Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
በእሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቅድመ አደጋ መከላከል አገልግሎት ውጤታማነትን በብቃት በማረጋገጥ በተቋሙ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ወደላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚገባ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አሳሰቡ።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን ያሳሰቡት በዛሬው እለት ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከማእከል እስከ ቅርንጫፍ ያሉ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ጋር በተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት፣ በሪፎርም ስራዎችና ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ነው።
በመድረኩ ላይ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አክለው እንደገለጹት ኮሚሽኑ የከተማውን ፈጣን እድገትና ተለዋዋጭ የአደጋ ተጋላጭነት ሁኔታ የሚመጥን የቅድመ አደጋ መከላከል ስርአትንና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ስራዎችን ለማጠናከር እየተካሄዱ ያሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የማስደገፍ ሰራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በየደረጃው ያለው አመራር በልዩ ቁርጠኝነትና ተነሳሺነት ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባው በአጽንኦት ተናግረዋል።
በተለይም ደግሞ ኮሚሽኑ አዲስ አበባን ከአደጋ እንደሚከላከል፣ ደህንነቷን እንደሚጠብቅና ዜጎች ከአደጋ ተጠብቀው በሰላም ወጥተው እንዲገቡ የማድረግ ሃላፊነት እንደተጣለበት ተቋም የሪፎርም ስራውን በላቀ ብቃት በመምራት፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጅ ትግበራ በማፋጠንና የሰው ሃብት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በማጠናከር፣ በዋነኝነት አደጋን ቀድሞ የመከላከል ስራው በልዩ ትኩረት ማከናወን ይጠበቅበታል። ከዚህም ጋር ተያይዞ ሕዝባችንን በበለጠ ተነሳሽነት፣ የሞራል ልዕልና ሰብአዊነትን በተላበሰ መልኩ ማገልገል ይጠበቅባችኋል ሲሉም አስገንዝበዋል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አህመድ መሃመድ በዚሁ ወቅት ኮሚሽኑ የአገልግሎት ውጤታማነት ለማረጋገጥና የመልካም አስተዳደር ከማስፈን ጋር በተያያዘ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ስራዎች አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ ሪፖርት አቅርበዋል።
በሪፖርታቸውም ኮሚሽኑ በከተማ አስተዳደሩ በአዋጅ የተሰጠውን የዜጎችን ህይወትና ንብረት ከአደጋ የመታደግ ተግባር ለመወጣት ያከናወናቸውን ስራዎች ገልጸው በተቋሙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ረገድ ለረዥም ጊዜ ስር የሰደዱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ተቋማዊ ለውጡን የሚያጠናክሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚልከንፋስ ስልክ ላፍቶ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል
መሬት ውስንና ስትራቴጂክ ሀብት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፍትሀዊ የመሬት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የአሰራር ስርአትን ለመዘርጋት በትኩረት እየተሰራ ነው ሲሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወድሙ ሴታ ተናገሩ፡፡ … See more
መሬት ውስን ሃብት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፍትሃዊ የመሬት ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ የአሰራር ስርአት እና የሰው ሃይልን ለማጠናከር የሚያስችል ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው- በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነ… See more
በመዲናችን አዲስ አበባ በቅርቡ ስራ ላይ የዋለው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት በኤጀንሲው እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ወደተሟላ ደረጃና ወደ አዲስ ምእራፍ ማሸጋገሩን በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አዲሱ የዲጂታል ስርአት አገልግሎት መስጠት የጀመረባቸውን ወረዳዎች ተወዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንዳስታወቁት በኤጀንሲው ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ ሲስተም ከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የማዘመንና በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ እያከናወነ ያለውን ዘርፈ ብዙ ስራና የሰጠውን ልዩ ትኩረት በተግባር የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ ስሉጥ፣ፈጣን፣የመንግስት አገልግሎት ለመስጠት የአገልግሎቶች ሁሉ መጀመሪያ በሲቪል ምዝገባና በነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የሚሰጠዉ አገልግሎት ነው ያሉት ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ኤጀንሲው በሪፎርም ዉስጥ ያለ ተቋም እንደመሆኑ ሪፎርሙ ከቴክኖሎጂ አንፃር የነበሩበትን ቀሪ ስራዎችን በማፋጠንና የተሟላ እንዲሆን በማድረግ ረገድ አዲሱ ሲስተም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቅሰዋል።
የኤጀንሲውን የወረዳ ጽ/ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከቱበት ወቅትም ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በሰጡት ገለጻ የወረዳ ፅ/ቤቶች ባለሙያዎች ተገልጋዩን የሚያከብሩበት መንገድ፣ለአገልግሎት የሚያስፈለጉ የቅድመ ሁኔታዎች የሚጠይቁበትና ተገልጋዮችን የሚያስተናግዱበት መንገድ በእጅጉ የተሻሻለና ይህም በባለጉዳዮች አስተያየት ጭምር እየተገለጸ እንዳለ አመልክተው ይህም ተገልጋዩ ከዚህ ቀደም ስለተቋሙ የነበረውን አመለካከት እንዲቀየር ያደረገ ነው ሲሉ አስረድተዋል።
ካለፈው ሳምንት ሰኞ እለት ህዳር 29/ 2018 አ.ም ጀምሮ አገልግሎት መስጠት የጀመረው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት በተለያዩ ተቋማት መካከል ቅንጅትና መናበብ የሚፈጥርና ተገልጋዮች የእጅ ስልካቸውን ጨምሮ ባሉበት ቦታ ሆነዉ የተለያዩ የቴክኖሎጅ አማራጮች በመጠቀም በኤጀንሲው የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
መዲናችን አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ፣ውብና ፅዱ እያደረጉ ያሉ ታታሪ የመንገድ ጽዳት ባለሙያዎቻችን በልደታ ክፍለ ከተማ የምሽት የጽዳት ተግባር ላይ፥… See more
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
በዛሬው እለት ታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 10:00 በዓለም ገና፣ በኢንዱስትሪ መንደር፣ በፉሪ ሬዲዮ ጣቢያ፣ በፉሪ፣ በሃጂ ሪልስቴት አካባቢ፣ በወርዶፋ ሎጅ፣ በዳርፉር ሰፈር፣ በጀሞ 2፣ በድሬ ከአስፋልት በታች፣ በጉዳ፣ በኬላ፣ በጉዮ፣ በታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ በቶልቻ፣ በጎፋ ካምፕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በጀርመን አደባባይ ፣ በጉራጌ ሰፈር፣ በትግሬ ሰፈር እና በካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:30 በአሸዋ ሜዳ የጋራ መኖሪያ ቤት፣ በዲያስፖራ፣ በፊሊደሮ፣ በአንፎ ዓለም ባንክ ጫፍ፣ በኮካ ማዞሪያ፣ በፍተሻ አካባቢ፣ በእንጦጦ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ፣ በሽሮ ሜዳ አካባቢ፣ በስፔስ ሳይንስ፣ በሽንቁሩ ሚካኤል፣ በአካኮ ገብርኤል፣ በ10 ኪሎ በከፊል፣ በዶሮ እርባታ፣ በቀንብሬ፣ በአፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ በጃክሮስ፣ በዓለማየሁ ሕንፃ ፣ በፊጋ ሆቴል፣ በገርጂ አጣና መሸጫ አካባቢ፣ በአቃቂ ኬላ፣ በገላን ኢንዱስትሪ መንደር ሙሉ፣ በወሰርቢ፣ በአርትስቲ፣ በባቡር ሐዲድ፣ በሲዳሞ አዋሽ፣ በገንደ ቆሬ፣ በገላን መኖሪያ ቤቶች፣ በገመዳ ማህበር እና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል ሲል Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
ስለሆነም ተቋሙ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ሲልም አክሏል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
መረጃ
ዛሬ ታህሳሥ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ሕንፃ ቁጥር 2 ውስጥ ጥገና በሚሰራበት ቦታ ከብረት ብየዳ በተፈጠረ ፍንጣቂ አንዲት ትንሽ ክፍል ውስጥ እሳት ተከስቶ የነበረ ሲሆን ምንም አይነት ጉዳት ከማድረሱ በፊት ወድያውኑ እንዲጠፋ ተደርጓል። በክስተቱ ምክንያት በመንገደኞች መውጫ እና መግቢያ ላይ የተከሰተ ምንም አይነት መስተጓጎል አለመፈጠሩን ለማሳወቅ እንወዳለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤
የስታር አሊያንስ አባል!
አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ስርአት ሲስተም ተግባራዊነት የአመራሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግለት ስርዓት ሲስተም ዙሪያ ለወረዳ እና ለክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ስልጠና ሰጠ፡፡
በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የኩነትና ነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥጋቡ ሹመይ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ስርአት ሲስተም ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል እና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ሲስተም ነው ያሉ ሲሆን በየደረጃው የሚገኘው አመራር የለውጡ አካል በመሆኑ የለማውን ሲስተም ከግብ ለማድረስ ለህብረተሰቡ የተቀላጠፈ እና የአገልጋይነት ስሜትን በመላበስ ማገልገል ይኖረብናል ሲሉ አመላክተዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በኤጀንሲው የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙዘሚል ሀሰን በኢትዮዽያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የበለጸገ አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት (Civil Registration and Vital Statistics with e-ID) የኤጀንሲውን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በተያያዘም የሚከሰቱ ኩነቶችን በወቅቱ መመዝገብ በሚቻልበት ሁኔታ ከኢምግሬሽን፣ ከጤና፣ ከፍርድ ቤት እና ከሎሎችም ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን የሚያጠናክር ነው ያሉት አቶ ሙዘሚል ሲስተሙ ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር የተሳሰረ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑ ተናግረዋል፡፡
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ ለረጅም ጊዜ ሲሰራበት የነበረ እና ፍሬ ያፈራንበት ሲስተም በመሆኑ የአገልግሎት ማነቆ የነበሩ ችግሮችን ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ ሲስተም ነው ያሉ ሲሆን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ስርአት ሲስተም አተገባበር ማነቆ እንዳያጋጥመን የአመራሩ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በቅርበት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም በመድረኩ በተነሱ ጥያቄ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው ስልጠናው ተጠናቋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በመዲናዋ በሚገኙ 119 ወረዳዎች "የጉባ ብስራቶች ፤ የመደመር መንግስት ቱሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ፣ በልማት እና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ዙርያ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ።
በልማት እና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ዙሪያ ከዚህ በፊት በማዕከል እና በክፍለ ከተማ ደረጃ ህዝባዊ ውይይቶች መደረጋቸው የሚታወስ ነው።
በዛሬው እለት ደግሞ በመዲናችን በሚገኙ በ119 ወረዳዎች ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በልማት እና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ዙርያ ውይይ ተካሂዷል።
በውይይ መድረኩ ላይ ህዝብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች አዳምጦ ተገቢ ምላሽ መስጠት የብልፅግና ፓርቲ መገለጫ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ ባለፉት የለውጥ አመታት መንግስት ከህዝብ ጋር ተቀራርቦ በመስራቱ የኢትዮጲያን ከፍታ የሚያረጋግጡ ስኬታማ ስራዎች ተከናውነዋል ተብሏል።
በዚህም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሰፋፊ የመሰረተ ልማት ስራዎች በመስራት አዲስ አበባ ከተማን የዓለም የስህበት ማዕከል፣ ለነዋሪዎቿ ውብና ፅዱ ከተማ እንዲሁም የዓለም የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ከተማ ማድረግ ተችሏል ተብሏል።
እነዚህ በለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ ሰፋፊ ስኬቶች ህዝብና መንግስት ተመካክረው በመስራታቸው የመጡ ውጤቶች መሆናቸውንም በውይይቱ ተገልፃል።
የዛሬው የውይይት መድረክ ዓላማም ከህዝብ ጋር በመወያየት የሚነሱ ሀሳብና አስተያየቶችን ለቀጣይ እቅድ እንደመነሻ በመጠቀም ለሀገራችን ከፍታ ከህዝብ ጋር በቅንጅት ለመስራ እንደሆነም ተመላክቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ ከማህበረሰቡ ለሚነሱ ለልማት እና ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥም ተገልፃል።
