinsa magaalaa keenyaa jalatti argamaniidha. Dabalataanis manneen barnoota bultii lama 100% dabarsuu danda'uun milkaa'ina hojii keenyaa kan mul'isuudha. Keessattuu har'a badhaasa jajjabiinsaa kanneen laanneef keessaa barattoota keenya ijan hin arginee fi gurraan hin dhageenye qormaata qaama miidhamummaa isaan muudateef osoo harka hin kennin qabxii olaanaa galmeessaniif kabaja olaanaa qaba. Qabxii seensa Univarsiitii kan galmeessitan qaaliiwwan barattoonni keenya turtiin univarsiitiiletti qabaattan caalaatti beekumsa kan itti argattan ogummaa biyyaa fi lammii fayyadu qabattanii kan itti baatan akka ta'un hawwa. Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu.