የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 309 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 167 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 365 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 309 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 502، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 48.88%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.10% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 309
المشتركون
+1624 ساعات
+1117 أيام
+50230 أيام
أرشيف المشاركات
+8
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከ3000 በላይ ለሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በሁለት ቋንቋ የተዘጋጀውን የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል የ2017 ዓ.ም የሞዴል (ናሙና) ፈተና ሐምሌ 13/2017 ዓ.ም ሰጠ፡፡
በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ እየተተገበረ የሚገኘውን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየያስተማሩ በሚገኙት በአዳማ መንበረ ጵጵስና ፤በቢሾፍቱና አካባቢው፣በዱግዳ፣በአዳሚ ቱሉ ጂዶ ኮምቦልቻ፣በቦሰት እና በፈንታሌ ወረዳ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን በተገቢው ሁኔታ የተማሩ የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሐምሌ 13/2017 ዓ.ም የሞዴል (ናሙና) ፈተና ተፈትነዋል፡፡
በአኅጉረ ስብከት ደረጃ የሚሰጠው የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና በሀ/ስብከቱ ለ2ኛ ጊዜ ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም በየወረዳዉ በተመረጡ የፈተና ጣቢያዎች እንደሚሰጥ የሀ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታውቋል፡፡
መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው፡፡
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 14/11/2017ዓ.ም
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ እየተሰጠ 7ኛ ቀኑን በያዘው የክረምት የመምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ላይ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በመገኘት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ብፁዕነታቸው ለእናንተ የመንግስተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቷችኋል" ማቴ 13፥11 በሚል ርዕስ ቃለ እግዚአብሔርና አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የመንግስተ ሰማያት ምሥጢር ለማወቅ ጾታና ማዕረግ ሳይለይ ለሁሉም የሰው ዘር የተሰጠ ጸጋ መሆኑንና ይህን ምስጢር አውቆ ማሳወቅ ከመምህራን የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል።
አያይዘውም ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት አሳስበው እንደ ሀገረ ስብከታቸው ሰሜን ወሎ ለሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰልጣኞችን በመላክና በመማርያ መጻሕፍት ግዥ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ሥልጠና በሚገባ ተከታትለው በየሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
+5
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአለፋት አራት ዓመታት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎችን የ2017 ዓ/ም የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል ብሔራዊ ተፈታኞችን ምዘና ሐምሌ 13/2017 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በተለያዩ የምዘና ማዕከላት ተሰጠ።
ምዘናው የተሰጠባቸው ማዕከላት
✅የቅዱስ ሉቃስ ምድብ አንድነት
አቡነ ቴዎፍሎስ አካዳሚ
✅በቅዱስ ማቴዎስ ምድብ አንድነት ማቴዎስ
ደብረ ዓባይ ቅዱስ ገብርኤል፣
✅በቅዱስ ዮሃንስ ምድብ አንድነት
መካነ ሰላም ድባንቄ መዳኒዓለም፣
✅በቅዱስ ማርቆስ ምድብ አንድነት
ደብረ ይባቤ ዘንዘልማ ሚካኤል
ምዘናው በሦስቱ ማዕከላት በጥሩ ሁኔታ የተሰጠ መሆኑ ሲገለጽ አንድ ማዕከላት የምዘና ወረቀት ብዜት ችግር ገጥሞ የነበረ መሆኑ ተገልጾል።
ዘገባው የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከ14,000 በላይ ለሚሆኑ የሰንበት ት/ ቤት ተማሪዎች በሀገረ ስብከት ደረጃ የብሔራዊ ፈተና ምዘና በዛሬው ዕለት አከናወነ።
ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ ሃድያ እና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ወቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራል ተገኝተው ምዘናውን በጸሎት አስጀምረዋል።
በዛሬው የአራተኛ የስምንተኛ እና የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች በአመቱ የተማሩትን ምን አውቀዋል ምን አላወቁም የሚለውን በወረቀት የሚያሰፍሩበት የተማሩት ሚዛን ላይ ወጥቶ የሚመዘንበት እውቀታቸው የሚለካበት ማጠቃለያ ምዘና መሆኑን ገልጸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ሁሉም ከክፍል ወደ ክፍል በሚዛን የሚዘዋወሩበት የሥርዓተ ትምህርት ሒደት መልካም ጅማሮ መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱም ከአራቱም አቅጣጫ ከ168 ሰንበት ትቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች እየተመዘኑ መሆናቸውን አሳውቀው፤ በስተመጨረሻም ለተፈታኞች መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
በዕለቱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ፣ የሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራሉ ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል አባ ተክለ ብርሃን ደስታ እና የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ እና የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች በተገኙበት በሀገረ ስብከት ደረጃ የመክፈቻ መርሐግብር ተከናውኗል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ እንደተናገሩት የሰንበት ት/ቤት ታዳጊዎች እና ሕፃናት ላይ መሥራት የነገ ቤተክርስትያንን ዛሬ ላይ ሆኖ መገንባት ነው ትውልድ ላይ መሥራት ቤተክርስትያንን ለቀጣይ ዘመን ማሻገር መሆኑን ጠቅሰው በሰንበት ት/ቤት እየተተገበረ ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በትኩረት ሊያግዙ እንደሚገባ በመግለጽ፤ በተለይም ሰበካ ጉባኤያት በየገዳማት እና አድባራቱ አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት ታሪካዊ ሐላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላእከ ኄራን መንክር ግርማ በበኩላቸው ተመዛኞች ዓመቱን ሙሉ በሰንበት ት/ቤቶች ሲማሩ መቆየታቸውን አስታውሰው በዛሬው ዕለት ከ168 ሰንበት ት/ቤቶች የተውጣጡ 14,800 የሚሆኑ ተመዛኞች የተፈተኑ ሲሆን፤ በሁሉም የመፈተኛ ጣብያዎች ፈተናዎቹ መሰጠታቸውን እንዲሁም የቋንቋ እና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች አስተርጓሚ እና አንባቢ ተመድቦላቸው እንደተፈተኑ በተጨማሪም የሰባቱም ክፍለ ከተማ አንድነት ጽ/ቤት እና ትምህርት ክፍሎች በየክፍለ ከተሞቻቸው ያሉ ተፈታኞችን የክትትል ጣቢያዎች አዘጋጅተው በጥሩ መልኩ ያስተባበሩ መሆናቸውን የክፍለከተማ ቤተክህነት ሐላፊዎችም በተመደቡበት ጣቢያ በመገኘት በጸሎት በመክፈት እና ጉብኝት በማድረግ ፤ የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎችም በጸሎት በመክፈት እና አስፈላጊ ድጋፍ በመስጠት ለመርሐ ግብሩ መሳካት ሁሉም የበኩላቸውን ተወጥተዋል።
በመጨረሻም የክፍለ ከተማ አስተባባሪዎቹ ከየፈተና ጣብያዎች የተሰበሰቡ የፈተና ወረቀቶችን ከቀኑ 9:00 ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከቱ አንድነት ትምህርት ክፍል አድርሰዋል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
+9
የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኞች መምህራን ሥልጠና ተጀመረ
(ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 07 2017 ዓ.ም
የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኝ መምህራን ሥልጠና በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ። በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይም አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የተገኙ ሲሆን ብፁዕነታቸው "እነሆ ጊዜው ደረሰ" በሚል መነሻ ቃለ ወንጌል ፣ አባታዊ ምክርና ቃለ ምዕዳን ለሰልጣኝ መምህራኑ አስተላልፈዋል። "እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትን ቃል መነሻ በማድረግ የማደራጃ መምሪያው ሐላፊ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በዛሬው የመክፈቻው መርሐ ግብር ላይ ሰልጣኞች በሚኖራቸው ቆይታ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቶ የመክፈቻ መርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው በዛሬው ዕለት በምሽት የሰንበት ት/ቤቶች መዋቅራዊ አደረጃጀትን በሚመለከት የሚቀጥል ሲሆን እስከ ሐምሌ 20 ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነትን ፣ የተለያዩ ክህሎትን የሚያዳብሩ እንዲሁም በሥርዓተ ትምህርቱ ላይ ትኩረት ያደረጉ ከ15 በላይ ሥልጠናዎችን የሚያገኙ ይሆናል። ሥልጠናውን ከ30 ሀገረ ስብከት የተወጣጡ 213 መምህራን የሚወስዱ ይሆናል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
"በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።" ዘፍ 18:1
እንኳን ለስጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ መታሰቢያ ብበሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 7 በዚህች ዕለት ቅድስት ሥላሴ በአብርሃም ቤት በመግባት በአንድነትና በሦስትነት ክብሩ የተገለጠለጡት ዕለት ነው!
መልካም በዓል!
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
ከየሀገረ ስብከቱ ለተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት መምህራን የክረምት የአሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ።
(ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሰኔ 25 2017 ዓ.ም
የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በዓመቱ መጨረሻ ከየሀገረ ስብከቱ ለተውጣጡ መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በማዘጋጀት አሠልጥኖ ወደየ ሀገረ ስብከታቸው ለአገልግሎት የማሰማራት ሥራ በየዓመቱ ሲያከናውን ቆይቷል። በዘንድሮም ዓመት ከ23 ሀገረ ስብከት በላይ ለተውጣጡና መመዘኛውን ለሚያሟሉ ከ200 በላይ ሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አንድነቱ አስታውቋል።
ሥልጠናው የሚሰጠው በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ ሲሆን ሠልጣኞች በቆይታቸው በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ዕውቀትን የሚያጎለብቱ፣ የግንዛቤ ለውጥ የሚያመጡ፣ ክህሎታቸውንም የሚያዳብሩ ሥልጠናዎች እንደሚሰጣቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በሥርዓተ ትምህርት ትግበራው ሰፊ ሥራ እንደሚሠሩ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታውቋል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
+6
በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሰከታተሉ ለነበሩት የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሰንበት ተማሪዎች የናሙና (ሞዴል) ፈተና ተሰጠ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሰኔ 23 2017 ዓ.ም
የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በትግበራ ላይ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ለተማሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የናሙና (የሞዴል ) ፈተና እሑድ ሰኔ 22 ቀን ሰጥቷል።
ለምዘና የቀረቡ የየአጥቢያው ሰንበት ተማሪዎች በ2015 ዓ.ም በሀገረ ስብከት ደረጃ የሚዘጋጀውን የ10ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱና ከክፍል ክፍል ተሸጋግረው ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና የደረሱ ተማሪዎች መሆናቸውን አንድነቱ አስታውቋል። የሙከራ ፈተናው በአዲስ አበባ እና በጉራጌ ሀገረ ስብከት በአጠቃላይ በ12 አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች የተሰጠ ሲሆን የማጠቃለያ ፈተናውም ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/category/ዜና/ማስታወቂያ
የሦስት ወር የክረምት ፕሮጀክት ሥራ ማስታወቂያ
፩. ለሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት የትግሪኛ ትርጉም ባለሙያ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️ በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች
▶️ በሰንበት ት/ቤት በማስተማር መምህርነት ልምድ ያለው
▶️ቢያንስ በሰንበት ት/ቤት የሚሰጡ ትምህርቶችን ያጠናቀቀ/ች
▶️በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ/ች
▶️የኮምፒወተር አጠቃቀም መሠረታዊ ዕውቀት ያለው/ያላት
፪. ለሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት የእንግሊዝኛ ትርጉም ባለሙያ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️ በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች
▶️ በሰንበት ት/ቤት በማስተማር መምህርነት ልምድ ያለው
▶️ቢያንስ በሰንበት ት/ቤት የሚሰጡ ትምህርቶችን ያጠናቀቀ/ች
▶️በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ/ች
▶️የኮምፒወተር አጠቃቀም መሠረታዊ ዕውቀት ያለው/ያላት
፫. የሥልጠና አስተባባሪ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️ በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች
▶️ በሰንበት ት/ቤት በማስተማር መምህርነት ልምድ ያለው
▶️ በሰንበት ት/ቤት አሰልጣኝነት ልምድ ያለው/ያላት
▶️በመምህርነትና በአሰልጣኝነት ስልጠና የወሰደ
▶️በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ/ች
▶️የኮምፒወተር አጠቃቀም መሠረታዊ ዕውቀት ያለው/ያላት
፬. የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️በሰንበት ት/ቤት እና በግቢ ጉባኤያት ያገለገለ/ለች
▶️በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ፣ ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/ች
፭. የግራፊክስ ዲዛይን ባለሙያ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ያገለገለ/ለች
▶️በሰንበት ት/ቤት ሥነ ጽሑፍና ሥነ ጥበባት፣ መዝሙር፣ ሚዲያ ክፍሎች ያገለገለ/ለች
▶️በዘርፉ ስልጠና የወሰደ እና ፍላጎት ያለው/ያላት
▶️በዘርፉ ሙያ ወይም ተመሳሳይ የተመረቀ/ች
፮. የሥዕል ባለሙያ
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ያገለገለ/ለች
▶️በሰንበት ት/ቤት ሥነ ጽሑፍና ሥነ ጥበባት፣ መዝሙር፣ ሚዲያ ክፍሎች ያገለገለ/ለች
▶️በዘርፉ ስልጠና የወሰደ እና ፍላጎት ያለው/ያላት
▶️በዘርፉ ሙያ ወይም ተመሳሳይ የተመረቀ/ች
▶️ከምፒዩተር ዕውቀት ያለው/ያላት
፯. ዳታ ኢንኮደር
ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ
▶️በሰንበት ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ያገለገለ/ለች
▶️በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የተመረቀ/ች
ለኹሉም የሥራ መስኮች፡-
✳️ ጾታ አይለይም፣
✳️የስራ ቦታ:- አዲስ አበባ፣
✳️የፕሮጀክቱ የቆይታ ጊዜ ከሐምሌ 1/2017 እስከ መስከረም 30/2018
አመልካቾች ሊያሟሉዋቸው የሚገቡ መስፈርቶች፡-
✳️ የሰ/ት/ቤት አባል የሆነ/የሆነች ብቻ፣
✳️ በአባልነት ከተመዘገቡበት አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት የአባልነት ማረጋገጫ ማቅረብ ፣
ለመመዝገብ ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) በመጫን የተዘጋጀውን የመመዝገቢያ ቅጽ እስከ ሰኔ 26/2017 ዓ/ም ድረስ ሞልተው ይላኩ።
👉 https://eotc-gssu.org/a/category/ዜና/ማስታወቂያ
+9
በሀገረ ሰብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማካኝነት ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የማጠቃለያ ፈተና ተጠናቀቀ::
በምዕራብ ሀረርጌ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማካኝነት በርዕሰ ከተማው ባሉ አድባራትና በጡሎ ዶባ ወረዳ በምትገኘው በሂርና ሁለቱ አድባራት በአዲሱ የሰ/ት/ቤት ሥርዓተ ት/ት ለ1ዓመት በትምህርተ ሃይማኖት፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ በምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ፣ በቤተክርስቲያን ታሪክ ፣ በክርስቲያናዊ ሥነ- ምግባርና በግዕዝ ትምህርት በአፋን ኦሮሞና በአማርኛ ሲያስተምራቸው ለነበሩና ትምህርታቸውን ላጠናቀቁ የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ2ት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ፈተና የተጠናቀቀ ሲሆን ብፁዕ አባታችን አቡነ እንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በፈተናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት ተፈታኝ ተማሪዎችን በማበረታታ ሃይማኖታቸውና ቤተክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ ፣ በፍቅርና በቅንነት እንዲያገለግሉ አባታዊ ምክርና መመሪያ በመስጠት አጠናቀዋል። እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ቆሞስ አባ ፍቅረ ዮሐንስ ብርሀኑ የማደራጃው ሐላፊ መጋቤ ሥርዓት ዘነበ ብርሀኑ የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ኃላፊዎች የሰ/ት/ቤት አንድነት በቦታው በመገኘት ተማሪዎችን አበረታተው ምክር እና ተግሳጽ ሰተው በሰላም ተጠናቋል ።
ዘገባው የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
