ar
Feedback
እዝራ ካሳሁን / Ezra Kassahun

እዝራ ካሳሁን / Ezra Kassahun

الذهاب إلى القناة على Telegram

❝ ስለተወዳጁኝ እንኳን ደስ አሎት 😁❞

إظهار المزيد
260
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
Accepting the Art of Getting Up ====================== ፧ Failure frequently appears as a black thread against the vivid colou
Accepting the Art of Getting Up ====================== ፧ Failure frequently appears as a black thread against the vivid colours of joy and achievement in the complex tapestry of life. However, beneath this gloomy hue comes the underlying reality that failure is a turning point rather than a point of no return. ፧ A journey through life is replete with missteps and falls. Every error and every loss appears to reverberate with the weight of failure. But our ability to get back up after falling is what makes humans unique, not the act of falling. ፧ The allure of a new beginning is that it can be made at any time. It is the first blossom following a hard winter, the peaceful daybreak following a long, stormy night. We command the chisel, we hold the brush. ፧ So, enjoy the missteps and love the falls. Perceive every setback as a learning opportunity, a mark on the masterpiece that is your life. Because you portray the picture of an unbroken, always changing, and infinitely beautiful soul. Have a blessing day😊

አንድ ወዳጄ ይሄን ጥያቄ ጠየቀኝ። እውነት ነው አባትን ማጣት ህመሙ ከባድ ነው። ሁላችንም ጥያቄዎች ይኖሩናል። በተለይ በእናትና አባት መፋታት፤ በትዳር መፍረስ የሚመጣው ህመም ለመቋቋም በመታገል ሂደት ውስጥ። አባታችን ለምን አይፈልገንም? በጣም ጥሩ ልጆቹ ኮ ነን እንዴት ጨከነብን? ልፋቱን በፍቃዱ ከንቱ ያደረገው ስለምንድነው? የእርምትና የክትትሉን ውጤት፤ የአብራኩ ክፋዮችን የመጨረሻውን መጀመሪያ ለማየት ያልፈለገው በምን ምክንያት ነው? እናቴ ኮ ይሄ አይገባትም ለምን ጨከነባት? ለምን በበደል ተለያት? ለምን ብቻዋን ተዋት? እንል ይሆናል። ሀቁ ግን ጠንካራና ጀግና እናት ያለው አባት አያስፈልገውም። ምክንያቱም የወለደ ሁሉ አባት አይደለምና! @melos3 @melos3

መጨነቅ ሳይሆን «ማሰብ» ነው የእኛ አቅም! ነገር ሁሉ ለበጎ ነውና፤ በዙሪያችን ያሉ ስለፈጠኑ እኛ አልዘገየንም። በሰውኛ ጊዜ ሳይሆን በፈጣሪ የስራ ሰዓት እንመን፤ ማርፈድ ከእርሱ ዘንድ የለምና'።
መጨነቅ ሳይሆን «ማሰብ» ነው የእኛ አቅም!  ነገር ሁሉ ለበጎ ነውና፤ በዙሪያችን ያሉ ስለፈጠኑ እኛ አልዘገየንም። በሰውኛ ጊዜ ሳይሆን በፈጣሪ የስራ ሰዓት እንመን፤ ማርፈድ ከእርሱ ዘንድ የለምና'። @melos3 @melos3

ማፅናኛዎችና ሀሳቦቻቸው ይደክሙኛል! የማይገባኝን ዋጋ የተከፈለልኝ እንደሆነ ከራሴ ጋር እንድሟገት ያደርጉኛል። በእርግጥ ከሰው በላይ ለሆነው፥ ባለማመን ለመሸሽ አልሞክርም። ደሞ ከባዱ ነገር በእውቀት
ማፅናኛዎችና ሀሳቦቻቸው ይደክሙኛል! የማይገባኝን ዋጋ የተከፈለልኝ እንደሆነ ከራሴ ጋር እንድሟገት ያደርጉኛል። በእርግጥ ከሰው በላይ ለሆነው፥ ባለማመን ለመሸሽ አልሞክርም። ደሞ ከባዱ ነገር በእውቀት ስም ካለርህራሔ የማራክሰው ነባር ሀቅ። ሀቅ ከእውነት ይበልጣል። ይህን አለመቀበሌ ውስጤን ያርደዋል። ጠፍቻለሁ? ምናልባት ይህን ስለምታዘብ ይሆን? ፡ ምክንያቱ ለውጤቱ የገዳል-ማሚቱ የሆነ እውቀት መሳይ የሰዋሰው ግርግር፤ ፡ ፋይዳ ቢስ፣ መመዘኛው ግለ-ተኮር የምክር ጋጋታ፤ ፡ ካልተኖረ ህይወት የሚቀዳ፥ መንገድ ጠራጊነኝ የሚል ተግሳፅ ቢጤ ጫጫታ፤ ፡ ቃሉን እየወደደ፣ እየሰማ፥ እየኖርኩት ነው እያለ የትንቢት መፈፀሚያነትን የሚሸሽ አማኝ እና የሀይማኖት አባት፤ ፡ እርግማንን በሳቅ የሚቀበል ትውልድ፤ ፡ ህልምን፣ ፍላጎትና እቅድን ከገደል የሚከቱ ህሊና እና ሆድን ማግባባት የቸገራቸው መሪዎች፤ ፡ የፀጉራቸው ቀለም የነጣ፥ እድሜ ያከበራቸው የባለ አንቱታዎች ምርቃት መሳይ የግል ምኞት፤ ፡ ክብርን ለመስጠት ከሰውነት ክብር መጉደል፤ ፡ በስመ' መሰዋዕትነት ከእራስ ጉድለት ላይ የባሰ መጉደል፤ ፧ ከእለት ተእለት የህይወት ቅኝት፤ ከማሰብ ከመብከንከኑ፤ ለዚህ ሁሉ ትዝብት መፍትሔ የሚሆን አንድ ጠጠር መጣል ያቃተኝ እኔ! ጠፍቻለው? እናንተስ? መልካም ሰኞ፤ በቸር ያውለን🤲 እያነበብን! @melos3 @melos3

ያመኑት ፈረስ በደንደስ እንዲሉ ጥርጣሬ ልኩን አይለፍ እንጂ ጉዳት የለውም ክፋትም አይደለም። በተለይ ደሞ በዚህ ዘመን። አምኖ በመከዳት ያሳለፍኩትን ያሳለፈ የምለውን ነገር በደንብ ይረዳዋል። ለዛም
ያመኑት ፈረስ በደንደስ እንዲሉ ጥርጣሬ ልኩን አይለፍ እንጂ ጉዳት የለውም ክፋትም አይደለም። በተለይ ደሞ በዚህ ዘመን። አምኖ በመከዳት ያሳለፍኩትን ያሳለፈ የምለውን ነገር በደንብ ይረዳዋል። ለዛም ነው የሀገሬ ሰው «ያመኑት ፈረስ በደንደስ» ብሎ የተረተው። በሌላ አባባል «ባጎረስኩ ተነከሱ» የሚተካው ይመስለኛ። ያለምንም ገደብ፣ ሀሳብና ከልካይ የሚታመነው ፈጣሪ ብቻ ነው። ለሰው ልክ ያስፈልገዋል። መከልከል ያለበት ብዙ አለ። ልብ ሙሉ ለሙ ክፍት አይደረገም። ይገባው' እንደሆን መጠናት አለበት። ምክንያቱም ሰዎች በፍላጎታችን የምንመራ፤ በነበርንበት ሁኔታና ጊዜ ፍልስፍናችንም፣ ርእዮተ አለማችንም፣ እቅድና ውጥናችን የሚለዋወጥ ከውሻ ያነሰ ታመኝነትን ያነገብን ብኩን ፍጡራን ነን። አይምሰልህ ወዳጄ አንዳንድ ሰዎች የሚታመኑት አንተ ላይ ላላቸው ፍላጎት ነው። ይህ ማለት በአጭሩ ከአንተ የሚፈልጉትን ካገኙ በኋላ ፍላጎታቸውን እንዳሳኩ ታማኝነታቸው ያበቃል። so ነቃ በል🙂 ከስህተት መማር፤ ከመውደቅ መነሳት፤ በማንበብ መሻል፤ በመሞከር ማወቅ ከሁሉም በላይ የራስን ዋጋ መረዳትና በተረዳኸው ልክ ለአዲስ ትግል እራስን በማዘጋጀት፤ በማብቃት ውስጥ መኖር። መራጭ እንሁን። ሁሉን አንቀበል፤ ሁሉን አንመን። ህልም፣ ምኞት፣ ሀሳብና ውጥን እንዲሁም ጊዜን አናግበስብስ እንኳን እኔና አንተ፥ ❝ንስር የበሰበሰ አይበላም❞።

በጸጥታ የመሰናበቻ ጊዜያት፣ የትዝታ ሹክሹክታን አንድም በደስታ አንድም በሀዘን ስስ ክሮች በልባችን ውስጥ ሸምነው ያቆያሉ። እያንዳንዱ መሰናበቻ ክብደትን የያዘ፣ በተለያዪ ነፍሳት እንደየ ቋንቋቸው የ
በጸጥታ የመሰናበቻ ጊዜያት፣ የትዝታ ሹክሹክታን አንድም በደስታ አንድም በሀዘን ስስ ክሮች በልባችን ውስጥ ሸምነው ያቆያሉ። እያንዳንዱ መሰናበቻ ክብደትን የያዘ፣ በተለያዪ ነፍሳት እንደየ ቋንቋቸው የሚዘፈን የስሜት ዜማ ነው። በዚህ ሁኔታ፥ በጋራ ሳቅ ላይ ፀሀይ ስትጠልቅ፥ በእንባ የሰውነታችንን ትስስር እንረዳለን። ጊዜያዊ ተፈጥሮን እንቀበላለን። በስንብት ክንዶች ውስጥ፥ እኛን የገለፁልንን ምዕራፎች ላለመልቀቅ፣ ለመንከባከብ እና ለማክበር ድፍረትን እናገኛለን። ስንብት ፍጻሜ ሳይሆን ለውጥ የሚያመጣ ቆም ማለት ነው። ከምን መሰናበት እንዳለብን ማሰብና ምርጫው ላይ ብልህ መሆን አስፈላጊ ቢሆንም እውነታው፤ ወደድንም ጠላንም ከአንዱ ባህር ዳርቻ ወደ ሌላው የሚያደርሰን ድልድይ ነው። ለዛም ነው በፍፃሜው ለአዲስ ጅምር መንገድ እንደሚጠርግ በመረዳት መጽናኛ የምናገኘው። ማንነት ይቀየር አይቀየር ምላሹ ወይም የፍፃሜው መደምደሚያ በምርጫ የሚቃኝ ቢሆንም ያለፈው የተተወው ባህሪ ግን ለዛሬ አዲስነት የጠባሳው ክብደት ቀላል አይደለም። ምክንያቱም ከትናት በዛሬ ወደ ነገ መሰደድ በምርጫ ሳይሆን በሁኔታዎች ጭካኔ በነፍስ ውስጥ ጥልቅ ቁስሎችን የሚተው ጉዞ ነው። ሆኖም፣ በስንብት መሀከል፣ በችግር ጊዜ የተስፋ ብርሃን የሆነ ጠንካራ መንፈስ ብቅ ይላል። የሀዘን ነበልባልን መቋቋም፣ መልሶ ለመገ'ንባት የሚያስችል ጥንካሬ እና ባልታወቁ እውነቶች ውስጥ አዲስ ጅምርን ለመጓዝ ቁርጠኝነትን ያላብሳል። so መተው ያለብንን እንተው፤ ማቆም ያለብንንም እናቁም፤ መሰናበት ያለብንን እንሰናበት። እናቴ ሁሌ እንደምትለው፤ ❝ጀምበር ስትጠልቅ ይመሻል እንጂ አይጨልምም።❞ ሁላችንንም የነፍሳችን ባለቤት የሆነው ፈጣሪ ይጠብቀን፤ ያበርታን🤲 መልካም ምሽት።

ሀላፊነት ዘርፈ ብዙ ነው። አይነቱም እንደየስራው ባህሪው ይለያያል። ያለባችሁን የስራ ሀላፊነት ሳትበድሉና በአግባቡ እየተወጣችሁ፥ ለቤተሰብ እምነት መብቃት፤ ለታናሽ ወንድምና እህቶች አረአያ መሆን፤
ሀላፊነት ዘርፈ ብዙ ነው። አይነቱም እንደየስራው ባህሪው ይለያያል። ያለባችሁን የስራ ሀላፊነት ሳትበድሉና በአግባቡ እየተወጣችሁ፥ ለቤተሰብ እምነት መብቃት፤ ለታናሽ ወንድምና እህቶች አረአያ መሆን፤ እውቀትን፣ ሀሳብን፣ ጊዜን ለቤተሰብ የተሻለውን መፈለግና ተግባራዊ እንዲሆን መጣር ላይ እንደማዋል ግን የሚያስደስትና ከባድ ሀላፊነት የለም። ይህ ፅሁፍ የሚገልፃችሁ ሁሉ ለእናንተ ያለኝ አክብሮት ከፍ ያለ ነውና፥ በርቱ እንበርታ🙂

“እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።”   — ማቴዎስ 28፥6 እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሠላም አደረሳችሁ!! ፧ @melos3 @melos3

❝ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሳዕና በአርያም እያሉ ይጬኹ ነበር ፦ ማቴ 21 ÷ 9❞                   ፧ «እባክህ እርዳ አሁን አድን»።🤲                   ፧ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።🙏

እየበረታን ወገን😊 በልካችን እንቀሳቀስ፤ ነገ የነገ ነው!
እየበረታን ወገን😊 በልካችን እንቀሳቀስ፤ ነገ የነገ ነው!

የማንችለው ብዙ ነገር አለ!
የማንችለው ብዙ ነገር አለ!

~ሕልሞችህ ላይ መንቃት፥ በመካከላቸው መመላለስ፤ በውስጣቸው መኖር እፈልጋለሁ፡፡ ድንቅ ሕልሞችህ ላይ፡፡እውንህ ላይ ብቻ መኖሬ አይበቃኝም ያንሰኛል፡፡እውን ነጠላ ነው!!ሌጣ ኑረት! ብዙ አለመቻሎች ፡በርካታ ጉድለቶች፡ አያሌ እንከኖች አሉበት!! ፧ በእውን እግር ተራማጅ እንጂ በራሪ አይደለም፡፡እግር ክንፍ አይደለም። በእውን አይን፥ ከግድግዳ አልፎ ከመጋረጃ ጀርባ፥ ከአድማስ ባሻገር ተሻግሮ አያይም!! የተከደነን፣ የተዘጋን፣ የታሸገን አልፎ በውስጥ ምን እንደሚገኝ አያይም። ፊት ለፊቱ የተደቀነን የተገሰጠበትን ያልራቀውን ብቻ ነው የሚያየው፡፡ ፧ በእውን ጆሮ የራቀን አይሰማም። ከየትዬ የለሌ የሚዜምን ጣፋጭ ማኅሌት አያደምጥም። ከሰባተኛው ሰማይ የሚመጣ፤ የሚያድነው ቃል የእውን ጆሮ ጋር አይደርስም፡፡ ያልተወራን አይሰማም፡፡ የእውን ጆሮ ከአጠገቡ የራቀን ድምፅ አይሰማ አይለማ፡፡ በእውን ልብ አይጨበጥም። አስደናቂ ፍቅሩና መሰጠቱ፥ በእውን ልብ በመዳፍ መካከል አይያዝም!!በእውን አካል ከገለባ የቀለለ፤ ከላባ የሳሳና የለሰለሰ አይሆንም፡፡አካል ጠጣርና ግዙፍ ነው። በእውን አካል ሲጠበድል ቋጥኝ፥ ሲኮሰምን ጠጠር ነው። በእውን፡ሲመቸው ትንቡክ፤ ድሎት ሲርቀው ጋጥ ባይ ነው አካል በእውን አየህ?!.....።ለምን ሕልምህ ላይ መንቃት እንደምፈልግ!? ሕልም ብዙ የማይቻሉ ነገሮች የሚቻሉበት ነው፡፡በተለይ፡ የእንዳንተ አይነቱ ድንቅ ሕልም ሲሆን፤ እራሱ ሕልሙ ይዋባል፡፡ ፧ <የቆንጆ ሕልም የተዋበ ነው!! ከቁንጅናዋ ወዘና ሩሑን ይጠነስሳል፤ ከውበቱ ናሙና ነፍስያውን ይቀምራል....።> #redu 21/06/16 (9:32) @melos3

❝በጣም ነው የምወድሽ ሲል አንድ አፍቃሪ፥ ከስሜቱ ፍስት ውስጥ የደስታውን ሲቃ እንደምትሰሚው፤ የልብ ምቱን እንደምታደምጪው፤ ስስቱን ከአይኑ እንዳታነቢ ቅንድቡን ወደታች ቢያደርግ፥ ሽፋሽፍቱን ቢገጥም፥ ከብሌኑ መንቀልቀል ሁሉን እንደምታቂ ፤ በአንደበትሽ ሸኝተሺው በአይንሽ እንደምትመልሺው ...እ.... ፤ እንደሱ ነው የምወድሽ አላት፡ ማፍቀሩንማ ከከንፈሩ ቀምሳለች😊❞ ©ezra kassahun 21/06/16 ምሽት 3፡43

የኢትዮጵያውያን የድል በአል ፤ የአፍሪካውያን የነፃነት አርማ ፥ አድዋ! ፧ 128ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን።

ዝናብ መልክ ያለው ይመስለኛል። ጠብታዎቹ ሁሉ ቀለም ያላቸው። ልክ እናት ውስጥ ያለው የፍቅር ወጥነት አይነት፤ መገለጫው ፤ መንገዱም ግን እንደሚለያይ ምንድነው የማወራው ግን? አንዳንዴ ያፈላስፈኛል መሰለኝ! ፧ ብቻዝናብ ሲዘንብ ካፊያም፡ ይሁን ዶፍ ከመብረቁ ፥ ከነጎድጓዱ ይልቅ ብልጭታው ያስፈራኛል ፤ መንፈሴን ይረብሸዋል ፤ ቀልቤንም ቆሌዬንም ነው የሚገፈው ( ቆሌ ግን ምንድነው😑) ደሞ ፈሪዬ መሆኔን ለማላምን እኔ፤ ብርሀን፥ ብልጭታ ያስፈራኛል። ቢገርመኝም ግን አይደንቀኝም ምክንያቱም ሁላችንም ፈሪዎች ነን (ብቻዬን አለመሆኔ 😂) ፧ ብቻምክንያቴ ምን መሰላችሁ፤ እንዴት እንደተገናኘ ባላቅም በህይወቴ ስለተከሰቱን ብልጭታዎች ተስፋቸው እንደ ነጎድጓዱ፥ ስለሆኑ ሁነቶች ስለሚያስታውሰኝ ነው መሰለኝ ...፤ ፧ ደሞ ሌላ እናቴ ስለምትለኝ አንድ የህይወት የኑሮዋኣ አባባል ማስረጃም ስለሚሆን መሰለኝ «ሰው እንደ አበባ ነው፤ እንዳይጠወልግ ተስፋ ብቻውን በቂ አይደለም»። ነጋቸው ከዛሬ ስለገዘፉ፥ የስኬታቸው የገደል ማሚቱ ለእኔ እፉዬ ገላ ነፍስ፥ ከመሰወሪያነት የሚበልጡ አንዳንድ ሁናቴዎች ስለሚያስታውሰኝ ይሆናል.. ፧ ብቻ ፧ ©ezra kassahun 21/06/16 ተስፋ ቡና 4kilo(7:25) @melos3 @melos3

እኔ አልተኛም ፥ መቆም ግን ይቆማል 😉 ፧ @melos3

እውነቴን ነው!

የታሪክ አባት ፤ ያለፈውን ዘመን አቅርቦ የትውልድን ገድል ሳይቀንስ ሳይጨምር አንድም እያዝና አንድም እያስተማረ እውቀቱን ያካፈለ ፤ ደራሲ ፣ ገጣሚ ፣ ጋዜጠኛ ፣ እግርኳስ ተጫዋች ፣ ግንበኛና እሯጭ
የታሪክ አባት ፤ ያለፈውን ዘመን አቅርቦ የትውልድን ገድል ሳይቀንስ ሳይጨምር አንድም እያዝና አንድም እያስተማረ እውቀቱን ያካፈለ ፤ ደራሲ ፣ ገጣሚ ፣ ጋዜጠኛ ፣ እግርኳስ ተጫዋች ፣ ግንበኛና እሯጭ በተለይም በሊብሮ መፅሔት አዘጋጅነት የምናውቀው ይርጋለም ተወልዶ ሻሸመኔ 09 ቀበሌ ያደገው እንቁ ሰው ገነነ መኩሪያ ከዚህ አለም ድካም በሞት ተለየን። ለመላው ቤተሰብ መፅናናትን ያድልን።

❝ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ እምቅድስት ድንግል ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ❞ ፧ እንኳን ለጌታችን ፥ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ፍቅር ይበርክት ፤ ተስፋ ያብብ፤ ስራ ይብዛ ፤ ሀገር ሰላም ይሁን። ፧ መልካም በዓል! @melos3 @melos3

እግዜር እና ሰው የሻይ ቡና ጨዋታ ፧ ሰው ጠያቂ፦ አምላክ ሆይ 100 ዓመት በአንተ                  ዘንድ ስንት ነው? ፧ መላሽ ፈጣሪ፦ በእኔ ዘንድ 1ደቂቃ ነው...፤ ፧ ሰው ጠያቂ፦ 100ሺ ብር ለአንተ ስንት ነው? ፧ መላሽ ፈጣሪ፦ 10 ሳንቲም...፤ ፧ ሰው ጠያቂ፦ እሩሩ ፥ ቸር ነህና 10 ሳንቲም                  ስጠኝ 🙄 ፧ መላሽ ፈጣሪ፦ እሺ 1ደቂቃ ጠብቀኝ 😉 @melos3 @melos3