The Legal Oracle(Ye_Hig Mahider)
الذهاب إلى القناة على Telegram
Official channel of Almaw Wolie https://www.linkedin.com/in/almaw-wolie-82775183?utm_source=share_via&utm_content=profile&utm_medium=member_android
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
1 968
المشتركون
+1124 ساعات
+887 أيام
+1 26730 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የአዲስ አበባ ከተማ የኮንስትራክሽን ማዕድናት ቁፋሮና አስተዳደርን የሚመራ አጠቃላይ መመሪያ ወጣ።
የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት በዝርዝር የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ አወጣ።
"የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 191/2018" የተሰኘው ይህ ሰነድ፣ ከዚህ ቀደም በዘርፉ ይታዩ የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በመድፈን ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ ነው ይላል።
መመሪያው ዋና ዋና የፈቃድ ዓይነቶችን የለየ ሲሆን፣ እነሱም አምርቶ የመሸጥ፣ ለመንግሥት ልማት ሥራዎች አምርቶ የመጠቀም፣ ምርት ለማንሳት የሚሰጥ ፈቃድ፣ ከስራው ጋር ተዘማጅነት ያላቸውን ማሽኖች መትከያ ፈቃድ እንዲሁም ሌሎች ፈቃዶች ይገኙበታል።
ፈቃድ የሚሰጥባቸው የኮንስትራክሽን ማዕድን አይነቶችም በዝርዝር የተቀመጡ ሲሆን ፦
- ጥቁር ድንጋይ፣
- ገረጋንቲ፣
- ቀይ አሸዋ፣
- ቀይ አፈር፣
- ነጭ የግንብ ድንጋይ (ጥርብ ድንጋይ)፣
- የወንዝ አሸዋ፣
- ጠጠር እና ሌሎችም ተመሳሳይ ማዕድናት ናቸው ተብሏል።
በጥቁር ድንጋይ ማምረት ላይ የተሰማሩ አልሚዎች እስከ 5 ዓመት፣ በገረጋንቲ፣ አሸዋና ነጭ ድንጋይ ላይ የተሰማሩ ደግሞ እስከ 2 ዓመት የሚቆይና በየዓመቱ የሚታደስ ፈቃድ ይሰጣቸዋል።
ህጋዊ የመሬት ባለይዞታ የሆነ ለንግድ ላልሆነ ዓላማ ለግንባታ ብቻ በግል ይዞታው ውስጥ ያለ ክፍያና ፍቃድ ሳያስፈልገው አምርቶ መጠቀም ይችላል።
ለንግድ ዓላማ ማዋል ሲፈልጉ ግን በሽርክና ወይም በማህበር ተደራጅተው ፈቃድ እንዲያወጡ ይደረጋል።
በመንግሥት ፕሮጀክቶች ላይ የተሰማሩ የግል ድርጅቶችም ከቀጣሪ መሥሪያ ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ በማቅረብ ማዕድን ማውጣት የሚችሉ ሲሆን፣ እንደማንኛውም አልሚ የሮያሊቲ ክፍያ የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
ለአካባቢ ደህንነት ሲባል ባለሥልጣኑ ማዕድን ማውጣት የተከለከለባቸውን ቦታዎች በግልጽ አስቀምጧል።
በዚህም መሠረት፦
• ከመኖሪያ መንደሮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በ500 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣
• ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣
• ከወንዝ ዳርቻዎች በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ቁፋሮ ማከናወን በጥብቅ የተከለከለ ነው።
በተጨማሪም ከመቃብር፣ከፓርክ ፣ከመሰረተ ልማት፣ ከሃይማኖታዊ ስፍራዎችና ከብሔራዊ መታሰቢያዎች ከቆሙባቸው ቦታዎች አቅራቢያ ፈቃድ አይሰጥም።
ማንኛውም አልሚ ፈቃድ ለማግኘት የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ (EIA) እና የአዋጭነት ጥናት ማቅረብ ይኖርበታል።
በተጽዕኖ ግምገማ ጥናት መሰረት በአካባቢው ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለማስተካከል አስፈላጊ ነው የተባለውን የፋይናንስ ፍላጎት፣ በመስሪያ ቤቱ ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ዋስትና ማስያዝ ግዴታ ሆኖ ተጥሏል።
አልሚዎች በየሦስት ወሩ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና በየወሩ የገቢ ሪፖርት ለባለሥልጣኑ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
መመሪያው የፈቃድ ባለቤትነትን በውርስ፣ በሽያጭ ወይም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማስተላለፍ እንደሚቻል ቢፈቅድም፣ ፈቃዱን የሚረከበው አካል ከማንኛውም ያልከፈለው ዕዳ እና ኪሳራ ነፃ መሆኑ መረጋገጥ አለበት።
አንድ አልሚ ተጨማሪ ቦታ ማስፋፋት የሚችለውም ቀደም ሲል ከተሰጠው ቦታ ቢያንስ 70 በመቶ የሚሆነውን አልምቶ ማጠናቀቁ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ሕገ-ወጥ ቁፋሮን ለመከላከል የክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽሕፈት ቤቶች የቅርብ ክትትል እንዲያደርጉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል።
አልሚው የተጣለበትን ግዴታ ካላከበረ፣ ተደጋጋሚ ሕገ-ወጥ ድርጊት ከተገኘበት፣ ወይም ማዕድኑ ሙሉ በሙሉ ካለቀ ፈቃዱ የሚሰረዝ ይሆናል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ የኮንስትራክሽን ማዕድናት ቁፋሮና አስተዳደርን የሚመራ አጠቃላይ መመሪያ ወጣ።
የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት በዝርዝር የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ አወጣ።
"የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 191/2018" የተሰኘው ይህ ሰነድ፣ ከዚህ ቀደም በዘርፉ ይታዩ የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በመድፈን ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ ነው ይላል።
መመሪያው ዋና ዋና የፈቃድ ዓይነቶችን የለየ ሲሆን፣ እነሱም አምርቶ የመሸጥ፣ ለመንግሥት ልማት ሥራዎች አምርቶ የመጠቀም፣ ምርት ለማንሳት የሚሰጥ ፈቃድ፣ ከስራው ጋር ተዘማጅነት ያላቸውን ማሽኖች መትከያ ፈቃድ እንዲሁም ሌሎች ፈቃዶች ይገኙበታል።
ፈቃድ የሚሰጥባቸው የኮንስትራክሽን ማዕድን አይነቶችም በዝርዝር የተቀመጡ ሲሆን ፦
- ጥቁር ድንጋይ፣
- ገረጋንቲ፣
- ቀይ አሸዋ፣
- ቀይ አፈር፣
- ነጭ የግንብ ድንጋይ (ጥርብ ድንጋይ)፣
- የወንዝ አሸዋ፣
- ጠጠር እና ሌሎችም ተመሳሳይ ማዕድናት ናቸው ተብሏል።
በጥቁር ድንጋይ ማምረት ላይ የተሰማሩ አልሚዎች እስከ 5 ዓመት፣ በገረጋንቲ፣ አሸዋና ነጭ ድንጋይ ላይ የተሰማሩ ደግሞ እስከ 2 ዓመት የሚቆይና በየዓመቱ የሚታደስ ፈቃድ ይሰጣቸዋል።
ህጋዊ የመሬት ባለይዞታ የሆነ ለንግድ ላልሆነ ዓላማ ለግንባታ ብቻ በግል ይዞታው ውስጥ ያለ ክፍያና ፍቃድ ሳያስፈልገው አምርቶ መጠቀም ይችላል።
ለንግድ ዓላማ ማዋል ሲፈልጉ ግን በሽርክና ወይም በማህበር ተደራጅተው ፈቃድ እንዲያወጡ ይደረጋል።
በመንግሥት ፕሮጀክቶች ላይ የተሰማሩ የግል ድርጅቶችም ከቀጣሪ መሥሪያ ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ በማቅረብ ማዕድን ማውጣት የሚችሉ ሲሆን፣ እንደማንኛውም አልሚ የሮያሊቲ ክፍያ የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
ለአካባቢ ደህንነት ሲባል ባለሥልጣኑ ማዕድን ማውጣት የተከለከለባቸውን ቦታዎች በግልጽ አስቀምጧል።
በዚህም መሠረት፦
• ከመኖሪያ መንደሮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በ500 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣
• ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣
• ከወንዝ ዳርቻዎች በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ቁፋሮ ማከናወን በጥብቅ የተከለከለ ነው።
በተጨማሪም ከመቃብር፣ከፓርክ ፣ከመሰረተ ልማት፣ ከሃይማኖታዊ ስፍራዎችና ከብሔራዊ መታሰቢያዎች ከቆሙባቸው ቦታዎች አቅራቢያ ፈቃድ አይሰጥም።
ማንኛውም አልሚ ፈቃድ ለማግኘት የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ (EIA) እና የአዋጭነት ጥናት ማቅረብ ይኖርበታል።
በተጽዕኖ ግምገማ ጥናት መሰረት በአካባቢው ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለማስተካከል አስፈላጊ ነው የተባለውን የፋይናንስ ፍላጎት፣ በመስሪያ ቤቱ ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ዋስትና ማስያዝ ግዴታ ሆኖ ተጥሏል።
አልሚዎች በየሦስት ወሩ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና በየወሩ የገቢ ሪፖርት ለባለሥልጣኑ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
መመሪያው የፈቃድ ባለቤትነትን በውርስ፣ በሽያጭ ወይም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማስተላለፍ እንደሚቻል ቢፈቅድም፣ ፈቃዱን የሚረከበው አካል ከማንኛውም ያልከፈለው ዕዳ እና ኪሳራ ነፃ መሆኑ መረጋገጥ አለበት።
አንድ አልሚ ተጨማሪ ቦታ ማስፋፋት የሚችለውም ቀደም ሲል ከተሰጠው ቦታ ቢያንስ 70 በመቶ የሚሆነውን አልምቶ ማጠናቀቁ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ሕገ-ወጥ ቁፋሮን ለመከላከል የክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽሕፈት ቤቶች የቅርብ ክትትል እንዲያደርጉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል።
አልሚው የተጣለበትን ግዴታ ካላከበረ፣ ተደጋጋሚ ሕገ-ወጥ ድርጊት ከተገኘበት፣ ወይም ማዕድኑ ሙሉ በሙሉ ካለቀ ፈቃዱ የሚሰረዝ ይሆናል።
@tikvahethiopia
በዚህ ውስጥ ስለ ፈጠራዎች፣ ስለ ትናንሽ ፈጠራዎችና ስለ ኢንዱስትሪ ንድፎች የወጣውን የኢትዮጵያ አዋጅ ቁጥር 123/1987 መሠረት በማድረግ የተዘጋጀውን "የዘላቂነት ተቃርኖ፡ የኢትዮጵያ የጸና የፓተንት ሥርዓት ላይ የተደረገ መዋቅራዊ የሕግ ድኅረ-ሞት ምርመራ" የተሰኘውን ሙሉ የጥናት ጽሑፍ ያገኛሉ። ይህ ጽሑፍ አዋጁ ላለፉት ሦስት አሥርተ ዓመታት በኢትዮጵያ ተለዋዋጭ የሕግ አወጣጥ ባህል ውስጥ ያሳየውን ያልተለመደ የሕግ መረጋጋትና የዘላቂነት ምሥጢር በወፍ በረር የሚመረምር ሲሆን፣ ከወቅታዊው የዲጂታልና የባዮቴክኖሎጂ ምጣኔ ሀብት አንጻር ያለበትን ክፍተቶችና ለወደፊቱ የኢትዮጵያ የሕግ አረቃቀቅ ሥርዓት የሚሰጣቸውን መሠረታዊ ሥርዓታዊ ትምህርቶች ይዳስሳል። ጽሑፉን ለመማማር ዓላማ እንጋብዛለን።
ውድ የቻናላችን ተከታዮች፣ የሕግ ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች፤
ከላይ ከተያያዘው ሰነድ ውስጥ ሌላ ሰው ራሱን እንዲያጠፋ ማነሳሳትን ወይም መርዳትን የሚደነግገውን የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 አጠር ያለ ምልከታ የያዘውን ሙሉ ጽሑፍ ያገኛሉ። ይህ ጽሑፍ የድንጋጌውን የቅጣት እርከን፣ የስነ-ወንጀል ፍልስፍና (Criminology) እና የሕግ መርሆዎች በወፍ በረር ለመዳሰስ ባለፈ፣ እ.ኤ.አ. በጥር 2025 የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የራስ-ማጥፋት ሙከራን ሕገ-መንግሥታዊ አይደለም በማለት ወንጀል ድርጊት ከመሆን ውጭ ያደረገበትን አዲሱን ታሪካዊ ውሳኔ ጨምሮ ከዩናይትድ ኪንግደም (Suicide Act 1961) እና ከካናዳ የሕግ ሥርዓቶች ጋር ያነጻጽራል። በግል ነፃነት (autonomy) እና በመንግሥት የጥበቃ ጣልቃ ገብነት (paternalism) መካከል ያለውን ሚዛን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶች በአገር ውስጥ ሕግ ላይ ያላቸውን ተጽዕኖ ለመረዳት ለሕግ ተመራማሪዎች፣ ለጠበቆች፣ ለዳኞች እና ለሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ሙሉዕ የሆነ ስራ ነው ባይባልም ጠቃሚ መነሻ ግብዓት እንደሚሆን ይታመናል ።
ሙሉውን ሰነድ ከ ከተያያዘው ፋይል በማውረድ እንዲመለከቱ በትሕትና እንጋብዛለን።
A_NEW_POLITICAL_SYSTEM_MODEL_SEMI_PRESIDENTIALMAURICE_GOV'T_BY_DUVERGER.pdf1.38 MB
The_politics_of_semi_presidentialism_SP_Chap_01_Introduction.pdf1.75 KB
የህግ ትርጉም በያዙ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ላይ አስኳል(Ratio Decidendi) እና እግረ መንገድ የሚነሱ ትንታኔዎች የሚለዩበት አግባብ
በታች ከተያያዘው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ (የሰ/መ/ቁጥር 182410) ላይ በመመስረት፣ የዚህን ውሳኔ አስኳል(Ratio Decidendi) እና እግረ መንገድ የተሰጡ ትንታኔዎችን (Obiter Dicta) በሚከተለው መልኩ ለመለየት ጥረት ይደረጋል፡፡
1. መግቢያ
§ ፍርድ ቤቱ፡- የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ደሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት
§ የሰ/መ/ቁጥር፡-182410
§ የተወሰነበት ቀን፡ 24/02/2013
§ ጉዳዩ፡- የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የስረ ነገር ሥልጣን (Jurisdiction) በሚመለከት የስነ ሥርዓት ሕግ (Procedural Law) ጉዳይ ላይ የቀረበ የሰበር አቤቱታ ነው፡፡
ይህ ውሳኔ በሕግ ጥያቄዎች ላይ ችሎቱ በሰበር ባለው ሥልጣኑ መሠረት አስገዳጅ ቅድመ ፍርድ (Binding Precedent) ሆኖ ያገለግላል፡፡ የውሳኔው ዋና አስኳል የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ሥልጣን በሚመለከት መሠረታዊ የሥርዓት ጉዳይ ላይ ያተኩራል፡፡
2. አስኳል የሆነው የውሳኔ ምክንያት (Ratio Decidendi)
የዚህ ጉዳይ አስኳል የሆነው የውሳኔ ምክንያት (Ratio Decidendi) ችሎቱ ውሳኔውን ለመስጠት አስፈላጊ የሆነውን እና አስገዳጅ ቅድመ ፍርድ የሚያስቀምጠውን የሕግ መርህ ያካትታል፡፡ ይህም ከችሎቱ የመጨረሻ ውሳኔ እና ለዚያ ውጤት ማዕከላዊ ከሆነው አመክንዮ የተገኘ ነው፡፡
2.1 አስኳል የውሳኔ ምክንያቱ (The Ratio):-
በህግ አግባብ የውክልና ስልጣን ባልተነሳበት የክልል መንግስት ግዛት ውስጥ የሚገኝን የማይንቀሳቀስ ንብረት (Immovable Property) በሚመለከት በሊዝ
94904መኪናው_የኔ_ነወe_ብሎ_ያስቆመ_በፍርዱ_ከተረታ_ለተቀቋረጠ_ጥቅም_ለባለመኪናው_ካሳ_የመክፈል_ግዴታ.docx0.11 KB
Oral Skills for Lawyers (Kevin Browne, Jacqueline Kempton).epub1.39 MB
Peter_T_Wendel_Deconstructing_Legal_Analysis_A_1L_Primer_Academic.pdf7.39 MB
