ar
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

الذهاب إلى القناة على Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
514
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ሐምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ዐዲስ አበባ ====================== *በቢላሉል አል ሐበሺ ሚውዚዬም ጉብኝት ተከናወነ። *ለኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የዕውቅ እና የምስክር ወረቀት ከሚውዚዬሙ ተበረከተለት፡፡ *ሚውዚዬሙ 25ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በቅርቡ ያከብራል። ---------------o----------------- የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣ ከሚመለከታቸው የተቋሙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ቢላሉል አል ሐበሺ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡ ቢላሉል አል ሐበሺ ሚውዚዬም በመዲናዋ ከሚገኙ ሃይማኖታዊ ሚውዚዬሞች አንዱ ሲኾን፣ የ25ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ለማክበር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ በቦታው ላይ በተገኘንበት ወቅት የተመለከትነው ጋዜጣዊ መግለጫ እማኝ ነበር፡፡ ሚውዚዬሙ በውስጡ በርካታ የሃይማኖቱ ታላላቅ የጽሑፍ ቅርሶችን፣ የታላላቅ የሃይማኖቱ አሊሞችን (ሊቃውንት) እና የእስልምና ጉዳዮች ፕሬዚዳንቶችን ፎቶ ግራፎችን እና አልባሳትን፣ ኢስላማዊ ይዘት ያላቸው መዛግብቶች እና ድርሳናትን፣ ደብዳቤዎችን፣ የሀገራችን ጥንታዊ መስጂዶች ፎቶግራፎችን፣ የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዓ.ወ.) ለኢትዮጵያ ንጉሥ የጻፉትን ደብዳቤ(ይዘቱ ታትሞ)፣ ስለ ባህል ሕክምና የተጻፉ ኪታቦችን እና ውዳሴያትን የያዙ ተፍሲሮች 'አጀሞች' እና የመንዙማ ግጥሞች ያሉበት፣ እንዲሁም ከ420 እስከ 520 ዓመታትን ያስቆጠሩ የቁርዓን ተፍሲሮች እና ከግብጽ ሀገር ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፓትርያርክ የተሠጠ ውዳሴ ማርያም፣ የቁርዓን የኪታብ የቅርስ እና የአልባሳት እንዲሁም የቀድሞ የሀገራችን  መገበያያ ገንዘቦችን ጭምር በውስጡ የያዘ ነው። ሚውዚዬሙ፥ እነዚህን ወድ እና ታላላቅ ታሪካዊ ቅርሶች ለመጪው ትውልድ ተጠብቀው እንዲሻገሩ ከማድረግ ተቀዳሚ ዓላማው ባሻገር፣ ያለፈውን ታሪክ የኋሊት መለስ በማለት እንድናይ የሚያደርግ  በጥራት እና በጥንቃቄ ለጎብኚዎች በሚመች መልኩ ተጠብቀው የሚገኙበት ሀገር በቀል ተቋም መኾኑን በጉብኝቱ ወቅት ተመልክተናል፡፡ በሚውዚዬሙ ያየነው ሌላው ልዩ ተግባር፥ ወጣቶችን እና አረጋውያን ሴቶችን በዐቅም እና በኢኮኖሚ አበልጽጎ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ የተቋቋሙት የማምረቻ ፕሮጀክቶች ናቸው። የጨርቃጨርቅ ውጤቶች ማምረቻ እና ማሠልጠኛ፣ የጫማ እና የቆዳ ውጤቶች ማምረቻና ማሠልጠኛ፣ እንዲሁም የቪድዮ ግራፊ እና ፎቶግራፍ ማሠልጠኛ ማዕከል በውስጡ በመክፈት ለሴቶች፣ ለወጣቶች እና ዐቅም ለሌላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች፤ ያለምንም የሃይማኖት ልዩነት ዐቅማቸውን ለማጎልበትና በኢኮኖሚ ለመደገፍ የሚረዱ ሥልጠናዎችን ጎን ለጎን እየሠጠ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ በጉብኝቱ መጨረሻም፥ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ላለፉት 80 ዓመታት የሀገርን ጥንታዊ እና አኹናዊ የጽሑፍ ሀብቶችን በማሰባሰብ፣ በተገቢው መንገድ በመጠበቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ እያደረገ ላለው ዘመን አይሽሬ ተግባር፣ እንዲሁም፥ የሐረሪን ጥንታዊ የሸሪዓዊ ሕግ ብይን ሠነዶችን በዘርፉ ከፍተኛ ምሁራን በማስጠናት በUNESCO Memory Of The World በዓለም የትዝታ መዝገብ ላይ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ እያከናወነ ላለው ታሪካዊ ተግባር በዘርፉ በዕጩነት ለማቅረብ እየተደረገ ያለውን ጥረት ቢላሉል አል ሐበሺ ሚውዚዬም 25ኛ ዓመቱን ለማክበር ጋዜጣዊ መግለጫ እየሠጠ በነበረበት መድረክ ላይ ለተቋሙ ያዘጋጀውን የዕውቅና የምስክር ወረቀት ለተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ለአቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት አበርክቷል፡፡

ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በታላቅ ድምቀት ሲካሔድ የነበረው የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ተጠናቀቀ። የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከንባብ ለህይወት ፐሮጀክት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከሐምሌ 24 እስከ ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት በድምቀት ሲካሔድ የነበረው የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ዛሬ ሐምሌ 27/2017ዓ.ም ተጠናቋል። በአውደ ርዕዩ ተባባሪ አዘጋጁ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የፎቶ ግራፍ  እና የመዛግብት አውደ ርዕይ፣የሕጻናት ንባብ አገልግሎት ሲያካሒድ እና ሲያስጎበኝ ሰንብቷል። በርካታ ደራሲያን በቦታው በአካል በመገኘት መጻፋቸውን ያስተዋወቁበትና ፊርማቸውን ያኖሩበት፤ የመጻሕፍት አሳታሚዎችና አከፋፋዮች በልዩ ልዩ ዘርፎች የተዘጋጁ መጻሕፍትን ለሽያጭ የቀረቡበት፤ ለልጆች የንባብ ልምምድ መጎልበት የሚያግዙና መፍትሔዎችን የሚጠቁሙ የባለሙያዎች የምክክር መድረኮች የተከናወኑበት እና የሃሳብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችም የተካሔደበት ነበር። በመጻሕፍት አውደ ርዕዩ ላይ ታላላቅ ደራሲያን፣ የመጻሕፍት አሳታሚዎች እና ሻጪዎች፣እንዲሁም በርካታ የመጽሐፍ ገዢዎች እና የሚድያ ባለሙያዎችና ታዳሚዎች፣ የኢትዮጵያ ልጆች አራቱንም ቀናት ልጆችን በማዝናናት የተሳተፉበት ነበር።

ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵ ያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በአዘጋጅነት የተሳተፈበት ታላቅ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ በይፍ ተከፈተ። የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) ከንባብ ለህይወት ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኤግዝብሽን ማዕከል ያዘጋጀው ታላቅ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ዛሬ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም  በይፍ ተከፍቷል። በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ፣ የንባብ ለህይወት ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ከበደ፣ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ፕሬዘዳንት አቶ አበረ አዳሙ ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ ፣ አንጋፍው የታሪክ ሊቅና ተመራማሪ ኢመሪተስ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ እንደዚሁም አንጋፍ ደራሲያን ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ክቡራን ታዳምያን ተገኝተውበታል። "የምናውቀውን ነገር ደጋግመን ስንሰማው የምንሰለች ይመስለኛል፣ የምናውቀው ነገር ደጋግመን መስማትም ትዕግስታችንን ይፈታተናል ። ነገር ግን ለራሳችን ታማኝ ሆነን የምናውቀው ሚመስለንን ነገር ደጋግመን ብንመረምረው በእውነት አናውቀውም። ...የንባብ ጉዳይ ከርዕሱ ጀምሮ እንዲያ ይመስለኛል። እውነት ግን ንባብ ምንድነው ቢባል ቀላል ጥያቄ አይሆንልንም ። ተግባሩ አንዳች የተፃፈ ነገር ላይ በአይን ትኩረት መመልከትን ስለሚመስል ከድርጊቱ ተነስተን ጥቂት ምላሽ ልንስጥ እንችላለን እንጂ በህይወታችን ውስጥ ባለው ዋጋ እና  በሚሰጠን የህይወት ትርጉም ልክ ልንገልጸው የሚቻለን አይደለም። ስለዚህ የምናውቀው የሚመስለን ነገር መጠርጠር ደግ ነው። ስለዚህ ስለ ንባብ፣ ስለ ንባብ ባህል ፣ ታላላቅ መጻሕፍትን አንብቦ ስለመረዳት ፣ ከንባብ በኋላ ሊኖር ስለሚገባው ጥልቅ እውይይት እንደገና ማሰብ፣ እንደገና መመርመር ጠለቅ ያሉ የንበብ ልምዶችን አስተውሎ ማየት እጅግ የተገባ ተግባር ነው:: " ያሉት አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የአውደ ርዕዩን መከፈት በይፍ ባበሰሩበት ወቅት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ፕ/ት አቶ አበረ አዳሙ ወመዘክር ካፈራቸው አንጋፍ ደራሲያንና መምህራን መካከል በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙትን ደራሲ ጋሽ ኃይለመለኮት መዋዕልን ጠቅሰው  ተቋሙን አመስግነዋል ። ኢመሪተስ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴም ባደረጉት ንግግር "ሁለተኛ ትምህርት ቤቴ" ሲሉ በግለ ታሪካቸው ላይ የገለፁትንና የማይተካ ሚና ያለውን የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ( ወመዘክር ) በህይወታቸው ትልቅ ስፍራ እንደሚሰጡት ገልጸው አመስግነዋል ። በመጨረሻም የንባብ አውደርዕዪ እስከ ሐምሌ 27/ 2017 እንደሚቆይ በመርሀግብሩ ላይ ተመላክቷል ።

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከንባብ ለህይወት ፐሮጀክት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከሐምሌ 24 እስከ ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆየው የመጻሕፍት አውደ ርዕይ የመክፈቻ መርሐ ግብር በድምቀት ተጀምሯል።

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል እንደ ሀገር የሚከናወነውን 7ኛው ዓመት በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሀግብር ዛሬ ሐ
+8
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል እንደ ሀገር የሚከናወነውን 7ኛው ዓመት በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሀግብር ዛሬ ሐምሌ 24/ 2017 ዓ.ም በቦሌ ቡልቡላ አከናወነ፡፡

ታላቅ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከንባብ ለህይወት ፐሮጀክት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከሐምሌ
ታላቅ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከንባብ ለህይወት ፐሮጀክት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከሐምሌ 24 እስከ ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም ለተከታታይ አምስት ቀናት የመጻሕፍት አውደ ርዕይ አዘጋጅተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በአውድ ርዕዮ ላይ በዋናነት የፎቶ ግራፍ እና መዛግብት አውደ ርዕይ፣የህጻናት ንባብ አገልግሎት ያካሒዳል፡፡ በርካታ ደራሲያን በቦታው በአካል በመገኘት መጻፋቸውን ያስተዋውቃሉ፣ፊርማቸውን ያኖራሉ፡፡ የመጻሕፍት አሳታሚዎችና አከፋፋዮች በልዩ ልዩ ዘርፎች የተዘጋጁ መጻሕፍትን በቅናሽ ያቀርባል፡፡ የሃሳብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችም እንዲሁ ተዘጋጅተዋል፡፡ ለልጆች የንባብ ልምምድ መጎልበት የሚያግዙና መፍትሔዎችን የሚጠቁሙ የባለሙያዎች የምክክር መድረኮች ይከናወናሉ፡፡ ከሐሙስ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በድምቀት በሚከፈተውና ለታዳሚ ክፍት በሚሆነው በዚሁ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ላይ እንድትታደሙ እንጋብዛለን፡፡ መግቢያ በነጻ