cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

اهدنا الصراط المستقيم

የአላህ ፍቃድ ከሆነ በዚህ ቻናል ውስጥ ጠቃሚ አስፈላጊና ወቅታዊ የሆኑ መረጃዎች በፅሁፍ እና በድምጽ የሚለቀቅበት ቻናል ነው قُل هذه سبيلي ادعو إلى الله على بصيرة انا ومن اتبعني وسبحان الله وما انا من المشركين 📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥 https://t.me/menhajalnebuwa

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
198
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-27 أيام
-530 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

.    قال تعالى : ﴿وَالْعَصْرِ۝إِنَّ الْإِنسَانَ لَفِي خُسْرٍ۝إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ۝﴾ [العصر : ١-٢-٣] قال الإمام العلامة السعدي     رحمه الله تعالى - : أقسم تعالى بالعصر، الذي هو الليل والنهار، محل أفعال العباد وأعمالهم أن كل إنسان خاسر، والخاسر ضد الرابح. والخسار مراتب متعددة متفاوتة : قد يكون خسارًا مطلقًا، كحال من خسر الدنيا والآخرة، وفاته النعيم واستحق الجحيم. وقد يكون خاسرًا من بعض الوجوه دون بعض، ولهذا عمم الله الخسار لكل إنسان، إلا من اتصف بأربع صفات : الإيمان بما أمر الله بالإيمان به ولا يكون الإيمان بدون العلم، فهو فرع عنه لا يتم إلا به. والعمل الصالح، وهذا شامل لأفعال الخير كلها، الظاهرة والباطنة، المتعلقة بحق الله وحق عباده الواجبة والمستحبة. والتواصي بالحق، الذي هو الإيمان والعمل الصالح، أي : يوصي بعضهم بعضًا بذلك، ويحثه عليه ويرغبه فيه. والتواصي بالصبر على طاعة الله وعن معصية الله، وعلى أقدار الله المؤلمة. فبالأمرين الأولين، يكمل الإنسان نفسه، وبالأمرين الأخيرين يكمل غيره، وبتكميل الأمور الأربعة، يكون الإنسان قد سلم من الخسار، وفاز بالربح [العظيم]. تفسير السعدي - صـ(٩٣٤) https://t.me/+R1-lDgxj3QMfMFf9 https://t.me/+R1-lDgxj3QMfMFf9
إظهار الكل...
አቂዳህን ከቁርዐን ከሀዲስ በሰለፎች አረዳድ ያዝ

من يرد الله به خيرا يفقهه في الدين رواه ابخاري ومسلم አላህ መልካም የሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል ቡሀሪና ሙስሊም

ሀብትን በኒካሕ መፈለግ
إظهار الكل...
4_6035314600121996017.m4a76.28 MB
00:54
Video unavailableShow in Telegram
🇸🇦☝️ هل استقبال القبلة شرط في الأضحية... 🇸🇦 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى
إظهار الكل...
1.20 MB
✅ ሰበር የምስራች ውድ የኢስላም ብርሃን የእውቀት ማእድ ቤተሰቦቻችን ዛሬ ማታ በኢትዮዽያ አቆጣጠር ከምሽቱ 3 : 00 ላይ ከዒደል አድሓ ህግጋት ጋር በተያያዙ ነጥቦች ላይ በውዱ ሸይኻችን አሽሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ሙሐመድ ፕሮግራም ይዘንላችሁ የምንቀርብ መሆኑን ስናበስራች በታላቅ ደስታ ነው ። https://t.me/boost/YeIslam_brhan_ye_ewket_maed
إظهار الكل...
የኢስላም ብርሃን የዕውቀት ማዕድ

Boost this group to help it unlock additional features.

🔷 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል ሶስት ነብዩላሂ ኢብራሂም ዳዕዋቸውን ከንግግር ወደ ተግባር ለመቀየር ወሰኑ ። ለጣኦት አምላኪያን የሚያመልኩዋቸው ጣኦታት ያልተገዛቸውን መጎዳትም ሆነ የተገዛቸውን መጥቀም እንደማይችሉ ከዚህም በላይ ራሳቸውንም ከጥቃት የማይከላከሉ መሆናቸውን ማሳየት እንዳለባቸው አመኑ ። የባአላቸው ቀን ጠብቀው ሁሉም ተሰባስበው ወደ በአሉ ሲሄዱ ነብዩላሂ ኢብራሂም መጥረጢያቸውን ተሸክመው ወደ ጣኦቶቻቸው አመሩ ። የተለያየ ስለት እንዲሁም ምግብም አጠገባቸው ተቀምጦ አዩ ‼ አትበሉም እንዴ እያሉ ያናግሯቸው ጀመር መልስ የለም ። ትልቁን ብቻ አስቀርተው ጣኦታቱን ፈላልጠው ጨረሱ ። ከዛም መጠረቢያውን በትልቁ ጣኦት ላይ አስቀምጠው ጥለው ሄዱ ። ጣኦትአምላኪያኖቹ ከባአል ማክበሪያ ሲመለሱ በጣኦቶቻቸው ላይ የተሰራውን ጉድ አዩ ። ስለጣኦቶቻቸው ደካማነትና ስለራሳቸው ዐቅለቢስነት ከማሰብ ይልቅ በአማልክቶቻችን ላይ ማነው ይህን የሰራው እያሉ መጠያየቅ ጀመሩ ። ኢብራሂም የሚባል ነው ተባለ ፈልገው ጠየቋቸው ። እሷቸውም ትልቁን ጠይቁት የሚናገር ከሆነ ብለው መለሱ ። ይህን ክስተት ቁርኣን በሚቀጥለው የአል ንቢያ ምእራፍ ከ59 – 67 በዝርዝር ያስቀምጥልናል : – قَالُوا مَن فَعَلَ هَٰذَا بِآلِهَتِنَا إِنَّهُ لَمِنَ الظَّالِمِينَ «በአማልክቶቻችን ይህንን የሠራ ማነው እርሱ በእርግጥ ከበደለኞች ነው» አሉ፡፡ قَالُوا سَمِعْنَا فَتًى يَذْكُرُهُمْ يُقَالُ لَهُ إِبْرَاهِيمُ «ኢብራሂም የሚባል ጎበዝ (በመጥፎ) ሲያነሳቸው ሰምተናል» ተባባሉ፡፡ قَالُوا فَأْتُوا بِهِ عَلَىٰ أَعْيُنِ النَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَشْهَدُونَ «ይመሰክሩበት ዘንድ በሰዎቹ ዓይን (ፊት) ላይ አምጡት» አሉ፡፡ قَالُوا أَأَنتَ فَعَلْتَ هَٰذَا بِآلِهَتِنَا يَا إِبْرَاهِيمُ «ኢብራሂም ሆይ! በአማልክቶቻችን ይህንን የሠራህ አንተ ነህን» አሉት፡፡ قَالَ بَلْ فَعَلَهُ كَبِيرُهُمْ هَٰذَا فَاسْأَلُوهُمْ إِن كَانُوا يَنطِقُونَ «አይደለም ይህ ታላቃቸው ሠራው፡፡ ይናገሩም እንደ ኾነ ጠይቋቸው» አለ፡፡ فَرَجَعُوا إِلَىٰ أَنفُسِهِمْ فَقَالُوا إِنَّكُمْ أَنتُمُ الظَّالِمُونَ ወደ ነፍሶቻቸውም ተመለሱ፡፡ «እናንተ (በመጠየቃችሁ) በዳዮቹ እናንተው ናችሁም» ተባባሉ፡፡ ثُمَّ نُكِسُوا عَلَىٰ رُءُوسِهِمْ لَقَدْ عَلِمْتَ مَا هَٰؤُلَاءِ يَنطِقُونَ ከዚያም በራሶቻቸው ላይ ተገለበጡ፡፡ «እነዚህ የሚናገሩ አለመኾናቸውን በእርግጥ ዐውቀሃል፤» (አሉ)፡፡ የዚህን ጊዜ ጥሩ መግቢያ አገኙ ። ጠንከር ባለ ሁኔታ ዳዕዋ አደረጉላቸው ። ይህንንም ቁርኣን በዛው ምእራፍ በሚቀጥሉት አንቀፆች ላይ ይነግረናል :– قَالَ أَفَتَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَنفَعُكُمْ شَيْئًا وَلَا يَضُرُّكُمْ «ታዲያ ለእናንተ ምንም የማይጠቅማችሁንና የማይጎዳችሁን ነገር ከአላህ ሌላ ትገዛላችሁን» አላቸው፡፡ أُفٍّ لَّكُمْ وَلِمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ أَفَلَا تَعْقِلُونَ «ፎህ! ለእናንተ ከአላህ ሌላ ለምትገዙትም ነገር፤ አታውቁምን» (አለ)፡፡ ጣኦት አምላኪያኑም በመረጃ ሲሸነፉ ሐቅን ከመቀበል ይልቅ ወደ ሀይል ተሸጋገሩ ። ይህ የሁሉም የባጢል ተከታዮች ባህርይ ነው ። መረጃ ሲያጡ ጡንቻን መረጃ ያደርጋሉ ‼ ። ኢብራሂምንም አቃጥሉ ጣኦቶቻችሁንም እርዱ አሉ ። ይህም እውነታ ቁርኣ በሚቀጥለው አንቀፅ ያስቀምጠዋል : – قَالُوا حَرِّقُوهُ وَانصُرُوا آلِهَتَكُمْ إِن كُنتُمْ فَاعِلِينَ «ሠሪዎች እንደ ኾናችሁ አቃጥሉት፡፡ አማልክቶቻችሁንም እርዱ» አሉ፡፡ (በእሳት ላይ ጣሉትም)፡፡ ዐቅለ ቢሶቹም ነብዩላሂ ኢብራሂምን ለማቃጠል ወሰኑ ። ጥፋታቸው ጣኦታትን ራቁ አላህን ብቻ ተገዙ ማለታቸው ነው ። በወቅቱ የነበረው መንግስት ግንብ ገንቡና እሳት አቀጣጥላችሁ እዛ ውስጥ ጣሉት ብሎ አዘዘ ። ይህን ክስተት ቁርኣን እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – قَالُوا ابْنُوا لَهُ بُنْيَانًا فَأَلْقُوهُ فِي الْجَحِيمِ «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ ፡፡ በመንግስት ትእዛዝ ከፍታው 30 ሜትር ጎኑ የተራራ ጫፍ የሚሆን ምሽግ ተገነባ ። ማንኛውም ህዝብ እንጨት እንዲሰበስብ ታዘዘ ። ሴት ወንድ ፣ አዋቂ ልጅ ሁሉም ወደ 40 ቀን አካባቢ ስራውን ትቶ መሰብሰብ ጀመረ ። በዚህ ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ክምር እሳት ተለኮሰበት ። ነበልባሉ ከሰማይ አሞራ ይጠልፍ ነበር ይባላል ። ጣኦት አምላኪያን ጉድ ተሰሩ ‼ ። ኢብራሂምን እንዴት በዚህ እሳት ይወርውሩ ? የሰው ሸይጣን መጥቶ ወስፈንጥር ( ምንጀኒቅ ) ዛሬ በዘመናዊ መልኩ መድፍ የሚባለው አይነት ማለት ነው እንዲሰሩና እዛ ላይ አድርገው እንዲወረውሩዋቸው ሐሳብ አቀረበ ። እንደተባሉት አደረጉ ። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ጅብሪል መጣ ምን ትፈልጋለህ አላቸው ? ነብዩላሂ ኢብራሂምም ካንተ ምንም አልፈልግም ። አላህ በቂዬ ነው ምን ያማረ መጠጊያ ነው አሉ ። ወዲያውም የአላህ እርዳታ መጣ ። አላህ እሳትን አናገረ ። ይንንም ቁርኣን እንዲህ ብሎ አረጋገጠው : – قُلْنَا يَا نَارُ كُونِي بَرْدًا وَسَلَامًا عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ الأنبياء ( 69 ) «እሳት ሆይ! በኢብራሂም ላይ ቀዝቃዛ፤ ሰላምም ሁኚ» አልን፡፡ فَأَرَادُوا بِهِ كَيْدًا فَجَعَلْنَاهُمُ الْأَسْفَلِينَ الصافات ( 98 ) በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው ፡፡ አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka
إظهار الكل...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

👉 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል ሁለት ነብዩላሂ ኢብራሂም አላህ ለትእዛዙ እጅ እንዲሰጡ ካዘዛቸው በኋላ ፍፁም ታዛዥነታቸውን ገልፀው ዳዕዋ ጀመሩ ። ማህበረሰባቸው አላህን አያውቅም ። ቤተሰቦቻቸው ጣኦት ያመልካሉ ያለባቸው ሀላፊነት ክብደት እረፍት አልሰጣቸውም ። ወደ አላህ መንገድ የመጣራቱን ሂደት ከጣኦት ቸርቻሪው አባታቸው መጀመር እንዳለባቸው ወሰኑ ። ወደ አባታቸውም ሄደው አባቴ ሆይ አላህ ሰዎች እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ልጣራ አዞኛል ። ዳዕዋዬን ካንተ መጀመር መረጥኩኝ እነዚህ የማይጠቅሙና የማይጎዱ የማይሰሙና የማያዩ ጣኦታትን ትተህ አላህን ብቻ ተገዛ እያሉ ወደ አላህ አምልኮት መጣራታቸውን አላህ በሱረቱል መርየም ከ41 – 45 ድረስ በሚከተለው መልኩ ይነግረናል : – وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِبْرَاهِيمَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صِدِّيقًا نَّبِيًّا በመጽሐፉ ውስጥ ኢብራሂምንም አውሳ ፡፡ እርሱ በጣም እውነተኛ ነቢይ ነበርና ፡፡ إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ يَا أَبَتِ لِمَ تَعْبُدُ مَا لَا يَسْمَعُ وَلَا يُبْصِرُ وَلَا يُغْنِي عَنكَ شَيْئًا ለአባቱ ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አባቴ ሆይ! የማይሰማንና የማያይን ከአንተም ምንንም የማይጠቅምህን (ጣዖት) ለምን ትግገዛለህ يَا أَبَتِ إِنِّي قَدْ جَاءَنِي مِنَ الْعِلْمِ مَا لَمْ يَأْتِكَ فَاتَّبِعْنِي أَهْدِكَ صِرَاطًا سَوِيًّا «አባቴ ሆይ! እኔ ከዕውቀት ያልመጣልህ ነገር በእርግጥ መጥቶልኛልና ተከተለኝ ፡፡ ቀጥተኛውን መንገድ እመራሃለሁና ፡፡ يَا أَبَتِ لَا تَعْبُدِ الشَّيْطَانَ ۖ إِنَّ الشَّيْطَانَ كَانَ لِلرَّحْمَٰنِ عَصِيًّا «አባቴ ሆይ! ሰይጣንን አትግገዛ ፡፡ ሰይጣን ለአልረሕማን አመጸኛ ነውና ፡፡ يَا أَبَتِ إِنِّي أَخَافُ أَن يَمَسَّكَ عَذَابٌ مِّنَ الرَّحْمَٰنِ فَتَكُونَ لِلشَّيْطَانِ وَلِيًّا «አባቴ ሆይ ! እኔ ከአልረሕማን ቅጣት ሊያገኝህ ለሰይጣንም ጓደኛ ልትኾን እፈራለሁ ፡፡» ነብዩላሂ ኢብራሂ በጣም አስደናቂና አስተማሪ በሆነ መልኩ ክብር በተሞላበትና እኔ አዋቂ ነኝ የሚል የኩራት ስሜት በሌለበት የሚገርም አካሄድ አባቴ ሆይ እያሉ ላደረጉት ለዚህ ጥሪ ከአባታቸው የተቸሩት ምላሽ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነበር ። የአባታቸው ምላሽ ምን እንደነበረ አላህ ሲነግረን እዛው በሱረቱል መርየም 46ኛው አንቀፅ እንዲህ ይለናል : – قَالَ أَرَاغِبٌ أَنتَ عَنْ آلِهَتِي يَا إِبْرَاهِيمُ ۖ لَئِن لَّمْ تَنتَهِ لَأَرْجُمَنَّكَ ۖ وَاهْجُرْنِي مَلِيًّا (አባቱም) «ኢብራሂም ሆይ! አንተ አምላኮቼን ትተህ የምትዞር ነህን ባትከለከል በእርግጥ እወግርሃለሁ ፡፡ ረዥም ጊዜንም ተወኝ» አለ ፡፡ ይሁን እንጂ ነብዩላሂ ኢብራሂም በአባታቸው መልስ ተስፋ ቢቆርጡም ሳይበሳጩ የሰጡት መልስ በዛው ምእራፍ 47 ኛው አንቀፅ እንዲህ የሚል መሆኑ ተነግሮናል : – قَالَ سَلَامٌ عَلَيْكَ ۖ سَأَسْتَغْفِرُ لَكَ رَبِّي ۖ إِنَّهُ كَانَ بِي حَفِيًّا «ደህና ኹን ፡፡ ወደፊት ከጌታዬ ምሕረትን እለምንልሃለሁ ፡፡ እርሱ ለኔ በጣም ርኅሩኅ ነውና» አለ ፡፡ ነብዩላሂ ኢብራሂም ዳዕዋቸው አባታቸው ዘንድ ፍሬ ባለማፍራቱ ስሜታቸው ቢጎዳም የዳዕዋ ጉዞዋቸውን ከመቀጠል አላገዳቸውም ። በዘመኑ ወደ ነበረው ነምሩድ ወደ ሚባለው ንጉስ ሄደው ዳዕዋ ማድረግ ጀመሩ የነመምሩድ ባለሟሎች ጌታችን ነምሩድ ነው የሚል መልስ ሲሰጡ ነብዩላሂ ኢብራሂም በቆራጥነትና በአላህ ላይ በመመካት ነምሩድ ጌታ እንዳልሆነና የሁላቸውም ፈጣሪ አላህ መሆኑን አስመልክቶ ያደረጉትን ዳዕዋ አላህ ሲነግረን እንዲህ ይለናል : – قَالَ بَل رَّبُّكُمْ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ الَّذِي فَطَرَهُنَّ وَأَنَا عَلَىٰ ذَٰلِكُم مِّنَ الشَّاهِدِينَ «አይደለም ጌታችሁ የሰማያትና የምድር ጌታ ያ የፈጠራቸው ነው ፡፡ እኔም በዚህ ላይ ከመስካሪዎቹ ነኝ» አለ ፡፡ የዚህን ጊዜ ነምሩድ ጌታ መሆኑን ሞገተ ። ነብዩላሂ ኢብራሂምም አላህ ማለት ምን አይነት ጌታ እንደሆነና የነምሩድን ደካማነት ያስመሰከሩበትን መረጃ አላህ በሱረቱል በቀራ 258 ኛው አንቀፅ ላይ ይነግረናል : – أَلَمْ تَرَ إِلَى الَّذِي حَاجَّ إِبْرَاهِيمَ فِي رَبِّهِ أَنْ آتَاهُ اللَّهُ الْمُلْكَ إِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّيَ الَّذِي يُحْيِي وَيُمِيتُ قَالَ أَنَا أُحْيِي وَأُمِيتُ ۖ قَالَ إِبْرَاهِيمُ فَإِنَّ اللَّهَ يَأْتِي بِالشَّمْسِ مِنَ الْمَشْرِقِ فَأْتِ بِهَا مِنَ الْمَغْرِبِ فَبُهِتَ الَّذِي كَفَرَ ۗ وَاللَّهُ لَا يَهْدِي الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ ወደዚያ አላህ ንግሥናን ስለሰጠው ኢብራሂምን በጌታው ነገር ወደ ተከራከረው ሰው አላየህምን ኢብራሂም «ጌታዬ ያ ሕያው የሚያደርግና የሚገድል ነው» ባለ ጊዜ «እኔ ሕያው አደርጋለሁ እገድላለሁም» አለ፡፡ ኢብራሂም፡- «አላህ ፀሐይን ከምሥራቅ በኩል ያመጣል (አንተ) ከምዕራብ በኩል አምጣት» አለው ፡፡ ያም የካደው ሰው ዋለለ ፤ (መልስ አጣ) አላህም በዳዮች ሕዝቦችን አይመራም ፡፡ ነምሩድ በዚህ መልኩ ማላገጥ ሲጀምር አላህ አዋርዶት ነብዩላሂ ኢብራምን በሐቅ ላይ የበላይ አድርጎ ተአምረኛው ጌታ ያ እኔ አምላክ ነኝ ሲል የነበረውን ነምሩድ አንድ ትንኝ በአፍንጫው ገብታ እራሱን እንኳን ከመከራ ማዳን እንደማይችል በማሳየት ለዘመናት ስታሰቃየው ቆይታ በዛው ፍፃሜው እንዲሆን አደረገው ። አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka
إظهار الكل...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

👉 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል አንድ የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ቁርኣን ላይ ቱክረት ከተሰጣቸው የነብያት ታሪክ ውስጥ በግንባር ቀደምትነት ይመደባል ። ታሪካቸው ቁርኣን ውስጥ በ17 ምእራፍ ወደ 69 ጊዜ ተጠቅሷል ። ይህ የሚያሳየው ታሪካቸው ምን ያክል አስፈላጊና ቁም ነገር አዘል መሆኑ ነው ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ዒራቅ ውስጥ ባቢል በሚባል ቦታ በጣኦት አምላኪ ማህበረሰብ ውስጥ ተወለዱ ። ከህብረተሰቡ ውስጥ ኮከብ የሚያመልክ ፣ ጨረቃ የሚያመልክና ፀሀይ የሚያመልክ እንዲሁም ከእንጨት የተሰራ ጣኦት የሚያመልክ ነበር ። አባታቸው ኣዘር ከእንጨት ጣኦት እየሰራ ይሸጥ ነበር ። እሳቸው በልጅነታቸው እርሻ ይሰሩ ነበር ። አባታቸው ጣኦት እያዞሩ እንዲሸጡላቸው ሲያዙዋቸው ተቀብለው መሬት ለመሬት እየጎተቱ የማይጠቅምና የማይጎዳ የሚገዛ እያሉ ያዞሩ ነበር ። በዚህም ምክንያት ማንም የሚገዛ ስለማያገኙ ይዘውት ይመለሳሉ ። እድሜያቸው 13 አመት ሲሞላቸው ፈጣሪዬ ማን ነው ብለው ማሰብ ጀመሩ ። ቤተሰቦቻቸውና ማህበረሰቡ በሚያመልኩት ነገር ደስተኛ አልነበሩም ። ለብቻቸው ሲሆኑ ማን ነው የፈጠረኝ እያሉ ይብሰለሰላሉ ። በዚህ ስሜት ውስጥ ሆነው ከቤት ወጥተው ወደ ሰማይ በሚያዩበት ጊዜ የተከሰተውን አላህ ሲነግረን በአል አንዓም ምእራፍ ከ75 – 79 ድረስ እንዲህ ይለናል : – وَكَذَٰلِكَ نُرِي إِبْرَاهِيمَ مَلَكُوتَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَلِيَكُونَ مِنَ الْمُوقِنِينَ እንደዚሁም ኢብራሂምን (እንዲያውቅና) ከአረጋጋጮቹም ይኾን ዘንድ የሰማያትንና የምድርን መለኮት አሳየነው ፡፡ فَلَمَّا جَنَّ عَلَيْهِ اللَّيْلُ رَأَىٰ كَوْكَبًا ۖ قَالَ هَٰذَا رَبِّي ۖ فَلَمَّا أَفَلَ قَالَ لَا أُحِبُّ الْآفِلِينَ ሌሊቱም በእርሱ ላይ ባጨለመ ጊዜ ኮከብን አየ ፡፡ «ይህ ጌታዬ ነው» አለ ፡፡ በጠለቀም ጊዜ ፡- «ጠላቂዎችን አልወድም» አለ ፡፡ فَلَمَّا رَأَى الْقَمَرَ بَازِغًا قَالَ هَٰذَا رَبِّي ۖ فَلَمَّا أَفَلَ قَالَ لَئِن لَّمْ يَهْدِنِي رَبِّي لَأَكُونَنَّ مِنَ الْقَوْمِ الضَّالِّينَ ጨረቃንም ወጪ ኾኖ ባየ ጊዜ፡- «ይህ ጌታዬ ነው» አለ፡፡ በገባም ጊዜ፡- «ጌታዬ (ቅኑን መንገድ) ባይመራኝ በእርግጥ ከተሳሳቱት ሕዝቦች እኾናለሁ» አለ ፡፡ فَلَمَّا رَأَى الشَّمْسَ بَازِغَةً قَالَ هَٰذَا رَبِّي هَٰذَا أَكْبَرُ ۖ فَلَمَّا أَفَلَتْ قَالَ يَا قَوْمِ إِنِّي بَرِيءٌ مِّمَّا تُشْرِكُونَ ፀሐይንም ጮራዋን ዘርግታ ባየ ጊዜ፡- «ይህ ጌታዬ ነው ፡፡ ይህ በጣም ትልቅ ነው» አለ ፡፡ በገባችም ጊዜ፡- «ወገኖቼ ሆይ! እኔ ከምታጋሩት ሁሉ ንጹሕ ነኝ» አለ ፡፡ إِنِّي وَجَّهْتُ وَجْهِيَ لِلَّذِي فَطَرَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ حَنِيفًا ۖ وَمَا أَنَا مِنَ الْمُشْرِكِينَ «እኔ ለዚያ ሰማያትንና ምድርን ለፈጠረው (አምላክ) ቀጥተኛ ስኾን ፊቴን አዞርኩ ፡፡ እኔም ከአጋሪዎቹ አይደለሁም» (አለ) ፡፡ በዚህ መልኩ ካስተነተኑ በኋላ አላህ የማይታይ የማይዳሰስ አምሳያ የሌለው ብቸኛ አምላክ መሆኑን አሰቡ አላህም በጅብሪል አማካይነት ለአላህ ትእዛዝ እጅ እንዲሰጡ አዘዛቸው ። እሳቸውም ለጌታቸው ትእዛዝ ፍፁም ታዛዥ መሆናቸውን አረጋገጡ ። ይህን እውነታ አላህ በተከበረው ቃሉ በላሚቷ ምእራፍ ( ሱረቱል በቀራ ) 131ኛው አንቀፅ ላይ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – إِذْ قَالَ لَهُ رَبُّهُ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ ጌታው ለርሱ ታዘዝ ባለው ጊዜ (መረጠው) ፡፡ ለዓለማት ጌታ ታዘዝኩ አለ ፡፡ አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka
إظهار الكل...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

የኢብራሂም ቱፋ  ንግግሮች ቃል በቃል ሲተሮገም እንደሚከተለው ነው፦ “በሌላ በኩል ሐይማኖት የፈጣሪ ነው፤ቁርኣንና መፅሐፍ ቅዱስ የሰው ቃል ሳይሆኑ የፈጣሪ ቃሎች ናቸውማንኛውም የሀይማኖት ተቋማት የአላህ ናቸው እንጂ የሰዎች አይደሉም። ከታቦትና ከቸርች የሚዋጋ (የሚያፈርስ) አካል ጥሉ ከሰዎች ሳይሆን የሚጣላው ከፈጣሪ (ከአላህ) መሆኑን ሊታወቅ ይገባል።” 👌 የምዕራብ ሐረርጌው ሸይኽ  ዐብዱል-ሐሚድ አወል (ሀፊዘሁላህ) ለኢብራሂም ቱፋ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተውታል፦ “አምልኮ ሚካሄድባቸው ተቋማት.... መስጂድም ሆነ የሌላ እምነት ተቋማት አምልኮ ሚካሄድባቸው ቦታዎችን የፈጣሪ ቤቶች ናቸው ይሉሀል። በአለማቱ ጌታ የሆነው በአላህ...ሺርክ እየተሰራበት ፣ኩፍር እየተካሄደበት፣በሱ እየተካደበት የዚህ አይነት ቤት የአላህ ቤት ነውን?! የአላህ ቤት ብሎ ማለት አላህ ብቻ ሚመለክበት አይደለምን?! ስለዚህ ኩፍር ሚካሄድበትን ቤት የአላህ ቤት ነው ብሎ ሲልህ፣አንተ ደግሞ ይህ ስሕተት ነው፤ትክክል አይደለም ብለህ ስትናገር... እከሌ ተሳዳቢ ነው፤እከሌ እንዲህ ነው...ብለው ይተቹሀል። እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሙሪዶች አይደሉምን?! የወጣላቸው ሙሪዶች ናቸው። እውነታውን እያዩ እንዳላዩ ይሆናሉ፤ እከሌ የሚፈለገውንም ያክል ቢሳሳት መነካት የለበትም ማለት ነው? በተዘዋዋሪ መንገድ መነካት የለባቸውም ማለቱ ነው። አንተ ሰው ሆይ! አላህ ይምራህ!፤ ታቦትን የሰበረ አካል ከአላህ ጋር ተጣልቷል ይላል (ኢብራሂም ቱፋ) ላ-ሀውለ-ወላ ቁወተ ኢል'ላ-ቢላህ!!!እንግዲህ ታቦትን የሰባበሩት እንደነ ነቢ ኢብራሂም ፣ ነቢ ሙሐመድ.. (ዐለይሂሙስ'ሰላም) እነሱ ናቸው የሰባበሩት። ታዲያ እነኝህ ብርቅዬ ነብያት በዚህ ምክንያት ከአላህ ጋር ተጣልተዋልን?!!!! እነ ጀሪር ዐብዱሏህ አል-በጀሊ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የመሳሰሉ ብርቅዬዎች ናቸው ጣኦቶችን የሰባበሩት... ከዕባ ውስጥ የነበሩ 360 ጣኦቶችን አልሰባበሩምን? የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ኧረ ሰባብረዋል። እንግዲህ ይህንን በማስረጃ ስትነግራቸው ጊዜ ነው እንዲሁም ስሕተት መሆኑን ስታብራራ ጊዜ፣እከሌ ሰው ይዘልፋል፣ ይነካል፣ ይሳደባል፣እከሌን ምን ነካው.... ይሉሀል። ታዳያ ይህ ሙሪድነት አይደለምን?! አይናቸውን ጨፍነው (ዓይኔን ግንባር ያርገው) ብለው በዘፈቀደ በባጢል ይጓዛሉ። የዚህ አይነት አካሄድ ደግሞ በእጅጉን የተጣላ ነው። በዚህ አይነት መዋቅር ውስጥ ያለ ሰው፣አንደዚህ አይነት ሰዎችን የሚያዳምጡ አካለት ትክክለኛ ሰዎች ናቸው ብለህ ታምናለህ?! ታቦቶችን ማፈራረስ የሚፈልግ አካል ጥሉ ከአላህ ጋር ነው ብሎ የሚል መዋቅርና እንዲሁም በዚህ መዋቅር (መጅሊስ) የሚመራ አካል ይህ ግልፅ ጥመት አይደለምን?! ኧረ ግልፅ ጥመት ነው። ታቦትን የሚያፈርስ አካል፣ከአላህ ጋር የተጣላ አካል ነው የሚል ሰው ፣ይህ ጠሞ አጥማሚ የሆነ አካል ነው፤ አይ እሱ (ኢብራሂም ቱፋ) መናካት የለበትም የፈለገውን ይናገር የሚል አካል ደግሞ ይህ እብደት ነው፣ሙሪድነት ነው። አላህ የእውነት ተከታዮች ያድርገን! የሐቅን መንሐጅ የምንለይ እንዲሁም በሙሉ ልብ፣በደስታ የምንቀበል አላህ ያደርገን፣አላህ ከተለያዩ ወስዋሶችና ጥርጥሮች አላህ ይጠብቀን!።” (የሸይኹ ንግግር አበቃ) የሸይኹን ድምፅ ያገኘሁት ከወንድማችን ከዶክተር ኸድር አቦምሳ ቴሌግራም ቻናል ላይ ነው። ግርድፍ፦ አቡ ሐፍሳህ @semirEnglish
إظهار الكل...
4_5882107649180306146.mp33.92 KB
ልዩ እና ገራሚ ሙሐደራ 🔍🔍🔍🔍🔍🔍 ✅ ስለ ዘውታሪው አለም አኸራ ዝርዝር ትንታኔ ✅ በተለይ ወደመሃሉ አካባቢ በለቅሶ ጭምር የቀረበ አስለቃሽ ትንታኔ አለበት። ➜ ይህ ሙሐደራ    ➧ ስለ አስፈሪው ቀጣይ ህይወት    ➧ ስለ አኸራ አስጨናቂ ክስተቶች    ➧ ስለ ነብያት መጨነቅ    ➧ የሰዎች መረበሽ    ➧ የአማኞች ደስታና ተድላ የምናፍቃንና ከሃዲያን ስቃይ    ➧ ምናልባት ያልሰማናቸው ድንቅ ክስተቶች    ➹ ሌሎችም በሚገርም አቀራረብ ተካተዋል።ሙሐደራውን አንድ ጊዜ ሳይሆን ተዳግሞ መስማቱ ተገቢ የሆነ በሚገርም የአቀራረብ ይዘት ይቀረበ አስለቃሽ ገሳጭና ወሳኝ ሙሐደራ ነው። ❴¯ወሬ አላብዛ አዳምጡትማ¯❵ 🎙 በተከበሩ ሸይኽ አቡ ዐብዱልሃሊም ዐብዱልሐሚድ ብን  ያሲን አል'ለተሚይ አሱኒይ አስሰ'ለፊይ አላህ ይጠብቃቸው 🏝 ይሄን ሁሉ ትንታኔ ያቀረቡት ሸይኹ በሂፍዛቸው ነው። በጣም ትልቅ ብቃት አላህ ሰጥቷቸዋል። በጣም አስገራሚ አሊም ናቸው። https://t.me/abdulham/2293 https://t.me/abdulham/2293
إظهار الكل...
ስለ መጪው አለም አኸራ.mp336.05 MB
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.