Fidel Tutorial (ፊደል የጥናት አገልግሎት)
الذهاب إلى القناة على Telegram
* Professional Tutorial service * Book online or via phone * Kg to university * Flashcards * online Tutorials Contact +251979795154 +251979795468 Youtube: https://www.youtube.com/@FidelTutorial To become a tutor join https://t.me/fideltutores
إظهار المزيد2 888
المشتركون
-324 ساعات
-97 أيام
-3230 أيام
أرشيف المشاركات
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ እና የ3ኛ ዓመት ተማሪዎች አድማ በመምታት ትምህርት ማቋረጣቸውን ሰምተናል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዓመት ተማሪዎች ያለ አግባብ የምንመረቅበት ጊዜ በተለይም የ2013 ባች ተማሪዎች እስከ ሁለት ሴሚስተር ያህል ማለትም ከመመረቂያ ጊዜያችን አንድ ዓመት ዘግይተን እንድንመረቅ ዩንቨርሲቲው ወስኗል በሚል ምክንያት ተቃውሟቸውን ክፍል ባለመግባት እየገለፁ እንደሆነ ከተማሪዎቹ ያግኘነው መረጃ ያመለክታል።
በጉዳዩ ላይ ግልፅ ውይይት ለማድረግ ኮሚቴ አዋቅረን ጥረት ብናደርግም ዩንቨርሲቲው የኛን ጥያቄ ከመስማት ይልቅ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አካላትን በማሰማራት ማስፈራሪያ እያደረሰብን ነው ሲሉ ከሰዋል።
ቤተሰቦቻችን ከኛ ብዙ ነገር ይጠብቃሉ የሚሉት ተማሪዎቹ በሌሎች ዩንቨርሲቲዎች ከሚገኙ ጓደኞቻችን እኩል መመረቅ ባለብን ካላንደር መሰረት ተመርቀን ተወዳዳሪ እንሁን ማለታችን እንደ ስህተት ተወስዶ አግባብነት ያለው ጥያቄያችን በጉልበት ሊታፈን አይገባም ብለዋል።
#share 👉@News_for_Students
#share 👉@News_for_Students
#share 👉@News_for_Students
AFTER SCHOOL PROGRAM WITH FIDEL.
fidel tutorial has invited every child to participate in the following activities
-football
-basketball
-swimming
-language
with
-easy learning
-fun Activities
-new experience
-professionals
contact us
0979795154/0979795468.
በትግራይ ክልል የመማር ማስተማር ሂደትን በቀጣዮቹ አምስት ወራት ለማስጀመር እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በትግራይ ክልል ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል።
በክልሉ የትምህርት ሥራን ለማስጀመር የሚያስችሉ ተግባራትን ለማከናወን እቅዶች መያዛቸውንና ዝግጅት መጀመሩን በሚኒስቴሩ የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎቶች ዴስክ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ለኢፕድ ተናግረዋል።
በክልሉ የሰው ሀብት የማደራጀት፣ የፈረሱ ትምህርት ቤቶችን የመጠገንና ግብዓት የማሟላት እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እንደሚደረግ ኃላፊው አመልክተዋል።
በትግራይ ክልል የመማር ማስተማር ሥራው ሲጀመር ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ እንደሚሆነ የጠቆሙት ኃላፊው፤ በትግራይ ክልል የተማሪዎች ምገባ ለማስጀመር አጋር አካላት እና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
@tikvahuniversit
ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የሁሉም ክልል ተማሪዎች በሁለተኛው ዙር ለፈተናው እንዲቀመጡ የተለየ ሲሆኑ እነርሱም፦
• የመጀመሪያ ዙር ፈተናን በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣
• በህግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው በነበረው መፈተኛ ሁኔታ ለመፈተን ያልቻሉ፣
• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣
• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘና ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣
• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣
• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣
• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!
Do you need help with your Degree?
We provide the best Assistants for your
-BA
-BSC
-MBA
-MSC Degree.
contact us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
ዕድሜያቸው ከ 17-21 ለሆኑ ተማሪዎች የተዘጋጀ ልዩ ሃካቶን (Hackaton)
በዚህ ውድድር መሳተፍ የሚፈልግ ተማሪ ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ መመዝገብ ይችላል።
ምዝገባው በነፃ ሲሆን ከህዳር 30 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ይቆያል።
ከእንድ እስከ ሦሥት ለሚወጡ ተማሪዎች ልዩ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
ለመመዝገብ 👉 hackathon.kibur.net
ለበለጠ መረጃ፦ 0113698558
0904848586
www.kibur.net
https://t.me/kiburcollege
ይመዝገቡ!
አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በሚቀጥለው ሳምንት አርብ 7:30 የአባልነት ምዝገባ ይጀምራል።
ይህም ለተጠቃሚዎች የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።
መጻሕፍትን በነጻ መዋስ እንዲሁም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ጆርናሎች እና ፅሁፎችን በኦንላይን ማግኘት አባል በመሆንዎ ከሚያገኟቸው ጥቅሞች መካከል ይጠቀሳሉ።
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሙሉ ወጪ በመሸፈን የሚሰጥ መሆኑንም የቤተ-መጻሕፍቱ አስተዳዳሪ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
Fidel tutorial
we can help you with math!
from KG to University
Contact Us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
How was your 1st semester grade?
which subjects can we help you with?
-Math
-Physics
-General Science
-Chemistry
-Or which Subject?
Call us
fidel Tutorial
0979795154/0979795468
የመውጫ ፈተናን በተመለከት ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና የውይይት መድረክ ተካሄደ።
**
በዚህ አመት ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናን በተመለከት ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሁም የስነ-ልቡና ግንባታ ስልጠና እና የውይይት መድረክ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስነ-ልቡና ምሁራን የሆኑ መምህራን እና የኮሌጅ ዲኖች በተገኙበት ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።
በመድረኩ መክፈቻ ስለመውጫ ፈተናው ሰፋ ያለ ማብራሪያ በማቅረብ ስልጠና የሰጡት የስነ-ልቦና ሙህር የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ የመውጫ ፈተና የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማንሳት ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ለተማሪዎች አስረድተዋል። ከነዚህ ጥቅሞች ውስጥ የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣ ተወዳዳሪ የሆነ ዜጋ ማፍራት እና እራስን ለመፈተሽ እንደሚያግዝ እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ የሆኑ ጥቅሞችን በመጥቀስ አስረድተዋል። አክለውም ተማሪዎች ፍራታቸውን አስወግደው ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመቀጠልም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የህግ ትምህርት ክፍል ዲኖች እስከ አሁን ለጤና እና ለህግ ተማሪዎች ይሰጥ በነበረው የመውጫ ፈተና ያላቸውን ልምድ ለተማሪዎች አካፍለዋል። ዲኖቹ አያይዘውም በሁለቱም ኮሌጆች እየተሰጠ ባለው የመውጫ ፈተና ተሞክሮው እንደሚያሳየው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተከታታይ ዓመታት ባስመዘገቡት ክፍተኛ ውጤት ዩኒቨሲቲው በደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ ሲካተት የቆየ መሆኑን አስታውሰው የነሱን አርአያ በመከተል ይህንን ልምድ ማስቀጠል እንደሚገባ እንዲሁም ከዘንድሮ ተመራቂዎችም ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቁ ገልፀዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ዲን መምህር ቃኘው ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ትምህርት ቤት የመውጫ ፈተና ሲጀመር የነበራቸውን ትዝታ ለተማሪዎቹ ያስታወሱ ሲሆን ተማሪዎች ስጋታቸውን አስወግደው ዝግጅቱ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ በማሳሰብ አሁንም ለመዘጋጀት በቂ ጊዜ እንዳላቸው አስታውሰዋል፡፡
በመድረኩ የተገኝተው ተማሪዎቹን ያወያዩት የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብቴ ዱላ እና የአካዳሚክ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ካሳሁን አቤ ስለመውጫ ፈተና ከተማሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ሀብቴ በበኩላቸው ተማሪዎች ለፈተናው ያላቸውን አሉታዊ አመለካከት በመቀየር ሰፋ ያለውን አውንታዊ አንድምታ መገንዘብ እንደሚያሻ ተናግረዋል፡፡ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለፈተናው ዝግጅት በቻለው አቅም ሁሉ እንደሚያግዛቸው እና ከጎናቸው በመሆን እንደሚረዳቸው ቃል ገብተዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ተማሪዎች ከራሳቸው የሚጠበቀውን ብቻ ካደረጉ የሚያስጨንቅ አንዳች ነገር እንደሌለ እንዲሁም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በመውጫ ፈተናዎች ላይ የነበረውን ውጤታማነት የዚህ አመት ተመራቂ ተማሪዎችም እንደሚያስቀጥሉ ባለሙሉ ተስፋ እንደሆኑ ገልፀዋል።
“ፈተናው ግቢ ላይ ከምትፈተኑት የተለየ ፈተና አይደለም” ሲሉ የገለፁት ረዳት ፕሮፈሰር ካሳሁን አቤ ፈተናው ጠቅላላ እውቀትን ያማከለ መሆኑን ገልፀው “አንድ ምግብ አብሳይ የሚያበስለውን ምግብ ለማዘጋጀት ምን እንደሚያስፈልገው በመጠየቅ ያንን ምግብ ለማብሰል ያለውን እውቀት እንደመገምገም ነው” ማለት በምሳሌ አስረድተዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ሚካኤል ያቦነሽ ፈተናው ከመሰጠቱ በፊት ማንኛውም ተማሪ በዩኒቨርሲቲው እና በህብረቱ የሚዘጋጁ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል፣ እርስ በእርስ በመተጋገዝ እንዲሁም በተናጠል በማንበብ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
እነሆ በውስጧ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የያዘችው ወርሃዊዋ የፊደል መፅሄት ቀኗን ጠብቃ ወደ እናንተ መጥታለች።
በውስጧ
-ትምህርት
-ቤተሰብ
-ልዩ ፍላጎት
-ሳይንስና ቴክኖሎጂ
-ፊደል ሜዲካል
-ፋሽን
-ምን አዲስ በኢትዮጵያ?
-ፊደል እንግዳ
-ፊደል በዚህ ወር
-ፊደል የመፅሀፍት ጥቆማ
-ፊደል የፊልም ጥቆማ
እነዚህንና ብዙ ጉዳዮችን አካታለች።
ተጋበዙልን!
እነሆ በውስጧ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የያዘችው ወርሃዊዋ የፊደል መፅሄት ቀኗን ጠብቃ ወደ እናንተ መጥታለች።
በውስጧ
-ትምህርት
-ቤተሰብ
-ልዩ ፍላጎት
-ሳይንስና ቴክኖሎጂ
-ፊደል ሜዲካል
-ፋሽን
-ምን አዲስ በኢትዮጵያ?
-ፊደል እንግዳ
-ፊደል በዚህ ወር
-ፊደል የመፅሀፍት ጥቆማ
-ፊደል የፊልም ጥቆማ
እነዚህንና ብዙ ጉዳዮችን አካታለች።
ተጋበዙልን!
እነሆ በውስጧ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የያዘችው ወርሃዊዋ የፊደል መፅሄት ቀኗን ጠብቃ ወደ እናንተ መጥታለች።
ተጋበዙልን!
#MoE
• መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር በተመሳሳይ ጊዜ ይሰጣል።
• 200, 000 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ እንደሚሰጥ የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ገልጸዋል።
መሪ ስራ አስፈጻሚው ኤባ ሚጀና ( ዶ/ር ) በጉዳዩ ዙሪያ በተዘጋጀ አውደጥናት ላይ እንደገለጹት መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር ለሁሉም ቅድመ መደበኛ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ ይሰጣል።
የመጀመሪያው ፈተና በሰኔ ወር ከተሰጠ በኋላ ቀጣዩ የመውጫ ፈተና ከ6 ወራት በኋላ እንደሚሰጥም ዶ/ር ኤባ አስረድተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰይድ መሀመድ በበኩላቸው ፈተናውን ለ200, 000 የመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፈተናው ለሁሉም ተማሪዎች በኦንላይን እንደሚሰጥ የጠቀሱት አቶ ሰይድ " ይህ የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የተሻለ አማራጭ በመሆኑ ነው " ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱም ሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው በተመሳሳይ ጊዜ በኦንላይን እንደሚሰጥ አውቀው ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቶ ሰይድ አሳስበዋል።
በመውጫ ፈተና ብቃትና የፈተና ኮርሶች ልየታና የተገቢነት ማረጋገጥ ዙሪያ በተዘጋጀው አውደጥናት ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ጉዳዩ የሚመለከታቸው መምህራን ተሳታፊ መሆናቸውም ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
(ትምህርት ሚኒስቴር)
Watch "የ 8ተኛ ክፍሉ ኮምፒዩተር ፕሮግራመር!" on YouTube
https://youtu.be/7UbIJORtJB8
