Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
በፋይናንስ ዘርፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ወሳኝ ምዕራፍ የሆነውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ በይፋ መጀመሩ በአዲስ አበባ ሁሉም ዜጋ የፋይዳ መታወቂያ እንዲኖረው እየተከናወነ ላለው ተግባር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ሲሉ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ።
የኢትዮጽያ ብሔራዊ ባንክ በአገሪቱ ያሉ ሁሉም ባንኮች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከደንበኞች የባንክ ሂሳብ ቁጥር ጋር የማጣመር ስራን በዛሬው እለት በይፋ ማስጀመሩ በዘመናዊ የዲጂታል ስርአት ግንባታ የፋይናንስ ዘርፉ የዲጂታል ሪፎርም የጀርባ አጥንት መሆኑን በተግባር ያረጋግጠበት ነው ሲሉም ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታውቀዋል።
አያይዘውም የዲጂታል የማንነት ስርአት አንድ ሰው በትክክለኛ አንድ ማንነቱ እንዲታወቅ ከማድረግ በተጨማሪ የመንግስትንም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን ፣ ከፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የዜጎች ሁሉም መረጃ ከአንድ ቋት የሚቀዳና ደህንነቱ የተጠበቀ በማድረግ ረገድ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸው ይህም ጊዜ ካለፈበትና ከተበታተነ የመረጃ አሰራር ስርአት ለመላቀቅ የሚያስችል እንደሆነም አስገንዝበዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በገለጻቸው የማንነት መለያ ስርአት በዲጂታል ቴክኖሎጅ ሲጠናከር በሁሉምዘርፍ ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ያለው፣ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽነትን የተላበሰ እንዲሆን በማድረግ የተገልጋዩን አርካታ የሚያረጋግጥ እንደሆነም አመልክተዋል።
አክለውም በአዲስ አበባ የዲጂታል የማንነት ስርአት የማጠናከር ስራ ውስጥ የኢትዮጽያ ብሔራዊ ባንክ የፋይዳ ዲጂታል ከባንክ ስርአት ጋር የማጣመር ተግባር ወሳኝ የሽግግር ምእራፍ መሆኑን ገልጸው ይህም ጊዜ ካለፈበት የተንዛዛ የወረቀት የአሰራር ስርአት፣ወጥነት ከሌለውና ከተዘበራረቀ የመረጃ ስርአትና ከመረጃ ማመሳከር ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ የአገልግሎት መዘግዬትን የሚቀርፍ እንደሆነ አስረድተዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ በማጠቃለያቸውም ለእያንዳንዱ ዜጋ አንድ የዲጂታል መታወቂያ መያዝ ማለት በተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት (Civil Registration and Vital Statistics with e-ID) ተግባራዊነት ፣በአንድ መስኮት ሁሉንም የመንግስት አገልግሎቶች ማለትም የመሬት፣ የታክስ እና ከቤቶች ልማት ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን እና ሌሎች መሠረታዊ አገልግሎቶችን በዲጂታል የክፍያ ስርአት መፈጸም የሚቻልበት እንደሆነም አብራርተዋል።
የፋይዳ መታወቂያ አገልግሎት የቴክኖሎጂ ሽግግር ብቻ ሳይሆን ግልጽነትና ፍትሃዊነት የተላበሰ ፈጣንነና ቀልጣፋ አገልግሎት የተረጋገጠባት አዲስ አበባን እውን በማድረግ ረገድ ፋና ወጊና እምርታዊ ለውጥ ማስመዝገብ የሚቻልበት ነው ሲሉም ኢንጅነር ወንድሙ በአጽንኦት ገልጸዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ማላዊቷ ዓለማቀፍ ዝናን ያተረፈች አርቲስት ኦሞ ሳንጋሬ በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎችን ጎበኘች።
አርቲስት ኦሞ ሳንጋሬ፥ የግራሚ አዋርድ ሽልማት አሸናፊ፣ የአፍሪካ ሴቶች መብት ተከራካሪ እና ዓለም አቀፍ ዝናን የተጎናፀፈች ድምጻዊት ናት፡፡
በእናቷ በኩል “የኢትዮጵያ የደም ሐረግ እንዳላት” የምትናገረው ኦሞ ሳንጋሬ፥ የእንጦጦ ፓርክን ጨምሮ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም፣ የመንገድ መሰረተ ልማት፣ ፓርኮችን እና መሰል የልማት ስራዎችን ጉብኝት አድርጋለች፡፡
ኦሞ ሳንጋሬ በሰጠችው አስተያየትም “ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት ከአምስት አመት በኃላ ነው። ባየሁተእ ለውጥ፣ በከተማዋ በፍጥነት መለወጥ እና በራሳችሁ አቅም ይህን የመሰለ ከተማና ጥራት ያለው ህንፃ መገንባታችሁ አስደንቆኛል” ብላለች።
ከከተማ ዕድገቱ ጋር የተሰሩ በርካታ ፓርኮችና የመዝናኛ ቦታዎች የሚደነቁ እንደሆነም አርቲስት ኦሞ ሳንጋሬ ተናግራለች።
በጉብኝቱ ከበርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ አርቲስቶች፣ ቲክቶኮሮች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎችም ተሳትፏል።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የህዳር ወር የስራ እንቅስቃሴን ያካተተውን የዜና መፅሄት በቀጣዩ ሊንክ በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ"! በሚል መሪ ቃል ለስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ አባላት ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል።
ለስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ከትናንትው እለት ህዳር 29 ቀን ጀምሮ በከተማ ልማት ዘርፍ፣ በግብርናና ገጠር ልማት፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች ላይ አተኩሮ ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በዛሬው እለት ህዳር 30/2018 ማምሻውን ተጠናቋል።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ ሰብሳቢና የእዲስ አበባ ከተማ ም/ዋ/ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ሞላ እንደተናገሩት የብልጽግና ራእይና ተግባራት በዋነኝነት ሰው ተኮር መሆናቸው በአግባቡ በመረዳት የዘርፎች እምርታም ሀገርን መለወጥ ላይ የሚያተኩር መሆኑን በመገንዘብ የፓርቲያችን አባላት በየተመደብንበት የስራ መስክ በምሳሌነት የምናገለግል ጠንካራ ፈጻሚ ልንሆን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
አክለውም በተለይም በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ላይ እንደተሰማራ ባለሙያ በፈጠራና በፍጥነት የታጀበ አገልግሎት አሰጣጥን ተግባራዊ ከማድረግ በተጨማሪ በታማኝነት፣ በቅንነትና በሀቀኝነት ለማገልገል የሚያስችል አስተሳሰብ፣ክህሎትና እውቀት በመላበስ፣ የተለወጠና ዲሞክራት አገልጋይ በመሆን የከተማችን የብልፀግና ተምሳሌትነት በተግባር በማረጋገጥ ረገድ የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በስልጠናው የሁለት ቀናት ቆይታ የስራ አስኪያጅ ልዩ ወረዳ አመራሮች ባቀረቡት ሰነድና ከአባላት ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ እንዳመለከቱት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በግብርናና ገጠር ልማት፣ በከተማ ልማትና በኢንዱስትሪ እንዲሁም በቱሪዝም ዘርፍ እንደ አገርም ሆነ በከተማችን በርካታ ስኬቶችና ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል።
አያይዘውም የመደመር ትውልድ አካል የሆነው የብልፅግና አባል በሀሳብና በሀገር በቀል እውቀት ላይ የተመሠረተ የመደመር እሳቤ በመያዝ ትውልዱ አዲሲቷን ኢትዮጵያን የሚቀበል፣ በገዢ ትርክት እየተገነባ በመደመር መንግስት እየተመራ የዘርፎችን እምቅ አቅም በፍጥነት፣በፈጠራና በዝላይ ወደ ብልጽግና ማሻገር ይገባል ሲሉም ሰነድ አቅራቢዎቹ አስረድተዋል። ከሰልጣኞች ለተነሱ የተለያዩ አስተያዬትና ጥያቄዎችም ምላሽና ማብራሪያ በዚሁ ወቅት ተሰጥቷል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የተጠገኑ የመንገድ መብራቶች ላይ ጉብኝት ተካሄደ
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ለረጅም ዓመታት ፓል ኖሯቸው ባለመብራታቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው የቆዩ የመንገድ መብራቶችን በመጠገን አገልግሎት እንዲሰጥ በተደረጉ መንገዶች ላይ ጉብኝት ተካሄደ።
ህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ያነሳቸው የነበሩ ችግሮችን ቀን ከሌት በመስራት ባለስልጣኑ ማብራት መቻሉን በጉብኝቱ ታይቷል።
በጉብኝቱ ከታዩት ውስጥ ከቱሉ ዲምቱ አደባባይ -አለም ባንክ፣ ከቱሉ ዲምቱ-አርሴማ፣ ከአቃቂ ድልድይ- ዩኒሳ፣ ከቃሊቲ ማሰልጠኛ - ዩኒሳ፣ ከአቃቂ ክ/ከተማ - የሴቶች ተሀድሶ ማዕከልና ቃሊቲ ቶታል ተርሚናል ተጠቃሾች ናቸው።
በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉ አመራሮች በመሰረተ-ልማቱ ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን በመከላከልና በመጠበቅ፤ መብራቱ ለታለመለት ዓላማ ውሎ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ በማድረግ በኩል ያለውን አደረጃጀት በመጠቀም ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
ዘመናዊ መብራት፤ ለብሩህ አዲስ አበባ!
ህዳር 30/2018
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ዛሬ ማለዳ ከኡራኤል ብራስ፣ ቦሌ መድኃኔዓለም ጎላጎል እስከ እንግሊዝ ኤምባሲ የሚዘልቀውን የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት እና የፒኮክ (ማዕከላዊ) ፓርክ ግንባታን ገምግመናል።
ይህ ኮሪደር በከተማችን በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ለማስፋት የተጀመረ ዘጠነኛው ኮሪደር … See more
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ይፋ ሆነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ይፋ አድርጓል፡፡
የአንዳችን ውበት ለሌላችን ውበት፤ የአንዳችን ክብር ለሌላችን ክብር የሆንባት ሀገር-ኢትዮጵያ። አንዱ ዝቅ ሌላው ከፍ ብሎ ሳይሆን ሁላችን እኩል ሆነን፣ በወንድማማችነት ዐይን ተያይተን በመደመር እሳቤ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን ማሻገር አለብን። በአባቶቻችን ደም የወረስነውን ነጻነት የኢትዮጵያን ብልጽግና በማረጋገጥ ማጽናት ከዚህ ትውልድ የሚጠበቅ ተግባር ነው።
ኢትዮጵያ እየተገነባች ያለችው በራሳቸው በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን ነው፤ አዲስ አበባ የተደራጀችው፣ ከተማዋን ለህዝቧ በዕውኑ እየቀየረች ያለች፣ ቆራጥ እና ታታሪ ሴት ከንቲባ ስላለቻቸው ነው”
አንያንጎ Thee Anyango ኬንያዊቷ የዘ-ስታንዳርድ አምደኛ)
ከሰሞኑ አንድ አንያያጎ (Thee Anyango) የተባለች ኬንያዊ ጋዜጠኛ ከተማቸችን አዲስ አበባን ጎብኝታለች፡፡ በቆይታዋም ስለከተማዋ እድገት ከናይሮቢ ከተማ ጋር እያነጻፀረች ሰፋ ያለ ማብራርያ ሰጥታለች፡፡ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
ቦሌ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ስትደርሱ መጀመሪያ የሚቀበላችሁ ነገር የቦታው ስፋት፣ ግዝፈት እና ብሩህ መብራት ነው። ከዚያም ስሜትን የሚያድስ ቀዝቃዛ አየር አለ። አዲስ አበባ የሰላም፣ የመረጋጋት እና የፀጥታ መንፈስ የተላበሰች ከተማ ነች።
መንገዶቹ በጣም ንጹህ እና እጅግ ውብ ናቸው። በዚህች ከተማ ጽዳት የሁሉም ሰው ኃላፊነት ነው። ቆሻሻ መጣል ነውር ነው፤ ያስቀጣልም፡፡ ህዝቡም ህጉን ያከብራል። በመንገዶች ላይ የሚታዩት የቆሻሻ መጣያ ገንዳዎች ሳይቀሩ ጽዳታቸውን የጠበቁ ናቸው።
በመሀል ከተማ ውስጥ እግረኞች በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። ትናንሽ ታክሲዎች እና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በዲሲፕሊን ይሽከረከራሉ። በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የቅንጦት ሳይሆኑ በተግባር የሚታዩ የአኗኗር ዘይቤዎች ሆነዋል። የአውቶቡስ እና የትራፊክ ስርዓቱም እጅግ የተደራጀ ነው።
የሚዲያ ተቋሞቻቸው (Media houses) ልክ እንደ ቶኒ ስታርክ (Tony Stark) ወርክሾፕ ዘመናዊ፣ ሰፊ፣ ንጹህ እና በምርጥ ቴክኖሎጂ የተደራጁ ናቸው።
ከሙዚቃ ጋር የተቀናጁ፣ ብሔራዊ መዝሙርን በድምጽ ማጉያ እያሰሙ የሚደንሱ የውሃ ምንጮች (Dancing water fountains) ለህዝብ ክፍት ሆነው ይታያሉ። እነዚህ ፕሮጀክቶች በብድር ሳይሆን በኢትዮጵያውያን የግብር ገንዘብ የተገነቡ ናቸው።
አዲስ አበባ እንደዚህ የተደራጀችው ከተማዋን ለህዝባቸው ለመቀየር ሌት ተቀን በሚሰሩ ጠንካራ ሴት ከንቲባ አማካኝነት ነው። በአጠቃላይ አዲስ አበባ በኢትዮጵያውያን እጅ ለኢትዮጵያውያን እየተገነባች ያለች መሆኗ በግልጽ ይታያል።
ኢትዮጵያ እየተገነባች ያለችው በራሳቸው በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን ነው። ይህም ግዙፉን የህዳሴ ግድብ ያካትታል። ይህ ግዙፍ የልማት ስራ የተከናወነው በኢትዮጵያውያን የግብር ገንዘብ እና በህዝብ ተሳትፎ ነው እንጂ፤ እንደተለመደው ከአይ ኤም ኤፍ (IMF) በተበደረ ገንዘብ አይደለም። ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ታሪክ በራሳቸው አቅም እየጻፉ ነው።
ምንጭ፦ ዘ-ስታንዳርድ (ኬንያ)
የ20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በውቢቱ ሆሳዕና ከተማ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በበዓሉ ባደረጉት ንግግር “የኢትዮጵያን ችግሮች ብቻ ሳይሆን አቅሞቿን መመልከት ይገባናል” ብለዋል።
በሚቀጥለው ዓመትም የጅማ ከተማ 21ኛውን በዓል እንደምታከብርም በፕሮግራሙ ላይ ተገልጿል።
The 20th Nations and Nationalities Day was colorfully celebrated today in the city of Hoseana, in the Central Ethiopia Region, in the presence of Prime Minister Abiy Ahmed and other high-level government officials. In his remarks on the occasion, Prime Minister Abiy Ahmed poignantly stated, “We need to not only see Ethiopia’s problems but also its potential.”
It was also announced during the program that the city of Jimma will host the 21st celebration next year.
#PMOEthiopia
መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል አደረሳችሁ!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
