ar
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

الذهاب إلى القناة على Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

إظهار المزيد
1 719
المشتركون
-224 ساعات
-77 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
In our 5th episode, the photographer challenged our poets to come up with a piece using this photo. በ5ተኛው ምሽታችን ላይ ፎቶግራፈሩ በዚህ
In our 5th episode, the photographer challenged our poets to come up with a piece using this photo. በ5ተኛው ምሽታችን ላይ ፎቶግራፈሩ በዚህ ምስል ላይ ተንተርሰን ግጥም መጻፍ እንችል እንደሆን ምርጥ ሶስቱን ሊሸልም ቃል ገብቶ ነበር።

ግጥም ሲጥም ፮ በ6ኛው የግጥም ሲጥም ምሽት የዓመቱን ቆይታ ልናጠናቅቅ ነው! እስካሁን አብራችሁን የተጓዛችሁ፣ በቅርብ የተሳፈራችሁም ሆናችሁ፣ ፌርማታ ላይ እየጠበቃችሁን ያላችሁ ሁሉ ተመስገኑልን! ከ
ግጥም ሲጥም ፮ በ6ኛው የግጥም ሲጥም ምሽት የዓመቱን ቆይታ ልናጠናቅቅ ነው! እስካሁን አብራችሁን የተጓዛችሁ፣ በቅርብ የተሳፈራችሁም ሆናችሁ፣ ፌርማታ ላይ እየጠበቃችሁን ያላችሁ ሁሉ ተመስገኑልን! ከወዲሁ መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን - ዝግጅታችን ላይ እንደምትገኙም ጭምር! በሉ ሽፍታ እንገናኝ የፊታችን ረቡዕ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 ልክ 12 ሰዓት ሲሆን ጀምሮ Gitem Sitem 6 The 6th Episode of our Open Mic Circle of Poetry and Fun is here for the last session in this Ethiopian year. Thank you for all who have been with us along the way, those who are joining us and even those who are considering to come to one of our events. We wish you a happy Ethiopian New Year! See you at Shifta #gitemsitem #heransyoga #seifetemam #shifta

What's Addis? Sehin Tewabe, a rising eccentiric photographer. Check out for her photography works of this outshining woman in
What's Addis? Sehin Tewabe, a rising eccentiric photographer. Check out for her photography works of this outshining woman in the upcoming Mn Ale Addis e-mag! Stay tuned! #mnaleaddis #emagazine #BakelEdition #SehinTewabe #photography

photo content

photo content

ተወኝ ተስፋ ፤ እንደ ጥላ አልሸሸም፣ /ልቤን... ደግፎታል ፤ናፍቆት እየመሸም። እንዴት ነው የናፍቆት /ምሽት እንዴት ነው የናፍቆት /ንጋት እንደ ፀሐይ ኹሉ ኹለት ፤ መግቢያ መውጫ ኹለት ፤ ፅንፍ አቅጣጫ (አለው ወይ እላለኹ..) ደግሜ ሸኝቼህ ፤ ደግሜ መጠበቅ ከጀንበር ተላልፎ ፤ ሐፀይን መታረቅ ጊዜ ተበድሮ ፤ በጊዜ መንፏቀቅ በዘገየ እርምጃ ፤ በምእራብ መጥለቅ ( ሲደንቅ! ) / ምን ማለት እደሆን ፤ አልገባህም አይደል? / በምስራቅ ማሕፀን ፤ ንጋት እንዲወለድ ጀንበር ነበረበት ፤ ወደ ጥልቁ መውረድ። ተስፋ እንደዚህ ፤ አይደል የሚንከራትተው ናፍቆት ሰውቶ ነው ፤ ፍቅርን የሚያትተው። አንተም... አለሁ ማለት ላ'ተው፣ እኔም ተስፋ ማድረግ ላልተው፤ አለን ናፍቆትን፤ ስንመጸውተው። ትሔዳለህ ትመጣለህ 'ሸኝካለኹ ጠብቃለኹ (እንዴት ልኹን...?) ጎዶሎ ጨረቃ ፤ ስትሞላ እያየኹ ተስፋ ልቆርጥ ስል፤ ምክንያት አጣለኹ። አታውቅም ወይ፤ ቆርጦ መሄድ አታውቅም ወይ ፤ እሩቅ መንገድ፤ ደከመኝ... እኔን ፍለጋ ፤ ወዳ'ንተ መንጎድ። ተወኝ ላንገናኝ አትቅጠረኝ በትዝታ አትጠረኝ ማረኝ እኔን ከብቻዬ ተወኝ ኮከብ ሆነህ አትታየኝ (ተወኝ !) / በብርሃን ካንተ ላልደርስ ፤ የመውደቅ ጸጋ አይራቀኝ።/ ©️መንበረማረርያም ኃይሉ መንቢ የሎዛ መነሻ ሐሳብ ( ተወኝ ) ፀ.ገ .መ https://t.me/GitemSitem

አንተ የምትወደው ሙዚቃን በሆንኩኝ አንተ የምትወደው ግጥምን በሆንኩኝ እንደ እሳት ነበልባል ልብህን በላስኩኝ፤ እንዲያው ወለል ወለል እንዲያው ከንበል ከንበል እንዲያው ፍስስ ፍስስ ከስጋህ ለይቼ ዛትህን ብነጥቃትስ ፤ መንፈስህ ስካር ቢሞላው ቀልብህን ነፋስ ቢነዳው እያገለበለበ የስሜት ገሞራው ኩራትህ በሟሟ የትም በበተነው፤ በቻልኩበት ፣ በሆንኩበት ፣ አንጀትህን መኮልኮል ሆድህን ማባባት አቅልህን መንሳት ኮከብ በፊትህ መንዛት፤ በሆነና በሆነልኝ በውበት መስዋት ትብትብ ብለህ በታሰረከኝ ሰውነቴ አይደል ወይ ፊትህ ያሳነሰኝ ?! ©️መቅደስ ሞገስ https://t.me/GitemSitem

አቢሲንያ እንዳለቻችሁ ስንቄን ቅዳሜ 8 ሰዓት ብሔራዊ ቲያትር ተገኝታችሁ መርቁልኝኝኝ . . . እ!. . . እንዳትቀሩ አደራአ! https://t.me/GitemSitem
አቢሲንያ እንዳለቻችሁ ስንቄን ቅዳሜ 8 ሰዓት ብሔራዊ ቲያትር ተገኝታችሁ መርቁልኝኝኝ . . . እ!. . . እንዳትቀሩ አደራአ! https://t.me/GitemSitem

ወደ ዳሞቻ ተራራ የሚደረግ ጉዞን የሚያሸልመው ውድድራችን ከ30 ደቂቃዎች በፊት ተጠናቋል! ሁላችሁም ተመስገኑልን! አሸናፊዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!!! ተመሳሳይ ውድድሮችን እያደረግን የምንቀጥል በመሆኑ ቤተሰቦቻችን በሙሉ እየተከታተላችሁን ቆዩ! ሶስተኛ፦ ኤደን ሙሉነህ @Oritethe 192 1 #ነፍስ_ቦታ መጽሐፍ ሁለተኛ፡- ቶፊቅ መሀመድ @Tufaw_muhe 193 ነጥብ 2 #ነፍስ_ቦታ መጽሐፍት አንደኛ፦ ናታን ኤርምያስ @UniqueDY 242 ነጥብ ከ @ma_trip ተጓዦች ጋር ነጻ ጉዞ ወደ ዳሞቻ *መግለጫ፦ ሁሉም ምልክቶች እንደ ድምጽ የተቆጠሩ ሲሆን 😍👍🏾😐 ሶስቱ ምልክቶች የተዘጋጁት እኩል ውጤት ቢገኝ እንደመለያ እንዲያገልሉ ነው። ይህንን በደንብ እና ሁኔታዎች ባለማካተታችን ይቅርታ እንጠይቃለን! በቀጣይ የሚኖሩን ውድድሮች ላይም በተሳትፎ እና በዳኝነት አብራችሁን እንደምትቀጥሉ እምነታችን ነው።

ጣፋጭ ነን ላላችሁኝ "ቸኮሌት ነን እኛ ጣፋጭ ተፈላጊ ውድ ነን በጣሙን ለመብላት አጓጊ" ብለው ያወራሉ ዋጋቸው እንዲገባኝ ጣፋጭ እንደሆኑ እኔ መቼ ጠፋኝ "እንደ ፍራፍሬ ተወዳጅ ነን" አሉ ሊያውም ልክ እንደ ሙዝ የላቀ ከሁሉ ደግሞ ሙዝስ ቢሆን ጣዕሙ ሚጨምረው ሊበላሽ ሲቃረብ ማርች ሊሆን ነው።(kal ኪዳን)

ቆይ ግን እኔምለው ዛሬ ትናንት ነው? 🤔🤔🤔🤔 ዛሬ ተቀምጨ ነገን እያሰብኩኝ ተውኝ እያልኳቸው ወደ ትናንት ሳቡኝ ትናንት ጦርነት ዛሬ ደግሞ ተስፋ ነገን ስጠብቀው.... ብርሀን አይቸ መለከት ልነፋ ግን በጣም ይገርማል ለክ እንደምታዩት ዛሬ ትናንት ሁኗል 😭😭😭 ✍Maru kefale @Maru21

ውዴታ እኔ ወድሀለው ልቤ እስኪጠፍ እመሰክራለው ላንተ ስል በኢፍ አንተን አስባለው ሳዝንም ስደሰት ሀዘንም ደስታዬም አንተ ጋር አስቀምቶት አንሺ ውቡ ጨረቃ ለፍቅሬ ንገሪው ያላንተ አታይም አትችልም በይው ፀሀፊ✍ ሰአደት @Seadet476

ከጠገበ ለተራበ ያ፣ሰንጋ በቅሎ ጠገበ ስንቱ ፈረስ እየተራበ እርካብ የለው ኮርቻ ልጓም የለው መቀነቻ እሳር አይቀምስ አራሙቻ እንዲያው ዝም ብሎ መላስ ብቻ። @Barye1

መንገድ ወሳጅ አምጪ፣ ለመድረስ፣ ለመቅረት ፣አንተው ነህ ሰጪ፤ ከእውነት፣ ከእምነት፣አብረህ የመጓዙ፣ ፈራጁ፣ አዋጁ፣ልብህ ነው መዘዙ። በ"ማሜ የኢክሩ አባት" @Mohammedkemalikru

የወረት ትዳር የተፋቀርን መስሎን ያኔ እደዋዛ ጥድፍድፍ ብለን ተዋክበን እደዛ ትዳር ወደሚሉት የስርቤት መቀጫ ድንገት ገባንና አቃተን መወጫ መለየት ፈልገን ታጥረን በይሉኝታ ምን ይሉኛል በሚል አልጋ ለየን ቦታ የእፍእፍ ፍቅር ወረታችን አልፎ መልካሙን አስበን ተዘፈቅን በመጥፎ። ተፃፈ በ ሃይማኖት ሙሉነህ። @Haymika

Book your spot!!!
Book your spot!!!

ወደ ማይደርሱበት ህልም ።።።።።።።።።።።።።።። ነገ ተስፋን አዝሎ ልባችን ላይ በብሩህ ፊደላት ደምቆ ታተመ ህልማችን በሰዎች መዳፍ ተይዞ ወደ ማንደርስበት አዘገመ በቀቢፅ እይታ ፅልመትን ለመርታት በችኮላ አረማመድ ተመልከቱት ሰውን ወደ ማይደርስበት ህልም ተያይዟል መንገድ @Dagifa

እውነት ስለ እውነት እውነት እልሀለሁ እውነት በመናገር የምታጣው ነገር በምድር ላይ ያለ ሀሰተኛን ፍጡር አትበይኝ አትበይኝ እስኪ አንችው ንገሪኝ የእውነት በዝች ምድር ስለ እውነት ኑሮ ስለ እውነት የሞተ ንገሪኝ ማን ነበር?? ከ ፈጣሪ በቀር

photo content