የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 479 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 043 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 334 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 479 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 530، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 23، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 39.14%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.20% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 666 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 477 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 479
المشتركون
+2324 ساعات
+1447 أيام
+53030 أيام
أرشيف المشاركات
ይህንን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ እንዲሁም ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር በማድረግ በስርአተ ትምህርቱ ዙሪያ የሚወጡ አዳዲስ መረጃዎችን እና የአንድነቱን መልእክቶች ይከታተሉ።
የ2015_ዓ_ም_የመስቀል_ደመራ_በዓል_በአዲስ_አበባ_መስቀል_አደባባይ_ በሰንብት ት/ቤቶች ፍሬዎች እጅግ በደመቀ መልኩ ተከበረ፡፡ በዚህ ዓመት በአምሰቱ ምዳባት በአዲስ አበባ የሚገኙ አድባራትና ገዳማት የሰንብት ት/ቤት መዘምራን በሀገር አቀፍ፣ አዲስ አበባ እና ክፍለ ከተማ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ሰፊ ዝግጅት በማድረግ ያከበሩ ሲሆን የቀረበው ትርዒትና ወረብ፡፡
1. በሰሜን ክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
- ትርዒት፡- ቤተክርስቲያን የሁሉም ናት
የተሳታፊ ብዛት፡- 800 የሰንበት ት/ቤት አባላት
2. በደቡብ ክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት፡-
- ትርዒት፡- መስቀል እና 2015 ዓ.ም በግእዝ ቁጥር
- የተሳታፊ ብዛት፡- 1300 የሰንበት ት/ቤት አባላት
3. በአቃቂ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ትርዒት፡- ሠላም ለሀገራችን ሰላም ለመላው አለም
የተሳታፊ ብዛት፡- 810 የሰንበት ት/ቤት አባላት
4. በምስራቅና ምዕራብ ክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በጋራ፡-
ትርዒት፡- ወረብ የወረቡ ግሥ
‹‹ መካነ አፍረየ፣ አፈልፈለ ቀላየ፣ አውኀዘ ለነ ደመ ወማየ።(2)
ዮም ንዜኑ ዘመስቀል ዕበየ ንዜኑ ዘመስቀል ዕበየ።(2)»
የተሳታፊ ብዛት፡- 1300 ምስራቅ + 850 ምዕራብ) በድምሩ 2150 የሰንበት ት/ቤት አባላት፡፡ አምላካችን ለሀገራችን ሰላም ለተቸገሩና ላዘኑ ሁሉ መጽናናት እንዲሁም በመስቀሉ ፍቅርን ያድለን፡፡ ✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ለሁሉም አኅጉረ ስብከትና ወረዳ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በሙሉ የ4ኛ እና 7ኛ ክፍል መጻሕፍትን በስስ ቅጅ ለሰንበት ት/ቤቶች ለማድረስ ስለተዘጋጀ በሥራችሁ ላሉ ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ሊንኩን ላኩላቸው እና መረጃውን ሞልተው እንዲልኩ በማድረግ መጻሕፍቱን በአድራሻቸው እንዲደርሳቸው ይደረጋል። ለዚህም ለሁሉም አጥቢያዎች ሊቃነ መናብርትና ትምህርት ክፍሎች የተላከውን ሊንክ ከታች ይጠቀሙ ፡፡
https://eotc-gssu.org/a/የመማሪያ-መጻሕፍት-ይላኩልን/
https://eotc-gssu.org/a/የመስቀል-መዝሙሮች/
የመስቀል መዝሙራት ሊንክ ነው። በዚህ ማስፈንጠሪያ /ሊንክ/ በመግባት መዝሙራቱን ይጠቀሙ።
ጥብቅ ማሳሰቢያ
****
ነሐሴ ፳፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፬ ዓ.ም
"""""""""""""""""""""""""""""
አዲስ አበበ -ኢትዮጵያ
""""""""""""""""""""""
ሰምኑን የቤተክርስቲያናችን ባልሆኑ ማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት የቤተክርስቲያናችንን አርማ በመጠቀምና የቤተክርስቲያናችን ማኅበራዊ መገናኛዎች በማስመሰል ልዩ ልዩ ዜናዎችን በመሥራት ሕዝበ ክርስቲያኑን ለማደናገር የሚሞክሩ ድረ ገጾች እየተሰራጩ መሆኑን ደርሰንበታል።
እነዚሁ ድረ ገጾች ላይም በተለይ የቤተክርስቲያናችን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የሰጡት መግለጫ በማስመሰል የሚያስተላልፏቸው ዘገባዎች ሐሰተኞች ከመሆናቸውም በላይ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ስም የተከፈቱ የቲዩተርም ሆነ የፌስ ቡክ አካውንት የሌለ መሆኑን እየገለጽን ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ማስተላለፍ የሚፈልጉት መልዕክት ካለ በቤተክርስቲያናችን መገናኛ ብዙሃንና በሕዝብ ግንኙነት ድረ ገጾች ብቻ የሚያስተላለፉ መሆኑን እየገለጽን ሕዝበ ክርስቲያኑ ከነዚህ ህጋዊ የቤተክርስቲያናችን መገናኛ ዘዴዎች ውጪ የሚተላለፉ መልእክቶች ሁሉ የሐሰት መረጃዎች መሆናቸውን በመረዳት ህዝበ ክርስቲያኑን ለማደናገር ከተከፈቱ ሐሰተኛ የማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን በመጠበቅና ለክፉ ዓላማ ማሳኪያ ተብለው የተከፈቱ መገናኛ አውታሮችን እንዲጋለጡ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።
መረጃው ለሁሉም እንዲዳረስ ሼር በማድረግ እንዲተባበሩን ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
" ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል "
መዝሙረ ዳዊት ፸፫÷፳፰
☞ ይህን ቃል የተናገረው በእግዚአብሔር እንደ ልቤ የተሰኘ ለእግዚአብሔር የቀረበ ቅዱስ ዳዊት ነው። ቅዱስ ዳዊት የሚመኘውና የሚሻለውን ሲናገር፦ ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል።" መዝ 118÷72
እኛስ በሕይወትና በኑሮአችን ውስጥ እንዲሆንና እንዲደረግ ይሻለኛል ብለን የምንመርጠው ምን ይሆን? ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ቅርበት የአባትና ልጅ ነው?
" በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና። አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።" ሮሜ ፰÷፲፬-፲፰ የአባትና የልጅ ቅርበት በምን ላይ የተመሠረተ ነው? ቢሉ? በፍቅር የተመሰረተ ነው፡፡
እኛ ትዕዛዙን መፈፀማችን ለእርሱም መገዛታችን ከፍቅር የተነሳ ነው፡፡ ይህንንም መጽሐፍ ቅዱስ ሲመሰክር፦ " ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።... የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።" ዮሐ ፲፬÷፳፪-፳፫ ብሎናል፡፡
ሰው እግዚአብሔርን እየቀረበ በሄደ ቁጥር ይበልጥ እያወቀው ለእርሱም በፍርሃት እየቀረበ ይመጣል፣ ኃጢአትን ይጠላል እንጂ ኃጢአትን በማብዛት እግዚአብሔርን አይገዳደርም፡፡ ዲያብሎስ ምንም እንኳ ሲፈጠር እግዚአብሔር አክብሮ ቢፈጥረውም ክቡሩን ባለማወቁ ለሀሰትና ለክደት ተጋልጦ ከፈጣሪው ተጣላ፡፡ በልቡ እግዚአብሔርን አልፈራምና ከአምላኩ በመራቅ ለዘላለም ሞት ተጋለጠ፡፡ "እግዚአብሔርን የመፍራት ድምጽ በልቡ ውስጥ የሌለው ሰው ነፍሱ እንደሞተ ይወቅ፡፡" አባ ቀልሚን (ዜና አበው)
✍️ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ሲል በምንድን ነው?
መቅረብ ፦ በሁለት መንገድ 1- በአካል 2- በመንፈስ
በአካል፦
፩- ማደርያው በሆነች እርሱንም በምናገኝባት በቅድስት ቤተክርስቲያን መኖር ይሻለኛል ሲል፡፡ ቅዱስ ዳዊት፦ " እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።" መዝ ፳፯÷፬ እንዲል፡፡
በመንፈስ፦
መቅረብ ሲል "በእግዚአብሔር መኖር" ማለት ነው፡፡
" በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ እኖራለሁ፡፡" ዮሐ ፲፭÷፬
✔️ ሕይወታችንን በአምላክ ትዕዛዝ ላይ በጽናት እንድንመሰርት የሚነግረን ነው፡፡
✔️ ከእግዚአብሔር ጋር የምንኖረው ስለ እኛ የቆረሰውን ሥጋውን ስንበላ ደሙንም ሰንጠጣ ነው፡፡
" ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።" ዮሐ ፮ ÷፶፮ እንዲል፡፡
" እግዚአብሔርን ከፈለግነው ራሱን ይገልጥልናል አጥብቀን ከያዝነው ከእኛ ጋራ አብሮ ይኖራል፡፡" ቅዱስ አርሳንዮስ
አንድም መቅረብ ሲል እግዚአብሔርን ማምለክ እርሱን መከተል (ሃይማኖትን) ነው፡፡
" እነሆ፥ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉና ከአንተ ርቀው የሚያመነዝሩትንም ሁሉ አጠፋኻቸው።" መዝ ፸፫÷፳፯ ያለው ከአምልኮተ እግዚአብሔር ወጥተው በአምልኮተ ጣዖት የሚሆኑትን ኁሉ አጠፋሀቸው ሲል፡፡ ሴሰኝነት የሴትና የወንድ ብቻ አይደለምና ጣዖት ማምለክ ሴሰኝት ከእግዚአብሔርም መራቅ ነው፡፡ " አቤቱ፥ የእስራኤል ተስፋ ሆይ፥ የሚተዉህ ሁሉ ያፍራሉ፤ ከአንተም የሚለዩ የሕይወትን ውኃ ምንጭ እግዚአብሔርን ትተዋልና በምድር ላይ ይጻፋሉ። " ት ኤር ፲፯÷፲፫
"እግዚአብሔርንም ማምለክ ክፉ መስሎ ቢታያችሁ፥ አባቶቻችሁ በወንዝ ማዶ ሳሉ ያመለኩአቸውን አማልክት ወይም በምድራቸው ያላችሁባቸውን የአሞራውያንን አማልክት ታመልኩ እንደ ሆነ፥ የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን። " ኢያሱ ፳፬÷፲፭
አንድም መቅረብ በንስሐ ወደ እርሱ እቀርባለሁ (እመለሳለሁ) ሲል
" ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።" ሐዋ ፫÷ ፲፱-፳
✔️ በፍጹም ልብ በፆምና በጸሎት ወደ እርሱ እቀርባለሁ ሲል፡፡ አምላክም የሚፈልገው ይህን ነውና
" አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ። " ት ኢዮ ፪÷፲፪እንዲል
👉 ወደ እግዚአብሔር እንዳንቀርብ የሚያደርጉን ነገሮች ምንድን ናቸው?
➊ ኃጢአታችን
"ንስሐ ግቡ ኃጢአትም እንቅፋት እንዳይሆንባችሁ ከኃጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ" ሕዝ ፲፰÷፴
➋ ቆራጥ አለመሆናችን
✔️ ከእግዚአብሔር የሚያርቀንን በልባችን ያለውን ክፋት ለመተው ዝግጁ አይደለንም እንሳሳለን፡፡
" በእኔ ማለት በሥጋዬ በጎ ነገር እንዳይኖር አውቃለሁና፤ ፈቃድ አለኝና፥ መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም። የማልወደውን ክፉን ነገር አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን በጎውን ነገር አላደርገውም። የማልወደውን የማደርግ ከሆንሁ ግን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፥ በእኔ የሚኖር ኃጢአት ነው እንጂ።" ሮሜ፯÷፲፰-፳
👉 ወደ እግዚአብሔር በመቅረባችን
➊ የጨለመው ሕይወታችን ይበራል፡፡
" ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።" መዝ ፴፬÷፭
♥️ በሕግ በአምልኮ ወደሱ ቅረቡ ብርሃነ ረድኤቱን ያበራላችኀል፡፡ አንድም ከመከራ አድኖ ደስ ያሰኛችኀል፡፡
ኃፍረት የሚገለጠው በፊት ነውና አታፍሩም ሲል አንድም ፊታውራሪያችሁ (መሪያችሁ) አያፍርም ሲል፡፡
➋ በሕይወት እንኖራለን
" ጆሮአችሁን አዘንብሉ ወደ እኔም ቅረቡ፤ ስሙ ሰውነታችሁም በሕይወት ትኖራለች፤ የታመነችይቱን የዳዊትን ምሕረት፥ የዘላለምን ቃል ኪዳን ከእናንተ ጋር አደርጋለሁ።" ኢሳ ፶፭÷፫
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዲ/ሚክያስ ግዛቸው
📚''ኑ አብረን ደስ ይበለን!'' የምርቃት ጥሪ
✝️የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2014 በጀት ዓመት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትግበራ ሲያካሂዱ የነበሩ 28 ቤተ ክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች 1600 በላይ ተማሪዎችን ያስመርቃል።
የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና፣ የየመምሪያ ኃላፊዎች፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣ የጽዋ ማኃበራት እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አመራር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የፊታችን እሑድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት አቡነ ገብረ መንፈቅ ቅዱስ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ያስመርቃል።
🌐 በባሕረዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሚዲያ ክፍል። SUBSCRIBE @AndnetMedia 👇 https://www.youtube.com/c/AndnetMedia 💠 የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን @EOTCBDSSU በመቀላቀል መረጃዎችን ይከታተሉ ለሌሎች ኦርቶዶክሳዊያንም ያዳርሱ... #Share
አባቶቻችን፥ መሐሪው ጌታ እኛን የወደደበትን ዘላለማዊ ፍቅርንና ለእኛ ያደረገውን የማዳን ሥራ በመጽሐፈ ቅዳሴ፦ “ኦ እንተ አፍቀርካ ለዛቲ ዘመድነ - ይህችን ባሕርያችንን የወደድሃት ሆይ” በማለት አድንቀዋል። እኛም ለእመቤታችን የተደረገው (ለአምላክ እናትነት መመረጧ፥ ዘላለማዊ ድንግልናዋ፥ ከፍጡራን ማንም የማይስተካከለው ቅድስናዋ፥ ከሞት ተነሥታ ማረጓ) ለድኅነታችን (ለመዳናችን) የተደረገና የእኛን ሰብዓዊ ባሕርይ ልዩ ክብር (glory) የሚያንጸባርቅ ስለሆነ በዚህ ሁሉ ደስ ይበለን፥ ሐሴትም እናድርግ። በሔዋን የተዋረደው ሰብዓዊ ባሕርያችን በዳግሚት ሔዋን (በድንግል ማርያም) ስለከበረ እንደ አባቶቻችን ትምህርት እመቤታችንን፦ “ትምክሕተ ኵልነ/ ትምክሕተ ዘመድነ” እንበላት።
ይህን እውነት ሲያመሰጥር፥ በሶርያዊው ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ስም የሚጠራው የኢትዮጵያውያን አባቶቻችን አኰቴተ ቊርባን፦ “ወካዕበ ተማኅፀነ በማርያም እምከ እንተ ይእቲ እግዝእትነ ወትምክሕተ ዘመድነ በወሊዶተ ዚአከ - ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማፅነናል፤ ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት” ይላል (ቊ. 99)።
በመጨረሻም፥ ሄኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አምላኩ እንደወሰደው (ዘፍ. 5፥24)፥ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ቀናዒ የነበረው ነቢዩ ኤልያስም በእሳት ሰረገላና በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ አንደተነጠቀ (2 ነገ. 2፥ 11) ከመጽሐፍ ቅዱስ ያነበበ ሰው፥ የወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ወደ መንግሥተ ሰማያት መወሰድ ጥያቄ ሊፈጥርበት አይገባም። “እነሆ፥ ሰማይ ከሰማያትም በላይ ያለው ሰማይ ይይዝህ ዘንድ አይችልም” (1 ነገ. 8፥27) የተባለለትን አምላክ፥ ድንግል ማርያም በማኅፀንዋ ተሸከመችው። ስለሆነም “ዳግሚት ሰማይ፥ ዳግሚት አርያም፥ ሰማይ ዲበ ምድር (በምድር ላይ ያለች ሰማይ)” ተባለች፤ ወንድሞቻችን ኦርቶዶክሳውያንም እንደ እኛ አባቶች፦ “O St. Mary, your womb is more spacious than the heavens” ብለው ዘመሩ።
ስለዚህ የድንግል ማርያምን ወደ ሰማይ ማረግ (ዕርገት) እየተቃወሙ የትዕቢት ቃላትን ከመሰንዘር ይልቅ፥ ኦርቶዶክሳዊውን አስተምሕሮ በትሕትና በመማር፥ ዳግሚት ሰማይ (ድንግል ማርያም) በዕለተ እሑድ ከተፈጠረው ሰማይ ጋር ኅብረት በማድረጓ እጹብ እያልን እናድንቅ፤ ይህን ሁሉ ላደረገ አምላካችንም የከንፈራችንን ፍሬ የምስጋና መሥዋዕት አድርገን እናቅርብለት (ዕብ. 13፥15) ።
ማደሪያ መቅደሱን ያከበረ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅድስት እናቱ ጸሎትና ልመና በሰማያውያንና ምድራውያን በረከቶቹ ሁሉ ይባርከን፤ ለቅዱሳን አባቶቻችን የሰጠውን የእመቤታችንን የእናትነት ጣዕምና ፍቅር ያብዛልን።
Dr.kesis Mebrtu kiros
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
