ar
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 430 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 084 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 336 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 430 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 543، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 21، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 36.43‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً N/A‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 252 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

14 430
المشتركون
+2124 ساعات
+1247 أيام
+54330 أيام
أرشيف المشاركات
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7309159732751781163?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7298773267170510
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7309159732751781163?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7298773267170510341 "እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።" ማቴ 18፡3

"የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።" 1ኛ ቆሮ 1፡18 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Yo
"የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።" 1ኛ ቆሮ 1፡18 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ዓለም ለዘመናት የተለያዩ መከራዎችንና ፈተናዎችን አስተናግዳለች። የብዙዎቹ ችግሮች ምንጮች ደግሞ ሰው ሠራሽ ናቸው። ሰው በእግዚአብሔር አርአያ መፈጠሩ፣ ዐዋቂና አስተዋይ ፍጡር መሆኑ ለችግሮቹ መፍቻ
ዓለም ለዘመናት የተለያዩ መከራዎችንና ፈተናዎችን አስተናግዳለች። የብዙዎቹ ችግሮች ምንጮች ደግሞ ሰው ሠራሽ ናቸው። ሰው በእግዚአብሔር አርአያ መፈጠሩ፣ ዐዋቂና አስተዋይ ፍጡር መሆኑ ለችግሮቹ መፍቻ ቁልፍ ለማግኘት እንዲችል አድርጎታል። በዚያው ልክ ራሱ ለፈጠራቸው ችግሮች መፍትሔ አጥቶ ሲባዝን ይታያል። በዚህም ምክንያት ሰው የስኬቱ ተጎጂ (the victim of his own success) ሆኗል። እሳትና ውኃ ቀርቦልሃል ወደ ወደድኸው እጅህን ጨምር ሲባል ሁለቱንም እጁን ወደ ሁለቱም የሚልክ ባክኝ ፍጡር እየሆነ ነው። የሰው ልጅን ሁሉ ሊያጠፋ የሚችል አቶሚክ ቦንብ ሠራ። በሽታንም የበሽታ መድኀኒትንም፣ ኮምፒዩተርን የኮምፒዩተር ቫይረስንም መፍጠሩ እሳትንም፣ ውኃንም ለመምረጡ ማሳያዎች ናቸው። ሞትንም፣ ሕይወትንም በአንድ ጊዜ ምርጫው አድርጎ ለመኖር የሚሻ ፍጡር ሰው ብቻ ሳይሆን አይቀርም። የሰው ልጅ ሕይወት በምድር ላይ ብርቱ ሰልፍ ነው እንደ ተባለ፣ በእያንዳንዱ ርምጃው ምርጫ አለው። ይህ ምርጫው ከመልካምና ከመጥፎ ብቻ ሳይሆን ከሁለት መጥፎዎች ውስጥ አንዱን እስከ መምረጥ ድረስ ይዘልቃል። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/በረሃብ-ከመሞት-በጦርነት-መሞት-ይሻላል/ በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ።" ራእይ 5፡8 እንኳን ለ24ቱ
"መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ።" ራእይ 5፡8 እንኳን ለ24ቱ ካህናተ ሰማይ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

+(አምላክ ለክብር ሊያረገን ሲወድ እንደሳኦል ያሉ ተቺዎች እንደ ጎልያድ ያሉ ትምክህተኞችን በፊታችን ያመጣል)+ + የእግዚአብሔር ምርጫ እንደ ዓለም መስፈርት እንዳልሆነ በዳዊት ታሪክ መማር እንችላለን።ዳዊት በአባቱ በእሴ ዘንድ በአይን የማይገባ በወንድሞቹ ዘንድ የተዘነጋ በሰዎች ዘንድ የተረሳ ውሎ በዱር ከበጎች ጎነ የሆነ እረኛ ነበር።እሴ ለንግስና መልከ መልካሞቹን ባለቁመና እና ለአይን የሚገቡትን ልጆቹን አቅርቦ ዳዊትን ግን ዘነጋው። 👉እኛም በቤተሰቦቻችን ዘንድ ተዘንግተን በወዳጆቻችን ዘንድ ተረስተን በሰው አይን አይሞሉም ተብለን ተገለን ይሆናል።የወለደን አባታችን ከነመፈጠራችን ዘንግቶን። ያሳደገች እናታችን በኛ ተስፋ አታ ይሆን ይሆናል። ነገርግን የፈጠረን ፈጣሪ አይዘነጋንም። እግዚአብሔር ከፊት ይልቅ ልብን ይመለከታልና እንደሰው አያደላም። + እግዚአብሔር ግን በረኝነት ስፍራ ከበጎች ጋር በዱር የሚውለውን ዳዊትን አስተወሰው አባቱ እሴ የረሳውን ዳዊትን እግዚአብሔር አስታወሰው ለንግስና አይበቃም ብለው ወንድሞቹ የተውትን ዳዊትን እግዚአብሔር ግን አከበረው። + የዳዊት መናቅ በአባቱ ቤት ብቻ አላበቃም በሳኦልም ንግስና ቀጠለ እንጂ።ሳኦል ጎልያድን ሊወጋ ባሰበጊዜ የዳዊትን ወንድሞች ይዞ ሲነሳ ዳዊትግን ከበጎቹ ጋር ነበር።ሳኦል ከትንሹ እረኛ ከዳዊት ይልቅ አካለ ፈርጣማዎቹን መረጦ ወሰደ።እግዚአብሔር ግን ፊቲን ሳይሆን ልብን ጉልበትን ሳይሆን እምነትን ይመለከታልና ዳዊትን በዛ ሰደደ።ዳዊትም በሳኣል አእምሮ እንኳን ሊደረግ ሊታሰብ የማይችል ቃልን ተናገረ። "ጎልያድን እገላለው "አለው። ሳኦልም ሰው ነውና ከልብ ይልቅ ፊትን ተመልክቶ"አንተ ገና ብላቴናነህ እሱ ከብላቴናነቱ ጀምሮ በጦር ነው ያደገነውና ይህን ፍልስጥኤማዊ ልተወጋ  አችልም። (1ኛሣ17፥34) 👉በእኛ ሕይወትም እንደሳኦል አይነቶች ብዙ አለመቻሎችን ይሰብኩናል። መንፈሳዊ ሕይወት ሊኖረን እንደማይችል ፍፁም ዓለማዊ ሰዎች እንደሆንን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንደማይቻለን እግዚአብሔር ለኃጣን ሳየሰሆን ለፃድቃን የመጣ አርገው የሚያሳምኑን አይጠፉም በእምነት እንችላለን ብለን ስንተጋ ለመተቸት የሚሽቀዳደሙ ከልባችን ይልቅ ፊታችንን የሚመለከቱ በእኛ ሕይወትም የሳኦል አይነት ብዙ ተቺዎች አሉ። + ዳዊት ግን እግዚአብሔር ለዚህ አላማ አስቦ በረኝነት እንዳሰለጠነው ያውቃልና እንዲህ ሲል መለሰ"እኔ ባሪያኸ አንበሳና ድብ መታኹ ይህንንም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያዋን አምላክ ጭፍሯች ተገዳድሯአል እና ከነዚህ እንደአንዱ ይሆናአል"(1ኛሣ17፥36)በማለት ያላንዳች ፍርሀት ተናገረ። 👉እግዚአብሔር በኛ ህይወት ንግስናን ሊሰጠን ሲያስብ በረኝነት አያያዛችንን ያያል።ሊያነግሰን ሲፉልግ ጎልያድን የሚያህሉ ፈተናዎች በፊታችን ያመጣል።እንደ ተጣልን እና እንደተረሳን ስናስብ እግዝአብሔር ቀና ያደርገናል።አምላክ ለክብር ሊያረገን ሲወድ እንደ ሳኦል ያሉ ተቺዎች እንደ ጎልያድ ያሉ ትምክህተኞችን በፊታችን ያመጣል። + ዳዊት በአባቱ አይን አለመሙላት በሳኦል ፊት መተቸቱ በጎልያድ መናቁ ጎልያድን ከመግደል አለከለከለውም "በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብኸለሁ" በማለት የጎልያድ ሰይፉና ግዝፈት ሳያስፈራው ከረኝነት ጀምሮ በጠበቀው በእግዚአብሔር አምኖ ጎልያድን በአንድ ጠጠር ገደለው። 👉እግዚአብሔር ከኛጋ ሲሆን እንደዳዊት በአንድ ጠጠር ትምክህተኛን ስንጥል። እግዚአብሔር ከኛ ከራቀ ግን ባንዲት ጠጠር እንደጎልያድ ሞትን እንቀምሳለን።በሰው ዘንድ ስንናቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እንታያለን በሰው ስንረሳ በአምላካችን እንታወሳለን።በሰው ዘንድ እረኛ ስንሰኝ በእግዚአብሔር ለክብር እንሆናለን። + ዳዊት በአባቱ በእሴ ዘንድ እረኛ ቢሰኝ በሳኦል ዘንድ ብላቴና ቢባል በውንድሞቹ ዘንድ ታናሽ ቢሰኝ በአምላኩ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንደልቤ ተብሏል። 👉እኛም ዛሬም በብዙ ሳኦሎች ዘንድ ብንተች በብዙ ጎልያዶች ፊት እንደ ኢምንት ብንቆጠር በፈጠረን አምላክ ዘንድ የማይፋቅ ቦታ አለን።እግዚአብሔር እንደዳዊት ሊያነግሰን ሲፈልግ እንደ ጎልያድ አይነት ትምክህተኞች እንደ ሳኦል አይነት ተቺዎች ያመጣብናል። ያንን እንደዳዊት በእምነት ካለፍነው እረኝነታችን ለክብር መውደቃችን መናቃችን  ለከፍታ መሆኑ አይቀርም ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ሰው ፊትን አይመለከትም ልብን እንጂ። ቤተልሔም ታምራት ከአፍሪካ ሕብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ሰ/ት/ቤት ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም ከብዙ ውኆች፥ አፋቸውም ምናምንን ከሚናገር፥ ቀኛቸው የሐሰት ቀኝ ከሆነ፥ ከባዕድ ልጆች እጅ አስጥለኝ።" መዝ 143፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻ
"እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም ከብዙ ውኆች፥ አፋቸውም ምናምንን ከሚናገር፥ ቀኛቸው የሐሰት ቀኝ ከሆነ፥ ከባዕድ ልጆች እጅ አስጥለኝ።" መዝ 143፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"ይህች እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ፥ እንደ ጨረቃ የተዋበች እንደ ፀሐይም የጠራች፥ ዓላማ ይዞ እንደ ተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ማን ናት?" መኃ 6፡10 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩ
"ይህች እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ፥ እንደ ጨረቃ የተዋበች እንደ ፀሐይም የጠራች፥ ዓላማ ይዞ እንደ ተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ማን ናት?" መኃ 6፡10 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

https://youtu.be/h7GnF0qAJEE ሳምንታዊውን ዜና ፈለገ ጥበብ ዛሬ ምሽት ከ2፡00 ጀምሮ ይከታተሉን!

"አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ። አሁንም ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይህን ቤት መርጫለሁ ቀድሻለሁም፤ ዓይኖቼና ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ።" 2 ዜና
"አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ። አሁንም ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይህን ቤት መርጫለሁ ቀድሻለሁም፤ ዓይኖቼና ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ።" 2 ዜና 7፡15 - 16 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።" 1ኛ ዮሐ 2፡6 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ
"በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።" 1ኛ ዮሐ 2፡6 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መምሪያ እሳቤዎች የቀጣይ ሥራዎች ላይ ሁለተኛ ዙር የግንዛቤ መስጫና የምክክር  መርሐ ግብር አከናወነ። ኅዳር 18/3/1016ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ባዘጋጀውና ወደ ትግበራ እንዲገባ በቅዱስ ሲኖዶስ መመርያ የተሰጠበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ቀጣይ አፈጻጸምና በውስጡ ሊያካትቱ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ዙርያ በልዩ ልዩ የቤት ክህነት መዋቅር ከሚያገለግሉ ኃላፊዎችና መምህራን ጋር ምክክር አደረገ። የምክክር መርሐግብሩን በፀሎት ያስጀመሩት የመምሪያው ኃላፊ መጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዮስ ሲሆኑ የመምሪያው የትምህርት ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክትና ስለ ሥርዓተ ትምህርቱ ጠቀሜታ የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በመቀጠል የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው የውይይት መነሻ የሚሆን ገለጻ ተደርጓል። በመቀጠልም በማደራጃ መምሪያው ምክትል ኀላፊ በመጋቤ ሐዲስ ፀጋ ወልደ ትንሳኤ አወያይነት ተጋባዥ መምህራንም ሥርዓተ ትምህርቱን በተመለከተ በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጓል። በመርሐ ግብሩ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት 1- ከሁሉም የቤተክርስቲያን የትምህርት ተቋማት ጋር የሚኖረው መስተጋብር ሥርዓት፣ 2- ከመደበኛ የአስኳላ ትምህርት አንጻር ተማሪዋቹን ተደራሽ ስለሚደረግበት አቅጣጫዎች 3- ከወቅታዊ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተገናዘበ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፓለቲካዊ ጉዳዮችን በምን ዓይነት ማካተት ይገባል በሚል ሰፊ ምክክር ተደርጓል። የመርሐ ግብሩ ተሳታፊ መምህራንም በማደራጃ መምሪያው እየተሰራ ያለው ሥራ በጎና ቤተክርስቲያ የሚጠቅም መሆኑን ገልጠው ሊካተቱ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ገንቢ ሐሳብና መልዕክትን አስተላልፈዋል። በመጨረሻም የማደራጃ መምሪያው ምክትል ኃላፊ መምህር ፀጋ ወልደ ትንሳኤ እንዲህ ዓይነት መድረኮችን ለተለያዩ በቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ስር ላሉ መምህራን በማዘጋጀት ግንዛቤ የመፍጠሩ ስራ እንደሚቀጥል መልዕክታቸውን በማስተላለፍ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኖአል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።" 1ኛ ጢሞ 3፥15 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ
"ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።" 1ኛ ጢሞ 3፥15 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu