የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
الذهاب إلى القناة على Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
514
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ጳግሜን 1/2017 ዓ.ም
አዳማ
==========0==========
በቡድን መስራት በሀገራዊ ድሎች የሚኮራና ደስታን የሚጋራ ትውልድ መፍጠር እንደሚያስችል ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ለሰራተኞቹ ስራዎችን በቡድን መስራት/Team Building/ እንዴት መገንባት፣ እንዴት ማደራጀት እና እንዴት እንደሚመራ የሚያስችል እንዲሁም በቡድን መስራት ስለሚኖረው ጥቅም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
ዛሬ የምናገኛቸው ስልጠናዎች ለምንሰራቸው ስራዎች እውቀትን የሚጨምሩ በመሆናቸው በጥሞና ተከታትለን ተግባር ላይ ልናውለው ይገባል ያሉት መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ናቸው።
Team Building & Management In Ethiopia Archieve and Library በሚል ርዕስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በባህልና ስፓርት ሚኒስቴር የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በአቶ አህመድ መሐመድ ተሰጥቷል።
ለተቋም ለውጥ ስራዎች ሲሰሩ በዕቅድና በዓላማ የሚመሩና ለማሳካት ጥሩና መልካም የሆነ የስራ ግንኙት ፣ቡድን ገምብቶ ሰፊ ግዜ ሰጥቶ በመነጋገር መስራት፣ ሌሎች የሚሰሩትን ስራ ማወቅ፣ በምንሰራው ሥራ አጀንዳ መያዝ፣የተቋም ስትራቴጂክ መኖር፣የተቋም አሰራር ስርዓት መዘርጋትና ወደ ተገልጋዮ መረጃ ማስገባት ጠቀሜታው የጎላ ከመሆኑ ባሻገር ለለውጥ መሰረት እንደሆነም ተናግረዋል።
" ማር የቡድን ስራ ውጤት ነው"
የቀጣይ ዘመን የከፍታ ማማ ማረጋገጫ መንገድ እውቀት ነው።
እውቀት የፈጠራ መሰረት ነው።ለፈጠራ ስራ የቡድን ስራ መሰረት ነው።በሚሉ አባባሎች የቡድን ስራን ጠቀሜታ አስረድተዋል።
በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሕግ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ አቶ በላቸው ድሪባ ከህግ አንጻር የተቋሙ ግዙፍ ተቋሙ እንደመሆኑ በትውልድ መካከል ድልድይ ሆኖ ለትውልድ መረጃ የሚያስተላልፍ ተቋም ከመሆኑ አንጻር ከህግ አንጻር እንዴት እንደሚሰራ?ባህሉ ምን እንደሚመስል ተቋሞች በነበራቸው መረጃ ለመስራት እንዲቻል የሚያግዝ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑንም ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ስልጠናውን በተመለከተ ቡድን ስራ አስፈላጊነትና ጠቀሜታውን የሚያስገነዝቡ መልመጃዎችን በመስራት የጠዋቱ መርሐ ግብር ሲጠናቀቅ።
በከሰዓቱ መርሐ ግብር በተቋሙ የለውጥ ሥራ አመራር ሥራ አስፈጻሚ በአቶ አበራ ገ/መድህን በመልካም አስተዳደር ዙሪያ የሲቭል ሰርቪስ ሥራ አመራር ፣የዕቅድ ዝግጅት፣የስራ አፈጻጸም አመራር፣ የአፈጻጸም መርሆች፣የእቅድ ዝግጅት፣ የአፈጻጸም ክትትል፣ግምገማና ምዘና፣ የሰራተኛ ዕቅድ ዝግጅት፣ የአፈጻጸም ስምምነት፣የድርጊት መርሐ ግብር፣ የአፈጻጸም ክትትል፣ግምገማና ምዘና፣የ የአፈጻጸም ምዘና፣የተቋማዊ ውጤት አመላካቾች፦የተልዕኮ፣የ ራዕይ፣ የግብ ስኬት፤የሰው ሀብት ልማት/አቅም ግንባታና ስራ አመራር፤አገልግሎት ማዘመን፤አስተዳደራዊ ፍትህ፤የአመራርና ሰራተኞች ሥነ ምግባር፤የዳይሬክተሮች የአፈጻጸም ምዘና፤የሰራተኞች የአፈጻጸም ምዘና፤የምዘና ደረጃዎች ፤ድህረ ምዘና ተግባራት በዝርዝር ቀርቧል።
ከሰራተኛው የተቋሙን አሰራርና የክፍሎች እና ባለሙያው በዘርፉ የሚሰጠው ኃላፊነትን በተመለከተ የተነሱ በርካታ ጥያቄዎችና ሃሳብ አስተያየቶች ላይ ማኔጅመንቱ እንዴት መስራት እንደሚገባ መልስ መስጠት ሳይሆን በጋራ በመወያየት ለለውጥ መትጋት እንደሚጠበቅ ተጠቁሞ ውይይቱ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ትምህርት ቢሮ እና ከወርልድ ቪዠን ጋር በመተባበር " የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በጅንካ ከተማ ከጳጉሜን 1 እስከ ጳጉሜን 3/2017 ዓ.ም የንባብ ሳምንት፣አውደ ርዕይና የፖናል ውይይት መድረክ ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በዝግጅቱም:-
👉የንባብ ሳምንት መርሐ ግብር ይካሔዳል።
👉የጎዳና ላይ አውደ ርዕይ ያካሒዳል።
👉በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የፓናል ውይይት ይደረጋል።
👉ተቋሙ በጅንካ ከተማ ቆይታው ታላላቅ ሰዎች በንባብ ላይ ተሞክሮ እንዲያካፍሉ ያደርጋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰዐወ) መውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የነብዩ መሀመድ (ሰዐወ) መውሊድ ስናከብር ነብዩ መሀመድ (ሰዐወ) በእስልምና ሀይማኖት በነበራቸው የሰው ልጆች ያለ ዘርና ሀይማኖት ልዩነት የምድር ፍጡር ሁሉ እኩል መሆናቸውን ሲያስተምሩ መቆየታቸውን የሀይማኖቱ አስተማሪዎች በሚገልጹት መሰረት አስተምእሮቱን በመላበስ ተግባራዊ በማድረግ በዓሉን በመከባበርና በመረዳዳት የምታከብሩት እንዲሆን የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከልብ ይመኛል።
ኢድ ሙባረክ!!
መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንላችሁ።
ነሐሴ 25/2017 ዓ.ም
አላጌ
ተቋሙ ከአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በመተባበር የተዘጋጀው መርሐ ግብር ተጠናቀቀ።
"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የቀድሞ የሕጻናት አምባ
ምሥረታ 45ተኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያና ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ሲካሔድ የነበረው የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና የፖናል ውይይት ተቋሙ ከኮሌጁ ጋር የነበረውን መርሐ ግብር አጠናቋል።
በሁለተኛ ቀን ውሎው ተገኝተው ተሞክሯቸውን ያነሱት የቀድሞው የብሔራዊ ጀግኖች ህጻናት አምባ መስራች ብርጋዴል ጄነራል ካሳዬ ጨሜዳ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በየአካባቢው
እየተዟዟረ የሚሰራውን ተግባር ምስጋናና አድናቆትን የሰጡበት መድረክ ነው።
በውጭም በውስጥም ኢትዮጵያን ለማጥቃት የሚሯሯጡ ተቀናቃኞች እንደማይሳካላቸው ጠቁመው
ተቋማቶች በራዕያቸው ተመርተው ስራዎችን ጠንክረው በመስራት ለሀገራቸው ብሎም ለመጪው ትውልድ ከዘረኝነት የጸዳች እና የበለጸገች ሀገር ለትውልዱ የሚያስረክቡበት እንደሚሆን ተናግረዋል።
በማከልም ጀነራሉ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከውጪም ከውስጥም ከሚወረወርባት ሀገር የማጥቃት ትንኮሳ የምትላቀቅበት ትንሳኤዋን የምናይበት ሩቅ እንደማይሆን ተመኝተው የጉብኝት መርሐ ግብር ተካሒዶ ተቋማቱ ያዘጋጁት ዝግጅት ተጠናቋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም
አላጌ
"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት ተካሔደ።
የቀድሞ የሕጻናት አምባ ምሥረታ 45ተኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና የፖናል ውይይት መድረክ በልዩ ድምቀት ተካሒዷል።
በዝግጅቱ የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው እና የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና ሥራ አስፈጻሚዎች፣የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር መርክነህ መሰኔ፣ደራሲ ይታገሱ ጌትነት እና ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ፣ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መ/ር ዶ/ር ተሻገር ሽፈራው እንዲሁም የአላጌ ጊዜያዊ ቁስለኞች ማገገሚያ አዛዠ ኮሎኔል ምስባሁ አረብ እና በማገገሚያ ማዕከሉ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት ተገኝተዋል።
በመርሐ ግብሩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በኮሎኔል ምስባሁ አረቡ በኮሌጁ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር መርክነህ መስኔ የመክፈቻ ንግግር ተደርጓል።
በተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው የመርሐ ግብሩን ዓላማ አንባቢ ትውልድን ለማፍራት የእኛ ተቋም አጠናክሮ እንደሚሰራ ተናግረው መረጃን አደራጅቶ በመያዝ ዛሬ ወደእናንተ ሲመጣ ስለእናንተ የተሰነዱ መዛግብትን ይዞ በምልከታቹ በዘመኑ የነበሩ ትዝታዎችን ወደኃላ ሄዳችሁ የምትመለከቱበትም ትልቅ አጋጣሚ መድረክም እንደሆነ ተናግረው ግምታቸው ከሦሥት መቶ አርባ አራት ሺህ ብር በላይ የፈጁ አንድ ሺህ መጽመፍት ይዘታቸው የትምህርት መርጃ እንዲሁም የታሪክና የፍልስፍና የሆኑ መጻሕፍት በስጦታ መበርከቱን ጠቁመዋል።
በመድረኩም አነቃቂ ንግግሮች እና የህይወት ተሞክሮዎች በታላላቅ ሰዎች ሲቀርቡ የጥያቄና መልስ ውድድርና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረቱ የሥነ ጽሑፍ ስራዎች መልዕክት አዘል ግጥሞችም ቀርበዋል።
የንባብ ባህል ለትምህርት ዘርፍ ስላለው አስተዋጽኦ በመ/ር ዶ/ር ተሻገር ሽፈራው፣ በአስር አለቃ ሳለ አማረ እውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተጻፈ "የተሰበረው ንስር" መጽሐፍ በጸሐፊው ቀርቧል።
በቤተ መጻሕፍት ሙያ እና በሰነድና መዛግብት አስተዳደር ስልጠና ወስደው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ያዘጋጀውን የምስክር ወረቀት እንዲሁም የሥነ-ጽሑፍና የጥያቄና መልስ ተወዳዳሪዎች የመጽሐፍት ስጦታ ከተቋሙ ሥልጠና እና ማማከር ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን ከፍ ያለ እጅ ተበርክቶላቸዋል።
በበጀት ከሦሥት መቶ አርባ አራት ሺህ ብር በላይ የፈጁ በይዘታቸው የትምህርት መርጃ እና ታሪክና ፍልስፍና የሆኑ በቁጥር አንድ ሺህ መጽሐፍ ለአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ፣ለሻላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት፣ለዘራይ ድረስ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም የቁስለኞች ማገገሚያ ማዕከል ለኮሌጁ ዲን ረ/ ፕ መርክነህ እና ለጊዜያዊ ማገገሚያው አዛዠ ኮሎኔል ምስባሁ የተቋሙ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው በስጦታ አበርክተዋል።
በዛው መድረክ ላይም ከዛጎል መጽሐፍ ባንክ በቁጥር ሁለት መቶ መጽሐፍት፣ ከኢትዮጵያን ሪድስ ስድስት መቶ በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋ የተጻፉ የልጆች መጽሐፍት እና ከአምባ ልጆች የተሰባሰቡ በርካታ መጽሐፍት ተበርክተው የመጀመሪያው ቀን መርሐ ግብር ተጠናቋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከአላጌ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ጋር በጋራ በመሆን " የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ከነሐሴ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና የፖናል ውይይት መድረክ ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
👉ተቋሙ በአላጌ ቆይታው ታላላቅ ሰዎች በንባብ ላይ ተሞክሮ እንዲያካፍሉ ያደርጋል።
👉በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ የሚያጠነጥኑ ጽሑፎችን በማቅረብ ከሚመለከታቸው ጋር ውይይት ይደረጋል።
👉በሪከርድ ስራ አመራር እና በመዛግብት አስተዳደር ዙሪያ በሪከርድና ማህደር ክፍል ለሚገኙ ባለሙያዎች እንዲሁም ለጸሐፊዎች፣ከመከላከያ ለተውጣጡ ለዘርፉ ባለሙያዎች የሙያ ስልጠና ወይም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ይሰጣል፡፡
በተጨማሪም የአረጋውያን ቤት የማደስ በጎ ስራ ላይ መሳተፍና መንደሮቹን የመጎብኘት ተግባር ያከናውናል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
+3
ነሐሴ 22 ቀን /2017 ዓ.ም
ዐዲስ አበባ
=======o=======
ተቋሙ በአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ በጋራ ከነሐሴ 23 ቀን/2017 ዓ.ም ጀምሮ ካዘጋጁት የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና ፓናል ውይይት መድረክ አንዱ የሆነውን በዘርፉ በክልሎችና በከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም በፍላጎት በመጋበዝ ሰልጣኞች በሚገኙበት አካባቢ በመሔድ ከዚህ በፊት ሲሰጥ የነበረውን የሙያ ስልጠና በአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ከነሐሴ 19 ቀን /2017 ዓ.ም ጀምሮ እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡
ስልጠናው በቤተ መጻሕፍት ሙያና በሪከርድ ስራ አመራር ሙያ ዘርፍ ሲሆን ስልጠናውን እየወሰዱ የሚገኙት ከአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እና ከመከላከያ ጊቢ ለተውጣጡ የሪከርድና የቤተ መጻሕፍት ሠራተኞች እየተሠጠ እንደሚገኝ መረጃውን የሰጡን በተቋሙ የአብያተ መጻሕፍት ስልጠና ምክር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ብዙወርቅ ተስፋዬ ጠቁመውናል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
+4
ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም.
ዐዲስ አበባ
======================
የጥናትና የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚያስችል ጉብኝት ተካሔደ
ተቋሙ የንባብ ባህልን ማዳበር ተቀዳሚ ዓላማው በመሆኑ ዓላማውንም እውን ለማድረግ በክልሎች፣ በከተማ መስተዳድሮች፣ በጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም ማረሚያ ቤቶች ቦታው ድረስ በመሔድ የንባብ ሳምንት በማዘጋጀት እቅዱን እያከናወነና ትውልዱን እየቀረጸ ይገኛል፡፡
ይህንን ዓላማውን የተረዱ ከተለያዩ በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች ከመምህራኖቻቸው ጋር ተቋሙ ድረስ በመምጣት የአገልግሎት መስጫ ክፍሎችን በመጎብኘት እውቀት የሚያገኙበት በመሆኑ ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም ኦፍላድ ከመንግስት ት/ቤት ተማሪዎች ጋር ባዘጋጀው የጥናትና የንባብ ባህልን ማዳበር ዓላማው ያደረገ ፕሮጀክት የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር አካል የሆነ ጉብኝት አካሒዷል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ፡https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም.
ዐዲስ አበባ
================
የጥንታውያ ኢትዮጵያውያንን ጥበብ መሠረት ያደረጉ የብራና መጻሕፍትና ሥዕላትን በመሥራት ትውልዱን በበጎ ምግባር ለመቅረጽ እየተጋ የሚገኘው ድርጅት ተጎበኘ፡፡
ሀገራችን የራሷ የኾነ ባህል፣ታሪክ፣ቅርስ፣ቋንቋ እና ፊደል ያላት ሀገር መኾኗ ይታወቃል፡፡ይህንኑ ጠብቆ ለትውልድ ለማሻገር በየዘርፉ በራስ ተነሳሽነት ከሚሰማሩ የግል ተቋማት በዐዲስ አበባ የሚገኘው "ሐመረ ብርሃን" የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት ነው፡፡
"ሐመረ ብርሃን" የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና በሚመለከታቸው የማኔጅመንት አባላት ሲጎበኝ፣ የሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ መ/ር ኪሩቤል ታምራት የተቋሙን ሥራዎች እና ርእይ በማብራራት አስጎብኝተዋል፡፡
አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት በንግግራቸው በተቋማዊ ትብብር ሥራዎችን በጋራ ብንሠራ ተቋማዊ ርእይና ተልዕኮውን እውን ሊያደርግ ከማስቻሉም ባሻገር ለትውልዱ ራሱን ፈልጎ ከማግኘትና ከመቅረጽ አንጻር መልካም አስተዋጽዖ ይኖረዋል፡፡
የቀደሙ አባቶቻችን ጥበብ ዛሬም ድረስ የምንደነቅባቸው ሲኾኑ፣ ብራና ፎቀው፣ ብዕር ቀርጸው፣ ቀለም በጥብጠው መጽሐፍ ጽፈው፣ ቅዱሳት ሥዕላትን ቀለም ከማዘጋጀት ጀምሮ ሥለው አሁን ላለው ትውልድ አስተላልፈዋል። እኛም የእነሱን አርአያ በመከተል አንድ ሰው ልጁን በበጎ ምግባር እያስተማረ ቢቀርጸው፣ ያ ልጅ ደግሞ መልሶ ልጁን በዚሁ መንገድ ቢመራው እና እንዲህ እያለ ቢቀጥል፣ የጥሩ ትውልድ ቅብብሎሽ እንደ ወርቃማ ሰንሰለት ከመኾኑ ባለፈ ሀገር ወዳድ ዜጋን እንደሚፈጥር እና ይህንኑ ራዕይና ተልዕኮን ለማሳካት ድርጅቱ ሥራዎቹ ትኩረት የሚያደርገው በ17ኛው እና 18ኛው ክ.ዘ ላይ የተሣሉ የግድግዳ ሥዕላት ፍልስፍናን መመረት አድርጎ፣ ሀገራዊ ትርጉም ያሏቸው ሥዕሎች፣ የጠልሠም ጥበብ፣ የቆዳና የእንጨት ሥራዎች፣ የመጽሐፍ ደጉስ (የመለበጥ) ሥራ፣ እንዲሁም በዘርፉ ኹለት ትምህርት ቤቶችን በመክፈት 400 የሚጠጉ ተማሪዎችን በአዳር እና በተመላላሽ እያስተማረ የሚገኝ ሀገር በቀል ድርጅት እንደኾነም የሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት ስራ አስኪያጅ መ/ር ኪሩቤል ታምራት ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎትም በርካታ የብራና መጻሕፍትን ጠብቆ እንደሚገኝና በUNESCO ከተመዘገቡት 12 የጽሑፍ ቅርሶች በተጨማሪ ሌሎችንም ለዓለም ለማስተዋወቅ እየሠራ የሚገኝ ተቋም ከመኾኑ አንጻር፣ እንዲህ ያሉ የእጅ ጽሑፍ፣ የሥዕል፣ እና የተለያዩ የጥበበ ዕድ ሥራዎችን የሚሠራን ተቋም እንደሚያበረታታ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
+6
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአብያተ መጻሕፍት ሙያ ለተሰማሩ ባለሙያዎቹ ስልጠና እንዲሰጥለት በጠየቀው ጥያቄ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ስልጠናውን በሶስት ምድብ በመክፈል ለ155 ስልጠና ፈላጊዎች በመሰረታዊ የቤተመጻህፍት ሙያ ስልጠና እና በቤተመጻሕፍት ቴክኒካል አገልግሎት (ካታሎጊንግና ክላሲፊኬሽን) ስልጠና እንደተሰጠ መረጃውን የጠቆሙን የተቋሙ የአብያተ መጻሕፍት ስልጠናና ምክር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ብዙወርቅ ተስፋዬ ነግረውናል፡፡
+5
ተቋሙ ፈረንሳይ 41 ኢየሱስ ቤተክርስትያን አካባቢ የሚገኘውን የወደቁትን አንሡ የነዳያን የበጎ አድራጎት ማኀበርን ጎበኘ
በጉብኝቱም በተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ የሥራ ክፍል ከተቋሙ ሰራተኞች የተሰበሰቡ ልባሽ ጨርቆችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ግምታቸው ከሰባት ሺህ ብር በላይ የሆኑ ከየሥራ ክፍሉ የተውጣጡ ተወካዮችን ቦታው ድረስ ይዞ በመሄድ አበርክቷል፡፡
