በረከተ እስጢፋኖስ | Saint Stephen's blessings
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
8 575
المشتركون
-224 ساعات
-307 أيام
-14630 أيام
أرشيف المشاركات
ከወሩ ደርሰን ንዑድ ክቡር የሚሆን የሰማዕታት መጀመሪያ የዲያቆናት አለቃ ቅዱስ እስጢፋኖስን ልንዘክር ተሰይመናል።
ነገ ሰኞ ግንቦት 17 ማታ 3:00 ላይ በዚሁ ቤት ከበረከተ ቅዱስ እስጢፋኖስን አንጉደል።
+ ኪዳነ ምሕረት ግን አይደክምሽም? +
.................................................................
ቀኑ የሐምሌ ኪዳነ ምሕረት ዕለት ነው። ሙሉውን ቀን ደጇን ሳልረግጥ ደግሞም ስቦዝን ነበር የዋልኩት። ቀኑ ምንም እንደ ዕቅዴ እየሄደልኝ ባይሆንም አንድ የተቀደሰ ዕቅድ ግን ከጠዋት ጀምሮ ነበረኝ፤ እሱም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ሄዶ መሳለም ነበር። እስከ ማታ ድረስ ራሴን ብዙ ሥራ እንዳለብኝና ጊዜ እንደሌለኝ እየነገርኩ ባሳንፍም ቀኑን ሙሉ ደግሞ አንድ ሥራ አለመስራቴን ሳስብ ቅዱስ ጳውሎስን ያዘገየ ሰይጣን እኔንም ሊያስቀረኝ ነው እንዴ ብዬ ማታ 12:00 ላይ ልሄድ ተነሳሁ። ታዲያ ምን አዲስ ነገር አለ 12:00 መሄድ ካላችሁኝ ከእኔ ቤት እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት ድረስ የ 3 ታክሲ ርቀት መሆኑ ነው።
የከፋውና ያዘነ ሰው ርቀት አያሳስበውም መሰለኝ የሚታየኝ በታክሲ ሰልፍ እና በመጓዝ የማጠፋቸው ሰዓታት ሳይሆን ደጇ እንደደረስኩ የምዘረግፈው የዕንባ ብዛት ብቻ ነበር። 12:00 ተነስቼ 2:15 ላይ ማታ ደጇን ረገጥኩኝ። ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ለመድረስ መንገዱ ሁሉ የመኪና ሰልፍ ብቻ ነው። ከገዳሟ ወጥቶ በእግሩ ወደ ቤቱ የሚገሰግሰው ሕዝብ እልፍ ነው። የገዳሟ ቅጽር ውስጥም ያለው የሰው ብዛት "ሕዝቡ እዚው ነው እንዴ የሚያድረው" እስኪያስብል ድረስ እልፍ ነው።
ሆኖም ግን በሯን ተሳልሜ የተነጋገርነውን ጉዳይ ከምን እንዳደረሰችው ልጠይቃት ወደ ሥዕሏ አመራሁ። ተደፍቼ ከተነጫነጭኩኝ፣ ካለቃቀስኩኝ፣ ካማረርኩኝና ብዙ ጥያቄ ካዘነብኩባት በኋላ ቤተ መቅደሷን መዞር ጀመርኩኝ። በቤተ መቅደሷ ዙሪያ የተቀመጡ ያማሩ የእሷና የተወዳጁ ልጇ ሥዕላት አሉ። በሁሉም ሥዕላት ፊት ብዙ ምዕመናን ቁጭ ብለዋል። ግማሹ ሰግዶ የመረረ የለቅሶ ሲቃ ድምጽ ያሰማል።... ግማሹ ዝምብሎ ቁጭ ብሎ ዕንባ ባቀረረው ዓይኖች ሥዕሏን ይመለከታል። ግማሹ ደግሞ ራቅ ብሎ ተቀምጦ በእጁ ይዞ ያበራው ጧፍ ላይ ዕንባ ባዘለው ዓይኑ ይተክዛል።.. ግማሹ ከእመ ብርሃን ጋር በልቡ እየተነጋገረ ቤተ መቅደሷን በእምብርክክም በእግሩም ይዞራል። በአጋንንት ፈተና የሚፈተነው ተቃጥሎ ይጮሃል።.... ባለሀብቱ በሚሊየኖች የገዛውን መኪና አቁሞ ከለበሰው ከነሱፉ በሥዕሏ ፊት ሰግዶ ያለቅሳል።
እመቤቴ ሆይ እስቲ ልጠይቅሽ፤ አንቺ ፊት ደጅ የማይጠናው ማነው? አንቺ ፊት የማያለቅስ፣ የማያዝን፣ ዕንባውን የማያፈስ ማነው? ..... "አሕዛብ ሁሉ በፊትሽ ይማለላሉ" የተባለልሽ እመብርሃን ከአንቺ ፊት የማይንበረከክ ሕዝብ የቱ ነው? ራስሽ "ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል" እንዳልሽው ብጽዕት ለሚልሽ ሁሉ ክብርት እናቱ ነሽ። ታዲያ እንዴት ቻልሺው እመብርሃን?.. ሁሉም ከሥዕልሽ ፊት መጥቶ ኃዘኑን፣ ሰዎች በጭካኔ የበደሉትን ሲነግርሽ በምን ትከሻሽ ቻልሺው? ለነገሩ "ሰላም ለዘባንኪ እምዘባነ ኪሩብ ዘዐብየ" እንዲል ትከሻሽ ከኪሩቤል ትከሻ ስለሚበልጥ ነው?... የአንድ ውሻ ውኃ ማጣት አራርቶሽ በጫማሽ ውኃ ያጠጣሽ ርኅርኅት እመቤት ሆይ የእኛስ ኃጢአት (ማጣት) የርኅራኄ አንጀትሽን ምን ያህል አቁስሎት ይሆን?....... ወላዲተ አምላክ ሆይ፤ ለመሆኑ በየቀኑ ስንት ጊዜ ነው የምታለቅሺው? “ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።” (ሮሜ 12፥15) ይላልና የቀራንዮዋ ኃዘንተኛ እመአምላክ ሆይ ሰዉ ሁሉ መጥቶ ሥዕልሽ ፊት ዕንባውን ሲያፈስ አብረሽ በቀን ስንቴ ታለቅሻለሽ?.... ስናለቅስ አብረሽ እያለቀሽ የምታጽናኚን ከአንቺ ሌላ ማን አለን?... ልጅሽ "በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል" ተብሎ እስኪተነበይልሽ ድረስ የኃዘንን ጥግ እንድትቀምሺ ያደረገው አሁን እኛ የምንነግርሽን የኃዘናት ብዛት እንድትችይው ነው አይደል? አመቤቴ እስቲ ንገሪኝ? ሁሉም እኮ አንቺ ፊት መጥቶ የሚያቀርበው ሮሮ አለበት። የራበው ሕጻን የእናቱን ጡት እንዲለምን፣ እኛም ሲርበን፣ ሲጠማን፣ ስናዝን፣ ስንደሰት ከአንቺ ከእናታችን ሌላ ወዴት እንሄዳለን?
ታዲያ እመአምላክ ግን አይደክምሽም? ሥዕለታቸው ሰምሮ ግቢሽን በእልልታ ከሚያቀልጡት እናቶች ጋር አብረሽ እልል ብለሽ ደስታቸውን ተጋርተሽ ትልኪያቸዋለሽ። አንቺ ፊት ተንበርክከው ከሚያለቅሱት ጋር አልቅሰሽ አረጋግተሽ ትሰጂያቸዋለሽ። ልባቸው የተሰበረውን ጠግነሽ፣ በኃጢአት የቆሰሉትን ከልጅሽ አማልደሽ ንጹሕ ታደርጊያቸዋለሽ። እናት የልጆቿን ጸባያት እንደምታውቅ፣ አንቺም ሁሉም ልጆችሽን እንደ ጸባያቸው የሚያስፈልጋቸውን ትሰጫቸዋለሽ። ታዲያ እናቴ ሆይ አይደክምሽም? ሐኪም እንኳን የሚያስተናግደው በሽተኛ ሲበዛ እኮ ርኅራኄው ይቀንስበታል። ይሰላቻል፣ ይበሳጫል፣ ይናደዳል።...... አንቺስ የዚያ ሁላ ሕዝብ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ በሽታና በደል እየሰማሽና እያከምሽ ርኅራኄሽ እንዴት አልጎደለም?
እመብርሃን እስቲ ንገሪኝ! እማዬ ላለሽ ሁሉ እናት መሆን አይደክምም? ከሥዕልሽ ፊት ቆሞ የሚያለቅሰውን ሁሉ ዕንባ ማበስ አይሰለችም? በኃጢአት ተጨማልቆ ከሥዕልሽ ፊት ምልጃሽን ደጅ ለሚጠና ሁሉ ከልጅሽ ዘንድ ሄደሽ ለእያንዳንዳችን ኃጢአተኞች ማርልኝ ብሎ መለመን አይታክትሽም?.... የእኔ እናት እመቤቴ እስቲ ንገሪኝ? መቼ ነው ራሱ የምታርፊው? በዚህች ዓለም የኖርሽባት 64 ዓመት ሙሉ የስቃይ እና የኃዘን ጊዜያት ነበሩ። አንዴ ስትሰደጅ፣ አንዴ ከቤተ መቅደስ ስትገፊ፣ አምላክሽን የምትወልጂበት ቦታ አጥተሽ ስትንከራተቺ፣ ልጅሽ ጠፍቶብሽ በኃዘን ስትፈልጊ፣ በልጅሽ ስቃይና ሞት ነፍስሽ በኃዘን ስትቆስል ነው የምናቀው። በዕድሜሽ ሙሉ አንድም ቀን አርፈሽ ስትስቂና ስትደሰች አይተንሽ አናውቅም። ለደስታ በሰርግ ቤት እንኳን ብትጠሪ ልታርፊ አልቻልሽም። የትህትና ዓይኖችሽ ከአስተናጋጆቹ ጋር ሆኖ የጎደለውን ወይን ማንም ሳይነግርሽ አውቀሽ ስታማልጂ ነበር።... እመንጉሥ ሆይ፤ የነገሥታት እናቶች እኮ ተቀማጥለውና ተደስተው ሲኖሩ ነው የምናውቀው፤ ታዲያ ምነው አንቺ የነገሥታት ንጉሥ እናት ሆነሽ ስቃይሽ በዛ?.. እንዴት አንዴ እንኳን ስትስቂ፣ ስትደሰቺና ስታርፊ አላየንሽም?...እመቤቴ ሆይ "የጻድቃን ዕረፍታቸው ሞታቸው ነው" ስለሚል አንዴ ልጅሽ በከበረ ሞትሽ በመንግሥተ ሰማያት ሲያሳርፍሽ ኃዘንሽና ስቃይሽ ያበቃለታል ብለን ስንጠብቅ አሁንም ከሚያዝኑ ልጆችሽ ጋር አብረሽ እያዘንሽ፣ ከአልቃሻ ልጆችሽ ጋር አብረሽ እያለቀሽ ነው ያለሽው። ለሁላችንም ኃጢአተኛ ልጆችሽ በከበረ ልጅሽ ፊት መማለድን አላቆምሽም። ታዲያ እመብርሃን የእውነት አይደክምሽም እንዴ?... የጌታዬ እናት መቼስ ነው የምታርፊው??
ኪዳነ ምሕረት ሆይ ደክሞሻል እረፊ አልልሽም። አንቺ ከምልጃሽ አረፍሽ ማለት የእኔ ነፍስ መገኛዋ ሲዖል ነው። እናቴ ሆይ ግድየለሽም እኛን ከማጽናናትና ዕንባችንን ከማበስ ለትንሽ ጊዜ እረፊ አልልሽም። አንቺ የእኛን ዕንባ ከማበስ አረፍሽ ማለት በኃዘን መሞታችን ግልጽ ነው።
እናቴ እመቤቴ እንደው ግን ዝምብዬ ልጠይቅሽ? የጌታዬ እናት ሰዓሊተ ምሕረት ሆይ የእውነት ግን አይደክምሽም?
............................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
በኪዳነ ምሕረት ዓመት ፍልሰታ ጾም አጥቢያ ተጻፈ
አዲስ አበባ
.
.
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በነገው ዕለት ንዑድ ክቡር የሚሆን ቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስን እንዘክራለን። የጌታችንን የትንሣኤውን ደስታ አብረን የምናከብርበት ዝክር ነውና እንዳትቀሩ!
During the holy fifty, where we tend to abandon our spiritual lives, we highly recommend this beautiful conversation between two beloved sisters.
https://youtu.be/AEu401xf3tU?si=JPMkpu0xutSl8hO_
A Beautiful sermon on the resurrection of our lord and saviour Jesus Christ by Deacon Estifanos Girma on EOTC TV.
Happy pascha!
https://youtu.be/fBvPWkQ_1hY?si=1r5YO8zoOv-kQ0x8
+2
+ ባየናትም ጊዜ ደምግባት አልነበራትም! +
.........................................................................
በጌታ በሕማሙ ቀን፣ በዚያች ሙሽርነቱ ቀን ገላው ሁሉ በደም ተለውሶ መስቀል ተሸክሞ ሲሄድ ከኋላው አንዲት በዕንባ እየተጠመቀች የምትከተል ውበቷ ከፀሐይ ይልቅ የሚያበራ አንዲት እናት አይታችሁ ይሆን?
ፍጹም ንጽሕናውን ከልጅነቱ ስታሳድገው የምታውቀው አንድ ልጇ ለንጽሕናው መስካሪ አጥቶ እንደ በደለኛ፣ እንደ ኃጢአተኛ በመስቀል ሲቸነከር በእናት ዓይኖቿ፣ የዕንባ ብዛት በከለሉት ዓይኖቿ ያየች አንዲት ደም ግባቷ ያማረ ብላቴና አይታችሁ ይሆን?
ወገኖቼ ሆይ፣ በዚያች በክርስቶስ በሕማሙ ቀን በልጅነቷ ያቀፈችው አንድ ብቸኛ ልጇ ዕርቃኑን ሲሰቅሉት የኃዘኗ ብዛት አላራምድ ያላት አንዲት ውብ ብላቴና እናቱን አይታችኋት ይሆን?
ፍጹም አምላክ እንደሆነ የምታውቀው ልጇ፣ በአንድ ትእዛዝ የሚያሰቃዩትን ሁሉ ማጥፋት እንዲቻለው የምታውቀው ልጇን "ሁሉንም አጥፋቸው" ብላ የኃዘኗን ብዛት ለማስታገስ ያልተናገረችው ያች ትሁት እናቱን አይታችኋት ይሆን??
በልጅነቱ ሲታዘዛት "ጎበዝ ልጄ" ብላ በሳመችው ራሱ ላይ የእሾህ አክሊል ጎንጉነው ሲያደርጉለት ያየች መከረኛ ውብ እናቱን አይታችኋት ይሆን?
አዎ እኛስ አይተናታል። ባየናትም ጊዜ ግን እርሷም እንደ ልጇ ደም ግባት አልነበራትም።
አዎ ያቺን ንጽሕት እናቱን ልጇን ስትከተል አይተናታል። ነገር ግን ልጇ 6666 ግርፋትን ሲገረፍ በእናት አንጀቷ "እኔን ልጄ" እያለች የእርሷም ልብ ይገረፍ ነበርና ባየናትም ጊዜ ደም ግባት አልነበራትም። በልጇ ግርፋት ልክ በእርሷም ነፍስ ሰይፍ ያልፍባት ነበርና ያቺ ምስኪን እናት በልጇ ሕማም ዕለት ባየናት ጊዜ ደም ግባት አልነበራትም።
ድንግልናዊ ወተቶቿን ባጠባችበት አፎቹ ሐሞት ሲያጠጡት እያየች ነበርና አዎን ያቺ ውብ እናት በዚያች ቀን ግን ላያት ሁሉ ደም ግባት አልነበራትም።
አዎን ያቺ ምስኪን እናት፣ ያቺ ፀሐይን ያስገኘች ምሥራቅ በልጇ ሕማም ቀን ግን ዕድሜዋን ሙሉ ከልጇ ያልተነቀሉ ከውብ ዓይኖቿ የሚፈሱት ትኩስ የዕንባ ምንጮች ውብ የሆነ ፊቷን ይሸረሽሩት ነበርና ያቺን መከረኛ እናት ባየናት ጊዜ ደም ግባት አልነበራትም።
የኃዘንን ጥግ ከእመቤታችን በላይ ያየ ማነው? አንድ እናት ልጇ ባልሰራው ወንጀል በሐሰት ተመስክሮበት ቢሞት ያ ልጅ እንደ እመቤታችን ልጅ እንደ ክርስቶስ ግን ፍጹም ከሁሉም ኃጢአት ንጹሕ ሊሆን አይችልም። አንድ ሰው ተገፋሁ፣ ተበደልኩ ብሎ ቢያዝን እንደ ልጇ ክርስቶስ የተበደለ የተገፋ በዚህ ዓለም ሊኖር አይችልም። ፍትሕ አጣሁ ብለህ ብታዝን በፍጹም ንጽሕናው ፍትሕ ካጣው ክርስቶስ ጋር ግን ልትወዳደር አትችልም።
ወገኖቼ ሆይ የፈለገ ብናዝን ከእመቤታችን በላይ ልናዝን አንችልም! የፈለገ ብንከፋ፣ የፈለገ ቢጨልምብን እመቤታችን ልጇ እንደ ሸራ ሲወጠር አይታ ከተከፋችው መከፋት በላይ ግን ልንከፋ አንችልም። "ማርያም የልብን ኃዘን ታቀላለች" የምንለውም የኃዘንን መጨረሻውን ጥግ ስለቀመሰችው ነው።
ዘወትር በሰዓታት ጸሎታችን እመብርሃንን እንዲህ እንላታለን!
"ናዛዚተ ዓለም ናዝዚ ለልቡናየ ኃዘኖ፣ እስመ ተማኅፀንኩ አንሰ ተማኅፅኖ በሥዕልኪ ሥዕለ አድኅኖ እሰግድ ለኪ"
" ዓለምን የምታረጋጊ ሆይ፣ የልቡናዬ ኃዘኑን አረጋጊው፤ አዳኝ በሆነ ስዕልሽ መማጸንን ተማጽኛለሁና። እሰግድልሻለሁ!
(መጽሐፈ ሰዓታት ፣ ለኖኅ ሐመሩ)
በቅዳሴ ጸሎታችንም ዘወትር እንዲህ እንላታለን:-
"ናዛዚትነ እምኃዘን በኃይለ ውርዙትነ እምርስዓን፣ ተማኅጸንኪ ተፀውረ ብሉየ መዋዕል ሕፃን፣ ኦ ማርያም ተስፋ ለቅቡፃን በጊዜ ጸሎት ወዕጣን፣ ወበጊዜ ቅዱስ ቁርባን ለናዝዞትነ ንዒ ኀበ ዝ መካን።"
"ከኃዘን የምታረጋጊን፣ ከእርጅና የምታድሺን፣ በማሕጸንሽ ቀዳማዊው ዘመን የማይወሰንለት ሕፃን የተወሰነ ተስፋ ለቆረጡት ተስፋቸው የሆንሽ ማርያም ሆይ፣ ጸሎት፣ ዕጣን እና ቅዱስ ቁርባን በምናሳርግበት ጊዜ፣ ከኃዘናችን ታረጋጊን ዘንድ ወደዚህ ቦታ ነይልን"
ባዘንን ጊዜ ወደ እመብርሃን እንጠጋ! እውነተኛ መጽናናት፣ እውነተኛ መረጋጋት ያለው የሚያረጋጋ አምላክን ከወለደች ከእመብርሃን ዘንድ ነው። ኃዘናችንን ከእመብርሃን በላይ ሊረዳን የሚችል ማንም የለም። በኃዘናቸው ጊዜ ወደ እመቤታችን መጠጋት ያቃታቸውን መናፍቃንን ስናይም "ማን ያጽናናቸው ይሆን" ብለን እናዝንላቸዋለን።
እንዲህ ብለን ወደ እመብርሃን እንጸልይ:-
"ማርያም ድንግል ምልዕተ ምሕረት ከመ ተከዜ፣ እስከ ማዕዜኑ እሄሉ ማእከለ ብካይ ወእንባዜ፤ ኦ ናዛዚት እንተ ወለድኪ ናዛዜ። ኦ ንግሥት በቋዒት ብቍዕኒ ይእዜ።"
"እንደተከዜ ወንዝ ይቅርታን የተመላሽ ድንግል ማርያም ሆይ፣
እስከ መቼ በኃዘን እና በልቅሶ እኖራለሁ?
አረጋጊውን የወለድሽ አረጋጊዋ ሆይ፣
ጠቃሚዋ ንግሥት ሆይ አሁን ጥቀሚኝ።"
(ተፈሥሒ ማርያም፣ በእሁድ ወበዓለ፶)
........................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
ሰሙነ ሕማማት ፣ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
........................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በሕማማት የሚደመጥ
ሕማማት | Himamat(13ቱ ሕማማተ መስቀል) ቀጥር ፩ የንስሓ አልበም ዲ.ን ጸጋ ሥላሴ https://youtu.be/fEtOXPn3YUk?si=obWB4cL0EMpDjsFw https://youtu.be/fEtOXPn3YUk?si=obWB4cL0EMpDjsFw https://youtu.be/fEtOXPn3YUk?si=obWB4cL0EMpDjsFw
+2
+ የማይረሳ ኃጢአት! +
..........................................
አንድ ሰው ከኃጢአቱ በንስሐ ተላቀቀም አልተላቀቀም ኃጢአትን እንደመርሳት የሚከብድ ነገር የለም።
ሰው ንስሐ የገባበትን ኃጢአት እያሰበ መጸጸት አይችልም። ምክንያቱም ንስሐ በገባበት ኃጢአት ተጸጸተ ማለት የእግዚአብሔርን መሐሪነት እና ይቅር ባይነቱን አለማመን ስለሚሆንበት ነው!
ምንም ቢሆን ግን ኃጢአት ንስሐ ገብተንበት እንኳን ቢሆን መርሳት እጅግ ከባድ ነው።
ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ለሐዋርያቱ ተገልጦላቸው ሶስቴ የካደውን ቅዱስ ጴጥሮስን ሶስት ጊዜ "ትወደኛለህን?" ብሎ ጠይቆት ነበር። (ዮሐ 21)
ቅዱስ ጴጥሮስም ለሶስተኛ ጊዜ ጌታ ሲጠይቀው ሶስት ጊዜ የካደው ኃጢአቱ ትዝ ብሎት አዘነ። ቅዱስ ጴጥሮስ ስለዚያች ክህደት ኃጢአቱ መራራ ዕንባን አልቅሶ በንስሐ ኃጢአቱን ቢያጥብም ትዝ ሲለው ግን አዘነ።
የፈለገ በዕንባና በንስሐ ኃጢአታችንን ብናጥብም፣ ያቺ ከእግዚአብሔር ተለይተን የኖርንባትን ጊዜ ስናስታውስ አለማዘን እንዴት ይቻላል?
የሰራነውን ኃጢአት እንረሳው ዘንድም የሚገባ ነገር አይደለም። ኃጢአትን መርሳት የእግዚአብሔርን መሐሪነት እና ይቅር ባይነትንም አብሮ መርሳትን ያመጣልና።
"እመቦ ዘወድቀ ውስተ ኃጢአት ኢይርሳዕ እስመ ዘኢይትረሳዕ"
"በኃጢአት የወደቀ ቢኖር አይርሳ፣ የማይረሳ ነውና"
(ቅዳሴ እግዚእ)
የወደቅንባቸው ኃጢአቶች ሁሉ የእግዚአብሔርን ወሰን የሌለው ምሕረቱን የሚያስታውሱን ማስታወሻዎች ናቸው!
..................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
መጋቢት 23/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
...............................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በገብርኄር ሳምንት በተሾምንበት አገልግሎት እንድንታመን በምንማርበት ሰሙን ለሥጋ የሚሆነውን መብል ለማሰናዳት ቢሰየምም፣ እርሱ ግን ቃለ እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እና ጸጋ የነፍስ መብልን ለምእመናን አስተምሮ መክሊቱን ያተረፈውን ንዑድ ክቡር የሚሆን የሰማዕታት መጀመሪያ፣ የዲያቆናት አለቃ ቅዱስ እስጢፋኖስን በነገው ዕለት እንዘክራለን።
ቸር አገልጋይ ማነው? ቅዱስ እስጢፋኖስ አይደለምን?
በነገው ዕለት ዝክር እንዳትቀሩ! ማታ 3:00 ሰዓት ላይ እንገናኝ?
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በደብረ ዘይት ሳምንት መጨረሻ ቆየት ያለ ስለ ጌታችን ምጽአት የተሰበከ አጭር ስብከት ተጋበዙልን!
የሚያስተምረን፣ የሚመክረን፣ የሚገሥጸን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
በጳጕሜን ወር በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ የተሰጠ ትምህርት ነው።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
+2
+ ከመልካም ነገር አለማጣት +
...................................................
ብዙ ሰው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር እናንተ ጋር ስለሌለ ቆጭቷችሁ አያውቅም? እግዚአብሔርን ለምን አሳጣኸኝ ብላችሁ አማራችሁትስ አታውቁም?
ዓለም ሁሉ መልካም ነው ብላ የተስማማችበትን ሀብት እና ዝነኝነትን ስላላገኛችሁ ተናዳችሁ አታውቁም?
በተቃራኒው ደግሞ እነኚህ በዓለም ዋጋ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ስላሏችሁ ኮርታችሁ ታውቃላችሁ? "እኔን እግዚአብሔር ከሌላው ሰው ይልቅ መልካም አድርጎልኛል" ብላችሁ አስባችሁስ ታውቃላችሁ?
እንግዲያውስ አንድ የሚያጽናና እና የሚያስጠነቅቅ ቃል ላስታውሳችሁ!
ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል:-
"እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር ሁሉ አያሳጣቸውም"
- መዝ ፹፫ (፹፬) ፥ ፲፩
የምታደርገውን ነገር ሁሉ በቅንነት እስካደረከው ድረስ ላንተ መልካም የሆነን ነገር ሁሉ ልታጣው አትችልም። ደሃ ሆነህ፣ ብዙ ነገር ጎድሎህ ብትኖር፣ ነገር ግን ልብህ ቅን ከሆነ አጣሁት ብለህ የምታስበው ሀብት ላንተ መልካም አልነበረም ማለት ነው።
ምክንያቱም በቅንነት እየተጓዝክ ላንተ መልካም የሆነን ነገር እግዚአብሔር ሊያሳጣህ አይችልም።
በበሽታ እና በሕመም ብትሰቃይ፣ ልብህ ግን ቅን ከሆነ፣ ያጣኸው ጤና ላንተ መልካም ነገር አልነበረም ማለት ነው።
በድሎት እና ተድላ ደስታ እየኖርክ፣ መልካም ነገር ሆኖልኛል ብለህ እያሰብክ፣ ቅንነት ከሌለህ ደግሞ ያገኘኸው ሀብት መልካም እንደሆነ እርግጠኛ መሆን አትችልም።
በሀብት እና ዝና ተከበህ፣ ብዙ ሰው እየቀናብህ ብትኖር እንኳን ልብህ ቅን ካልሆነ ግን ያገኘኸው ባዕለጸግነት ብዙ ሰው መልካም ነው ብሎ ስለተስማማ መልካም ነው ብለህ ማረጋገጥም አትችልም።
የልባችንን ቅንነት እስካረጋገጥን ድረስ፣ ለእኛ ከራሳችን በላይ የሚያስብልን እግዚአብሔር የሚረባንን መልካም ነገር ሁሉ አያሳጣንም!
...................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
መጋቢት 09/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
....................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እምቢም እኮ መልስ ነው | "NO" is also an answer
.
.
ይህን ቪድዮ ተመልከቱት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://vt.tiktok.com/ZSuQw6fcA/
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እምቢም እኮ መልስ ነው! | "NO" is also an answer!
.
.
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
.
Follow and share our tiktok page!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://vt.tiktok.com/ZSuQw6fcA/
+2
+ ይማርህ አይመራመርህ! +
..........................................
በነገራችን ላይ ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" ብቻ አይባልም።
ከዕለታት በአንድ ቀን በጉንፋን እየተሰቃየሁ በኃይለኛው ሲያስነጥሰኝ አንዷ ወዳጄ እንደማንኛውም ሰው "ይማርህ" ብላ መረቀችኝ። "አሜን" ብዬ ስመልስላት "አይመራመርህ" ብላ ጨመረችልኝ።
ሰው ሲያስነጥስ "ይማርህ" የሚባለው የልብ ምቱ በሚያስነጥስበት ጊዜ ለቅጽበት ስለሚያቆም ነው። ይህች አስተዋይ እህቴ "አይመራመርህ" ብላ የጨመረችው ደግሞ እግዚአብሔር ኃጢአትህን አይመራመርህ፣ አይተሳሰብህ አይቁጠርብህ ማለቷ ነው።
እውነቷን ነው። እግዚአብሔር እያንዳንዷ ኃጢአታችንን ቢቆጥርብን፣ ቢመራመረን፣ ቢቆጣጠረን ምን እንሆን ነበር?
በጌታ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ ብዙ አስፈሪ ልብን ቀጥ የሚያደርጉ ትእዛዛትን ሲያውጅ ሰምተነው ይሆናል።
ይ.ዲ:-
"የአሳብ ነውር ያለበት ቢኖር አይቅረብ!
"አሳቡ ድውይ የሆነ ቢኖር ይራቅ!
" ኃጢአትን የሚሠራ ንጹሕም ያልሆነ ቢኖር ይወገድ!
"በኃጢአት የወደቀ ቢኖር አይርሳ፣ የማይረሳ ነውና!
"ከኢየሱስ ትእዛዝ ልዩ የሆነ ቢኖር ይከልከል!!"
ደግነቱ ፈርተን እንዳንሸሽ ቤተ ክርስቲያን እዚያው በምንመልሰው ተሰጥዖ ታጽናናናለች እንጂ ይህን ሰምቶ ማን ይቆም ነበር?
ዲያቆኑ እንዲህ እያለ ሲያውጅ በሚታወጁት ሁሉ ኃጢአቶች ተዘፍቀን የምንኖረው እኛ እንዲህ ብለን እንመልሳለን።
"አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁን"
ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ቸርነት ሆኖ እንጂ በየደቂቃው የምናስበው የኃጢአት ሀሳብ ነውራችን እኮ ወደ እግዚአብሔር ባላቀረበን ነበር።
እንደ ቸርነቱ ሆኖ እንጂ ንጹሕ ስላልሆንን፣ ኃጢአት ስለምንሰራ ብቻ መወገድ ነበረብን።
እግዚአብሔር ቸር ሆኖ ኃጢአታችንን ንስሐ ስንገባ ስለሚረሳልን እንጂ እንደ በደላችን ቢሆንማ ኃጢአት የሚረሳ እኮ አልነበረም።
እንደ በደላችን ቢሆንማ እንደ ዳታንና አቤሮን ምድር ተከፍታ ብትውጠን በተገባ ነበር። እንደ በደላችን ቢሆንማ የሰራነው ኃጢአት ሊያስቀስፈን በተገባ ነበር።
እንደ በደላችን ቢሆንማ እሳት ከሰማይ ወርዶ ቢበላን፣ ከምድረ ገጽ ብንጠፋ ለእኛ የተገባ ነገር ነበር።
እግዚአብሔር ግን ቸር፣ መሐሪ፣ ይቅር ባይ ስለሆነ፣ ምሕረቱ መዓቱን እየቀደመ ስለሆነ እንጂ አንዳችንም በሕይወት ባለኖርን ነበር።
የምንተነፍሰው፣ ተኝተን የምንነሳው፣ የምንበላው የምንጠጣው፣ ሁሉን ነገር የምናደርገው እንደ እግዚአብሔር ቸርነት እንጂ እንደ በደላችን ስላልሆነብን ነው። ዓለም እስከአሁን ያልጠፋችው "የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ስለመላች" ነው። (መዝ ፴፪ (፴፫) ፥ ፭)
"አቤቱ ኃጢአትን ብትጠባበቅ በፊትህ ማን ይቆማል?"
መዝ ፻፳፱ ፥ ፫
እግዚአብሔር አምላክ ይማረን፣ አይመራመረን!!
.................................
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
መጋቢት 3/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
...................................
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨ @ststephenblessings ✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ለረጅም ዓመታት ቤተ ክርስቲያንን ያለ ድካም ሲያገለግል የኖረ፣ በጊዜ ብዛት ያልተለወጠ፣ በቃልም በሕይወትም ያስተምር የነበረ መምህራችን ዘላለም ወንድሙን ዛሬ በክብር እንሰናበተዋለን። የስንብት መርኃ ግብሩም እንደሚከተለው ነው:-
1. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት በመምህራነ ወንጌል በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣት ዘማርያን እና በበርካታ ምእመናን ታጅቦ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ እስከ 5:00 ሰዓት ድረስ መስቀል አደባባይ ይደረሳል።
2. ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የተለያዩ የአሸኛኘት መርሐግብሮች የሚከናወኑ ሲሆን በዚህም ቦታ
ከጠዋቱ 5:00 – 8:00 ሰዓት ድረስ የተለያዩ ክንውኖች ይኖሩናሌ። እነዚህም:-
ከጠዋቱ 5:00 – 5:30 የመርሐ ግብር መክፈቻ እና ጸሎት
ከ5:30 እስከ 6:00 ያሬዳዊ ዝማሬ የዘማርያን ኅብረት ዝማሬ እና ቅኔ ይቀርባል ።
ከ6:00 – 6:15 የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ በንባብ ይቀርባል ።
6:15 – 6:40 ከተለያዩ ተቋማት የሚቀርቡ የስንብት መልዕክቶች ይቀርባሉ ።
ከ6:40 – 7:00 ከቤተሰብ እና ከወዳጅ ዘመዶች ስለወንድማችን የሚቀርቡ ምሥክርነቶች በተለያዩ አካላት ይሰጣል።
ከ7:00 – 7:30 የወንጌል መርሐ ግብር ይካሄዳል ።
ከ7:30 – 7:40 በሰንበት ትምህርት ቤቶች እና በዘማርያን የጋራ ዝማሬ ይቀርባል።
ከ7:40 - 8:00 ቃለ ምእዳንና ቡራኬ በብፁዓን አባቶች ይሰጣል
ከቀኑ 8:00 ላይ የመስቀል አደባባዩ መርሐ ግብር ተጠቃሎ ጉዞ ወደ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ጉዞ የሚያደርግ ሲሆን ከቀኑ 9:00 ላይ አጭር ጸሎት ተደርጎ ሥርዓተ ቀብሩ የሚፈጸም ይሆናል።
© የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
