HOP Ministry
الذهاب إلى القناة على Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
445
المشتركون
+224 ساعات
+237 أيام
+6630 أيام
أرشيف المشاركات
445
This World Is Not My Home
Song by Jim Reeves
"This world is not my home
I'm just a-passing through
My treasures are laid up
Somewhere beyond the blue
The angels beckon me
From heaven's open door
And I can't feel at home
In this world anymore
Oh Lord, you know
I have no friend like you
If heaven's not my home
Then Lord, what will I do?
The angels beckon me
From heaven's open door
And I can't feel at home
In this world anymore
I have a loving mother
Just up in Gloryland
And I don't expect to stop
Until I shake her hand
She's waiting now for me
In heaven's open door
And I can't feel at home
In this world anymore
Oh Lord, you know
I have no friend like you
If heaven's not my home
Then Lord, what will I do?
The angels beckon me
From heaven's open door
And I can't feel at home
In this world anymore
Just over in Gloryland
We'll live eternally
The saints on every hand
Are shouting victory
Their songs of sweetest praise
Drift back from heaven's shore
And I can't feel at home
In this world anymore
Oh Lord, you know
I have no friend like you
If heaven's not my home
Then Lord, what will I do?
The angels beckon me
From heaven's open door
And I can't feel at home In this world any more."
445
#ሰማያዊ_መኖሪያችን
2ኛ ቆሮንቶስ 5 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ መኖሪያችን የሆነው ምድራዊ ድንኳን ቢፈርስም፣ በሰው እጅ ያልተሠራ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የሆነ ዘላለማዊ ቤት በሰማይ እንዳለን እናውቃለን።
² እስከዚያው ግን የሰማዩን መኖሪያችንን ለመልበስ እየናፈቅን እንቃትታለን፤
³ በርግጥ ከለበስነው ራቊታችንን ሆነን አንገኝም።
⁴ በዚህ ድንኳን እስካለን ድረስ ከብዶን እንቃትታለን፤ ምክንያቱም ሟች የሆነው በሕይወት እንዲዋጥ ሰማያዊውን መኖሪያችንን ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ አንፈልግም።
⁵ ለዚህ ዐላማ ያዘጋጀን እግዚአብሔር ነው፤ ሊመጣ ላለው ዋስትና እንዲሆነን መንፈሱን መያዣ አድርጎ የሰጠንም እርሱ ነው።
⁶ ስለዚህ ሁል ጊዜ በመታመን እንኖራለን፤ በሥጋ እስካለን ድረስ ከጌታ ርቀን እንደምንገኝ እናውቃለን፤
⁷ ምክንያቱም የምንኖረው በእምነት እንጂ በማየት አይደለም።
⁸ ከሥጋ ተለይተን ከጌታ ጋር መኖርን እንደምንመርጥ ርግጠኛ ሆኜ እናገራለሁ።
⁹ ስለዚህ በሥጋ ብንኖርም ወይም ከሥጋ ብንለይም ዐላማችን እርሱን ደስ ማሰኘት ነው።
2ኛ ቆሮ 5 (1954)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።
² በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና
³ ለብሰን ራቁታችንን አንገኝም።
⁴ በእውነትም የሚሞተው በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ የማንወድ ስለ ሆነ፥ በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን።
⁵ ነገር ግን ለዚሁ የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን።
⁶-⁷ እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥
⁸ ታምነናል ይልቁንም ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር በጌታም ዘንድ ማደር ደስ ይለናል።
⁹ ስለዚህ ደግሞ ብናድር ወይም ተለይተን ብንሆን እርሱን ደስ የምናሰኝ ልንሆን እንቀናለን።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
“ስለዚህ በሥጋ ብንኖርም ወይም ከሥጋ ብንለይም ዐላማችን እርሱን ደስ ማሰኘት ነው።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥9 (አዲሱ መ.ት)
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
https://t.me/hopministry10
445
የሕይወት #scope ሰፊ እንደሆነ ሁሉ ጠባብም ነው። ስፋቱ በምድር ልንኖር በተሰጠን ዘመን የምናልፍባቸው መንገዶች፣ የምንፈጽማቸው ተግባራት፣ የምንደርስባቸው ስፍራዎች፣ የምናገኛቸውና የሚያገኙን ሰዎች፣ ስኬቶች፣ ውጣ ውረዶች፣ ማግኘትና ማጣቶች፣ ክፉና መልካም ነገሮች.... ብዛት ላይ ሲሆን፤ ጠባብነቱ ደግሞ በእግዚአብሔር እንደተጠራና ለእርሱ እንደተለየ ሰው በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የነገሮቻችን ሁሉ ዋና ማእከል ሊሆን የሚገባው #የእግዚአብሔር_ፈቃድ መሆኑ ላይ ነው።
ምንም ሆነ ምን ለእግዚአብሔር ሕዝብ መነሻ ነጥቡም ሆነ መድረሻ ወደቡ #የእግዚአብሔር_ፈቃድ መሆኑና ከፈቃዱ ውልፍት ማለት ግቡ አለመሆኑን ስናስብ የሕይወት #scope ጠባብ ነው ያስብላል። ማለትም እጅግ ዘርፈ ብዙ ነገር እየከወኑ የነገሩን መነሻ ምክንያቱንም ሆነ መድረሻ ግቡን በሰማይ ያለውን የእግዚአብሔር ፈቃድ መፈጸም ላይ መስፋት፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከመፈጸም ውጪ ሌላ ዓላማና ግብ ማጣት እንደማለት ነው።
#በሰማይ_ያለውን_የእግዚአብሔር_ፈቃድ_ለማስፈጸም_በምድር_አለን። ይህ አስተሳሰብ በልባችን ሲሞላ እና አሳባችንን ሲቆጣጠረው ወደ ራሳችን አቅጣጫ፣ ወደ ልባችን መሻት የምንዘረጋበት ፍጥነት እጅግ እየቀነሰ ይሄዳል። ለነገሮች ያለን እይታም የተበታተነና የተዛባ ሳይሆን ስብስብ ያለ እና የእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ የተተከለ ይሆናል።
የሕይወትም ትርጉም ብዙ ነገር አድርጎ፣ ሮጦ...ሮጦ... ከማለፍ እልፍ! ይልና እግዚአብሔር ባሰመረልን መስመር ላይ በማጠብጠብ፣ በፈቃዱ ክልል ውስጥ በመሰንበት ሩጫውን በድል መጨረስ ይሆናል።
በውትድርና የተሰማራ ሰው የጦር አዛዡ ደስታ የልብ ትርታው የሆነ ያኽል እንደሚጠነቀቅለት ሁሉ፤ አዛዣችን እግዚአብሔርም ደስታውን በእኛ ይፈጽም ዘንድ ሕይወታችንን ለእርሱ መሰዋት፣ መሪውንም ለእርሱ መልቀቅ ምንኛ መታደል ነው።
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ ሌላ በምድር የመሰንበቻ ምክንያት እስከምናጣ ድረስ በልቡ አሳብ መጠመድ ይሁንልን!! ፈቃዱ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁ በምድር በእኛ ይሁን!! ለፈቃዳችን ታጥተን፣ ለፈቃዱ ኖረን ማለፍ ይሁንልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 13, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
የሕይወት #scope ሰፊ እንደሆነ ሁሉ ጠባብም ነው። ስፋቱ በምድር ልንኖር በተሰጠን ዘመን የምናልፍባቸው መንገዶች፣ የምንፈጽማቸው ተግባራት፣ የምንደርስባቸው ስፍራዎች፣ የምናገኛቸውና የሚያገኙን ሰዎች፣ ስኬቶች፣ ውጣ ውረዶች፣ ማግኘትና ማጣቶች፣ ክፉና መልካም ነገሮች.... ብዛት ላይ ሲሆን፤ ጠባብነቱ ደግሞ በእግዚአብሔር እንደተጠራና ለእርሱ እንደተለየ ሰው በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የነገሮቻችን ሁሉ ዋና ማእከል ሊሆን የሚገባው #የእግዚአብሔር_ፈቃድ መሆኑ ላይ ነው።
ምንም ሆነ ምን ለእግዚአብሔር ሕዝብ መነሻ ነጥቡም ሆነ መድረሻ ወደቡ #የእግዚአብሔር_ፈቃድ መሆኑና ከፈቃዱ ውልፍት ማለት ግቡ አለመሆኑን ስናስብ የሕይወት #scope ጠባብ ነው ያስብላል። ማለትም እጅግ ዘርፈ ብዙ ነገር እየከወኑ የነገሩን መነሻ ምክንያቱንም ሆነ መድረሻ ግቡን በሰማይ ያለውን የእግዚአብሔር ፈቃድ መፈጸም ላይ መስፋት፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከመፈጸም ውጪ ሌላ ዓላማና ግብ ማጣት እንደማለት ነው።
#በሰማይ_ያለውን_የእግዚአብሔር_ፈቃድ_ለማስፈጸም_በምድር_አለን። ይህ አስተሳሰብ በልባችን ሲሞላ እና አሳባችንን ሲቆጣጠረው ወደ ራሳችን አቅጣጫ፣ ወደ ልባችን መሻት የምንዘረጋበት ፍጥነት እጅግ እየቀነሰ ይሄዳል። ለነገሮች ያለን እይታም የተበታተነና የተዛባ ሳይሆን ስብስብ ያለ እና የእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ የተተከለ ይሆናል።
የሕይወትም ትርጉም ብዙ ነገር አድርጎ፣ ሮጦ...ሮጦ... ከማለፍ እልፍ! ይልና እግዚአብሔር ባሰመረልን መስመር ላይ በማጠብጠብ፣ በፈቃዱ ክልል ውስጥ በመሰንበት ሩጫውን በድል መጨረስ ይሆናል።
በውትድርና የተሰማራ ሰው የጦር አዛዡ ደስታ የልብ ትርታው የሆነ ያኽል እንደሚጠነቀቅለት ሁሉ፤ አዛዣችን እግዚአብሔርም ደስታውን በእኛ ይፈጽም ዘንድ ሕይወታችንን ለእርሱ መሰዋት፣ መሪውንም ለእርሱ መልቀቅ ምንኛ መታደል ነው።
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ ሌላ በምድር የመሰንበቻ ምክንያት እስከምናጣ ድረስ በልቡ አሳብ መጠመድ ይሁንልን!! ፈቃዱ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁ በምድር በእኛ ይሁን!! ለፈቃዳችን ታጥተን፣ ለፈቃዱ ኖረን ማለፍ ይሁንልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 13, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
የፍጥረታት ሕልውና በእግዚአብሔር እጅ ነው። በእርሱ እና ከእርሱ ሁሉ ነገር ተፈጥሮአል። ፍጥረተ ዓለም የእግዚአብሔር ጥገኛ ነው።
እግዚአብሔርም ለፍጥረቱ የሚያስፈልገውን አቅርቦት ወቅቱን ጠብቆ በመስጠት የታወቀ የሁሉም ተስፋ የሆነ አምላክ ነው።
በእግዚአብሔር ደስ ይበለን ፤ መልካም መጋቢ አለን!
መዝሙር 104 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸው ዘንድ፣ እነዚህ ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ።
²⁸ በሰጠሃቸውም ጊዜ፣ አንድ ላይ ያከማቻሉ፤ እጅህንም ስትዘረጋ፣ በመልካም ነገር ይጠግባሉ።
²⁹ ፊትህን ስትሰውር፣ በድንጋጤ ይሞላሉ፤ እስትንፋሳቸውንም ስትወስድባቸው ይሞታሉ፤ ወደ ዐፈራቸውም ይመለሳሉ።
³⁰ መንፈስህን ስትልክ፣ እነርሱ ይፈጠራሉ፤ የምድርንም ገጽ ታድሳለህ።
³¹ የእግዚአብሔር ክብር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር፤ እግዚአብሔር በሥራው ደስ ይበለው፤
³² እርሱ ምድርን ሲመለከት፣ ትንቀጠቀጣለች፤ ተራሮችም እርሱ ሲዳስሳቸው ይጤሳሉ።
³³ በሕይወት ሳለሁ ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ ቆሜ እስከ ሄድሁ ድረስም አምላኬን እወድሳለሁ።
³⁴ እኔ በእግዚአብሔር ደስ እንደሚለኝ፣ የልቤ ሐሳብ እርሱን ደስ ያሰኘው።
³⁵ ኀጥአን ከምድር ገጽ ይጥፉ፤ ዐመፀኞች ከእንግዲህ አይገኙ። ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ፤ ሃሌ ሉያ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 May 21, 2022
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የመጣሁትን መንገድ ሳስብ እርሱ ባያገኘኝ፣ በእነዚያ አስከፊ የሞት መንገዶቼ ላይ ጣልቃ ባይገባ፤ የእኔ ምርጫ የነበረው ነገር ሁሉ ልክ ከአራጁ ጋር እንደዋለ በሬ ሊገድለኝ ያደባ፣ ቀን እየጠበቀ ያለም ነበር።
ለእኔ ድንገት በሚመስል፣ ለእርሱ ግን የዘላለም ዕቅድ በሆነው ጥሪ ውስጥ ከኢየሱስ ጋር ስንገናኝ፦ ከመጥፎ ስብዕና፣ ከክፉ ባህሪዬ፣ ከነውረኛና ረብ የለሽ የኋላ ታሪኮቼ ውጪ አንዳች መልካም ነገር በእኔ የማይገኝ፣ ከእኔም የማይወጣ አመጸኛ፤ በበደሌና በኃጢአቴ ሙት የሆንኹ ነበርሁ። ነገር ግን የአዳኛችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ ስላደረግኹት የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነኝ። ያዳነኝም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው።
ዛሬ ያለፍኹበትን የሞት መንገድ፣ ቆሻሻ የኋላ ታሪኬን፣ ስብራቴን፣ እድፋሙን ማንነቴን እያሰብኹ፤ ዘወር ብዬም እያየሁ በኢየሱስ መወደዴ እንደ አዲስ ድንቅ አለኝ። ኢየሱስ ሲጠጋኝ፣ እርሱን ሳገኝ ከዘላለም ሞት ወጥቼ ዳግም ልደትን አግኝቻለሁ። ዳግም ልደቱ ዘላለሜን የቀየረ መሆኑ ዋና ነገር ሆኖ ሳለ የምድር ኑሮዬንም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። የሰማይ ብርሃን በርቶለት በብርሃን የሚኖር፣ ሕያው አምላክ የልብ ወዳጁ የሆነ፣ በሚያልፍበት መንገድ ሁሉ የማይለየው፣ ከኢየሱስ ጋር የተቆራኘ፣ በፍቅሩም የተሸነፈ፣ ሊያስደስተውና ሊኖሮለትም የሚተጋ አዲስ ሰው ሆኛለሁ።
በመንገዴ ላይ ከሞቴ ቀድመህ የተገኘህ፣ የደረስኽልኝ፣ አዲስ ፍጥረት ያደረግኸኝ፣ በመረቅኽልን አዲስ እና ሕያው መንገድ እንድሄድ ጸጋህን የምታበዛልኝ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመስገን!! በዋጋ ስለገዛኸኝ፣ መድኃኒት ስለሆንኸኝ ደስታዬ ወደር የለውም። ተባረክ!!
ኢየሱስ ለሁለንተና ፈውስ፣ መድኃኒት፣ አዳኝ ነው። ወደ እርሱ ኑ!! በሕይወት ኑሩ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 10, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
#ሊቁ_እርሱ_ነው!
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርት እርሱ በምድር በነበረበት ወቅት በመውጣት መግባቱ ሁሉ አብረውት ቢገኙም፣ እርሱም ሳይታክት እነርሱን በአደባባይም ሆነ በጓዳ ማስተማሩን፣ የመንግሥቱንም ምስጢር ለእነርሱ መግለጡን ባያቋርጥም፤ በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እነርሱ በፊቱ ሁልጊዜ እንደ ልጅ፣ ተምሮ እንዳልጨረሰ፣ ብዙ እንደሚቀረው ሰው መሆናቸውን አያቆሙም ነበር። እርሱ ልኳቸው በእጆቻቸው ድንቅና ተአምራት ተፈጽሞ ቢመለሱም በቀጣዩ ቀን ከእርሱ ለመስማት፣ ከእርሱ ለመቅዳት "ጌታ ሆይ...." እያሉ ከእግሩ ስር አይጠፉም። ምክንያቱም አገልጋይ ከጌታው፣ መልእክተኛም ከላከው አይበልጥምና።
ይህ መምህራቸው ደግሞ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባርም የበረታ፣ ተግባሩም ቃሉ የሆነ ፍጹም ምሳሌ ነውና ሲያደርግ ያዩትን ለመቅዳት እጅግ በመጓጓት ተግባሩን እንዲያስተምራቸው መለመንን አይተዉም።
“አንድ ቀን ኢየሱስ በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር፤ ጸሎቱንም እንደ ጨረሰ፣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፣ “ጌታ ሆይ፤ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን ጸሎት እንዳስተማራቸው አንተም መጸለይን አስተምረን” አለው።”
— ሉቃስ 11፥1 (አዲሱ መ.ት)
"መጸለይን አስተምረን" ፣ " ምሳሌውን ተርጕምልን" ፣
"እምነት ጨምርልን" .......
" እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።"
(የማቴዎስ ወንጌል 24:3)
እነዚህ ሁሉ የእነርሱ ያላሰለሱ ከእርሱ ለመቅዳት የሚደረጉ ፍለጋዎች ናቸው።
በአጠቃላይ አንዴ ቀርበነዋል ብለው ዳግመኛ ወደ እርሱ መቅረብን አይተዉም፤ አንዴ ከእርሱ ሰምተናል ብለው ዳግመኛ ቃሉን ላለመስማት ልባቸውን አይዘጉም፣ ጆሮአቸውንም አይነፍጉትም፤ የአላዋቂነት ጉድለታቸውንም ከእርሱ አይሸሽጉም፤ ይህ ነገር አልገባንም ተርጉምልን ማለትም አያሳፍራቸውም። ብቻ ግን ተማሪ ልባቸውን ይዘው ዘወትር ወደ እርሱ ይገሰግሳሉ። እርሱም " #ከእኔ_ተማሩ " ማለቱን ሳያቋርጥ እያስተማረ ያስተምራቸዋል። ምክንያቱም #ከእኔ_ተማሩ ሊል የተገባው፤ ደግሞም ሲል የሚያምርበት #ሊቅ እርሱ ብቻ ነውና።
ዘወትር በፊቱ እንደ ልጅ መሆን፣ በእግሮቹም ስር እርፍ ብሎ ከእርሱ መማር ይሁንልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 9, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
“ግን እኔ የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ።”
— ኢዮብ 23፥10 (አዲሱ መ.ት)
“But He knows the way that I take (He has concern for it, appreciates, and pays attention to it). When He has tried me, I shall come forth as refined gold (pure and luminous).”
— Job 23፥10 (AMP)
ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ፣ ከእርሱ እውቅና ውጪ በሕይወታችን የሚሆን ምንም ነገር የለም።
ለምሳሌ አካባቢውን እና የመሬቱን አቀማመጥ የማያውቀው ስፍራ ዓይኖቹን በጨርቅ ታስሮ መንገድ እንዲሄድ የተደረገን ሰው ብናይ ከመጀመሪያው እርምጃው አንስቶ ቀጣዩን እስከሚዘረጋ ድረስ በብዙ ጭንቀት፣ የውድቀት ፍርሃት፣ ግራ መጋባት ውስጥ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ቀጣዩ እርምጃው ጉዞውን የሚያስቀጥለው ይሁን ወይንም ለውድቀት የሚያበቃው እንደሆነ አያውቅም ፤ ከፊቱ ለጥ ያለ ሜዳ፣ ተራራ፣ ሸለቆ፣ ገደል...ምን እንዳለ ለእርሱ ግልጽ አይደለም።
ከእግዚአብሔር ጋር ስንጓዝ የመንገዳችን እያንዳንዱ ዝርዝር በእኛ መታወቅ የለበትም። ምክንያቱም እኛ ሂደቱ ቢገባንም ባይገባንም ፣ መንገዱ ቀላል ወይም ከባድ ቢሆንም እግዚአብሔር የምንሄድበትን መንገድ ከማንም በላይ አጥርቶ ያውቀዋል።
መልካም እረኛ ፣ ሁሉን አዋቂ አምላክ እንዳለው ሰው ቀጣዩን እርምጃችንን በእርሱ ታምነን፣ ድፍረታችን ስለ መንገዳችን ያለን እውቀት ሳይሆን አምላካችን መሆኑ ገብቶን እንቀጥል።
ለወርቅ ያማረ፣ ውድ እና ተፈላጊ ሆኖ መውጣት ምክንያቱ ተፈትኖ ያለፈበት እሳት ነውና ከምንፈተንበት እሳት በላይ ስንወጣ ይዘን የምንወጣውን ማንነት እያሰብን እንታገስ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 May 23, 2022
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
445
#Guide_the_Blind
በስልጠና (Training) ወቅት አሰልጣኞች የተሳታፊዎችን፣ የሰልጣኞችን ተሳትፎ ለመጨመር፣ ስልጠናውን አሳታፊ ለማድረግ፣ እንዲሁም ቁልፍ የሆኑ ነጥቦችን በማይረሳ መልኩ ለማስጨበት የተለያየ ጨዋታዎችን፣ አሳታፊ የቡድን ስራዎች (Activities) ይጠቀማሉ።
በአንድ ወቅት ታዳሚ ሆኜ በተገኘሁበት ስልጠና ላይ አሰልጣኙ የተጠቀመው #Guide_the_Blind (ማየት የተሳነውን ሰው መምራት) የተሰኘ የቡድን ስራ (group activity) ነበር። ጨዋታውን (ስራውን) ሁለት ሁለት ሆነን፣ የአንዱ ሰው አይን ምንም በማያሳይ ጨርቅ ታስሮ፣ አንዱ ሰው ደግሞ ልክ ማየት የተሳናቸውን ሰዎች በምንመራበት መንገድ የማያየውን ሰው እጅ ይዞ በመምራት ነበር የሚተገበረው።
በአጋጣሚ እኔ አይናቸውን ከታሰሩት ሰዎች አንዷ ነበርኹ። በጊዜው ሥልጠናው ሲሰጥበት የነበረው አዳራሽ ደግሞ የሚገኘው ባለ ሶስት ወለል ሕንፃ ላይ፣ ሶስተኛው ወለል ላይ ነበር። ሕንጻው ሊፍት ስለሌለው መወጣጫችን ደረጃዎች ነበሩ።
ለጨዋታው አሰልጣኙ የሰጠው መመሪያ፦ ከላይ ከስልጠና አዳራሹ ጀምሮ መሪው አይኑ የታሰረውን ሰው እየመራ፣ ደረጃውን ሁሉ በጥንቃቄ ወርዶ፣ ስልጠናው የተዘጋጀበት ጊቢ የውጪው በር ጋር ደርሶ፣ ተመልሶ ደግሞ የሕንጻውን ደረጃዎች በመውጣት፣ ከሌሎች ቡድኖች ቀድሞ ወደ ስልጠናው አዳራሽ መድረስ ነው።
ለዚህ የቡድን ስራ መሳካት የሁለቱ ሰዎች መናበብ፣ መደማመጥ፣ የመሪው በሳል የመሪነት ክህሎት፣ የተመሪው ንቁ አድማጭነትና መሪውን መታመን ወሳኝ ነገሮች ናቸው። መሪው እግርህን ጣል ወዳለው አቅጣጫ ተመሪው እግሮቹን ይጥላል፣ አንሳ ወዳለው አቅጣጫ ደግሞ ያነሳል፤ እንዲህ እያሉ ደረጃውን በጋራ ይወርዳሉ፣ በጋራ ተመልሰው ይወጣሉ።
አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ስለ አመራር፣ ንቁ አድማጭነት፣ ቡድን መመስረት (Leadership, Active listening, Team Building) ነው። ጨዋታው ጨዋታ ተብሎ በወቅቱ ቢያዝናናንም በውስጡ ቁልፍ መልዕክቶች ነበሩት። ጨዋታውን ጨርሰን ከተመለስን በኋላ በሂደቱ ወቅት ምን እንደተሰማን አሳባችንን፣ ስሜታችንን እንድናጋራ አሰልጣኙ ለተወሰኑ ሰዎች እድል ሰጠ፤ እድል የደረሳቸው ሰዎችም ከራሳቸው እይታ አንጻር የተሰማቸውን ገለጹ።
እኔ ግን ከስልጠናው ርዕስ ውጪ፣ አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ ከፈለገው መልዕክት ለየቀል የሆነ ነገር በውስጤ ተፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለኝ ሕብረት፣ ስለ እምነት አንዳች ነገር እግዚአብሔር ሲናገረኝ፣ ያንን ምሳሌም ተጠቅሞ ሲያስተምረኝ ተሰማኝ፤ ደጋግሜ እያሰላሰልኹት ግን ለማንም ትንፍሽ አላልኹም፤ ወይ ጉድ! ብዬ መልዕክቴን ይዤ ቀኑ አለፈ።
ነገሩ እንዲህ ነው፦ እኔ አይኔ ታስሮ፣ አሰልጣኙ አደራ የሰጠው አንድ ሰው እጄን ይዞ ጉዞ ጀመርን። መሪዬ እንዳልወድቅ ከመፍራቱ የተነሳ እጆቼን ግጥም አድርጎ ይዟል፤ እንዳልፈራና በእርሱ ላይ እንድታመን ደጋግሞ አይዞሽ፣ እኔ አለሁ፣ ደርሰናል ይለኛል። እኔ ግን ከሚናገረኝ ከእርሱ ድምጽ ይልቅ የውስጤ ፍርሃት ጮኽ ብሎ ይሰማኝ ነበር። ከዛ ሕንጻ ላይ ስገለበጥ፣ ወድቄ ስሰበር ይታየኛል፣ ከአሁን አሁን ለቀቀኝ፣ ተጋጨሁ፣ እግሬ የማይሆን ቦታ ረገጠ፣ አደናቀፈኝ እያልኹ ራሴን ለመጠበቅ፣ ለራሴ ለመጠንቀቅ ብዙ ጣርኹ፣ በአጠቃላይ በመሪዬ ላይ ራሴን መጣልና በመሪነቱ መታመን አልቻልኹም፤ ከእርሱ ይልቅ እኔ ለራሴ የማስብ፣ የምጠነቀቅ፣ የማውቅ መስሎ ታየኝ። እንዲሁ እንደፈራሁ፣ እንደ ጮኽሁ፣ እንደታገልኹት፣ እንዳስቸገርኹት ምንም ሳልሆን ጨዋታውን በሰላም ጨረስን።
ለእኔ ግን አንድ ትምህርት ቀረልኝ። እግዚአብሔር ላይ ራሴን አለመጣሌ፣ በፍጹም ልቤ እርሱን አለመታመኔ፣ ተጠራጣሪነቴ፣ ከአንተ በላይ ለራሴ አውቃለሁ፣ እጠነቀቃለሁ ባይነቴ ፍንትው ብሎ ታየኝ፤ ልክ ጨዋታው ላይ መሪዬ የነበረውን ሰው አላምን ብዬ እንዳስቸገርኹት ሁሉ እግዜርንም ማስቸገሬ ታየኝ።
በዚህ Guide the Blind በተሰኘ ጨዋታ ውስጥ ከተመሪው ኃላፊነት የመሪው ኃላፊነት ይከብዳል። የመሪው ኃላፊነት አንድን መንገዱን የማያውቅ፣ የማያይን ሰው፦ ኃላፊነት ወስዶ፣ ተጠንቅቆ፣ ተንከባክቦ፣ አይን ሆኖ፣ መንገድ እየመረጠ፣ አደጋ ሳያደርስበት ከግቡ ማድረስ ነው፤ ቢወድቅ፣ አንዳች ጉዳት ቢደርስበት ኃላፊነት የወሰደው፣ ተጠያቂው እርሱ ነውና ክፉ እንዳይነካው አብዝቶ ይጠነቀቅለታል። ተመሪው ግን ስለ እርሱ ኃላፊነት የወሰደ መሪ፣ የሚጠነቀቅለት መሪ አለውና እርሱን አምኖ፣ ታምኖ፣ ራሱን መሪው ላይ ጥሎ መሄድ፣ መንገዱን የሚመርጥለትን በሙሉ ልብ መከተል ነው።
የዚያች ዕለት ስልጠናው እስኪያልቅ፣ ወደ ቤቴም ገብቼ ትኩረቴ በዚህ አሳብ፣ ጸሎት ተወስዶ ነበር፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!!
ዛሬም እግዚአብሔርን ስለ ማመን፣ ስለ መታመን፣ ራስን እርሱ ላይ ጥሎ እርሱን ስለመከተል ሳስብ፣ ሳሰላስል፣ ስጸልይ ይህ ከዛሬ አራት ዓመት በፊት የተፈጠረ ምሳሌ ትዝ አለኝ፤ ትማሩበት እና ጸሎቴንም ትጋሩኝ ዘንድ ለእናንተም ላካፍላችሁ ወደድኹ።
ዛሬም ጸሎቴን አልቀየርኹም ያው ነው፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 5, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
