Kea Med College
الذهاب إلى القناة على Telegram
Official Kea Med College channel to communicate with students Kea Med College Tel: +251-116629507 / 30 email: kea.edu2013@gmail.com e.learningkea@gmail.com
إظهار المزيد1 555
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-530 أيام
أرشيف المشاركات
1 555
Repost from Ministry of Education Ethiopia
ማስታዎቂያ
ለቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ምዝገባ https://exam.ethernet.edu.et የሚለውን ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የሚቻል መሆኑ እንገልጻለን።
1 555
ለሁሉም አባል ተቋማት
ሰኔ/2017 ከሚሰጠው የቅድመ-ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ጀምሮ ለተፈታኝ ተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደ ቅድመ-ሁኔታ የተቀመጠ መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ሸኚ ደብዳቤ አስታውቋል።
ስለሆነም አባል ተቋማት ተፈታኝ ተማሪዎቻቸው ፋይዳ መታወቂያ እንዲኖራቸው የማድረግ ሂደት ከወዲሁ እንዲያስጀምሩና ተፈፃሚነቱንም እንዲከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።
1 555
ቀን፡ 29/12/2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን እንደ ፈተና ማዕከል ለመረጣችሁ የ ‘NGAT’ ተፈታኞች በሙሉ
ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜ 01/ 2016 ዓ.ም ድረስ በመላው ሀገሪቱ ይሰጣል ተብሎ በእቅድ የተያዘው የ “NGAT’ ፈተና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን በፈተና ጣቢያነት ለመረጣችሁ ተፈታኞች ብቻ የፈተናው ጊዜ የተለወጠ መሆኑን እያሳወቅን ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ወደፊት የምናሳውቅ ሆኖ በሌሎች የፈተና ጣቢያዎች (ዩኒቨርሲቲዎች) ፈተናውን ለመውሰድ ያመለከታችሁ በሙሉ ፈተናው በተያዘው ዕቅድ መሰረት ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም ከ8:00 (ከስምንት ሰዓት) ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር
1 555
Update
NGAT ፈተናን በተመለከተ የተሰጠ ማብራሪያ
► የመፈተኛ ተቋም እና የመፈተኛ Schedule በ portal በኩል ታገኛላችሁ።
► ማንኛውም ተፈታኝ በ Portal በኩል የተላከለትን Pass Card ሳይዝ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የማይችል መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
► Pass Card የሚገኘው በእያንዳንዳችሁ Poral Dashboard ላይ ብቻ ነው።
► የፖርታል አድራሻ ngat.ethernet.edu.et ነው።
Pass Card ላይ ያሉ መረጃዎች፦
1. የተፈታኝ ሙሉ መረጃ
2. የሚፈተኑበት ተቋም እና ካምፓስ አድራሻ
3. የሚፈተኑበት የትምህርት ዘርፍ
4. የሚፈተኑበት Session እና የፈተና ሰዓት
5. የተፈታኝ ፎቶ።
ሁሉም ተፈታኞች Pass Card Print አድርገው ወደፈተና ማዕከል መሔድ ይጠበቅባቸዋል።
ፈተናውን ለመስጠት የተቀደው ነሐሴ 30 እና ጳጉሜን 1/2026 ዓ.ም ሲሆን፤ ለውጦች ካሉ በዚሁ ላይ እንደሚገለፁ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል። #MoE
@tikvahuniversity
1 555
Repost from Ministry of Education Ethiopia
ማስታወቂያ
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 24 - ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
1 555
+1
#ጥቆማ
"በጎ ስጦታ" የበጎ አድራጎት ድርጅት የተባለ አገር በቀል ድርጅት ከውጪ ካሉ ለጋሽ አካላት ጋር በመተባበር በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ያላቸው ግን በአቅም ማነስ ምክንያት ትምህርታቸውን ለመከታተለ የከበዳቸውን ተማሪዎች ድጋፍ ለማረግ ማቀዱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ተቋሙ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ በኪያሜድ ኮሌጅ በነርሲንግ ዲፓርትመንት በዲፕሎማ መርሀ ግብር 20 ሴት ተማሪዎችን ተቀብሎ ከትምህርት ጋር የተያያዙ ሙሉ ወጪያቸውን በመሸፈን ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እድሉን ማመቻቸቱን ገልጿል።
የዚህ እድል ተሳታፊ የሆኑ ልጆች ምን ማሟላት አለባቸው?
- ከ 2014 እስከ 2015 የ 12 ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈትነው ለዲፕሎማ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ፤
- በዲፕሎማ በቀን መርሀ ግብር ነርሲንግ መማር ፍላጎት ያላቸው።
- አቅም እንደ ሌላቸው ከቀበሌ ማስመስከር የሚችሉ፤
- ትምህርቱን ከጀመሩ በኋላ ውጤታቸውን አስጠብቀው መጓዝ የሚችሉ፤
- ተቋሙ ከትምህርት ውጪ ያሉ ወጪዎችን ስለማይሸፍን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
ይህንን የምታሟሉ / በአከባቢያችሁ በትምህርታቸው ጎበዝ የሆኑ የምታቋቸው ካሉ በዚህ እድል እንዲጠቀሙ ይህንን መልዕክት አድርሷቸው።
ለበለጠ መረጃ በቴሌግራም @elzabet18/@Dr_Daniel_D ወይም በስልክ ቁጥር +251912671410 /+251938327771/ +251953146834 ላይ ያግኙ።
BegoSitota.com
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
1 555
Repost from Ministry of Education Ethiopia
ማ ስ ታ ወ ቂ ያ
የመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ
በ2016 ዓ.ም ሰኔ ወር ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ አመልካቾች በሙሉ፤
ምዝገባ የሚከናወነው ከግንቦት 14 – 21/2016 መሆኑን አውቃችሁ የምዝገባ ክፍያ አምስት መቶ (500.00) ብር በመክፈል በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፤
1. ለመጀመሪያ ጊዜ የመጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚካሄደው እና የአገልግሎት ክፍያ በተቋማችሁ በኩል መሆኑን እየገለጽን አስፈላጊ የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማችሁ የሚደርሳችሁ መሆኑን እናሳውቃል።
2. የድጋሚ ተፈታኞች የአገልግሎት ክፍያ አምስት መቶ ብር (500.00 ብር) በቴሌ ብር ብቻ የሚከናወን ይሆናል።
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር
1 555
Repost from N/a
Anyone not appearing on the specified date will be missed from the data to be sent to ETA (HERQA)
1 555
Repost from N/a
Urgent Notice
Those of you who have successfully passed the second round exit exam are expected to report to your campus dean with a printout copy of your screenshot result till Tuesday March 26, 2024
1 555
Repost from Ministry of Education Ethiopia
#ማ ስ ታ ወ ቂ ያ
ለድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ
የካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የ ድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍቃል (Password) ከታችበተዘረዘሩት አማራጮች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
1. በምዝገባ ወቅት በሞላችሁት email በኩል
2. https://exam.ethernet.edu.et ላይ በመግባት የከፈላችሁበትን Transaction Number በማስገባት እንዲሁም
3. ከተመደባብችሁብት የመፈተኛ ተቋም ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ
• ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች የይለፍቃል (Password) የምታገኙት ከምትማሩበት ወይም ከተመደባብችሁበት የመፈተኛ ተቋም ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን።
• ሁሉም ተፈታኞች የሞዴል ፈተናን እስከ የካቲት 5/2016 ዓ.ም መውሰድ ይኖርባቸዋል።
ትምህርት ሚኒሰቴር !
የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
1 555
ማስታወቂያ
2ኛ ዙር Exit Exam ከየካቲት 6 - 9 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታውቃል። ስለዚህም ከዚህ በፊት ፈተናውን ያልውሰዳችሁ ተማሪዎች (አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ የምትወስዱ) እስከ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የምዝገባ ብር 500 በመያዝ ትምህርት ቤት (22 ካምፓስ) በመምጣት የመፈተኛ ኮዳችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን።
