የጥበብ እመቤት 📜
الذهاب إلى القناة على Telegram
╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
270
المشتركون
+224 ساعات
+107 أيام
+15330 أيام
أرشيف المشاركات
270
270
ህይወት ስታስጠላህ እና ስትሰለችህ ታሪክህን ለሁሉም አትዘርዝር።ነገር ግን ለእውነተኛ ጓደኛ አማክር። ሲደብርህ የፊትህ ፈገግታ ጠፍቶ ሴለሚታይ ብዙ አስመሳይ ሰወች ምን ሁኖ ነው አያሉ ሊስልሉህ ይችላሉ በዚያ ስአት የህይወት ታሪክህንና ገመናህ ለሁሉም ሰው አትዘርዝር የሳቁልህ ሁሉ ከውስጥ አይደለም። ይሉቁን ያንተን ዋጋ ለሚያውቅ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለሚረዳህ ለአንድ እውነተኛ ወዳጅ ወይም ለቤተሰብ ደውለህ ተጨዋውት ልብህን በፈገግታ ከሚመርዙ ሳይሆን ካንተ ጋር በቁርጠኝነት ከሚቆሙት ጋር አድርገው።
270
የፍላስፎቾ ንግግር... 🗣️
ሀብታም የደከያል ሀኪም ይሞታል
ጎበዝ ይሸነፋል ብልህ ይሳስታል
የበራውን ጠፍቶ የሰሩትን ይፈርሳል
የቆመው ወደቆ የሳቀ ያለቅሳል
ግጥም ሆነ #ጥበብ 💫
ውበት ሆነ ክብርም
ያማረበት ነገር ማስቀየሙ አይቀርም ✨
270
ሁሉ ሴት የብር ወይ የጥቅም አይደል እንደዝቺ አይነት ልባም ሴት አፍቃሪ አለቺ።
ፍቅር በምንም አይነት አይገዛም አይለወጥም 🥰
እግዚአብሔር የተባረከ ትዳር ያደርግላችኋል
ትክከለኛ ፍቅር ማለት እንደዚህ ነው 🙏❤🥰
270
ሁሉን ነገር ለፈጣሪ መስጠት የሚያመጣው ትልቁ ስጦታ ሰላም ነው።
መለወጥ የማትችለውን በፀጋ ተቀብለህ ለፈጣሪ ስትሰጠው፣ ልብህ ይረጋጋል፣ እንቅልፍህ ይጣፍጣል፣ ደስታህም ይሞላል።
ሁሉን ነገር መቆጣጠር አይጠበቅብህም፤ መታመን ብቻ ይበቃል።
ለፈጣሪ የተሰጠ ሸክም ይቀላል፤ ለፈጣሪ የተሰጠ ልብ ደግሞ በሰላም ይኖራል። የከበዳቹህ ነገር ካለ ለፈጣሪ ስጡት
270
➨#ወዳጄ_ሆይ_አስተውል
የአንድ ሰው ጥንካሬ የሚለካው በወደቀበት ብዛት ሳይሆን፣ በወደቀ ቁጥር ተመልሶ በመነሳቱ ነው። ማንም ሊያቆምህ አይችልም — አንተ ራስህ ካላቆምክ በስተቀር። ድንጋይ ለመሆን አትሞክር፣ በቀላሉ ይሰበራል፤ ይልቅስ እንደ ውኃ ሁን — ውኃ የገጠመውን አለት አልፎ፣ ሰርጎና ፈልፍሎ መንገዱን ያበጃል። ለስላሳ ሁን ነገር ግን የማይበገር።
#ቻናሉን_ለወዳጆቻችሁ_ሼር_በማድረግ_እንዲቀላቀሉ_አድርጓቸው::
#Never_give_up
270
Repost from የጥበብ እመቤት 📜
"ህይወት እንደ መፅሀፍ ናት፤ አንዳንድ ምዕራፎች ያስለቅሳሉ፣ አንዳንዶቹ ያስደስታሉ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ እጅግ ይፈትናሉ። ነገር ግን አንድ ምዕራፍ መጥፎ ስለሆነ ብቻ የመፅሀፉ ታሪክ አበቃ ማለት አይደለም። ዛሬ ያለህበት ቦታ መጨረሻህ አይደለም፤ የጉዞህ
አንድ አካል እንጂ። በርታ! ታሪክህ ገና አላለቀም።"
270
ያ የምንወደው ትናት እንደቀልድ አለፈ
ዛሬንም አስመስለን አለፍነው!!!
ደግሞ በስስት የምንናፍቀውም ነገ ምናልባት
ላንኖርበት እንችለን-----!?
270
'' አለማወቅ ተስፋ መሆኑን ዘነጋን፡፡ ሰው በተስፋ የሚኖረው ስለማያውቅ ነው፤ ብዙው ነገር የሚሆን የሚመስለን ለዚያ ነዉ፡፡ መንግስት የሚሻሻል የሚመስለን፣ ሌላው ሁሉ ሠው ልብ የሚገዛ የሚመስለን፥ በተስፋ በታጀለ የውሽት እምነት ውስጥ ስንኖር ነው፡፡ የተስፋ ተቃራኒው ተስፋ መቁረጥ መሰለን፤ የተስፋ ተቃራኒው ግን እውነት ነው፡፡ ይህንን ባለማወቃችን በተስፋ ከመኖር አፈነገጥን። እዉነትን አወቅን፡፡ የእውነት ችግሯ ምንድነው?' ብዬ ጠየቅሁት፤....
''የእውነት ችግሯ መልከ ብዙ መሆኗ ነው የሚመስለኝ፥ ቢያንስ ሁለት ፊት አላት፡፡ ሁልጊዜ በጎ አይደለችም፡፡ መራራነቷ ጣዕሟ ነው፡፡....
📚አለማወቅ
270
ህይወት አንደንድ ጊዜ እጅግ ዉስብስብ ፈታኝ እና ግራ የሚያጋባ
ትመስላለች አንደንድ ቀናት እንደ ተራራ ከባድ ሌሎች ቀናት ደግሞ
እንደ ወንዝ የሚፈሱ ሆነዉ ይሰማሉ
ህይወት በምታቀርብልን ፈተናዎች ዉስጥ መማርን ከመረጥን
ምንም ያህል ካባድ ቢሆንም ወደፈት መኀዝ እንችላለን
270
ሕይወት የምትፈትንህ በሸክምህ አይደለም ሸክምህን ተሸክመህ እስከ መጨረሻ መጓዝህን ነው።
ይህን መኪና ስታይ መጀመሪያ የምታስተውለው የተጫነበት ከባድ ሸክም ነው ነገር ግን ሸክሙ ብዙ ስለሆነ ጉዞውን አላቆመም አሁንም መንገዱን ቀጥሎ እየተጓዘ ነው።
እኛም እንደዚሁ ነን የቤተሰብ ኃላፊነት የኑሮ ጫና ያልተነገረ ህመም ያልታየ እንባ... ሁሉንም ተሸክመን በፈገግታ የምንጓዝ ሰዎች ነን።
ሰዎች የሚያዩት ሸክምህን ነው ፈጣሪ ግን የሚያየው ጽናትህን ነው ሰዎች የወደቅክበትን ቀን ሊረሱ ይችላሉ ከወደቅህ በኋላ እንዴት ተነስተህ እስከ መድረሻህ እንደደረስክ ግን ፈጽሞ አይረሱም።
ሸክምህ ቢከብድም ጉዞህን አታቁም ምክንያቱም መድረሻህ ከሸክምህ ይበልጣል።
270
የመጀመሪያ ስህተት ትምህርት ነው…
ሁለተኛው ግን ግዴለሽነት ነው።
ካለፈው ስህተት መማር ካልቻልክ
በገዛ እጅህ ለውድቀትህ እየፈረምክ ነው።
270
ገና ነኝ
ብዙ ዘምርያለሁ ብል ስለ ጌታ ብዙ በአንደበቴ ተናገርያለሁ ብዙ ቅኔ ተቀኝቻለሁ ስለ እርሱ ብዙ ፅፊያለሁ ነገር ግን ገና ነኝ እርሱን በማወቅ ደረጃ ገና ነኝ ምክንያቱም ይሄ ጌታ ከነገር ሁሉ በላይ የሆነ የጠበብ አባት በፍጥረቱ በመግቦቱ በአባትነቱ ያህል ገና አልተረዳሁትም የፍቅር ጅማሬ የሆነውን ጌታ አውቄዋለሁ እል ይሆናል ነገር ግን ገና ነኝ አውቄ አልጨረስኩም
ያን በቃል መግለፅ የማይቻል ጌታ እወድሃለሁ እለዋለሁ እንጂ ከመወደድ ገና ዘግይቻለሁ። ለነገር ሁሉ ገና ነኝ
እኔ ሙሉ ነኝ የምለው እርሱን ለማወቅ በይበልጥ ስተጋ እርሱን በህይወቴ ለመግለጥ ስተጋ ብቻ የእርሱን መልካም ፈቃድ በህይወቴ እንዲገለጥ ስፈቅድ ያኔ ሙሉ ሰው ነኝ
አሁን ግን ገና ነኝ ምንም ትንሽዬ መንፈሳዊእወቀት። ቢኖረኝም ገና ነኝ አዎ ገናነኝ
የ አ ብ
ዕለተ ቅዳሜ በሀሳብ ሰሌዳ ላይ ተፃፈ📜
270
የሰው ልጅ "እሱማ ምን አለበት " አይባልም
ይህች አጭር ቃል በብዙዎቻችን አንደበት ላይ በቀላሉ የምትመላለስ ነገር ግን በሰሚው ልብ ውስጥ ትልቅ ስብራት የምትፈጥር ከባድ ቃል ናት።
ሸክሙን የሚያቀው ባለቤቱ ነው
እያንዳንዱ ሰው እኛ በማናውቀው የሕይወት አውድማ ውስጥ ከባድ ውጊያ እየተዋጋ ነው።
please ሰዎችን ውጫዊ ገጽታቸውንና ሳቃቸውን ብቻ በማየት "አንተማ ምን አለብክ" አትበሉ 😊
