ተቅዋ የሱና እና የተውሒድ ቻናል
الذهاب إلى القناة على Telegram
ተውሒድና ሱና የአንድነት ምንጭ ሲሆኑ ሺርክና ቢድዓ ደግሞ የልዩነት ምንጭ ናቸው። ስለዚህ ተውሒድና ሱና አጥብቀህ ያዝ ሺርክና ቢድዓ ደግሞ በእጅጉ ራቅ አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በደጋግ ቀደምቶች መንገድ አረዳድ ተረድተው ከሚጓዙ ምርጥ ባሮቹ ያርገን
إظهار المزيد1 295
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
-2730 أيام
أرشيف المشاركات
1 295
ይድረስ!
~
1- ይድረስ ሚስትህን ለፈታኸው፡
ልጆችህን ለዒድ አስበሃቸዋል? ወይስ እነሱንም ከእናታቸው ጋር ፈተሃቸዋል?
2- ይድረስ የየቲሞች አጎት ለሆንከው፡
የሟች ወንድምህን ልጆች ትጠይቃለህ? ወይስ ከቀበርከው ወንድምህ ጋር ረስተሃቸዋል?
3- ይድረስ ባሏ የሞተባት እህት ያለችህ:
እህትህን ትኑር ትሙት ጠይቀሀል? በልታለች ወይስ ተርባለች? ወይስ እህትነቷ ቁጥር ብቻ ነው?
ይድረስ ለሁላችን፡
እጃችንን የሚጠብቁ፣ ከኛ የቀረበ ሰው የሌላቸው ቤተሰቦቻችን በምን ላይ ናቸው? በዒድ በምን መልኩ እንዲያስታውሱን እንፈልጋለን? ያቅማችንን ያክል ከልባቸው ውስጥ ደስታ ማስገባት ያሳስበናል? ወይስ ሀዘን ትካዜያቸው ምንም አይመስለንም?!
-
ተነካክቶ ከዐረብኛ የተመለሰ
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 295
ሰዑዲያ ነገ ረቡዕ ረመዷን የረመዷን የመጀመሪያ ቀን እንደሆነ አውጃለች። እንኳን አደረሰን። አልሐምዱ ሊላህ ቢኒዕመቲሂ ተቲሙ ሷሊሓት!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 295
* የሰው ሐቅ ተሸክመህ ወደ ረመዷን አትግባ። መክፈል እየቻልክ የሰው ሐቅ ይዘህ አታጉላላ። አቅቶህ ከሆነ ጊዜ እንዲሰጡህ በትህትና አስረዳቸው። እየቻልክ ከሆነ ስላዘገየህ ይቅርታ ጠይቀህ፣ ለውለታቸው አመስግነህ መልስ።
* የበደልከውን ይቅርታ ጠይቅ። ነገ ከባድ ቀን ነው።
* የበደሉህን ይቅር በል። በይቅርታ ውስጥ ብዙ ኸይር አለ።
* መክፈል የማይችል ሰው ላይ ሐቅ ካለህ ብትችል እለፍ ወይም ቀንስላቸው። ካልሆነ ጊዜ ስጣቸው። "የትም ገብታችሁ አምጡ" አትበል። ወንጀል ላይ ገብተው ቢሰጡህ ሐላል አይሆንልህም።
* ስትሸጥም ስትገዛም ገር እና ቅን ሁን። ገዥም ሻጭም ሆነህ ሶደቃ የምታደርግበት ሁኔታ እንዳለ አስተውል።
* ግብይትህ ላይ ከውሸት፣ መሀላ ከማብዛት፣ ከማታለል፣ ... ተጠንቀቅ። ጊዜ ካለህ ቁርኣን ቅራ። ዚክር አድርግ።
* ቤትህ ውስጥ ሰላም ሁን። ከጭቅጭቅ ራቅ። ሶብር ይኑርህ። ለሚስትህ፣ ለልጆችህ አሳቢ፣ ተቆርቋሪ ሁን። ከአላህ በታች ያላንተ ማን አላቸው? ለባልሽ ምቹ ሁኚ። አንቺ ፈተና ከሆንሽበት ውሎውን ሁሉ ሰላም ያጣል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 295
ቁርአን እየቀራህ እንቅልፍ እንቅልፍ የሚልህ ከሆነ፤ ቂርአት እየቀራህ የሚሰለችህ ከሆነ፤
ስራ ስትሰራ ዝም ብሎ ሚደክምህና ሰውነትህ ልፍስፍስ የሚል ከሆነ ከአይነ ናስ ምልክቶች መካከል ነውና ለራስህ ሩቃ አድርግ። የጠዋት የማታ ዚክር ላይ ጠንክር፣ ቁርአን በኢባዳና በሩቃ ንያ አብዝተህ ቅራ ፍቱን መድሀኒቱ ይህ ነው።
=
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
1 295
✍ተገላልጠሽ ወተሽ የዛሬ ጊዜ ወንዶች አትበይ
ሰተር በይና የዛኔ የዛሬ ጊዜ ወንዶች ትያለሽ።
ምክኒያቱም እንደፈለግሽ ተገላልጠሻል።
ማሳበበያ የለሽም።
1 295
የእኛ የሰው ልጆች ትልቁ ጥበብ ጌታ አላህ /ሱ.ወ/ መፍራት ሲሆን ትንሹ ጥበባችን ደግሞ ራሳችንን ማወቅና በምንችለው አቅም ልክ የሚመጥነን የሆነን መልካም ነገር መፈፀም ነው
1 295
የእኛ የሰው ልጆች ትልቁ ጥበብ ጌታ አላህ /ሱ.ወ/ መፍራት ሲሆን ትንሹ ጥበባችን ደግሞ ራሳችንን ማወቅና በምንችለው አቅም ልክ የሚመጥነን የሆነን መልካም ነገር መፈፀም ነው
1 295
ከሰለፎች አንደበት
~
ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ "እስቲ ዱንያን ግለፅልን?" ተብለው ተጠየቁ።
* ''ላስረዝም ወይስ ላሳጥር? " አሉ።
- "አይ አሳጥር" አሏቸው።
* "ሐላሏ ሒሳብ አለበት። ሐራሟ እሳት አለበት" አሉ።
[አዙህድ፣ ኢብኑ አቢ ዱንያ፡ 17]
ወዳጄ! ከሐራም ተቆጠብ። በሐላል ሪዝቅህ ደግሞ አላህ ግዴታ ያደረገብህን ግዴታ ተወጣ። ባልተገባ ቦታ አታውጣው። ገንዘብ ለማይጠቅምበት ቀን ለነገ ስንቅ የሚሆንህ ኸይር ስራ ላይ ተካፈልበት።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 295
اسلام عليكم ورحمتالله وبركاته
የሚሸጥ የቆየ ግሩፕ ያላችሁ
2021
2022
ወይም 2023 ያለው ስለምገዛ በውስጥ ያላችሁ በውስጥ አዋሩኝ👇👇👇
@ibnidrisimam
@ibnidrisimam
1 295
⎗ كونوا رجالا....!
⎘ ወንድ ሁኑ !
وصونوا بناتكم وحافظوا عليهن وعلموهن وأدبوهن وراقبوهن ولا تتركوا لهن المجال في الإنحراف والخروج عن #الآداب_الإسلامية .
« ሴት ልጆቻችሁን ጠብቁ፣ አስተምሯቸው፣ገስጿቸው እና ተመልከቷቸው፣ ከኢስላማዊ ሥነ ምግባርም እንዲያፈነግጡ እና እንዲርቁ አትፍቀዱላቸው።
☈ t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
1 295
🎴ብዙ የሚመክርህ ሰው እኮ
ችግርን በድንብ ያየው እና
በብርቱ የተማረበት ሰው ነው
ትክክለኛው መካሪ ማግኘት መታደል ነው🟣
📝ግን እቢሊስም በሰው ተመስሎ ይመክር
እንደነበረ አንርሳ✔️
1 295
*የዱንያ ነገር!!*
~
ዐሊይ ብኑል ሀይሠም እንዲህ ይላሉ:–
"አምሳያ ያላገኘሁለት የዘመን መገለባበጥ፣ የጊዜ መለዋወጥ አይቻለሁ።
★ የአልፈድል ብኑ ረቢዕ ንብረት በአንድ ሺህ ግመል ተጭኖ አይቻለሁ። ሌላ ጊዜ ግን ደህይቶ ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተደብቄ አይቻለሁ። በውስጧ መድሃኒቶቹ ተጨምረው።
★ አልሐሰን ብኑ ሰህልን ደግሞ ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተመልክቻለሁ። ሌላ ጊዜ ግን ሀብታም ሆኖ ንብረቱ በአንድ ሺ ግመል ላይ ተጭኖ አይቼዋለሁ።"
||
ሱብሓነላህ!!
ዱንያ እንዲህ ነች። መርጋት የማታውቅ ወላዋይ!!
♣️ ሃያላን ይዋረዳሉ። ደካሞች ይነግሳሉ።
♣️ ሀብታሞች ጎዳና ላይ ይወድቃሉ። ምንዱባን በሰማይ ጠቀስ ህንፃ ይንፈላሰሳሉ።
♣️ ሳር ቅጠሉን የተፀየፈው ጨፍ .ጫፊ አረ .መኔ አለም ጠብባው ከአይጥ ጎሬ ሲያደፍጥ ታየዋለህ። የትላንቱ ተሳዳጅ ተራውን ሲያሳድድ ትመለከታለህ።
® ይቺው ነች ዱንያ!! ብልጭ ብላ ድርግም፣ ቦግ ብላ እልም የምትል። ሁሌ ሳቅ የለም! ሁሌ ድል የለም።
|
♣️ በድር ላይ ለያዥ ለገናዥ ያስቸገሩ፣ ጥጋብ ያስከራቸው ቁረይሾች፣ 70 መኳንንቶቻቸው ትላንት ሲያሳድዷቸው በነበሩ ሶሐቦች ሰይፍ ተበልተው፣ ሌላ 70 ደግሞ በምርኮ አስረክበው የሐዘን ማቅ ለብሰዋል። መካ በዋይታ ተንጣለች።
|
♣️ ኡሑድ ሌላ ቀን ነው። ሌላ ተራ!! አጋሪዎች የፈነደቁበት፣ እነ ሐምዛን፣ እነ ሙስዐብን ጨምሮ ከ70 በላይ ታላላቅ ጀግኖች ወድቀው ሌላ 70 የቆሰሉበት፣ አሳዝኝ ክስተት እውን የሆነበት ቀን። ሶሐቦች አካላቸው በስለት፣ ልባቸው በሐዘን ቢቆስል ጊዜ አላህ እንዲህ ሲል አሳሰባቸው: –
(إِنْ يَمْسَسْكُمْ قَرْحٌ فَقَدْ مَسَّ الْقَوْمَ قَرْحٌ مِثْلُهُ ۚ وَتِلْكَ الْأَيَّامُ نُدَاوِلُهَا بَيْنَ النَّاسَ)
"ቁስል ቢያገኛችሁ ሰዎቹንም መሰሉ ቁስል አግኝቷቸዋል፡፡ እናም እነዚህን ቀናት በሰዎች መካከል (በመልካምና በሌላ) እናቀያይራቸዋለን፡፡" [ኣሉ ዒምራን: 140]
|||
ዱንያ አመሏ ነው። ዛሬም እንዲሁ ናት።
ግን ማነው የሚማረው? ግን ማነው የሚመረምረው? ግን ማነው የዱንያን ከንቱነት ተገንዝቦ ለዘላለም ቤቱ ከልብ የሚጨነቀው?
እስከ መቼ ነው የምናንቀላፋው?
እስከ መቼ ነው የምንዘናጋው?
እስከ መቼ ነው በከንቱ የምንባዝነው?
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!
ኢላሂ ልብ ስጠን!
=
የቴሌግራም አድራሻ
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 295
እየተስተዋለ!
~
ላይክ አጅርም ወንጀልም ይኖርበታል። የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማችንን እያስተዋልን። ወንጀልን፣ ጥፋትን ፣ ክፋትን በላይክ፣ በኮመንት መደገፍና ማሰራጨት በስራ መዝገባችን ላይ ወንጀል ማስመዝገብ ነው። ጥፋት በማስራጨት፣ ዲንን በመጉዳት፣ ሹቡሃ በመንዛት፣ አጥፊዎችን በማስተዋወቅ ላይ የተሰማሩ አካላትን ፎሎው፣ ላይክ፣ ሰብስክራይብ፣ ጆይን፣ ... ማድረግ ለጥፋታቸው እገዛ መስጠት ነው። ስለዚህ ከንዲህ አይነት ገፆች ወይም አካላት ዛሬ ነገ ሳንል በጊዜ እንራቅ።
በሌላ በኩል የዲንም ይሁን የዱንያ ጠቃሚ ትምህርቶችን ስናገኝ በላይክ፣ በኮመንት፣ በማሰራጨት እናግዝ። ይህንን ማድረግ አጅር እንዳለው አይረሳ። ሶደቃ መልኩ ብዙ ነው። ላይክና ሼር ምን ያህል ነው ወጪው? አምስት ሳንቲም ላናወጣበት አጉል እንሰስታለንዴ? ብንሰስት እኛው ነን የሚቀርብን። ኸይር በማሰራጨትና በመደገፍ የሚገኘው አጅር ነው የሚያልፈን። ስለዚህ በምንገኝባቸው ፕላትፎርሞች ሁሉ ወገናቸውን ለመጥቀም ደፋ ቀና እያሉ ያሉ አካላትን ስራቸውን እንደግፍ። እዚህ ግባ የሚባል ቁም ነገር የሌላቸው እንቶ ፈንቶዎች በሺ፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ላይክና ቪው እያገኙ የቁም ነገር ስራዎች የተመልካች ድርቅ ሲመታቸው ማየት አሳፋሪ ነው።
ብቻ ለራሳችን ለነጋችን ስንል እንወቅበት። ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ይላል :-
{ فَمَن یَعۡمَلۡ مِثۡقَالَ ذَرَّةٍ خَیۡرࣰا یَرَهُۥ (7) وَمَن یَعۡمَلۡ مِثۡقَالَ ذَرَّةࣲ شَرࣰّا یَرَهُۥ (8) }
"የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል። የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል።" [አዘልዘለህ: 7-8]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
