cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Let's Save Orthodoxy and humanity( ሰብእናንና ኦርቶዶክሳዊነትን እንታደግ)!!⁉️

ሰብእናንና የመንፈስ ልዕልናን ካዳበሩ ቤተሰቦች ጋር በመተባበር በሰብእናና በኦርቶዶክሳዊነት ላይ የሚፈጸምን(የተፈጸመን) ሥርዓታዊ፣መዋቅራዊ፣ሕጋዊ፣መናፍስታዊ፣ስነልቦናዊ ..ጥቃቶችንና አጥቂዎችን እንዲሁም ከጥቃት የመዳኛ መንገዶችን(መፍትሔ) የሚመለከትበት ቻናል ነው::

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
856
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
+3730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

በባሌ ሀገረ ስብከት በአጋርፋ ወረዳ ኦዳ ነገሌ ቀበሌ ነዋሪዎቾ የሆኑ ስድስት የቤተክርስቲያናችን አባላት አንድ ካህን እና እና አምስት ምእመናን ግንቦት 13/2016ዓ,ም ከምሽቱ 4:00ሰዓት ባልታወቁ ግለሰቦች ታግተው መወሰዳቸውን ከተሰማበት ሰዓት ጀምሮ የባሌ ዞን የፀጥታ አካላት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ያሉ መሆኑን ያረጋገጥን ቢሆንም እስካሁኗ ሰዓት ያሉበት ቦታ ባለመታወቁ ሁላችንም ከፍተኛ ሀዘን ላይ እንገኛለን። ስለሆነም የሚመለከተው አካል ሁሉ እንዲያውቀው እና ወገኖቻችን በሰላም ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ አምላከ ቅዱሳን ፈቃዱ ይሆን ዘንድ በጸሎታችሁ አግዙን። ከሀገረስብከቱ ሕዝብ ግንኙነት ገጽ
إظهار الكل...
"ቋንቋ፣ ብሄርና ጎሳ ለይተህ እየወደድክ ክርስትያን ነኝ አትበል። ክርስቶስ እኔን ምሰል ሲልህ ዓለሙን ሁሉ ወዶና አፍቅሮ ነው።አንተም እገሌ ኃጥእ ነው፣እገሌ ፃድቅ ነው፣እገሌ ደካማ፣ብርቱ ሳትል በእርሱ ዓይን እንድታይና በእርሱ ሚዛን እንድትመዝን ይፈልጋል።በእርሱ ዘንድ ሰዎች የሚለኩት በሚዛን ነውና! ምናልባትም አንተ ኃጥአን ናቸው ብለህ የምትፀየፋቸው ሰዎች 49 ወንጀል ፡ 51 በጎ የተገኘባቸው እንደሆነ እንኳ ፃድቃን ሊላቸው ስለሚችል እንዳይፈረድብህ በማንም ላይ አትፍረድ።"(ማቴ 7:1) #ወዳጄ_ሆይ_ተመከር!"ጠላቶቼን ወዳጆቼ ባደርጋቸው፤ በዘዴ አጠፋኋቸው ማለት አይደለምን? ይልሀል Abraham lincoln። "ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ"((ማቴ 5:43-45)) "በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ።ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።" ((1ኛ ቆሮ 13:1-3)) ስንፋቀር እና ስንቻቻል ያምርብናል እላለሁ። ከሀብታሙ ኪዳነማርያም ገጽ የተገኘ 2012
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
✏የፍርድ ቤት ውሎ 👉በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዛሬ ጠዋት በዋለው ችሎት መርጌታ ብርሀኑ ተ/ያሬድን ጨምሮ በአንድ መዝገብ 20  ሰዎች የቀረቡ ሲሆን የክሰ ቻርጅ ተሰጥቷቸው ለዋስትና ብይን ከሰአት ተቀጥሯል 👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://t.me/ethiobeteseb
إظهار الكل...
የእኛዎቹ ግን 70ሺ ደሞዛቸው፥የሆነች ቦታ በተጓዙ ቁጥር የሚያገኙት አበላቸው፥ በዓመት ለኪስ ተብሎ የሚሰጣቸው 300ሺ ብር ፥ቪ8 መኪናቸው አይጉደልባቸው እንጂ ቤተ ክርስቲያን ተደፈረች አልተደፈረች ደንታቸው አይደለም። ሰማይ ሆይ ሰማ ምድርም አድምጪ እንዲጠብቁን የተሾሙ ጳጳሳት ለተኩላው አሳልፈው ሰጥተውናልና።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
በዚያም ዘመን ንጉሡ ሄሮድስ መከራ ያጸናባቸው ዘንድ ከቤተ ክርስቲያኑ ባንዳንዶቹ ላይ እጁንጫነባቸው። የዮሐንስንም ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው ።አይሁድንም ደስ እንዳሠኛቸው አይቶ ጨምሮ ጴጥሮስን ደግሞ ያዘው ። የቂጣ በዓልም ወራት ነበረ ።ጴጥሮስም በወህኒ ይጠበቅ ነበር ፤ ነገር ግን ፥ በቤተ ክርስቲያን ስለ እርሱ ወደ እግዚአብሔር ጸሎት አጥብቆ ይደረግ ነበር ።"የሐዋርያት ሥራ 12:5
إظهار الكل...
02:50
Video unavailableShow in Telegram
"#በህግ አምላክ"አትበል‼️ የህግ፣ አምላኩን፣ የስርዐት ጥጉን የማያውቁ መረኖች ወንበር ይዘው እስከቀጠሉ የመከራችን ማብቂያ ቀን አትብትም። የትኛውንም ተቋም፣ ብትመራ እና ሃብት ብታካብት፣ የትኛውንም ኮሌጅ በጥሰህ ክብረ ሙያ ላይ ብትቆናጠጥ… እኝህ የዘመድ ጉድ አውሬዎችን ባላዬ ለማለፍ እስከዳዳህ… በአደባባይ እንደ ውሻ ቀጥቅጠው ሳያዋርዱህ አይቀሩም። ይህ፣ የተረኛው ስርዓት ባለጊዜዎች ፀሀይ የሞቀው በሀረር ከተማ የተፈፀመ ግፍና ገመና ነው። ጊዜ፣ አይ ጊዜ! https://t.me/Moamediamoresh
إظهار الكل...
4.42 MB
አስቸኳይ የሥራ ማስታወቂያ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤ ምሩቃንን ተጠቃሚ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ግንኙነት እያደረገ ይገኛል። በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ  የግቢ ጉባኤ ምሩቃን  በማኅበሩ ሕንጻ 2ኛ ወለል ላይ በሚገኘው የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ቢሮ በአካል በመቅረብ እና የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ እንድታመለክቱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የትምህርት መስክ ፡- በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና ተዘማጅ ዘርፍ ከታወቀ የትምህርት ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/የተመረቀች የሥራ ልምድ ፡- ዜሮ ዓመት የሥራው አድራሻ፡- አዲስ አበባ ብዛት ፡- 15 የማመልከቻ ቀን፡- ከግንቦት 27 ቀን እስከ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በሥራ ሰዓት ብቻ
إظهار الكل...
አስቸኳይ የሥራ ማስታወቂያ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤ ምሩቃንን ተጠቃሚ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ግንኙነት እያደረገ ይገኛል። በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ  የግቢ ጉባኤ ምሩቃን  በማኅበሩ ሕንጻ 2ኛ ወለል ላይ በሚገኘው የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ቢሮ በአካል በመቅረብ እና የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ እንድታመለክቱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የትምህርት መስክ ፡- በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና ተዘማጅ ዘርፍ ከታወቀ የትምህርት ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/የተመረቀች የሥራ ልምድ ፡- ዜሮ ዓመት የሥራው አድራሻ፡- አዲስ አበባ ብዛት ፡- 15 የማመልከቻ ቀን፡- ከግንቦት 27 ቀን እስከ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በሥራ ሰዓት ብቻ
إظهار الكل...