http://www.youtube.com/@Orthodox_Secular_FantahunWakie
=====================
እንደ አንድ የክርስቲያን ቤተሰብ አባል ራሳችንን እንፈትሽ ፡-
ቅጣት የጠራነው በሚከተሉት ግልጽና እንኳንስ በሌሎችና በአግዚአብሔር እኛው ራሳችን በየከተማውና በየገጠሩ ሲፈጸም በዓይናችን በምናየው የክርስቲያኖች ርኵሰት ነው፡-
(1)
የክርስቲያን ሴቶች ነፍሰ ገዳይነት፡- በዓመት ወደ
1,000,000 ሕፃናት በክርስቲያን ሴቶች ይገደላሉ (ውርጃ) (
https://pubmed.ncbi.nlm.nih.gov/28825902/)። ይህ ቁጥር በኦሮሚያና በቡኒሻንጉል፣ በወያኔ ምከኒያት በአፋርና በአማራ፣ በትግራይ ሕዝብ በጦርነት ከሚያልቀው ነፍስ ይበልጣል።
(2)
ትዳርን ማፍረስ፡- በኢትዮጵያ ውስጥ በሴቶች ከሚፈጸሙ ትዳርን የማፍረስ አጠቃላይ ብዛት
70 በመቶ በኦርቶዶክሶች ይፈጸማል (
https://core.ac.uk/reader/234691210).
ትዳርን ማርከስ፦ በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአንድ ችሎት ብቻ ከመስከረም 7 ቀን 2012- እስከ ሰኔ 8 ቀን 2014 (እ.አ.አ)
16,035 ጥንዶች ትዳራቸውን አፍርሰዋል (
https://www.facebook.com/265784033571676/posts/divorce-in-the-capital-ethiopia-staggeringly-high-some-are-still-with-an-opinion/512951702188240/) \
(3)
የወጣት አመንዝራነት፡- በ2014 ዓ.ም.
ዕድሜቸው ከ15-24 የተማሪ ወጣቶች አመንዝራነት (የወዲፊቶቹ አገር ተረካቢዎች) ፡-
በ2014 ለጥናት በናሙና (ሎተሪ) ተመልምለው መጠይቅ ከተደረገላቸው ወጣቶች መላከል
41.4% አመንዝራ ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ
37.1% ከሁለትና ከዚያ በላይ ሰው ጋር ያመነዝራሉ፤ (
https://bmcpublichealth.biomedcentral.com/articles/10.1186/1471-2458-14-301)
(4)
የወጣት ሱሰኝነት፡- የዩኒቭረሲቴ ተማሪዎች by
67%, 67%, እና 33% በቅደም ተከተል የጫት፣ የሲጋራ፣ የአልኮል ሱሰኞች ናቸው (
https://www.researchgate.net/publication/353241458_Substance_Abuse_and_Legal_Consideration_in_Ethiopia )
(5)
ሰዶማዊነት፡- ቱሪሰት ከሚርመሰመስባቸው ከላሊበላ፣ ጎንደር፣ ባህር ዳር፣ ሐዋሳ፣ አርባ፣ ምንጭ፣ አዳማ፣ ወዘተ ያለውን የሰዶማዊያን መረጃ ሳንጨምር
በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ በ2021 (እ.አ.አ) ራሳቸውን በግልጽ ሰዶማዊ ነን የሚሉና የገለጡ ሰዎች 60,000 ናቸው (
https://africlaw.com/2021/10/01/time-to-consider-decriminalising-homosexuality-in-ethiopia/)
የኃጢአታችንና የርኵሰታችን ውጤቱ፡-
በመጽሐፍት እንደተነገረ ለዘረኛ፣ አመንዝራ፣ ርኵስ፣ ነፍሰገዳይ፣ ሰዶማዊ ትውልድ የሚገባው ቅጣት ነው (ዘሌ 18፣22፤ ሕዝ 11፣21፤ ኢሳ 1፣20፤ ዘኁል 5፣27)። በፍቅሩ ጽናት ሙሉ በሙሉ በዘንጋኤ አንዳንጠፋና ስሙም ከምድር አንዳይደመሰስ በቅጣቱ በኩል የእግዚአብሑር ይጠራናል። ጥሪው ይህ የሚካሄደው ጥፋት አንዲያበቃ ንስሐ ግቡ ነው። በትንቢተ አሞጽ 4፥11 "ሰዶምንና ገሞራን እግዚአብሔር እንደ ገለበጣቸው፥ እንዲሁ ገለበጥኋችሁ፥ እናንተም ከእሳት ውስጥ እንደ ተነጠቀ ትንታግ ሆናችሁ፤ ነገር ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡" እንዳለው አግዚአብሔር እኛም ከላይ በጥቂቱ ያነሳናቸው እጅግ አጸያፊና በእግዚአብሔር የተጠላ፣ ክርስቲያኖች ነን በሚሉ ሰዎች የሚፈጸም ርኵሰትና ኃጢአት ውጤት ፍሬው፡- 👇🏿
(1) ዘርኝነት፡- የንዑስ ማንነት ፖለቲካ ያሳወረው መንግሥትና የፖለቲካ ንቅንቃዎች ክርስቲያኖችን በቡድን መካፈል (ከክርስቶስ የወይን ግንድነት ላይ የነበራቸውን ቅርንጫፍነት ቆርጦ መጣል (የነፍስ ሞት)) (1ዮሐ 2፣11፤ ዮሐ ቀ5፣5)
(2)
የእርስበርስ ጦርነትና ሥርዓታዊ ፍጅት፡- በዘረኝነት ፖለቲካ የሚፈጸም ጦርነት መተላለቅ፣ እንድ ክርስቲያን ሕዝብ በጅምላ መገደልና መሳደድ፣ በመዋቅራዊ እቅድ ለድኽነት መጋለጥ
(3) መበታተንና ድንዛዜ፡- አለመግባባትና አለመዋስተዋል፣ በከንቱ ንግርት፣ በባዶ ተስፋ ራስን ከጥፋት አለመከላከል፣ ድንዛዜ
(
4) በጎችን በተኩላ የሚያስጠብቅ እረኛ መብዛት፡- ከክርስትና አስተምህሮ ውጭ በሆነ መንፈስ በዘር መከፋፈል፣ እርኛውና በጉ አለመግባባት፣ የግልና የሠፈር ጀግና አበጅቶ ንጉሥ አንደሌለው ንብ መበታተን፣ በድሎትና ምቾት ፍተወት ኃላፊነትን መዘንጋት፣ ወንጌልን ለሆድ አገልግሎት መዋል
💠መፍትሑው፡-
1- ንስሐ መግባት፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋት፣ ይርታን የሕይወታችን መገለጫ ማድረግ፤
2-
ትዳርን መልሶ መቀደስ፤
3- አመንዝራና ሰዶማዊውን ከአጠገባችን ማስወገድ (ንስሐ እንዲገባ የሚገባውን ትምህርትና ጠቃሚ ቅጣት መስጠት)፤
4- ከሱሰኝነት ሁሉ ራስን ነፃ በመዋጣት አካላችንን ለእግዚአብሔር በቅዱስ ቁርባን መቀደስ፤
5- ዘረኝነትና ዘረኞችን መቃወምና ራስን ከማንኛውም እግዚአብሔር ከማይቀደስበት ኢክርስቲያናዊ የቡድን አደረጃጀት መለየትና በክርስትና እና ከመልካሞች ጋር በሰብእና መሥፈርት ብቻ መደራጀት፣ መተባበር፣ ኃይል መሆን፤
6-
ሐሰትን፣ ኢክርስቲያናዊ፣ ኢሰብአዊና ኢ-ሀገራዊ ርእዮቶች፣ ትርክቶችና የአስተዳደር ሥርዓትን ያለ ይሉኝታ መቃወም፣ በምንም መንግድ አለመተባበር፤
7-
ከዘረኞችና አራዊታዊ መንፈስ ካደረባቸው መሪዎችና ስብስቦች ተለይቶ ሰውን በሰውነቱ ብቻ ከሚቀበሉ ጤናማዎች ጋር በመደራጀት የጥፋትን ሠራዊት ፊት ለፊት መግጠም
—- ድል ከእግዚአብሔር ወገኖች ጋር ናውና ክፋትና ክፉዎች ይሸነፋሉ!!!
—-ኦሪት ዘሌዋውያን 26፣6-7 በምድራችሁም ላይ ሰላምን እሰጣለሁ፥ ማንም ሳያስፈራችሁ ትተኛላችሁ፤ ክፉዎችንም አራዊት ከምድራችሁ አጠፋለሁ፥ ሰይፍም በምድራችሁ ላይ አያልፍም። ጠላቶቻችሁንም ታሳድዳላችሁ፥ በፊታችሁም በሰይፍ ይወድቃሉ።
ከከንቱ ልፋት ራስን መጠበቅ፡-
ዘረኝነትን ሳይተዉ፤ ማመንዝረን ሳያቆሙ፤ ውርጃና ሰዶምን እየፈጸሙ፤ ትዳርን እያረከሱ፤ በሱስ እየናወዙ፤ ጾምና ጸሎት፣ ምጽዋትንና ይቅርታን ሳይታጠቁ የአጋንንትን ሠራዊት ማሸነፍ አይቻልም!!!
https://t.me/Fantahun_Wakie