ar
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

الذهاب إلى القناة على Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

إظهار المزيد
1 810
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
በእያንዳንዳችሁ እግዚአብሔር መስራት የሚፈልገው ትልቅ ስራ አለ፤ የእርሱን ስራ ለመጀመር የራሳችሁን ስራ መተው ግን ግዴታ ነዉ፤ እግዚአብሔር የሚሰራው በጠንካራ ሰዎች አይደለም በራሳቸው ተስፋ በቆረጡ እና የአንተ ምንድነው ብለው በሚጠይቁት ሰዎች ነዉ። -Victor @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።” — ገላትያ 5፥24 ሰጋን የመስቀል ሥራ መንፈሳዊ እንጂ አካላዊ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበል ስጋችን( ኃጢአተኛው ተፈጥሮአችን) ከእርሱ ጋር እንደተሰቀለ ነው የሚነግረን፤ ይህ የሚሆነው በእምነት ነዉ። ስለዚህ ይህ ኃጢአተኛ ተፈጥሮ በዚያ በቀራንዮ መስቀል ላይ መሰቀሉ ኢየሱስ በቀራኒዮ የመስቀሉን ያህል እውነት ነዉ። ታዲያ ለምን አሁንም ይህ ኃጢአተኛ ተፈጥሮ(ስጋ) ተጽእኖ ያሳድርብናል? መልሱ ቀላል ነዉ፤ በክርስትና ጉዞ ውስጥ ከስጋም፣ ከዓለምም ከሰይጣንም ተጽእኖ ነጻ የምንወጣው ባለን መንፈሳዊ እውነት መጠን ነዉ። ከምታውቁት መንፈሳዊ እውነት በላይ ነጻ አይደላችሁም፤ ይህ ማለት እውቀታችን እና ነጻነታችን እኩል ነዉ። በፍጹም የእግዚአብሔርን እውነት ከምናውቀው በላይ ነጻ መሆን አንችልም፤ ሁልጊዜ እውነትን መጠማት ያለብን በዚህ ምክንያት ነው፤ ጌታችን እንደዚህ በማለት የገለጸልን ነዉ፤ “እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።” — ዮሐንስ 8፥32 ስለዚህ ከስጋ ወይም ከኃጢአተኛው ተፈጥሮ ተጽእኖ(ሃይል) ነጻ የምትሆነው፤ ከክርስቶስ ጋር አንድ ላይ የመሰቀልህን እውነት በተረዳህበት ልክ ነዉ። መጀመሪያ ላይ እንዳስቀመጥኩት ጥቅስ "ስጋዬ ከክፉ መሻቱ እና ምኞቱ ጋር ተሰቅሏል" የሚለው እውነት የሃሳብህ ክፍል እንዲሆን አድርግ ሁልጊዜ ያለማቋረጥ ይህንን አስብ፤ ይህንን በማድረግ ስጋን መስቀል ላይ እንደሆነ ማቆየት ነዉ። ሚስጥሩ ቀላል ነው፤ ለዚህ ነው ብዙዎች ማድረግ የማይችሉት። ከላይ የጻፍኩትን የተረዳ እና በሕይወቱ የሚያደርግ ሰው ስጋውን ሙሉበሙሉ ሃይል ያሳጣዋል። ፀጋ ይብዛላችሁ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አድምጥ ዝምታህን~ ዘማሪት ሃና ተክሌ @TheDeepThingsOfTheSpirit

ስጋን መስቀል የመጀመሪያው እና ትልቁ የመንፈሳዊ እና ሞራላዊ ሃይል የሚገኝበት መንገድ ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ስጋን መስቀል(Crucifying the flesh) ✅ በመጀመሪያ ስጋ ማለት ምን ማለት ነዉ? ስጋ ማለት ምን ማለት ነዉ? ስጋ የሰው ኃጢአተኛው ተፈጥሮ(ባሕሪይ) ማለት ነዉ። ስጋ(flesh) እና ሰውነት(body) የተለያዩ ናቸው። ስጋ የሚለው ቃል ሰውነትን( our body) ለመግለጽም ጥቅም ላይ የዋለ ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስ ስጋን ስለመስቀል ስናገር ሰውነትን( Body) ስለመስቀል ሰይሆን ኃጢአተኛ ተፈጥሮን (flesh,the sinful nature) ስለመስቀል ነው የሚያወራው። ✅መስቀል የሚለው ቃል ያዘለውን ሃሳብ ለመረዳት አይሁድ ኢየሱስን የሰቀሉበት ሂደት እንዴት እንደሆነ ማየት በቂ ነዉ፤ መስቀል ማለት የመጀመሪያው አለመቀበል(Rejecting) ነዉ፤ ሁለተኛው ደግሞ መግደል(killing or depriving of power) ነዉ። አይሁድ ኢየሱስ ላይ ያደረጉት ይሄንን ነዉ፡ የመጀመሪያ አልተቀበሉትም ማንነቱን፣ ትምህርቱን እና ስራውን አልተቀበሉትም፤ ጠልተውት ነበር፤ ሁለተኛው ደግሞ በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት። እኛም በክርስቶስ ኢየሱስ ስናምን የኃጢአተኛው ተፈጥሮ ላይ ያደረግነው እና ማድረግ ያለብን ይሄንኑ ነዉ፤ የመጀመሪያው ያንን ኃጢአተኛ ተፈጥሮ፣ ትምህርቱን እና ስራውን አለመቀበል! መጥላት ነዉ/ rejecting the sinful nature/፤ ከዚህ በኃላ የሚቀጥለው መግደል ነዉ፤ መግደል ማለት ሃይል ማሳጣት ማለት ነዉ/ ቆላ 3:5/። ስጋን መስቀል ማለት፤ ኃጢአተኛውን ባሕርይ፤ ትምህርቱን( ሃሳቡን) እና ስራውን መጥላትና አለመቀበል ከዛም መግደል ወይም ሙሉ በሙሉ ሃይል እንዳይኖረው ማድረግ ነዉ። ስጋና ሰውነት(flesh and body) ያላቸው ልዩነት በግልጽ የሚያሳይ አንድ ሃሳብ ልስጣችሁ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ሰውነታችንን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው መስዋዕት አድርገን እንድናቀርብ ይጠይቀናል፤ ስጋችንን ግን እንድንሰቅለው እና በቀጣይነት እንድንገድለው ያዘናል፧ (ሮሜ 12:1 እና ቆላስይስ 3:5)፧ ስጋችሁን ስቀሉት ሰውነታችሁን ግን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡ። በጣም የሚደንቀው የክርስቶስ ኢየሱስ ስንሆን ስጋን ወይንም ኃጢአተኛውን ባሕሪይ ሰቅለነዋል፤ አሁን ጥያቄው ለምን ታድያ ብዙ ክርስቲያኖች እስከአሁን በስጋ ናቸዉ? የሚል ነዉ። በቀጣይ ጠብቁኝ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ይህንን ጥያቄ መልሱልኝ🥰 👇👇👇👇👇👇 ስጋን መስቀል ማለት ምን ማለት ነዉ??

ስጋችሁን ስቀሉት! Crucify the flesh! ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤ ⁸ በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም።

መጽሐፍ ቅዱስ የማነበው ለምንድነው? ...በዛሬው ዓለም መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነበው ወገን ክርሲቲያን የሆነ ብቻ አይደለም፤ ክርሲቲያን ያልሆኑ የተለያዩ ሰዎችም መጽሐፍ ቅዱስን ለተለያየ አላማ ያነባሉ፣ ያጠናሉ፣ ይመረምራሉ እናም ይጠቀማሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጆች ሁሉ በተለያየ መልኩ የሚጠቅም ጥበብ አለው፤ በዚህ ዓለም ላይ በጣም ስለሚጠቅሙም ሆነ ስለሚጎዱ ነገሮች መጽሐፍ ቅዱስ ፍጹም የሆነ ምክር ይሰጣል ከዚህም የተነሳ ነዉ ብዙዎች የሚያነቡት፤ ነገር ግን የመጀመሪያው መጽሐፍ ቅዱስ የማንበብ አለማ ምንድነው? ይሄንን የሚያውቁ እና የሚያደርጉ እዚሁ ምድር ላይ ከሚቀር ያለፈ ሕይወት ያገኛሉ። የመጀመሪያው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ዓላማ እግዚአብሔርን እና መንገዱን ማወቅ ነዉ። እኔ በግሌ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረኝ ይሄንን ነዉ፤ አንድ ሰው መጽሐፍ ቅዱስን ስመረምር የመጀመሪያው ዓላማ መሆን ያለበት ሃይል(ቁሳዊ እና መንፈሳዊ) ማግኘት ወይም ስለነገሮች ማወቅ ሰይሆን እግዚአብሔር እና መንገዱን ማወቅ ነዉ። ትልቅ ሚስጥር ነዉ የምነግራችሁ። መጽሐፍ ቅዱስ ማንበባችን ብቻውን በቂ አይደለም ከንባባችን የምንጠብቀው ምላሽ ትልቅ ቦታ ያለው ነዉ። ሌሎች ብዙ ነገሮች አሉ፤ አሁን ግን ለመጻፍ የወደድኩት ስለመጀመሪያው የቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት ዓላማ ነዉ። እግዚአብሔርን እና መንገዱን ማወቅ፤ ጆሮ ያለው ይስማ። 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መለኮታዊ ግንኙነት:-ከተለመደው ተራ ሕይወት የሚያስወጣ ምስጢር። አብርሃም በዑር ምድር ከቤተሰቦቹ ጋር ተራ ኑሮ ከሚኖርበት የወጣውና ለምድር ሕዝቦች ሁሉ የበረከት መንገድ የሆነው እግዚአብሔርን መለኮታዊ በሆነ መንገድ በሁለት ወንዞች መካከል ከተገናኘ በኋላ ነዉ። ያዕቆብ ከ 21 አመታት የበረከት ፍለጋ እና ልፋት በኋላ በግዞት ከኖረበት ከላባ ቤትና ከሶሪያ በብዙ በረከት የወጣው እግዚአብሔርን መለኮታዊ በሆነ መንገድ በቤቴል ከተገናኘ በኋላ ነዉ። ሙሴ ለ 400 አመታት ባሮች እና የፈርዖን ገባሮች ሆነው በብዙ ጭንቅ በግብጽ የነበሩትን ወንድሞቹን እስራኤላዊያንን ከባርነት ምድር አስወጥቶ በምድር በዳ ለአርባ አመት በድንቅ መርቶ ከነዓን ያስገባቸው በኮሬብ መለኮታዊ በሆነ መንገድ እግዚአብሔርን ከተገናኘ በኋላ ነዉ። ጳውሎስ የቤተክርስቲያን አሳዳጅ ከነበረበት ተለውጦ በሰፊው ዓለም ላይ ቤተክርስቲያንን የተከለው፣ ከአእምሮ በላይ የሆኑ ተዓምራቶችን ያደረገው በሮም አንገቱ ተበጥሶ መስዋዕት እስኪሆን ድረስ ከ ሃያ ሰባቱ የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት አስራ አራቱን በመንፈስ ቅዱስ የጻፈው በደማስቆ መንገድ እግዚአብሔር መለኮታዊ በሆነ መንገድ ከተገናኘ በኋላ ነዉ። አስራ ሁለቱ ሐዋሪያት ገሊላ ከምትባል የገጠር መንደር ተነስተው ወንጌልን የሰበኩት፣ ሙታንን ያስነሱት፣ ከአእምሮ በላይ የሆኑ ድንቆችን እና ምልክቶችን ያደረጉት፣ ዓለምን ሁሉ በወንጌል ያወኩት መለኮታዊ በሆነ መንገድ እግዚአብሔርን በኢየሩሳሌም ስለተገኙ ነዉ። ስለ መሳፍንት ሁሉ፣ ስለ ሳሙኤልም፣ ስለ ዳዊትም፣ ስለ ነቢያትም ሁሉ ለመናገር ጊዜ ያጥረኛል። እግዚአብሔር ተገልጦላቸዋል፤ እግዚአብሔርን ያውቁታል። ወዳጆቼ ይህንን ስታነቡ እግዚአብሔርን ለማወቅ እና ለመገናኘት ረሓብ ውስጣችሁ እንዲፈጠር እየጸለይኩ ነዉ። Share ♻️ Join ♻️ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በመንፈሴ እንጂ። የዳንነው በመንፈሱ እንጂ በእኛ ሃይልና ብርታት አይደለም፤ የክርስቲያን ሕይወት በራሱ ሃይልና ብርታት የሚኖረው ሰይሆን ከእግዚአብሔር በተቀበለው በመንፈስ ቅዱስ ሃይልና ብርታት ነዉ። መጽሐፍ ለጌታ ቀን እንኳ የተጠበቅነው በእግዚአብሔር ሃይል እንደሆነ ይናገራል፤ ይህ ማለት እስከመጨረሻው ጠብቆ የሚያቆየውን መንፈስ ቅዱስ እንጂ የእኛ ሃይልና ብርታት አይደለም። ወዳጆች መቀደስ በእኛ ሃይል አይደለም፤ በመንፈሱ እንጂ፤ ማገልገል በእኛ ብርታት አይደለም በመንፈሱ እንጂ፤ ነጻ መውጣት በእኛ ሃይል አይደለም በመንፈሱ እንጂ። ለእግዚአብሔር ለመኖር መታገል አቁሙ የእናንተ ሃይልና ብርታት ለእግዚአብሔር እንድትኖሩ የሚያበቃችሁ አይደለም፤ ነገር ግን በዚህ ፈንታ መንፈስ ቅዱሱን አትረፍርፎ እንዲሰጣችሁ ለምኑ። የእግዚአብሔርንም ስራ በራሳችን ቴክኒክ እና ልህቀት ማከናወን አንችልም፤ ምንአልባት በጣም ብልጣብልጥ እንሆን ይሆናል ወይም ደግሞ ጥሩ የሚያስብ አእምሮ አለን ይሆናል እንዚህ ነገሮች ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የሚውሉ አይደሉም፤ እግዚአብሔር ሞኙን ነገር በመምረጥ እና በመጠቀም የዓለምን ጥበብ ሞኝነት ማድረግ ይወዳልና፤ በመንፈሱ እንጂ በሃይልና በብርታት አይደለም። እግዚአብሔር የሚሰራው በመንፈስ ቅዱስ እንጂ በእኛ ሃይልና ብርታት አይደለም፤ ይሄንን ማወቅ በራሱ ከትዕቢት ነጻ ያደርጋችኋል ትሁት መሆንም ያስችላችኋል ምክንያቱም የለመንፈስ ቅዱስ ምንም ናችሁ። እኔ የለ መንፈስ ቅዱስ ምንም ነኝ! የሆንኩትን ሁሉ የሆንኩት የምሆነውንም ሁሉ የምሆነው በሃይልና በብርታቴ ሰይሆን በመንፈስ ቅዱስ ነዉ። “ በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” — ዘካርያስ 4፥6 👇👇👇👇👇👇👇👇 Share ♻️ Join ♻️ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በኢየሱስ ስም በኢትዮጵያ ምድር የክርስቶስ ደም ይረጭ፤ ኢትዮጵያ የተሻለ በሚናገረው በጌታ ደም ትሸፈን።

ሰዎች ሁሉ በአንድነት በእግዚአብሔር ላይ አምጸዋል ስለዚህም የሰዎች ሁሉ የጋራ በሽታ ኃጢአት ነዉ፤ የኃጢአት ዋጋ ወይም የመጨረሻ ውጤት ደግሞ ሞት ነዉ፤ መድኃኒቱ ደግሞ ኃጢአት እና ነውር የሌለበት ቢሆንም ለሰዎች ሁሉ ኃጢአት መከራ የተቀበለውን፣ በመስቀል የተሰቀለውን፣ የሞተውን እና በሦስተኛ ቀን ከሙታን የተነሳውን ኢየሱስ ክርስቶስን መቀበል እና በስሙ ማመን ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ መከራ፣ ሞትና ትንሳኤ በማመን የዘላለምን ሕይወት ለመቀበል: ቀጥሎ ያለውን ጸሎት በእምነት ከልብ ይጸልዩ: ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመሰግንሃለሁ፤ በቅዱስ መንፈስህ ወቀሳ ኃጢአተኛ መሆኔን መረዳት ችያለሁ፡ ስለእኔ ኃጢአትም አንድያ ልጅህ መከራን እንደተቀበለ፣ በመስቀል እንደተሰቀለ፣ እንደሞተ እና እኔንም ለማጽደቅ መጽሐፍ እንደሚል በሦስተኛው ቀን ከሙታን እንደተነሳ አምናለሁ፤ ከዛሬ ጀምሮ በዚህኛው በሚመጣው ዓለም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ በአንደበቴ አውጃለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ ለዘላለም የኃጢአት ይቅርታን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን አግኝቻለሁና ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፤ በመንፈስ ቅዱስህም እንድትሞላኝ እለምናለሁ፡ አሜን። ይህንን ጸሎት በእምነት ከልብ ከጸለይክ/ሽ ከዛሬ ጀምሮ የኃጢአት ይቅርታን በኢየሱስ ክርስቶስ አግኝተሃል/ሻል። የእግዚአብሔር ወንድና ሴት ልጆችም ለመሆን ሃይልን ተቀብላችኋል። እንግድህ በእምነት እያደጋችሁ እንድትጠነክሩ የእግዚአብሔርን ቃል ወተት ተመኙ። እንኳን ደስ አላችሁ!🥰 ✅TheDeepThingsOfGod✅ የቃል እና የጸሎት ጊዜ Share ♻️ Join ♻️ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔርን ቅባት መቀበልና ጠብቆ ማቆየት የሚቻለው በዚህ መልኩ ነዉ። እግዚአብሔር በሃይል በሕይወታችን እንዲሰራ የጸሎት ጊዜ ሰይሆን የጸሎት ሕይወት ሊኖረን ይገባል። የ ጀነራል ቲ.ቢ ጆሽዋ የጸሎት ሕይወት ይህንን ይመስል ነበር። JOIN👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በእግዚአብሔር ቃል ስትሞሉ መንፈስ ቅዱስ ለመንፈሳችሁ መናገር ይጀምራል፤ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የመንፈስ እርዳታ እና መሪነት ከእናንተ ጋር ይሆናል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

20/10/2013 ዓ.ም እግዚአብሔር በራዕይ እንደዚህ አሳየኝ: በሚመጣው ዘመን እንደዚህ ነዉ የሚሆነው በጽዮን ተራራ ላይ ነጻ ማውጣት ይሆናል፤ ነዋሪዎቹም የተቀደሱ ይሆናሉ፤ ርስታቸውንም ይወርሳሉ። ነጻ አውጭዎች ከጽዮን ተራራ ይነሳሉ፤ በሌሎችም ተራራዎች ላይ ይፈርዳሉ፤ መንግስትም የጌታችንና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል። በጽዮን ተራራ ላይ እንደዚህ ተብሎ ይዘመራል 'በዚህ ተራራ ላይ ነጻ መውጣት ይሆናል፤ እግዚአብሔር መልካም በሃይሉም የበረታ ነውና። በእኔ፣ በአንተ፣ በአንቺ ሕይወትና አገልግሎት የሚፈጸም ትንቢት ነዉ። ራዕዩ ይሄ ነው በሚነበቡ ቃላት ተቀርጿል፤ አንባቢው ይፍጠን፤ ራዕዩ አይዋሽ፤ አይዘገይም በእውነት ይፈጸማል። -ProphetVictor @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👇የማይለወጥ እውነት👇 ዳግም መወለድ የቻልነው(የዳነው) እግዚአብሔር የራሱን ሕይወት ስለሰጠን ነዉ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በእኛ እንድሰራ የምንፈልግ ከሆነ እኛ ሕይወታችንን ለእርሱ መስጠት ይኖርብናል። -Victor @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

-ምንኛ መልካም ነው -ዘማሪ~ አገኘሁ ይደግ የእግዚአብሔር መገኘት ይሸፍናችሁ! 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ምንኛ መልካም ነው በመገኘትህ ውስጥ መቆየት ከዚህ ዓለም ግርግር መለየት ክብርህን ማየት😭 -አገኘሁ ይደግ🥰

-እንግዳ ነገር አለ ፊቴ -ዘማሪ~ ዮሐንስ ግርማ የእግዚአብሔር ልጆች በዚህ መዝሙር ዘመናችሁ ላይ ተናገሩ( ትንቢት ተናገሩ) 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ፍጹም ለውጥና መንፈስ ቅዱስ አንድን ለውጥ ፍጹም ነዉ ማለት የምንችለው ለውጡ እውነተኛ እና ዘላቂ ስሆን ብቻ ነዉ። ለውጥ የእውነት ሆኖ ዘላቂ የማይሆን ከሆነ እንኳ ለውጥን ፍጹም ማለት አንችልም። አሁን ከየትኛውም ጊዜ በላይ እያንዳንዱ የክርስቶስ የአካል ክፍል ፍጹም ለውጥ ያስፈልገዋል፤ አንተ ፍጹም ለውጥ ያስፈልግሃል አንቺም ፍጹም ለውጥ ያስፈልግሻል፣ ሁላችንም ፍጹም ለውጥ ያስፈልገናል። አብዛኛው ሰው በሕይወቱ ለውጥ ፈላጊ እንደሆነ ግልጽ ነዉ፤ ከዚህ በፊት ይሄንን ለውጥ ለማምጣት የተለያዩ መንገዶች ተከትለን ይሆናል ነገር ግን የተፈለገውን ለውጥ ማየት አልተቻለም! ለምን? ወዳጆቼ ፍጹም ለውጥ ወደ ሕይወታችን የሚመጣው የእግዚአብሔርን ቃል በመንፈስ ቅዱስ ስንረዳ እና የመንፈስ ቅዱስን ሃይል ስንቀበል ነዉ። ተከታታይ ትምህርቶች ፣ የእሁድ እና የሌሎች ቀናት መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ተካፍለን ፍጹም ለውጥን መለማመድ ያልቻልነው መንፈስ ቅዱስን ከቦታው ስለገፋነው ነዉ። በሕይወታችን ለመንፈስ ቅዱስ ትልቁን ቦታ መስጠት ስንጀምር ፍጹም ለውጥ ያኔ ይጀምራል፤ የክርስቶስ ሕይወት በትግል የምንኖረው ሰይሆን ለመንፈስ ቅዱስ ራስን አሳልፎ በመስጠት የምንለማመደው ነዉ። ለመንፈስ ቅዱስ ሁለንተናችንን እንስጥ፤ ከራስ ፀጉራችን እስከ እግር ጥፍራችን እርሱ የሌለበት ቦታ መኖር የለበትም፤ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥና በእኛ ላይ ይግዛ! መንፈስ ቅዱስ ተቆጣጠረኝ እንበለው! መንፈስ ቅዱስ በሃይል ይቆጣጠራችሁ። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ! ✅TheDeepThingsOfGod✅ 🔥 መንፈስ ቅዱስ 🔥 የቃል እና የጸሎት ጊዜ 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit