TheDeepThingsOfGod
الذهاب إلى القناة على Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
إظهار المزيد1 810
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
1 810
When Your eye is single your whole body will be full of light.
እኔ ለእናንተ እናንተ ለእኔ!
#Prayer_For_me!🥰
#I_Victor_Love_you_all!🥰
1 810
እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ቃል መንፈስና ሕይወት ነው፥ የእግዚአብሔር ቃል እውነት እንዲሆን እና እንድናምነው በተለያዩ ጥቅሶች ደርጅቶ ስልታዊ ትምህርት መሆን አይጠበቅበትም፥ መንፈስ እንደሚለው እንደዛው ሊታመን እና ሊተገበር ይገባዋል።
-Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“በኋለኛው ዝናብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዝናቡን ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል፤ እርሱም የበልግ ዝናብን ለእያንዳንዱም በሜዳ ውስጥ ሣርን ይሰጣል።”
— ዘካርያስ 10፥1
1 810
የዌልስ ሪቫይቫል
የዌልስ ሪቫይቫል ከ1902-04 በታላቅ ሁኔታ እግዚአብሔር ክብሩን የገለጠበት ሪቫይቫል ነው።
በዚህ ሪቫይቫል እግዚአብሔር የተጠቀመበት ኢቫን ሮበርት የሪቫይቫሉ መሪ ነበር። በዚህ ሪቫይቫል ወቅት በምድሪቱ ላይ የሆኑ ነገሮች ላካፍላችሁ።
1፦ ሌብነትና ወንጀል ስላልነበረ ፖሊሶች ስራ አልነበራቸውም።
2፦ በዚያን ወቅት የመፅሐፍ ቅዱስ ማህበሩ መፅሐፍ ቅዱስ ለማከፋፈል አቅም እስኪያጣ መፅሐፍ ቅዱስን ሰዎች ማንበብ የጀመሩበት ጊዜ ነበር።
3፦ በዚያን ዘመን የህዝቡ ልብ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰበትና ወደ እግዚአብሔር ቤት መምጣት የጀመረበት ነበር።
4፦ አጠቃላይ በምድሪቱ የድህነት አሰራርን እየሰበሩ በስራም እየተባረኩ የመጡበት ነበር።
5፦ መጠጥ ቤቶች መዘጋት፤ የሰው ልብ እግዚአብሔር መፈለግና መፍራት፣ ቅድስናን መውዱድ የነፍሳት መዳንና መፈወስ የነበረበት ሪቫይቫል ነው።
ሪቫይቫል አገር አቀፋዊ መልክና የትውልድና የሐገርን ለውጥ የያዘ የእግዚአብሔር ቤትና መንገድ ያስከበረ ሲሆን ፍሬው ብዙ ይሆናል።
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መፍትሄው!
አሁን ያለበት ችግር ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሰው ሰያውቅ ችግሩን እየመገበው እና ችግሩ በሕይወት እንድቆይ እየረዳው ነዉ፥ ትኩረታችሁን የምትሰጡት የትኛውም ነገር በሕይወታችሁ ያድጋል ያሸንፋል፤ ስለዚህ ችግር ላይ ሰይሆን መፍትሔው ላይ ትኩረት አድርጉ፥ የእግዚአብሔር ቃል ላይ ትኩረት አድርጉ የእግዚአብሔርን ቃል አሰላስሉ፤ የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችሁ እያደገ ያሸንፋል።
ሰይጣንን ሰይሆን እግዚአብሔርን አስቡ!
ኃጢአትን ሰይሆን የክርስቶስ ጽድቅ አስቡ!
በሽታን ሰይሆን ጤንነትን እና ፈውስን አስቡ!
ያላችሁበትን ዝቅታ ሰይሆን የምትወጡበትን ከፍታ አስቡ!
ድህነትን ሰይሆን የአብርሃምን በረከት አስቡ!
ሞትን ሰይሆን ሕይወትን አስቡ!
በሕይወታችሁ እንዲያድግ እና እንዲያሸንፍ የምትፈልጉትን ነገር ያለማቋረጥ አስቡ፣ አሰላስሉ፥ ምክንያቱም የሕይወታችሁ አይነት የሚወሰነው ልባችሁ በተሞላው ሃሳብ ነዉ።
“አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና።”
— ምሳሌ 4፥23
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የእግዚአብሔር ቃል የሌለው ሰው ዝናብ እንደሌለው ደመና ነዉ።
ዝናብ የሌለው ደመና በሰማይ ላይ አይታችሁ እንደምታውቁ እርግጠኛ ነኝ፥ በንፋስ እየተገፋ ይበራል ንፋሱ ስበረታ ተበጣጥሶ ይበተናል፥ ብዙም ሰይቆይ ከሰማይ ገጽ ላይ ይጠፋል፤ ይዘንባል ብለው በተስፋ የሚጠብቁትን ሰዎች ያሳፍራቸዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የሌለውም ሰው እንደዚህ ነዉ በዚህ ዓለም ላይ ያለውን ንፋስ፣ ዝናብ እና ጎርፍ አሸንፎ መቀጠል አይችልም፥ ይጀምር ይሆናል እንጂ አይጨርስም። እኛ ግን የጀመርነውን ሁሉ እንጨርሳለን የእግዚአብሔር ቃል ዋጋ ይገባናል፤ የእግዚአብሔር ልጆች ወደ እግዚአብሔር ቃል ግቡ ተመልከቱም አግኙ ሕይወትን አትርፉ።
የእግዚአብሔርን ቃል የቅዱሳት መጽሐፍትን ውበት እና ትልቅነት ማየት እንዳንችል በዓይናችን ያለ መጋረጃ በጌታ ኢየሱስ ስም ይነሳ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Get in to the word!
አንድ ሰው በፍጥረታዊውም በመንፈሳዊውም ዓለም የሚኖረው ክብደት የሚወሰነው በተሞላው በእግዚአብሔር ቃል ነው፥ በእግዚአብሔር ቃል የተሞላ ሰው ቀላል መሆን አይችልም።
The Word in you is what determines your weight in the realm of the natural and the spiritual, when you're filled with the word you can't be simple.
-Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እጅግ በጣም ብዙ ልጆች የጸሎት ርዕሰ ልካችሁልኛል የሁላችሁንም አንድ በአንድ እያነበብኩ እና እየጸለይኩ ነዉ፣ የአብዛኞቻችሁ ጸሎት ርዕሰ መመሳሰሉ አስደንቆኛል፥ የብዙዎቻችሁን ጥያቄ የሚመልስ የትምህርት እና የጸሎት ምሽት በቅርቡ አዘጋጃለሁ🥰 ፥ personal የሆኑ ነገሮች የነገራችሁኝ ልጆች ሙሉበሙሉ እስክትፈቱ ስለእናንተ መጸለይ አልተውም!🔥
1 810
የምወዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ዛሬ ስለ እናንተ መጸለይ በእናንተ ላይ ትንቢት መናገር አለብኝ፥ በጸሎት ሃይል የምታምኑ ከሆነ ብቻ የጸሎት ርዕሳችሁን @GFI777 ላኩልኝ!
1 810
የእድገት ሚስጥር
በራሱ የተሞላ ሰው በመንፈስ ቅዱስ መሞላት አይችልም፥ መንፈስ ቅዱስ የሚሞላው ራሳቸውን ባዶ የሚያደርጉ ሰዎችን ነዉ።
ጌታችን በማቴዎስ 5፥3 “በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።” ያለን ያደግን እንኳ ቢመስለን ሁልጊዜ በመንፈሳችን የእግዚአብሔርን ነገር የምንመኝ እንድንሆን ነዉ፥ ድሃ ምንድነው የሚያደርገው? የተሻለ ነገር ሲያይ የእኔ በሆነ" ብሎ ይመኛል፥ ቁሳዊ ድህነት አይመከርም! ለእኔ ቁሳዊ ድህነት መንፈሳዊነትም ትህትናም አይደለም፥ በመንፈስ ድሃ መሆን ግን ትልቅ መንፈሳዊነት ነዉ🤗።
ሁልጊዜ በመንፈስ ድሃ መሆን የማያቋርጥ የእድገት ሚስጥር እንደሆነ አምናለሁ። እኔ ጋር የሌለ የእግዚአብሔርን ፀጋ አንድ ወንድሜ ወይም እህቴ ጋር ስመለከት፥ እግዚአብሔርን ለማመስገን እና ለማድነቅ ወደ ኃላ አልልም፥ ምክንያቱም በዚህ ሰው ሕይወት ያለውን ፀጋ የምካፈለው እና የማድገው በዚህ መንገድ እንደሆነ አውቃለሁ፤ የእግዚአብሔር ልጆች አንዱ የምታድጉበት ሚስጥር ይህ ነዉ፥ የእግዚአብሔርን ፀጋ ስታዩ ማድነቅ፣ መቅናት ተለማመዱ። ምንም አይነት መንፈሳዊ ልምምድ ሰይኖረው ረክቶ እየኖረ በላ ትውልድ መካከል ነው ያላችሁት፥ እናንተ ግን በትልልቅ መንፈሳዊ ልምምዶች ሁሉ እንኳ አትርኩ በደረሳችሁበት አትቁሙ እግዚአብሔር ሌላ በዓይን ያልታየ፣ በጆሮ ያልተሰማ እና በልብ ያልታሰበ አለው።
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ጸሎት እና መንፈስ ቅዱስን መቀበል
በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት በተለያዩ ክፍሎች ተጽፎ በግልጽ እንደምናየው ሳይጸልይ ወይም ሳይፀለይለት መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ ሰው የለም፤ ይሄ ማለት መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል ጸሎት የግዴታ አስፈላጊ ነው ማለት ነዉ።
ሉቃስ 3 :21-22፤ ኢየሱስ ሲጸልይ ሰማይ ተከፈተ፥ መንፈስ ቅዱስም በአካል መልክ እንደ ርግብ በእርሱ ላይ ወረደ፤
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ሐዋርያት 1:14 ሐዋሪያት መንፈስ ቅዱስን ከመቀበላቸው በፊት ከወንድሞች እና ከሴቶች ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር፤
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ሐዋርያት 4:31 ሐዋሪያት እና ሌሎች አማኞች በደረሰባቸው ስደት ምክንያት ተሰብስበው ከጸለዩ በኋላ ተሰብስበው የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፥ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው ፥ የእግዚአብሔርንም ቃል በግልጥ ተናገሩ።
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ጳውሎስ በደማስቆ መንገድ ላይ ከገጠመው አስደናቂ መለኮታዊ ግንኙነት በኋላ ወደ ከተማ ገብቶ ለሦስት ቀን ይጸልይ ነበር፥ ጌታም ሐናንያ የሚሉትን ደቀመዝሙር በመላክ አይኑ እንዲከፈት እና መንፈስ ቅዱስን እንድቀበል አድርጓል፥ በዚህ ጊዜ ጳውሎስ(ሳውል) በደማስቆ ከተማ ቅን በሚባል መንገድ ላይ በለው በይሁዳ ቤት እየጸለየ ነበር።
ሐዋርያት 9:11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ሐዋርያት 19:1-6 ጳውሎስ ወንጌልን እየሰበከ በኤፌሶን ስዘዋወር አስራ ሁለት ሰዎችን አግኝቶ በመኑ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበለው እንደሆነ ጠየቃቸው እነርሱም መንፈስ ቅዱስ እንዳለ እንኳ እንደማያውቁ ነገሩት፥ በዚህ ጊዜ ሐዋሪያው እጁን ጭኑ ጸለየላቸው መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፥ በልሳኖችም ተናገሩ፥ ትንቢትም ተናገሩ።
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ጸሎት እና መንፈስ ቅዱስን መቀበል ምክንያት እና ውጤት ሆነው ታይተዋል፥ ጌታችን በሉቃስ 11፥13“... የሰማዩ አባታችሁ ታዲያ ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን እንዴት አብልጦ አይሰጥ!" በማለት ሰዎች መንፈስ ቅዱስን መቀበል የሚችሉት በመለመን(በመጸለይ) እንደሆነ ገልጧል።
ጸሎት መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል መንፈሳችሁን፥ ነፍሳችሁን እና ስጋችሁን ያዘጋጃል።
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
prayer(ጸሎት)
Earnest, heartfelt and continued prayer is one of the ancient mystery of power in the Spirit.
-Victor
በእምነት በቀጣይነት የሚደረግ ጸሎት አንዱ ጥንታዊው የመንፈሳዊ ሃይል ሚስጥር ነዉ።
ያዕቆብ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
¹⁸ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በመንፈስ ቅዱስ ሃይል
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ለኢየሱስ ክርስቶስ እና ለመንግስቱ ትልልቅ ነገሮችን ለማድረግ ወስኑ።
ትንንሽ ነገሮችን አይደለም፤ እጅግ ትልቅ የሚባል ነገር ለመስራት ወስኑ፤ እግዚአብሔር የሚደጋገም ነገር የለውም ሁልጊዜ አድስ ነዉ በአንተ በአንቺ በእኔ አይን ያላየውን፣ ጆሮ ያልሰማውን እና በሰዎች ልብ ከቶ ያልታሰበውን ድንቅ ነገር መስራት ይችላል።
ወጣቶች እራሳችሁን ምንም መስራት እንደማይችል አታስቡ፤ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ለእግዚአብሔር መንግስት ወጋቸው ከፍ ያሉ ስራዎች መስራት ትችላላችሁ።
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መንፈስ ቅዱስ እና እኔ ሕብረት አለን ስል ለዘላለም አብሮ ነዋሪ ነን፣ አብሮ ሰራተኛ ነን፣ ተባባሪ እና ተካፋይ ነን ማለቴ ነዉ።
1 810
የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን የጻፈውን መልእክቱን የጨረሰው --“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።” በማለት ነዉ።
— 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥14
እኔ ዛሬ የምናገረው ስለመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ነው።
መንፈስ ቅዱስን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሁሉም ክርስቲያን ያዉቀዋል። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሰልናገር ከእርሱ ጋር ስለምናደርገው ሕብረት ለመናገር መጀመሬ ለዚሁ ነዉ።
በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ከተወሰኑ የተመረጡ ሰዎች ጋር ህብረት ያደርግ ነበር: እነዚህ ሰዎች ሙሉበሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ: እግዚአብሔር ለንግስና፤ ለክህነት ወይም ደግሞ ለነቢይነት የመረጣቸው ነበሩ። ህብረቱም ቢሆን ቀጣይና ዘላለማዊ አልነበረም/ the fellowship of the Spirit was on and off in the old testament/ ይህም የሆነው ከሰው የልብ ክፋት የተነሳ ነበር። “እግዚአብሔርም፦ መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም፥ እርሱ ሥጋ ነውና፤ ዘመኖቹም መቶ ሀያ ዓመት ይሆናሉ አለ።”
— ዘፍጥረት 6፥3
“እግዚአብሔርም የሰው ክፉት በምድር ላይ እንደ በዛ፥ የልቡ አሳብ ምኞትም ሁልጊዜ ፈጽሞ ክፉ እንደ ሆነ አየ።”
— ዘፍጥረት 6፥5
በዚህ ምክንያት የእግዚአብሔር መንፈስ ለተለየ ዓለማ ከልሆነ ከሰዎች ጋር ህብረት አያደርግም ነበር: ነገር ግን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሕብረት ነበር ይህንን ከንጉሡ ዳዊት ልመና መረዳት እንችላለን!
“ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።”
— መዝሙር 51፥11
ንጉሡ ዳዊት ይህንን ልመና ያደረገበት ምክንያት አለው። የእግዚአብሔር መንፈስ በእርሱ ላይ ስሆን እና ትቶት ስሄድ ያለውን ልዩነት በግልጽ የተረዳው በመሆኑ ነዉ። ስለዚህ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ጋር እንድኖር በመፈለግ ይህንን ጸሎት አድርጓል!
ሕብረት ማለት ምን ማለት ነዉ? በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስና ሰዎች ቀጣይና ዘላለማዊ አብሮ ነዋሪነት ስላልነበራቸው "ሕብረት" የሚለውን ቃል አናገኝም። መዝሙረ ዳዊት "በወንድሞች" መካከል መኖር ስላለበት ሕብረትና ስለበረከቱ ይናገራል: ከዚህ ያለፈ ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ግን አናይም።
በአድስ ኪዳን ግን ሕብረት የሚለው ቃል በሰፊው ጥቅም ላይ ውሏል: መጀመሪያ ከጠቀስኩት የንባብ ክፍል "ሕብረት" የሚለው የግሪክ ቃል "κοινωνία" /koinonia/ የሚል ቃል ነዉ: ይህ ቃል በእንግሊዝኛው
fellowship, association, community, communion, joint participation, intercourse; የሚሉ ትርጉሞች አሉት። ሁሉም ቃላት፤ አብሮ ነዋሪነት፣ አብሮ ሰራተኝነትን፣ ተባባሪነትን፣ ተካፋይነትን የሚገልጹ ቃላት ናቸው።
መንፈስ ቅዱስ ከእኔ ጋር ሕብረት አለው ወይም እኔ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት አለኝ ስንል: በቀጣይነት አብሮ ነዋሪ ነን፤ አብሮ ሰራተኛና ተባባሪ ነን፤ አንዳችንም የአንዳችን ተካፋይ ነን ማለት ነዉ።
1ኛ-ለዘላለም አብሮ ነዋሪ ነን!
“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16
ለዘላለም አብሮኝ ነዋሪ የሚለው ቃል ሁሉንም የሚገልጽ እንደሆነ አስባለሁ። ለምሳሌ ለዘላለም ባይሆንም ለዓመታት አብራችሁ የምትኖሯቸውን ወላጆቻችሁን፤ ወንድም እህቶቻችሁን አስቧቸው!? አብሮ ነዋሪ በመሆናችሁ ብቻ: አብሮ ሰረተኛ ተባባሪ፤ ናችሁ....ሌላው አንዳችሁ የአንዳችሁን አሰብ፣ አነጋገር ስሜት፣ አደራረግ... ወዘተ ትጋራላችሁ...ምክንያቱም አብሮ ነዋሪ በመሆናችሁ ነዉ።
ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላችሁ ሕብረትም ልክ እንደዚሁ ነዉ! መንፈስ ቅዱስ የክርስቶስን አሳብ ያከፍላችኋል!... አስተሳሰባችሁን አነጋገራችሁን፣ ድርጊታችሁን ሁሉ ይቀርጸዋል!.... እናንተም የምታስቡትን፣ የሚሰማችሁን ሕመማችሁን ደስታችሁን ሐዘናችሁን ሁሉ ታካፍሉታላችሁ...እርሱም ከእናንተ ወስዶ ይሸከመዋል! እርሱም ደስታውን ሐዘኑን ሁሉ ይነግራችኋል.... ሕብረት ማለት ይህ ነዉ።
JOIN
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ወዳጆቼ እባካችሁ ይህንን ጥያቄ መልሱልኝ፧
ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለማቋረጥ መሰበክ ያለበት መልእክት ምን መሆን አለበት ትላላችሁ?
1 810
እንዴት ያለ ድንቅ ፍቅር ነዉ
እንዴት ያለ ግሩም ፍቅር ነዉ
ሁልጊዜ መዝሙሬ ይህ ነው
እንዴት ያለ ድንቅ ፍቅር ነዉ
አዳኛ ለእኔ ያለው!
የማይለዋወጥ ፍቅር አውቃለሁ
ሌላ አይደለም ፍቅር እንደዚህ ነዉ
እርሱ እኛን እንደወደደን ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ወርቅ ለመሆን መፈለግ የሁሉም ነው፤ ነገር ግን ወርቅ የመሆንን ሂደት ተቀብሎ፣ ተስፋ የሚያስቆርጥ ዝለትን በብርታት ተክቶ፣ የዓላማ ጽናትን በእሳት አንጥሮ ወርቅ መሆን ጥቂቶች ብቻ የሚያልፉት ፈተና ነዉ።
-Victor
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ንስር እና እባብ
ሁለቱም የራሳቸው ብቃት አላቸው ነገር ግን በተለያየ ክልል ላይ ነዉ፤ የእባብ መንገዱ በድንጋይ ውስጥ ነዉ፤ የንስር ደግሞ ከደመና በላይ ነዉ። ንስር እባብን ለማጥቃት ስፈልግ የግዴታ ከደመና ወደታች ይወርዳል ነገር ግን ንስር እባብን እታች ማጥቃት አይችልም፧ እባብ ድንጋዮች ውስጥ አድል አለው፤ በዚህም ምክንያት ንስር ድንጋዮች ውስጥ አያጠቃውም፤ በፍጥነት ከድንጋዮች ውስጥ አውጥቶ ወደ ሰማይ ይዞት ይበራል በዚህ ጊዜ እባብ መተንፈስ እያቃተው ለመናደፍ ይቸገራል፤ ንስር ከፍታውን በጨመረ ቁጥር እባብ ይሞታል፤ ምክንያቱም ከደመና በላይ የእርሱ ክልል ባለመሆኑ ነዉ።
የትኛውንም ችግራችሁን በሚገባው ቋንቋ አታናግሩት፤ ችግራችሁን ወይም ጠላታችሁን ለማያውቀው ክልል አጋልጡት። ለችግሮች አእምሮአዊ መፍትሔ ከማሸት የእግዚአብሔርን ቃል ማጋፈጥ እጅግ የተሻለ ነዉ። ጠላቶቻችሁን በአማርኛ ከማነጋገር በልሳን መናገር እጅግ የተሻለ ነዉ፤ ጠላቶች የምላችሁ በዋናነት ሰዎችን አይደለም፤ በክርስቶስ እንደሆነ ሰው በሽታ የእናንተ ጠላት ነዉ፣ የእግዚአብሔርን እውነት አለማወቅ ጠላታችሁ ነዉ፣ ኃጢአት፣ዓለም፣ ማጣት፣ አለመሳካት፣ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ መርገም፣ ሞት ወዘተ የእናንተ ጠላቶች ናቸው። ከእናንተ በላይ በሚያውቁት መሬት ላይ ከምትገጥሟቸው፤ ወደ ደመናው ወደ እግዚአብሔር ፊት ከፍ አድርጋችሁ ትንፋሽ አሳጧቸው።
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
