Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
ፅዳት የዕለት ተዕለት ተግባራችን እንጂ የአንድ ቀን ስራ ሊሆን አይገባም" በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ
የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በህዳር ወር ሙሉ ሲያካሂደው የነበረውን "ህዳር ሲፀዳ አካባቢያችን ጤና!" በሚል መሪ ቃል በሁሉም ክ/ከተሞች የተካሄደውን ታላቅ የፅዳት ንቅናቄ እና የግንዛቤ መፍጠር ስራ በማዕከልነት በተመረጠው በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ሰሚት 3ኛ አካባቢ በስኬት አጠናቋል።
በማጠቃለያ መርሀግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ "ፅዳት የአንድ ቀን ስራ ብቻ ሳይሆን ይልቁንም በየቀኑ የምናመነጨውን ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ የምንሰበስብበት፣ የምናስተዳደድርበት እንዲሁም ፅዱና ንፁህ መሆንን ባህል የምናደርግበት ነው" ብለዋል።
ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ አክለውም፣ ከተማዋ ፅዳትን ባህል ለማድረግ ከለውጡ ወዲህ በርካታ ተጨባጭ እና አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስራዎችን መስራቷን ጠቁመው ይህም ስራ አዲስ አበባን በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን አስችሏል ብለዋል
ከተማዋ ለፅዳት እና ለአካባቢ ጥበቃ የሰጠችው ትኩረት ፍሬ በማፍራቱ፣ አዲስ አበባ በ2027 በአውሮፓውያን አቆጣጠር ለሚካሄደው 32ኛው የኮፕ (COP32) የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ አዘጋጅ ከተማ ሆና መመረጧን ዋና ስራ አስኪያጁ አስታውቀዋል።
"የዛሬው ንቅናቄ ማጠቃለያ ቢሆንም የፅዳት ስራን ጨርሰናል ብለን ወደ ቤት የምንገባበት ሳይሆን ግለቱን ጠብቆ የሚቀጥልበት ፅዳትን ባህል አድርገን የአካባቢያችንን ፅዳት የምንጠብቅበት ነው" ሲሉ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ አሳስበዋል።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው ፅዳት የአካባቢን ንፅህና ከመጠበቅ ባሻገር የአንድ ማህበረሰብ ስልጣኔ መገለጫ እና የጤና ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በፅዳት እና በንፅህና አጠባበቅ ረገድ ዘላቂ መሻሻሎችን ለማምጣት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው ገልፀዋል።
በፅዳት ንቅናቄ መርሀግብሩ ላይም በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ክቡር ኢንጂነር ወንድሙ ሴታን ጨምሮ የከተማና የክ/ከተማ አመራሮች፣ የፅዳት አምባሳደሮች፣ አርቲስቶች፣ የፀጥታ አካላት፣ ወጣቶች ፣ የተለያዩ አደረጃጀቶች ፣ ማህበራቶች እና የአካባቢው ነዋሪ ህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ታህሳስ 4/2018 አ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ 106 የቀበሌ ቤቶችን ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አቅመ ደካሞች፣ የአካል ጉዳተኞች እና የአገር ባለውለታዎች ለሆኑ እና እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ የከተማችን ነዋሪዎችን ለይተን በእጣ አስተላልፈናል ።
ከህዝብ ጋር ባደረግነው ውይይት የተሰጡንን ጥቆማዎችን ጭምር ተጠቅመን ባደረግነው ማጣራት የለየናቸውን ነዋሪዎቻችንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ፣ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባ የተዘነጉ፣ ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን አቅመ ደካማ ወገኖችን እንባ በማበስ እና ከነበሩበት አስከፊ ሕይወት በመታደግ ነገን በተስፋ እንዲያዩ የሚያስችል ስራ ተከናውኗል ።
በተለይም ከአራዳ ክፍለ ከተማ ከቁርጡሚ ወንዝ ዳርቻ ለተነሳችሁ፣ በሶስተኛ ወገን ክርክር ምክንያት ስትንገላቱ የቆያችሁ ዛሬ ችግሩን ፈተን የመኖሪ የቤት ስላገኛችሁ እጅግ ደስተኞች ነን፤ እንኳን ደስ አላችሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በከተማችን እየተተገበሩ ካሉ የዜሮ ግብ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ተረጂነት እና ልመናን ዜሮ ማድረግ ነው።… See more
አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት ቀድሞ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ የአገልግሎት ፈላጊዎችን እንግልት መቅረፉን በድንገተኛ ጉብኝት መረዳታቸዉን በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ዋና ስራ አስ… See more
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባሉ 50 ወረዳዎች አገልግሎት መስጠት የጀመረው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት የዲጂታል አሰራር ስርአት በተመረጡ ወረዳዎች በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ የአገልግሎት አሰጣጡ ያለበት ደረጃ ተጎበኘ።
በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በከተማችን በተመረጡ 50 ወረዳዎች በያዝነው ሳምንት ሰኞ ህዳር 29 ቀን ጀምሮ አገልግሎት መስጠት በጀመረው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግልት የዲጂታል አሰራር ስርአት ነዋሪዎች በየወረዳቸው ተገኝተው አገልግሎት ሲያገኙ በመስክ ምልከታ አረጋግጠዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በተለይም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 እና 6 እንዲሀም በኮልፌ ወረዳ 8 የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ጽ/ቤት ተገኝተው ነዋሪዎች በአዲሱ ሲስተም አገልግሎት ሲያገኙ ከስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት እና ከሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን ተመልክተዋል።
በዚሁ ወቅት ተገልጋዮቹ አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት ሲስተም ከዚህ ቀደም በከፊል በወረቀት ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን ያስቀረና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያደረገ፣ የፋይዳ መታወቂያ ከከተማ የነዋሪነት አገልግሎት መታወቂያ ጋር የተሳሰረ የመታወቂያ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስቻለና የተለያዩ እንግልቶችን ያስቀረ መሆኑን ገልጸውላቸዋል።
ተገልጋዮቹ አክለውም በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ያለ የባለፋይሎቹ ባለቤቶች ይሁንታ ሳይገኝ ለማንም በእነርሱ የቤት ቁጥር መታወቂያ እንዳይሰጥ መቆጣጠር እንደሚያስችል ግንዛቤ እንዳላቸውም ነዋሪዎች በጉብኝቱ ወቅት አረጋግጠውላቸዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት በመዲናችን አዲስ አበባ የስማርት ሲቲ ግንባታ ሂደት የከተማችን ነዋሪዎች የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ረገድ የሚሰጠውን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጅ የዘመነ ስሉጥ፣ ዘመናዊና ፍትሃዊ በማድረግ የአገልግሎት እርካታ ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት የአዲሱ ሲስተም ትግበራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል።
አክለውም አዲሱ ሲስተም በከተማችን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት አሰጣጥን በይበልጥ በማጠናከር ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የተላበሰ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ከማስቻሉም በላይ በወረዳ ጽ/ቤቶች አገልግሎት ለማግኘት ነዋሪዎች ሲያጋጥማቸው የነበረውን ተደጋጋሚ ምልልስና እንግልት ያስቀረ መሆኑን በጉብኝታቸው ወቅት መመልከታቸውን አስረድተዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በእርግጠኝነት የሃገር ሃብት፤ለሃገር ልማት በማዋል በኩል ረጅም መንገድ መጓዝ ችለናል፡፡"ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በዛሬዉ እለት 22ኛዉ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ከተማ አቀፍ ንቅናቄ የማጠቃለያ መደረክ አድዋ በሚገኘዉ ፓንአፍሪካ አዳራሽ ተካሔዷል።
"ትዉልድን በስነ-ምግባር፤ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያየ ደረጃ እና በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር መቆየቱና የዛሬዉም ከተማ አቀፍ ማጠቃለያ መድረክ መሆኑ ታዉቋል፡፡
በክብር እንግድነት ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት ሙስና ፀያፍ የሆነ፤የሃገርን ገፅታ የሚገታ፤ትዉልድን የሚጎዳ እና ኢ-ፍትሃዊነትን የሚያነግስ ተግባር በመሆኑ የመላዉ ማህበረሰብን እና የሁሉንም ተቋማት ትግል የሚጠይቅ ቀዳሚ ጉዳይ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ መንግስት በወሰደዉ ቁርጠኛ አቋም ፤በተሰራዉ ስራ እና በተፈጠሩ አስቻይ ሁኔታዎች ሙስናን በመከላከል በእርግጠኝነት የሃገር ሃብት ለሃገር ልማት በማዋል በኩል ረጅም መንገድ መጓዝ ችለናል ብለዋል፡፡፡
በዚህም በየዘመናቱ በነበሩ የየስርዓቱ መሪዎች የሃገር ሃብት ወደ ዉጪ በማሸሽና በማከማቸት፤ ከባለሃብቶች ጋር ከሃገር ዉጪ በመስራት የሃገራችንን ልማት እና እድገት የሚያቀጭጭ ተግባር በዚህ ዘመን ታሪክ ሆኖ አልፏል ብለዋል፡፤
ይህን ጅምር ስራ የበለጠ ለማጠናከር በእያንዳንዱ ስራችን ሙስናን የሚፀየፍ ትዉልድ በማፍራት ረገድ ትላልቅ ሃላፊነት ያለብን ተቋማት አቅደን መስራት እና ለዉጥ ማምጣት ይጠበቅብናል በማለት ገልፀዋል፡
አክለዉም ሁልጊዜ በምንሰራዉ ስራ ሙስና እንዳይተገበር መከላከል ብቻ ሳይሆን ሙስናን የሚፀየፍ ትዉልድ መገንባት ላይ ስለመሆናችን ራሳችንን መጠየቅ እና ከምንናገረዉ ባሻገር የምንናገረዉን ሁነን መገኘት ትዉልድ እንዲከተለን የሚያደርግ እዉነታ ስለሆነ ይህን መርህ በጥብቅ ልንተገብረዉ ይገባል ብለዋል ከንትባዋ፡፡
መላዉ አመራር በፀረ-ሙስና ትግሉ ላይ የሃሳብና የተግባር አንድነቱን በማፅናት በግለሰቦች ደረጃ ሳይቀር በመንግስት ኃላፊዎችና በሠራተኞች የሚታዩ ሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ ሁላችንም እጅለ ለእጅ ተያይዘን መስራት እና ትዉልድ ላይ የሞራል ልእልና እንዲበለፅግ ስር የሰደደዉን ኢፍትሃዊ አካሄዶችን መዋጋት ይጠበቅብናል በማለት ገልፀዋል፡፤
በመጨረሻም ዛሬ ያገኘነዉን ዉጤት ለማወደስ ሳይሆን የበለጠ የፀረሙስና ትግሉን በማጠናከር ተጠያቂነትን ለማስፈን ቃል የምንገባበትና የገባነዉን ቃል የምናድስበት ስለሆነ ሃላፊነታችንን በአግባቡ በመወጣት፤አሰራራችንን ግልፅ በማድረግ ፤ከሰዉ ንኪኪ ነፃ ሆነን ህዝባችንን እናገልግል በማለት መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡
በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ በከተማዋ በተደረገዉ የፀረ-ሙስና ትግል ላይ የላቀ አስተዋፅአ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጧል::
ሙስናን የመከላከል ትግል መላው ማህበረሰብ ፣ ሁሉም ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት ይገባል!
ዛሬ 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን “ትውልድን በስነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ሀሳብ ስናከብር ሙስናን ለመዋጋት ያለንን ቁርጠኝነት እና የገባነውን ቃል በማደስ ነው።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሙስናን የብልፅግናችን ፀር፣ የኢፍትሀዊነት ምንጭ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ አድርገን ያፋፋምነው ትግል ከዚህ ቀደም የነበረን አስከፊ መንግስታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት አስችሏል። በዚህም እንደ አገር ብሎም እንደ ከተማ የህዝብና የመንግስትን ሀብት በተገቢው የልማት ስራዎች ላይ በማዋላችን አስደናቂ የልማት ውጤቶች ማሳየት ችለናል።
መንግታዊ / ስርአታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት ብንችልም፣ በግለሰብ ደረጃ የሚታይ በመንግስት ሃላፊዎች እና ሰራተኞ የሚፈፀመው ሌብነት እና ጉበኝነት ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ለሙስና አጋላጭ አሰራሮችን ለመዝጋት እና ከምንጩ ለማድረቅ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር፣ መንግስታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆንና ተጠያቂነትን በማስፈን ሙስናን በተሟላ መልክ ለመከላከል የሁሉንም ተቋማት ትግል እና የሁሉንም ሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛ ርብርብ ይጠበቃል።
ቤተሰብ፣ ማህበረሰቡ፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት … ወዘተ ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ በፀረ ሙስና ትግል ውስጥ በአመለካከትም በተግባርም ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር የማይተካ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ።
በመሆኑም የፀረ ሙስና ትግላችን ይበልጡን ውጤታማ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራትን ማጠናከር አስፈላጊ ነው ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ 3 ዘመናዊ ባለ 10 ወለል ስማርት የወረዳ የአስተዳደር ሕንፃዎችን ገንብተን ወደ ሥራ አስገብተናል።
በከተማችን የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ከተከናወኑ በርካታ ተግባራት መካከል አንዱ ለህዝብ ቅርብ የሆኑ የወረዳ አገልግሎት መስጫዎችን ማዘመን፣ በበቂ የሰው ኃይል ማደራጀት፣ በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ እንዲሁም ለአገልግሎት ሰጪውና ለተገልጋዩ ማኅበረሰብ ምቹ የስራ ቦታን መፍጠር ይገኝበታል።
እነዚህ ስማርት የአስተዳደር ሕንፃዎች አገልግሎትን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ የተገልጋዩ ጊዜና ሀብት እንዳይባክን በማድረግ፣ እንግልትና ውጣ ውረድን በመቀነስ፣ በአንድ ማዕከል ፈጣንና ቀልጣፋ የወረዳ አገልግሎቶችን ማግኘት እንዲያስችሉ ተደርገው የተገነቡ ናቸው።
ሕንፃዎቹ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ፤ የልጆች ማቆያና መጫወቻ ስፍራ፤ ውብ፣ ጽዱና አረንጓዴ ቅጥር ጊቢ እንዲኖራቸው ተደርገው ተገንብተዋል። በተጨማሪም አካል ጉዳተኞችንና አቅመ ደካሞችን ታሳቢ ያደረጉ ሊፍቶች የተገጠሙላቸው ናቸው።
በመሆኑም ዛሬ በልደታ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በሶስት ወረዳዎች ስራ ያስጀመርናቸው ባለ 10 ወለል ስማርት የአገልግሎት መስጫ የአስተዳደር ሕንፃዎች ከተማችንን ስማርት/ስሉጥ ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ስራ አካል በመሆናቸው፣ በቀሪዎቹ ወረዳዎች ላይ የማስፋትና የማብዛት ሥራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በመደመር መንግሥት እይታ የከተሞች ልማት ዘርፍ እምርታ- አዲስ አበባ የአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት መዲና- በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ከኢትዮጽያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት… See more
