የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 477 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 026 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 324 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 477 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 526، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 12، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.31%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.22% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 538 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 477 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 477
المشتركون
+1224 ساعات
+1357 أيام
+52630 أيام
أرشيف المشاركات
"እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ፤ በጸጋውም እን ደግ!" መጽሐፈ ቅዳሴ በእንተ ቅድሳት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ፣ 12ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከግንቦት 26 –27 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ይካሄዳል፡፡
ሔኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ቢያደርግ እግዚአብሔር ስለወሰደው አልተገኘም። ዘፍ 5፡24 ነብየ እግዚአብሔር ኤልያስም እግዚአብሔርን በማስደሰቱ በእሳት ሰረገላ ወደ ሰማይ አረገ። 2ኛ ነገ 2፡1 ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ፍቁረ እግዚእ የተባለ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሞትን እንዳያይ በአምላኩ ተነገረው። ዮሐ 21፡22 እንደዚሁ ኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅ ፣ የመጽሐፍት ደራሲ ፣ ካህን ፣ የነገረ ሃይማኖት ሊቅ ምሑር ቅዱስ ያሬድም በዚህች ዕለት በግንቦት 11 ወደ ብሔረ ሕያዋን የሄደበት የተሰወረበት ዕለት ነው። በረከቱ ከኛ ጋር ትሁን ለዘለዓለሙ አሜን!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ዕርገተ ክርስቶስ
“እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው” ሐዋ. 1÷9
ዕርገት ማለትወደላይ ከፍ ከፍ ማለት ሲሆን የመሬትን የስበት ኃይል የሚያሸንፍ ከፍታ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ያረገው የመሬት የስበት ኃይልሳይገድበው ነው፡፡ የክርስቶስ ዕርገት ቀድሞ በትንቢት የተነገረ፤ በሚያምኑት ዘንድ በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየ እና በራሱ በጌታችንየተሰበከ ነው፡፡�
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ፴፫ ዓመታት ከሦስት ወራት በምድር ኖሯል፡፡ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀለ፫ ዓመታት አስተማረ፣ ስለ ኃጢአታችን በመስቀል ላይ ቤዛ ሆነልን፡፡ በሦስተኛውም ቀን ከሙታንተለይቶ ተነሣ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ተገለጠላቸው፡፡
ዛሬም ጌታችን ኢየሱስ ከዕርገቱ በፊት ከተነሣ በኋላ ስላስተማራቸው ትምህርቶች፣ ደቀመዛሙርቱን ስላዘዛቸው ትዕዛዝ እናያለን፡፡
ጌታችን ከተነሣ በኋላ ባሉት ፵ ቀናት በተለያዩ ጊዜያት ለደቀመዛሙርቱ ተገልጾ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ያስተምራቸው ነበር፡፡ ስለክርስቶስ የተነገረውን የቅዱሳት መጻሕፍትትንቢት ከዚያ በፊት አላስተዋሉም ነበር፡፡ ጌታችንም ስለ እርሱ የተጻፉትን ተረጎመላቸው፣ አዕምሮቸውንም ከፈተላቸው መጻሕፍትንም አስተዋሉ፤ እምነታቸውን አጸናላቸው፡፡ ስለ ትንሣኤው የነበራቸውንጥርጣሬም ከልቦናቸው አጸዳላቸው፡፡
የሚከተሉትን ትዕዛዛት እና ኃላፊነቶችም ሰጣቸው፡-
* ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፡፡ ማር ፲፮ ፥ ፲፭
*¹ ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስትጠመቃላችሁ፡፡ የሐዋ ፩ ፥ ፭
¹ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስምእያጠመቃችሁ… አስተምሯቸው፡፡ ማቴ. ፳፰ ፥ ፲፱ - ፳
¹ እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ፡፡ የሐዋ.ሥ ፩ ፥ ፰�በወንጌል ለመስበክ እና በስሙ ለማጥመቅ ወደ ዓለም ሲወጡ፣ እንደሚገረፉ ወደ ነገሥታትየፍርድ አደባባይም እንደሚያወጧቸው ነገሯቸዋል፡፡ እስከመጨረሻም የጸና ግን ይድናል በማለትእስከ ዓለም ፍጻሜ ከእነርሱ ጋር እንደሚሆንና መንፈስ ቅዱስን ሲቀበሉ ኃይልን እንደ ሚያገኙምቃል ገብቶላቸዋል፡፡
ከሙታን በተነሣ በ፵ ኛው ቀን ደቀመዛሙርቱን ወደ ደብረዘይት ወሰዳቸውናባረካቸው፡፡ ተሰብስበው ትምህርቱን እየሰሙም ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ወደ ሰማይም ዐረገ ደመናም ከዓይናቸው ሰወረው፡፡
ደቀመዛሙርቱ ክርስቶስ ወደ ዐረገበት ቀና ብለው እየተመለከቱ ሳለ ሁለት መላዕክት ነጫጭልብስ ለብሰው በአጠገባቸው ቆመው “ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይሄ ከናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ።
ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል አሏቸው፡፡ ኢየሱስ ሞትን አሸንፎ በተነሣ በአርባኛው ቀኑ በድል ዐረገ፡፡ ወደ ሰማይ እያረገ ሲሄድ እንዳዩት ደግሞ ባልዳነው ዓለም ላይሊፈርድ ይመጣል፡፡ እናማረጉን አምነን ዳግም መምጣቱን እንናፍቅ፡፡�
” ደቀመዛሙርቱም ጌታ ካረገበት ከደብረ ዘይት እግዚአብሔርን እያከበሩ ተመለሱ፡፡ እንደታዘዙት መንፈስ
ቅዱስን እስኪቀበሉም በኢየሩሳሌም ቆዩ ፡፡
እኛም በኢየሩሳሌም በተመሰለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለጸሎትና ለአገልግሎት በመትጋት ልንቆይ ይገባል ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሔኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ቢያደርግ እግዚአብሔር ስለወሰደው አልተገኘም። ዘፍ 5፡24 ነብየ እግዚአብሔር ኤልያስም እግዚአብሔርን በማስደሰቱ በእሳት ሰረገላ ወደ ሰማይ አረገ። 2ኛ ነገ 2፡1 ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ፍቁረ እግዚእ የተባለ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሞትን እንዳያይ በአምላኩ ተነገረው። ዮሐ 21፡22 እንደዚሁ ኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅ ፣ የመጽሐፍት ደራሲ ፣ ካህን ፣ የነገረ ሃይማኖት ሊቅ ምሑር ቅዱስ ያሬድም በዚህች ዕለት በግንቦት 11 ወደ ብሔረ ሕያዋን የሄደበት የተሰወረበት ዕለት ነው። በረከቱ ከኛ ጋር ትሁን ለዘለዓለሙ አሜን!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ኃሢሠ አእምሮ 2ኛ ዙር የ7ኛ ክፍል ጥያቄ እና መልስ ውድድር ከምሽቱ 2፡00 ጀምሮ በEOTC Tv ይጠብቁን!
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጀንዳዎችን አርቅቀው እንዲያመጡ ሰባት አባላትን ያቀፈ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን መሰየሙ ይታወሳል። የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴው ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮናሲዎስ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ፣ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ ፣ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ እና ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የተሰየሙ ሲሆን። ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአስረጅነት ተሳትፈዋል።
በዚሁ መሠረት በአጀንዳ አርቃቂው ኮሚቴ አማካኝነት የቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ያጸደቃቸው ፲፰ ቱ የመወያያ አጀንዳዎች፦
፩. የቅዱስነታቸው የመክፈቻ ንግግር በተመለከተ
፪. የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት
፫. ስለ ሀገር ሰላም
፬. ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግሮችን በተመለከተ
ሀ. በትግራይ ክልል ስለሚገኙ አህጉረ ስብከት
ለ. በኦሮምያ ክልል ስለሚገኙ አህጉረ ስብከት
፭. ስለ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ
ሀ. ክፍት የሆኑትና በተደራቢነት የተያዙት አህጉረ ስብከት ስንት እንደሆኑ መለየት
ለ. ስንት አባቶች መሾም እንዳለባቸው መወሰን
ሐ. ሕገ ቤተ ክርስቲያን በሚያዝዘው መሠረት የሚሾሙትን አባቶች መልምለው የሚያቀርብ ኮሚቴ መሰየም
መ. የሚሾሙበትን ቀን መወሰን
፮. በውጭ ያሉ አህጉረ ስብከት መተዳደሪያ ደንብ በተመለከተ፤
፯. ስለ ብፁዓን አበው ዝውውር
ሀ. ስለ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ
ለ. ስለ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ
፰. ችግር ስላለባቸው አህጉረ ስብከት
ሀ. አዊ ሀገረ ስብከት
ለ. በትግራይ ክልል የማይጨው እና ደቡብ ምሥራቅ አህጉረ ስብከት
፱. ስለ ዋልድባ ዳልሻህ ኪዳነ ምሕረት ማኅበረ ደናግል ገዳም
፲. ስለ መንፈሳዊ ኰሌጆች ማቋቋም
ሀ. ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት
ለ. ኢሉ አባ ቦራ ሀገረ ስብከት
ሐ. ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት
መ. በምዕራብ ኦሮምያ ማዕከላዊ በኾነ ቦታ አንድ ኮሌጅ እንዲከፈት ተጠንቶ እንዲቀርብ
፲፩. ስለ አብነት ትምህርት ቤት
፲፪. ከመሪ ዕቅድ መምሪያ ስለ ቀረበ የ፲ ዐመት መሪ ዕቅድ
፲፫. ስለ ቤቶች እና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በአጣሪ ኰሚቴ የቀረበ ሪፖርት
፲፬. ለኹሉም መንፈሳዊ ኰሌጆች በማዕከል ደረጃ ሊያገለግል ስለሚችል መተዳደሪያ ደንብ
ሀ. የሐዋሳ ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኰሌጅ መተዳደሪያ ደንብ
ለ. የወልቂጤ ዜናማርቆስ መንፈሳዊ ኰሌጅ መተዳደሪያ ደንብ
፲፭. ከበጀት እና ሒሳብ መምሪያ ስለ ቀረበ መግለጫ
፲፮. ስለ ጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት የአስተዳደር፣ የጽሙና የትምህርት፣ የሥልጠና እና የጥናት ምርምር ማዕከል መመሥረቻ ፕሮጀክት ሰነድ
፲፯. ስለ ጡረተኞች የአበል ጭማሪ
፲፰. ስለ ቋሚ ሲኖዶስ አባላት ምርጫ
ኃሢሠ አእምሮ 2ኛ ዙር የ7ኛ ክፍል ጥያቄ እና መልስ ውድድር ዘወትር ማክሰኞ ከምሽቱ 2፡00 ጀምሮ በEOTC Tv ይጠብቁን!
በዛሬው መርሐ ግብራችንም ደብረ ታቦር ከ ደቂቀ መዊዕ ሰንበት ት/ቤት ውድድራቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ልደታ ለማርያም
Nativity of St.Mary
በምስራቅም በምዕራቡም የኦርቶዶክሳውያን፣ እንዲሁም በካቶሊካውያን ትምህርት ውስጥ ሰፊ ቦታ ካለው ትምህርት መካከል አንዱ ነገረ ማርያም (Mariology) ትምህርት አንዱ ነው።
በብሉይም በሐዲስ ኪዳንም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ስለ ቤተሰቧና የልጅነት ታሪክ የሚተርክ ታሪክ የለም። ነገር ግን የነገረ ማርያምን ታሪክ በሰፊው የጻፈልን በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን (175 ዓ.ም) የተጻፈው የያዕቆብ ወንጌል (St. Jems protoevangelion) ነው።
የቅዱሳንን የልደት ቀንን የማክበር ልምድ በኦሬንታል ኦርቶዶክሳውያኑ ዘንድ የለም። ቲዎሎጂውና ጽሑፎቻቸው ትውፊታቸው የነገሩን ግን ይኽንን ነው። ይሁን እንጂ በተለየ ሁኔታ የእመቤታችን እና የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን ልደት ብቻ ለይተው ያከብራሉ። ቅዱሳኑ ሰማያዊ ልደታቸው ነው የሚከበረው። ከእናት አባት የተወለዱበት ልደት ልዩ አይደለም የሚል ነጥብ አላቸው። የዮሐንስ ልደት ቀድሞም በልዩነቱ በቅዱስነቱ በማሕጸን ተመስክሮለት ስለ ተወለደ ያከብሩታል።
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመወለድ ነገር እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ አይደለም። "ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ሕሊና ታስባ ትኖር ነበር"። በእግዚአብሔር ሕሊና ሳይታሰብ የመጣ ምንም ፍጥረት የለም። የእመቤታችን መታሰብ ግን ልዩነቱ ለአምላክ እናት መሆን ነው።
መጽሐፍት ስለ ልደቷ ያበሰሩን ገና በገነት ከሰው ድቀት ዕለት ጀምሮ ነው። "በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ"ያለው የዘንዶውን ራስ የሚቀጠቅጠው ወንድ ልጅ የሆነው ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው "ዘር" ነውና። ዘፍ3:15
ጠቢቡ ሰሎሞን " አሐቲ ይእቲ ለእማ ወኅሪት ይእቲ ለእንተ ወለደታ ፤ ለእናቷ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት ሲል ፤ ቅዱስ ዳዊት " መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱስን። መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ነው ሲሉ ተንብየውላታል።
ኢሳይያስ በትንቢቱ " ትወጽዕ በትር እምስርወ እሴይ ወየአርግ ጽጌ እምኔሃ ከርሴይ ሥር በትር ትወጣለች አበባም ከእርሷ ይወጣል ማለቱ በትር እመቤታችን አበባ የሆነ ጌታ መገኘቱን የተናገረው ትንቢት ነው። ኢሳ 11:1
በተለይም በኦሪት ዘፍጥረት ያዕቆብ ያየው ሕልም በጥንት ሊቃውንት ትርጓሜ በጥልቀት የተፈታ ትርጉም ነው። "እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ ነው፤ እኔ አላወቅሁም ነበር አለ። ፈራ፥ እንዲህም አለ፦ ይህ ስፍራ እንዴት ያስፈራ፤ ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህም የሰማይ ደጅ ነው። ያዕቆብም ማልዶ ተነሣ፥ ተንተርሶት የነበረውንም ድንጋይ ወስዶ ሐውልት አድርጎ አቆመው፥ በላዩም ዘይትን አፈሰሰበት" ዘፍ.28:17
መሰላል ከላይ ወደ ታች እንዲወረድበት አምላክ በእመቤታችን በኩል ፍጹም ሰው ሆነ በማሕጸንዋ ዘጠኝ ወር ተሸከመችው። በዚኽም ያዕቆብ እንዳየው እመቤታችን የእግዚአብሔር ቤት ተባለች። በኋላም በጉባኤ ኤፌሶን እመ እግዚአብሔር (Theotokos) ተብላለች።
በሐዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 1 ነገረ ማርያምን አስነብቦናል። ለሐናና ለኢያቄም እግዚአብሔር ድንቅ ነገርን አደረገላቸው። ይስሐቅ ከሳራ፣ ሳሙኤል ከሐና ዮሐንስ ከኤልሳቤጥ እንደ ተገኙበት መንገድ መካን ከሆኑት የካህናትና የቤተ መንግሥት ወገን ከሆኑት ደጋግ ቅዱሳን ተወለደች።
ቅዱስ ያሬድ የእመቤታችንን መወለድ ከአዳም ባሕርይ (ቃል ኪዳን) ውስጥ አልፋ መገኘቷን በምሥጢር ገልጦ ሲናገር "ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸአዳ፣ ማርያምማ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ (ጸአዳ እንቊ) ታበራ ነበር" ብሎላታል። ሰው ምንም ኀጢአተኛ ቢሆን በደጋግ አባቶች ውስጥ በብዙ ቸርነት ትገለጥና ታልፍ ነበር።
በሌላም ስፍራ ቅዱስ ያሬድ "ዘእንበለ ይትፈጠር ሰማይ ወምድር ወዘ እንበለ ትሳረር ምድር ገነት ሀለወት ስብሕት ቅድስት ወቡርክት ይእቲ ማርያም” ብሏታል።
አባ ሕርያቆስ በምስጋና ድርሳኑ ላይ "ኦ ማርያም አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ። ማርያም ሆይ በኃጢአት በሆነ ፍትወት የተጸነሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከኢያቄም ከሐና ተወለድሽ እንጂ" ብሏታል። የእመቤታችን ልደት ለጌታ ልደት ዋዜማው ነው
ስለ እመቤታችን ከጻፉት ሊቃውንት መካከል ቅዱስ ኤጲፋንዮስ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ኤፍሬም፣ ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ ፣ ሶርያዊው ሴባስቲየን ይገኙበታል። በዚህም ጽሑፋቸው ከመውለዷ በፊት በወለደች ጊዜ ከወለደች በኋላ ድንግል መሆኗን አስተምረዋል።
በመጀመሪያ የእመቤታችንን ልደት ማክበር የጀመረው ቀደም ብሎ ቢሆንም በዓለም አቀፍ ሁኔታ በዓል እንዲሆን ያደረገው በ 740 ዓ.ም ቅዱስ እንድርያስ ነው። በልደታ ስም ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ያሠራችው ቅድስት እሌኒ በኢየሩሳሌም ሲሆን በምዕራባውያን ዘንድ የልደቷ በዓል የሚከበረው መስከረም 8 ሲሆን እኛ ተአምር ማርያም መቅድም እንደሚነግረን "አባቶቻችን እንደ ነገሩን ልደቷን ግንቦት ፩ ነው እንላለን" እንዳሉት ይኽንኑ ይዘን ልደቷን በደስታ እናከብራለን። የእመቤታችን በረከትና ምልጃ አይለየን።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
ኃሢሠ አእምሮ 2ኛ ዙር የ4ኛ ክፍል ጥያቄ እና መልስ ውድድር ከምሽቱ 2፡00 ጀምሮ በEOTC Tv ይጠብቁን!
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱
ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ
🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱
⚡⚡⚡ሰኞ⚡⚡⚡
👉ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
⚡⚡⚡ማክሰኞ⚡⚡⚡
👉ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
⚡⚡⚡ረቡዕ⚡⚡⚡
👉አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
⚡⚡⚡ሐሙስ⚡⚡⚡
👉አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
⚡⚡⚡ዓርብ⚡⚡⚡
👉ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
⚡⚡⚡ቅዳሜ⚡⚡⚡
👉ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
⚡⚡⚡እሁድ⚡⚡⚡
👉ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ይህ ፍጹም ሊሆን እንደማይችል ሕሊናችን ሳይቀር ይመሰክርብናል፡፡ ታድያ መፍትሔው ምንድን ነው? ያልን እንደ ሆነ መፍትሔውማ ንስሐ መግባት ነው እንላለን፡፡ ንስሐ መግባት ማለት ይከተሉት የነበረውን ክፉ ተግባር ሙሉ በሙሉ እርግፍ አድርጎ በመተው ወደ ደገኛው ተግባር መመለስ ማለት ነው፡፡ ንስሐ ማለት ትናንት በጥይት ሲጠፋ የነበሩ ወገኖች ዛሬ እሱን አቆመውና በክብ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ችግራቸውን በፍቅር ለመፍታት መወያየት መቻል ማለት ነው፡፡ ትክክለኛው ንስሐ እንዲህ ያለው ነው፡፡
ይህንን የመሰለ ጥሩ አርአያ ያለው ንስሐ በሀገራችን በቅርቡ ሲፈጸም አይተናል፤ ይህንን ያደረጉ ወገኖች በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናቸዋለን፤ ይህን ያደረጉ ወገኖች ትክክለኛውን ትንሣኤ ተነሥተዋል፤ የትንሣኤውንም በዓል በትክክል አክብረዋል፡፡ ሆኖም ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ የሚያስገኘው ከእምነት ሲነሣ ነውና ነገሩ ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር ተብሎ በእምነት ሊደረግ ይገባል፤ ገና ወደ ጠረጴዛ ያልመጣችሁ ወገኖችም ንስሐ ገብታችሁ ወደ ውይይት እንድትመጡና የጋራ ሀገራችንን በጋራ እንድናገለግል በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ መፎካከር ይቁም፤ መወያየት ይቅደም፤ ከሰላም፣ ከአንድነትና ከፍቅር ተጠቃሚ መሆናችንን አንዘንጋ፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም በቂ ብቻ ሳትሆን፤ ከበቂም በላይ ናት፡፡ ኢትዮጵያ የሁላችንም ናት፤ ይህ የኔ ነው ይህ የኔ ነው በሚል ደካማ አመለካከት ራሳችንን በራሳችን አንጉዳ፣ ከእንግዲህ ወዲህ የጥይት ድምፅ ይብቃ፤ የዕለቱ ዓቢይ መልእክታችን ይህ ነው፡፡
በመጨረሻም፡-
የትንሣኤውን በዓል ስናከብር የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጨነቁትን በማጽናናት፣ እንደዚሁም የተገኘውን የሰላም ጭላንጭል ይበልጥ ለማስፋትና የሀገር አንድነቱን በዕርቅ ዘላቂ ለማድረግ ቃል በመግባት የፋሲካን በዓል እንድናከብር በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እነሆ፤
በስመ አብ፣ወወልድ፣ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
• ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
• የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፋ የቆማችሁ፣
• በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
• እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵውያት በሙሉ!
ትንሣኤና ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!
“እሙታን ተንሢኦ ሲኦለ ከይዶ በሞቱ ለሞት ደምሰሶ፡- ከሙታን ተነሥቶ ሲኦልን ረግጦ በሞቱ ሞትን ደመሰሰው” /መጽሐፈ ኪዳን/
ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሥጋ ሰብእ ተገልፆ ዓለምን ከሞተ ኃጢአተ እንደሚታደግ ከጥንት ጀምሮ ነቢያት ሲያስተምሩና ሲመክሩ ኖረዋል፡፡ እግዚአብሔር በጠባዩ በደለኛውን ከቶ የማያነጻ አምላክ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በአንጻሩ ደግሞ ለፍጥረቱ ፈጽሞ የማይጨክን አምላክ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ እግዚአብሔር ሰውን በፈጸመው በደል ምክንያት ቢቀጣውም የኋላ ኋላ ቅጣቱን ወደ ራሱ አዙሮ በመቀበል ሰውን በሚያስደንቅ ምሕረቱ ተቀብሎታል፡፡ በዚህም አድራጎቱ እግዚአብሔር ሕግን በማክበር፣ ፍርድን በመጠበቅ፣ ምሕረትን በማድረግ ትክክለኛነቱን በሚገርም ሁኔታ ፈጽሞ እናየዋለን፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ሲያመሰጥር እንዲህ በማለት ይገልጸዋል፡-
• “ሁሉም ኃጢአትን ሰርተዋልና የእግዚአብሔር ክብር ጐድሎአቸዋል በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ፤ እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስርያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎት ስለመተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፤ ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው” ይለናል (ሮሜ. 3፡23-26)
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!!
ለጌታችን መሰቀልና መሞት መንሥኤ የሆነው የእኛው በደል ነው፡፡ በደላችን እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ አሳጥቶ ኃጢአተኞች እንድንሆን አድርጎናል፡፡ የኃጢአት ደመወዝ ደግሞ ሞት ስለሆነ በኃጢአታችን ለሞት ተዳርገናል:: በዚህ ምክንያት ከተጫነብን የሞት ዕዳ ሊገላግለን ጌታችን በእኛ ፈንታ ተሰቅሎ፣ ንጹህ ደሙንም መሥዋዕት አድርጎ በማቅረብ የሞት ዕዳ ከኛ እንዲነሣ አደረገልን፡፡
እግዚአብሔርም በኢየሱስ ክርስቶስ ንጹህ ደም ምክንያት ሙሉ ይቅርታን ሰጥቶ ታረቀን፤ ወደ እሱም አቀረበን፤ ተቀበለንም፡፡ እግዚአብሔር የኢየሱስ ክርስቶስን ደም በፊት ለተደረገውም ሆነ ለወደፊት ለሚሆነው ኃጢአት መደምሰሻ ወይም ማስተሰረያ አድርጎ በቀዋሚነት አጸናው:: በመሆኑም ቀደምት አበውም ሆኑ ደኃርት ውሉድ የሚድኑት በኢየሱስ ክርስቶስ ንጹህ ደም መሆኑን ክርስቲያኖች ሁሉ ሊገነዘቡት፣ ሊቀበሉትና ሊያምኑበት ይገባል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ “እግዚአብሔር በዚህ መሥዋዕት እኛን በማጽደቁ ፍጹም ጻድቅ ወይም እውነተኛ መሆኑን አሳየ” በማለት ያረጋግጣልና ነው:: እንግዲህ ጌታችን በዚህ መሥዋዕትነቱ የቀደመውን ኃጢአት ሙሉ በሙሉ ስላስወገደው በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወረደ፤ ቀጥሎም ከአዳም ጀምሮ እስከ ዕለተ ስቅለቱ ድረስ በሰቆቃና በስቃይ የነበሩ ነፍሳተ አበውን ወደ ጥንተ ሀገራቸው ወደ ገነት መለሳቸው፡፡ በዚህም በደልና ፍዳ ኃጢአት ሲኦልና ዲያብሎስ ተሸንፈው ባዶ እጃቸው ስለቀሩ ሲኦልን ረግጦ በሞቱ ሞትን ደመሰሰው ተብሎ የምስራቹ ተነገረን፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!!
ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን በከፍተኛ ደረጃ የምታከብረው በዓለ ትንሣኤ በእግዚአብሔር ችሎት የሚያስፈርድብንና የሚያስቀጣን በደላችን ስለተሰረዘ፣ ቅጣታችንም ስለተነሣ፣ እኛን ለመዋጥ አፋቸውን ከፍተው የሚጠብቁትን ሞትና መቃብርም ባዶአቸው የቀሩበት አምላካዊ ድል የተፈጸመበት በመሆኑ ነው፡፡ ለዚህም ማረጋገጫችን የጌታችን ትንሣኤ ነው፡፡
ጌታችንም ከመሞቱ በፊት በቃልና በተግባር ያረጋገጠልን ይህንን ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታችን በቅዱስ ወንጌል፡- “ኃጢአትህ ተሰረየልህ ወይም ተሰረየልሽ” በማለት ኃጢአትን ሲሰርዝ አይተናል:: በሰው ሁሉ ላይ የበላይነት አግኝተው በመርዛም ተግባራቸው ሰውን ሲያሰቃዩ የኖሩ ሰይጣንና ሠራዊቱ “አንተ ርኩስ መንፈስ እልሃለሁ ከሱ ውጣ” እያለ በማስወጣት ወደ ጥልቁ ሲያሠጥማቸው አይተናል፡፡ በአጋንንት ጠንቅ በልዩ ልዩ ደዌና በሽታ ተይዘው ሲሠቃዩ የነበሩ ሰዎችንም ከበሽታቸው ገላግሎ ፍጹም ጤንነት ሲሰጣቸው አይተናል፡፡ መቃብርን ቤታቸው አድርገው የነበሩትንም ሙታን “ና ውጣ ከመቃብር” እያለ ከመቃብር ሲያስነሣቸው አይተናል፡፡ የሞቱትንም “ተነሥ፤ ተነሽ” እያለ ሲያስነሣቸው ተመልክተናል:: በተሰቀለበት ዕለትም በቅድስት ሀገር በኢየሩሳሌም አምስት መቶ ሙታን ተነሥተው በከተማው ውስጥ ለብዙ ጊዜ መቆየታቸውን ተምረናል፡፡ ታድያ እነዚህ አምላካዊ ድርጊቶች በሙሉ በደልና ፍዳ ኃጢአት፣ ሞትና ሲኦል፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ የእነዚህ አጋፋሪ የሆነው ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ ተሸንፎ ባዶውን ወደ ጥልቅ መስመጡ የሚያሳዩን አይደሉምን? ልብ ብለን ከተመለከትነውና ካስተዋልነውስ ትንሣኤው የጌታችንን እውነተኝነት፣ የዲያብሎስና ሠራዊቱን ተሸናፊነት ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩን አይደሉምን? የዚህ ሁሉ ማረጋገጫ ማዕተምስ የጌታችን ከሞት መነሣት አይደለምን? ከዚህ አኳያ ጌታችን ሲነሣ ብቻውን አልተነሣም እንላለን፡፡ ነገር ግን እሱ ሲነሣ ገና ሳይሞት ያስተማረው ትምህርትና የፈጸመው ተአምራት ሁሉ አብሮ ተነሥቶአል፤ ምክንያቱም ትንሣኤው የእውነተኝነቱ ማረጋገጫ ነውና፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!!
እኛ የትንሣኤ ልጆች ነን፤ ጌታችን ሞትንና መቃብርን ድል ነሥቶ የተነሣው እኛም እሱን ተከትለን ሞትንና መቃብርን ድል እንድንነሣ እንጂ የእነሱ ሢሣይ ሆነን እንድንቀጥል አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ እንዳለመታደል ሆኖ የሰው ልጆች ዛሬም ምርጫቸው ትንሣኤ ሳይሆን ሞት ሆኖ መገኘቱ እጅግ በጣም የሚቈጭና የሚያሳዝን ነው፡፡ ዛሬም ሰዎች እርስ በርሳቸው እየተጣሉና እየተገዳደሉ የሞትና የመቃብር ሢሣይ በመሆን ቀጥለዋል፤ ከዚህ አስከፊና ጎጂ ድርጊታቸው ለመቆጠብም ዝንባሌ አይታይባቸውም፤ ታድያ እኛ ሰዎች የሞትንና መቃብርን ጎጂነት፣ የትንሣኤንና የጤናማ ሕይወትን ጠቃሚነት ለይተን በማወቅ ለጥቅማችን መቆም የማንችል ከሆነ የጌታችን ትንሣኤ አከበርን ማለቱ ጥቅሙ የቱ ላይ ነው ከመገዳደልና ከመጨካከን ሳንመለስ የምናከብረው በዓልስ እግዚአብሔር ይወድልናል ወይ? ይቀበለዋል ወይ?
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
