uz
Feedback
Eotc Task Force

Eotc Task Force

Kanalga Telegram’da o‘tish

ወቅታዊ ጉዳይ

Ko'proq ko'rsatish
7 370
Obunachilar
+424 soatlar
+907 kunlar
+34030 kunlar
Postlar arxiv
photo content

"አዲሲቷ ኢትዮጵያ?" 👉 ኦርቶዶክስ ጠል ናት 👉ኦርቶዶክስ በጣም ዝቅተኛ የሆነባት 👉በምንም ዓይነት ኦርቶዶክሳዊ ፖሊሲ የማይታወቅባት 👉ስለ ኦርቶዶክስ ምንም ዓይነት ድምፅ የማይሰማባት 👉ኦርቶዶክስ ሞተ አልሞተ ተብሎ የማይነገርባት 👉በኦርቶዶክሳውያን  ላይ የሚደርሰው ጥቃት ሁሉ የውሻ ደም የሆነባት 👉ኦርቶዶክስ መሪ መሆን አይችልም 👉ኦርቶዶክሳውያን የሆኑ አሳባቸው ተደማጭ ሊሆን አይችልም 👉የኦርቶዶክሳውያን አኗኗር ህግ ሊሆን አይችልም 👉 ቤተ ክርስቲያን እንደ አካል መገለጽ አትችልም ወንጀለኛ ናት 🔏እኛ ደግሞ እያልን ያለነው ወንጀለኛ ሆነን  መቀጠል አንችልም ነው።አለቀ።አራት ነጥብ። https://t.me/EotcTaskForce

❝አትግደል፣አትገደል፣ተጋደል❞ የመ/ር ፋንታሁን ዋቄ መልእክት

እስኪ እንወያይ 1) ቀድሞ የክርስቲያን ሀገር የነበሩ አሁን ግን የእስላም ሀገር የሆኑ ሀገራትን እስኪ ዘርዝሩአቸው። 2) በአክራሪ ወሀቢያ የፈራረሱ ሀገራትስ እነ ማን ናቸው?

ሁለት መረጃዎች 1) ከየገጠሩ ተሰደው አቦምሳ ከተማ የተጠለሉ 1271 በላይ የሚሆኑ ኦርቶዶክሳውያን አባወራዎች "ከተማችንን እያጣበባችሁ ነውና ለቃችሁ ውጡ"የሚል ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው ነው።ይኽ ሕዝብ ወዴት ይሂድ? 2) ሰሞኑን ምዕራብ አርሲ አሳሳ ወረዳ ሻሼ የሚባል አከባቢ ላይ ጫካ ያለው ኀይል በከፈተው ድንገተኛ ጥቃት 36ፖሊስና ሚሊሻ ተገድሏል።ከእነዚህ መካከል 33 ኦርቶዶክሳውያን ናቸው።ከዚህ በፊትም ከ አሰላ ከተማ ኦርቶዶክስ የሆኑ ፖሊሶችን  ብቻ ሰብስበው ልከው እንዳስፈጇቸው አሁንም በአሳሳ ያንን ታሪክ ነው የደገሙት።ባገኙት አጊጣሚ ሁሉ ኦርቶዶክሱን የመምታት መንግሥታዊ ፕሮጄክት።

+2
10 የዘር ማጥፋት ደረጃዎች(Ten Stages Of Genocide) አሉ።አሥሩም ተፈጽመውብናል።የመጨረሻው(10)መካድ(Denial )ነው። ለእነዚህ ሰዎች የእኛ እልቂት ልማት ነው፣የእኛ መሰደድና መሰቃየት ልማት ነው።ብቸኛው አማራጭ ራስን መከላከል ነው

እኛ አትግደሉን ስንል ፖለቲካ ከሆነ የእናንተ መግደልና ማፈናቀልስ ምን ሊባል ነው?

👉እንደዜጋ የማትቆጥረን ሀገር ሀገራችን ልትሆን አትችልም 👉በሃይማኖታችን ምክንያት የሚገድለን የሚያፈናቅለን መንግሥት መንግሥታችን ሊሆን አይችልም 👉 ሊጠብቀን ሊታደገን ሲገባው ከገዳይ ጋር ተባብሮ በሞታችን የሚሳለቅ ሞታችን የሚሸፋፍን እረኛ አባት ሊሆነን አይችልም እንደ ዜጋ የምትቆጥረን ሀገር፣በሃይማኖታችን የማይ

በአርሲ ምድር በሚደረገው ኦርቶዶክስን የማጥፋት ዘመቻ ውስጥ ወጣቱም፣ሽማግሌውም፣ህጻናቱም ይገደላሉ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ግን ወንዶች ናቸው።ለምን ወንዶችን አብዝተው ይጨፈጭፋሉ? 👉 የሚገዳደራቸ
በአርሲ ምድር በሚደረገው ኦርቶዶክስን የማጥፋት ዘመቻ ውስጥ ወጣቱም፣ሽማግሌውም፣ህጻናቱም ይገደላሉ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ግን ወንዶች ናቸው።ለምን ወንዶችን አብዝተው ይጨፈጭፋሉ? 👉 የሚገዳደራቸው የ ሚያጠቃቸው እንዳይኖር 👉 የክርስቲያን ዘር እንዳይተካ 👉 ሴቶችን ያገባሉ ያሰልማሉ ✍ ሀብት ንብረታቸውን ያሰልማሉ

እንዳይረሳ
+1
እንዳይረሳ

ጥንቃቄ‼️ ወሀቢያዎች በAI የተቀነባበሩ ፎቶዎችን እያሠራጩ ነው።ከዚያን ኦርቶዶክሱ እውነት መስሎት ሲቀባበልላቸው "በሐሰት ስማችንን አጠፉት " እያሉ ለማጯጮኽ ነው።ተነቃቅተናል ።
ጥንቃቄ‼️ ወሀቢያዎች በAI የተቀነባበሩ ፎቶዎችን እያሠራጩ ነው።ከዚያን ኦርቶዶክሱ እውነት መስሎት ሲቀባበልላቸው "በሐሰት ስማችንን አጠፉት " እያሉ ለማጯጮኽ ነው።ተነቃቅተናል ።

ለበርገር የመነኮሱ ሰዎችን አጀንዳ ማድረግ እናቁም።አጀንዳችንን አንቀይርም
+1
ለበርገር የመነኮሱ ሰዎችን አጀንዳ ማድረግ እናቁም።አጀንዳችንን አንቀይርም

ቁሳዊ ውድመት፦ ከ600 በላይ የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል/ተቃጥለዋል። የሃይማኖት ተቋማት፦ ሁለት ታሪካዊና ትልልቅ አብያተ ክርስቲያናት (የ101 ዓመቷ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የጃዊ አቦ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ) ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። የመፈናቀል ቀውስ፦ በአሁኑ ወቅት በርካታ ሴቶች፣ ሕፃናትና አዛውንቶች የለበሱትን ልብስ ብቻ ይዘው፣ ያለ መጠለያና ያለ ምግብ በተለያዩ ከተሞች ተሰደው ይገኛሉ። ባጠቃላይ፤ ሪፖርቱ በአርሲ አካባቢ የሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች "በሕይወት የመኖር ዋስትና" ሙሉ በሙሉ ማጣታቸውን እና ችግሩን ለመፍታት መዋቅራዊና ገለልተኛ የሆነ ጣልቃ ገብነት (ፍትህ) እንደሚያስፈልግ በነዋሪዎች ሕመም የተሞላ አንደበት የሚያስረዳ ታሪካዊ ሰነድ ነው።

የአርሲው ሪፖርት የቀረበው የመስክ ዳሰሳ ሪፖርት በአርሲ ዞን ውስጥ በተለይም ከጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም. እስከ ግንቦት ወር 2018 ዓ.ም. ባሉት ስምንት ወራት ውስጥ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸሙ ተከታታይ ጥቃቶችን፣ የደረሱ ሰብአዊና ቁሳዊ ውድመቶችን፣ የነዋሪዎችን የስነ-ልቦና ስብራት እና የመንግሥትና የፀጥታ አካላትን ሚና በጥልቀት የሚያሳይ ነው። ይህን ሪፖርት በስፋትና በጥልቀት ለመረዳት በሚከተሉት 6 ዋና ዋና ጭብጦች ከፍሎ መተንተን ይቻላል፦ 1. ጥቃቶቹ ሃይማኖታዊ መሆናቸውንና የየቆዩ መሆናቸውን 2 የስምንት ወራቱ የጥቃትና የጭፍጨፋ የጊዜ ሰሌዳ (Timeline of Violence) ሪፖርቱ በጥቅምት፣ የካቲት፣ ሚያዚያ እና ግንቦት ወራት 2018 ዓ.ም. የተፈጸሙትን ሰቅጣጭ ድርጊቶች በዝርዝር አስቀምጧል፦ ጥቅምት 13–15 (ጉናና እና መርቲ ወረዳ)፦ በሁለት ቀናት ውስጥ 36 ኦርቶዶክሳውያንተገድለዋል። የጥቃቱ አሰቃቂነት የሚገለጠው ከተገደሉት ውስጥ 14ቱ አስከሬናቸው ሳይነሳ ቀርቶ በእርሻ ማሳዎች ላይ በጅብ መበላታቸው ነው። ጥቅምት 17 (ሽርካ ወረዳ)፦ 5 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ፣ የሃይማኖት አብሮነትን ለማሳየት የሞከረና ክርስቲያኖችን በቤቱ የደበቀ 1 ሙስሊም ነዋሪ አብሮ ተሰውቷል። ጥቅምት 19 (ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)፦ የሃይማኖት አገልጋይ (ካህን) ጨምሮ 6 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል፤ 18 ሰዎች (15 አባወራዎችና 3 ሴቶች) ታፍነው እስካሁን የት እንዳሉ አይታወቅም። የካቲት 20 (ሽርካ ወረዳ - ጃዌ ዋጩ ቀበሌ)፦ በሁለት ቀናት ውስጥ 28 ምዕመናን ተገድለዋል። የጃዊ አቦ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ተዘርፎና ተቃጥሎ 7 አስከሬኖች በግቢው ውስጥ ተገኝተዋል (አንድ መነኩሲትና ሁለት አቅመ-ደካሞችን ጨምሮ)። ግንቦት 23 (አሰኮ ወረዳ - ጠለታ ጨፋ ቀበሌ)፦ 13 አባወራዎች በጥይት ተመትተው፣ በስለት ተጨፍጭፈው ተገድለዋል። እድሜ ጠገቧ (የ101 ዓመት) የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት እንድትወድም ተደርጓል። 3. የማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ መዋቅር መናጋት (Socio-Psychological Impact) ጥቃቱ ሰዎችን ከመግደል ባለፈ፣ ማህበረሰባዊ ህይወትን ሙሉ በሙሉ አሽመድምዶታል፦ የቤተሰብ መበታተን፦ አባወራዎች የእርሻ መሬታቸውን ላለማጣት ሲሉ ብቻ በስጋት ማሳ ላይ ሲያድሩ፣ ሴቶችና ልጆች ደግሞ ወደ አሰላ ከተማ ተሰደው ይኖራሉ። የማንነት ማደናገር (Identity Labeling)፦ በሪፖርቱ ላይ ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ በጥቃቱ ወቅት የብሔር ማንነት ዋጋ ያጣል። አንድ ሰው የኦሮሞ ወይም የጉራጌ ተወላጅ ቢሆንም እንኳ፣ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ከሆነ ብቻ "አማራ/ነፍጠኛ" የሚል ታርጋ ተለጥፎለት ጥቃት ይፈጸምበታል። የእምነት ቦታዎች መታወክ፦ በስጋት ምክንያት የአብያተ ክርስቲያናት ምዕመናን ቁጥር በእጅጉ ተመናምኗል። አገልግሎት የሚያቀርቡት ጥቂት ቆራጥ ካህናትና ዲያቆናት ብቻ ሲሆኑ፣ ጥቃቱ  ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን ማውደም ላይ ያተኮረ ነው። 4. የመንግሥት፣ የፀጥታ አካላት እና የቤተክህነት ሚና (Institutional Failures) ሪፖርቱ በፍጅቱ ወቅት ተቋማት የነበራቸውን ደካማ ወይም አጋዥ ሚና በምሬት ይተቻል፦   የአካባቢው መዋቅር ግዴለሽነትና ዛቻ፦ ነዋሪዎች ጥቃቱ ከመፈጸሙ በፊት ለወረዳ አስተዳደርና ለፖሊስ ቢያመለክቱም፣ የተሰጣቸው ምላሽ ግን ጥበቃ ማድረግ ሳይሆን *"የነፍጠኛ አስተሳሰባችሁን ትታችሁ ኑሩ፤ ካልሆነ ወደመጣችሁበት ተመለሱ"* የሚል የማግለልና የማስፈራራት ቃላት ነበር።   የፀጥታ ኃይሎች መዘግየትና ቸልተኝነት፦ በመርቲ ወረዳ ጥቃት ሲሰነዘር የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ይመጣል ተብሎ ነዋሪው ጥበቃ ሳያደርግ እንዲዘናጋ ከተደረገ በኋላ፣ ኃይሉ የደረሰው ጥቃቱ ተፈጽሞ ብዙ ሰው ካለቀ ከሁለት ሰዓት በኋላ ነው። በሌላ በኩል በህዳር 1 ቀን ጥቃት ሲፈጸም የመንግሥት ኃይሎች በቅርብ ርቀት ላይ ቢኖሩም አልተከላከሉም፤ ሲጠየቁም *"ስማችንን እያጠፋችሁ ነው"* የሚል ንቀት የተሞላበት ምላሽ ሰጥተዋል።በሌሎች ወረዳዎችም እንዲሁ ተመሳሳይ ነው።   የመረጃ ማዛባት (Manipulation of Information)፦ የሃይማኖት ጉባኤ አጣሪ ኮሚቴ መረጃ ለመሰብሰብ ሲመጣ እውነተኛ ነዋሪዎች እንዳያገኟቸው ተደርጎ፣ በአስተዳደሩ የተመረጡ ሰዎች ብቻ መረጃ እንዲሰጡ ተደርጓል። በርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ፊት በተደረገ ስብሰባም የተወሰኑ  የሃይማኖት አባቶችና ሁለት ጳጳሳት ችግሩን ከማጋለጥ ይልቅ "የማሞገስና ጥቃቱን የማቃለል" ስራ ሰርተዋል። የቤተክህነት ድክመት፦ ለአርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ ቢደወልም "ከመንግሥት ጋር እየተነጋገርን ነው፤ ራሳችሁን ለመከላከል ሞክሩ"* ከሚል የተለመደ ምላሽ ውጪ የነፍስ አድን ስራ አልተሰራም። 5. ኢኮኖሚያዊ ዘረፋና እገታ (Economic Warfare) ጥቃቱ ኦርቶኮክሳዊነትን ማጥፋት ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ የኢኮኖሚ ጥቅም ማከመቻ እየሆነ መጥቷል፦   ማስፈራሪያዎች የሚጀምሩት በክረምት ወራት (አዝመራ ከመድረሱ በፊት) ሲሆን፣ አላማው ነዋሪው ጥሎ እንዲጠፋና የእርሻ መሬቱን ለመንጠቅ ታስቦ ነው። በሰላም ስም የተመለሱ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ የገንዘብ እገታ ይፈጸማል (ለምሳሌ የአንድ ቤተሰብ አባላት ታፍነው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቀው፣ 1.5 ሚሊዮን ብር ቢከፈልም አባወራው ተገድሏል)። ይህ የሚያሳየው ጥቃቱ ወደ "የገንዘብ ማግኛ ንግድ (Kidnapping Industry)" ጭምር መቀየሩን ነው። 6. አጠቃላይ የጉዳት መግለጫ (ማጠቃለያ) በስምንት ወራት (ከጥቅምት - ግንቦት 2018 ዓ.ም.) ውስጥ የደረሰው አጠቃላይ ውድመት፦ የሰው ህይወት፦ ከ100 በላይ ንጹሃን ምዕመናን በእምነታቸው ምክንያት ብቻ ተለይተው ተገድለዋል።

photo content
+2

Share 'Arsi_Report_2018.pdf'

..................መጋቢት ወር ላይ በወረዳችን ብዙ የፀጥታ ኃይል ስለተሰማራ “የተፈናቀሉት ይመለሱ፤ ሙሉ ጥበቃ እናደርጋለን” ተብሎ ስለነበር፣ ስጋት ቢኖርም በከፊል ነዋሪው ወደ አካባቢው እንደተመለሰ ነዋሪዎች ያስረዳሉ። በመንገድ ላይ አልፎ አልፎ እገታዎች እንደነበሩና በገንዘብ ድርድር እያስለቀቁ እንደነበርም ገልፀውልናል። ሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም. ለበዓል የተሰበሰቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት ድንገተኛ በተደረገባቸው እገታ በድምሩ 2 ሚሊዮን ብር እንደተጠየቀባቸው ተገልጿል። ከህዝብ ተሰብስቦ 1.5 ሚሊዮን ብር ቢሰጣቸውም፣ የቤቱን አባወራ ገድለው ሌላውን የቤተሰብ አባል እንደለቀቁ ነዋሪዎች ያብራራሉ። “በምርጫ ሰሞን አካባቢው ላይ የነበረው የፀጥታ ኃይል በአብዛኛው ለቆ ስለወጣ ስጋታችን ጨምሮ ነበር” የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች፣ ከወረዳ አመራሮች ጋር በተነጋገሩበት ጊዜ “ትዕዛዙ ከክልል የመጣ ስለሆነ ለእናንተ በቂ ጥበቃ እንመድባለን” ተብሎ እንደተገለጸላቸው ያስረዳሉ። ግንቦት 23/2018 ዓ.ም. በአሰኮ ወረዳ ጠለታ ጨፋ ቀበሌ በድንገት በተከፈተ ተኩስ 13 አባወራዎች ሲገደሉ፣ ቁጥራቸው እስካሁን በውል ያልታወቀ ሰዎች ታግተው እንደተወሰዱ ነዋሪዎች ገልፀዋል። “ድርጊቱ እጅግ አሰቃቂ ነበር፤ በጥይት መትተው ብቻ አልተዋቸውም፣ ተከታትለው በስለት ጨፍጭፈዋቸዋል” ሲሉ በሐዘን ያብራራሉ። በአካባቢው 101 ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠረችው የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት መውደሟም ተገልጿል። ይህች ቤተክርስቲያን በግፍ ተጨፍጭፈው የተገደሉ ምዕመናን የተቀበሩባት ቦታ እንደነበረች ተነግሯል። “አሁን በሕይወት ያለው ብቻ ሳይሆን በግፍ የሞቱትም ረፍት አላገኙም” ሲሉ ነዋሪዎች በሐዘን ገልፀዋል። እኛም በተፈናቀሉበት ቦታ ተዘዋውረን እንደተመለከትነው፣ ከለበሱት ልብስ በስተቀር ሌላ ምንም ንብረት ያልያዙ ሴቶች፣ ሕፃናትና አዛውንቶችን ተመልክተናል። በካራ ኩፍቴ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይም ጥቃት መደረሱ ተገልጿል። “ጽላቱን ይዘን አሁን ወዳለንበት ደርሰናል” የሚሉት ነዋሪዎች፣ ቤተክህነቱም ሆነ መንግሥት ምንም ትኩረት እንዳልሰጣቸውና ፍርድን ከመድኃኔዓለም እንደሚጠብቁ በለቅሶ ገልፀዋል። “ዛሬ እዚህ በተፈናቀልንበት ቦታ በሰላም ለማደር እንኳን ዋስትና የለንም፤ ለዘመናት ለፍተን የገነባነው ሀብትና ንብረታችን ወድሟል፤ ስናዝን መፅናኛችን የነበረው ቤተክርስቲያን ዛሬ የለም” የሚሉት ነዋሪዎች፣ “እየደረሰብን ያለውን መከራ ታሪክና የኢትዮጵያ ሕዝብ ይመዝግብልን” ሲሉ በምሬት ይገልፃሉ። በተመሳሳይ ዕለት በሚታና ዋጂ ቀበሌ ሁለት ወጣቶችን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አርደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉ ነዋሪዎች ገልፀዋል። በስለት የታረደው ወጣት በደህንነት ስጋት ምክንያት ተፈናቅሎ ከሄደ በኋላ በቅርቡ እንደተመለሰም ተገልጿል። በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ምዕመናንና የቤተሰብ አባላት በአንድ መቃብር ተሰብስበው ተቀብረዋል። በዚሁ ዕለት 3 ወጣቶች ታፍነው እንደተወሰዱ የተገለፀ ሲሆን፣ በአካባቢው የተሰማራው የፀጥታ ኃይል ባደረገው የተኩስ ልውውጥ በሕይወት ማስለቀቅ እንደተቻለም ተነግሯል። በአጠቃላይ በስምንት ወራት ውስጥ ከ100 በላይ ምዕመናን በእምነታቸው ምክንያት ሲገደሉ፣ ሁለት አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ በሙሉ ወድመዋል፤ ከ600 በላይ ቤቶችም ፈርሰዋል። “ስንገደል አንበዛም፤ ስንገደል እየቀነስን ነው” ሲሉ ነዋሪዎች በሐዘን ይናገራሉ። ሁንድሳ በላይ ዋቅጅራ

በነጋታው ደግሞ በእርሻ ቦታ ላይ 21 ሰዎች ተገድለዋል። ብፁዕ አቡነ ኤልሳ ሀገረ ስብከቱ ላይ ከተመደቡ በኋላ፣ ከዞንና ወረዳ አመራሮች ጋር በየጊዜው የሚካሄዱትን የኦርቶዶክሳውያንን ጭፍጨፋ ለማስቆም ብዙ ጥረት እንዳደረጉና፣ ጥረታቸው ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ፍሬ ያፈራ ቢመስልም፣ ከተወሰኑ ወራት በኋላ ተደጋጋሚ ዛቻዎች እንደመጡ የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ አሁንም ከፍተኛ ስጋት ስላለ አካባቢውን ሸሽቶ ከመሄድ ውጪ አማራጭ እንደሌለ ይናገራሉ። ይቀጥላል....

ከዚህ በታች የቀረበው ሪፖርት በአካል በቦታው በመገኘት፣ ከተለያዩ ሃይማኖቶችና ብሔሮች ነዋሪዎች አንደበት የተሰበሰበ መረጃ ስለሆነ ምንም ዓይነት ወገንተኝነት የለውም። በአርሲ አካባቢ በተደጋጋሚ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸም ጥቃትና ጭፍጨፋ ምክንያት፣ በቦታው ተገኝተን ስለሚካሄደው ተደጋጋሚ ግድያ መረጃ እንድንሰበስብ ላገዛችሁን ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ። “አርሲ ላይ ለምን ጥቃት ይካሄዳል?” የሚለውን ጥያቄ ነበር ያነሳነው። አርሲ የተለያዩ ብሔሮችና ሃይማኖቶች በብዛት ከሚኖሩባቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ከግጦሽ ግጭት እስከ ሃይማኖታዊ ግጭቶች ድረስ በተደጋጋሚ የሚስተዋሉበት አካባቢ ነው። ይህንም ባለፉት አርባ ዓመታት የተዘገቡ ሪፖርቶችን ዋቢ በማድረግ ማረጋገጥ ይቻላል። ዳሰሳ ለማድረግ የሞከርነው ከጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ያለውን ሁኔታ ነው። ከክረምት ጀምሮ ከአካባቢው ለቀው እንዲወጡ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ሲደርሷቸው እንደነበር የገለጹልን ነዋሪዎች፣ በሁለት ሃሳብ መካከል ተጠምደው እንደቆዩ አስረድተውናል። “ከዚህ በፊትም በግጦሽና በእርሻ ዙሪያ ግጭቶች ቢኖሩም፣ በእርቅና በሽምግልና ይፈቱ ነበር። አሁን ግን በመሣሪያ የታገዘ ማስፈራሪያ ማድረግ ጀምረዋል” በማለት የጀመረው የአንድ ነዋሪ አስተያየት፣ ሁኔታው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄዱን ያመለክታል። ይህን ተከትሎ ብዙ ነዋሪዎች ጫና በመበርታቱ ወደ አሰላ ከተማ በመሸሽ፣ የእርሻ መሬታቸውን በመመላለስ ለመከታተል ሞክረዋል። አብዛኞቹ ሴቶችና ልጆቻቸውን በአሰላ በማስቀመጥ፣ አባወራዎቹ በእርሻ ማሳቸው በመዋልና በማደር አስቸጋሪ ጊዜያቶችን እንዳሳለፉ የሚናገሩት ነዋሪዎች ናቸው። በሁሉም ወረዳዎች ያሉ አብያተ ክርስቲያናትም በስጋት ምክንያት የምዕመናኑ ቁጥር የተመናመነ ሲሆን፣ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት የተወሰኑ ካህናትና ዲያቆናት ብቻ መሆናቸውን ገልጸውልናል። ከጥቅምት ወር በፊት አልፎ አልፎ አፈናዎች ቢኖሩም፣ ከጥቅምት አጋማሽ ጀምሮ የታጠቁ አካላት በሰፊው ማጥቃት የጀመሩበት ጊዜ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ያስረዳሉ። ለአብነት፦ • ከጥቅምት 13/2018 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም. ሌሊት ድረስ በጉናናና በመርቲ ወረዳዎች በተከታታይ በተፈጸመ ጥቃት 36 ሰዎች ተገድለዋል። ከእነዚህ ውስጥ 22 ዕለቱን የተቀበሩ ሲሆን፣ 14 ሰዎች ግን ከቀናት በኋላ በእርሻ ቦታዎችና በተለያዩ ቦታዎች ተገለው ተገኝተዋል። ግማሹ በጅብ ተበልተው ሰብስበን የቀበርናቸው ሲሆን፣ 8 ሰዎች ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። • ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም. ሌሊት በሽርካ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት 5 ክርስቲያኖች ተገድለዋል። አንድ ሙስሊም ደግሞ በቤቱ ክርስቲያኖችን በመደበቁ ምክንያት መገደሉ ተገልጿል። • ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም. በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት አንድ አገልጋይ ካህንን ጨምሮ 6 አባወራዎች ተገድለዋል። በዚሁ ወረዳ በተመሳሳይ ቀን 15 አባወራዎችና 3 ሴቶች ታፍነው ተወስደዋል፤ እስካሁን ድረስ ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም። • ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም. ከሽርካ ወረዳ በመሸሽ ላይ የነበሩ አባወራዎች “አካባቢው ሰላም ሆኗል፤ ተመልሳችሁ ግቡ” ተብለው ሲመለሱ፣ ከሚሊሻዎች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት 4 አባወራዎችና አንዲት ሕፃን ያዘለች ሴት ተገድለዋል። በአጠቃላይ በጥቅምት ወር በተካሄደው ተከታታይ ጥቃት፦ • 53 ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ተገድለዋል፤ • 1 ሙስሊም በተጨማሪነት ተገድሏል፤ • 500 ቤቶች ወድመዋል። እነዚህ ጥቃቶች ከመከሰታቸው በፊት ተደጋጋሚ ዛቻና እገታ ይፈጸምብን ነበር የሚሉት ነዋሪዎች፣ ለወረዳው አስተዳደርና ለፖሊስ በተደጋጋሚ ማመልከታቸውን ገልጸዋል። ነገር ግን የተሰጣቸው ምላሽ፣ “የነፍጠኛ አስተሳሰባችሁን ትታችሁ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተከባብራችሁ ኑሩ፤ ካልሆነ ወደየመጣችሁበት መመለስ ትችላላችሁ” እንደተባሉ የሚገልጹት ነዋሪዎች፣ “ተወልደን ካደግንበት ሀገራችን ወዴት እንሄዳለን?” በማለት በሐዘኔታ ይናገራሉ። ግድያው በዋናነት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ያነጣጠረ ቢሆንም፣ ለመከላከልና ለመደበቅ የሞከሩ የእስልምና እምነት ተከታዮችም አብረው እንደተገደሉ ነዋሪዎቹ ይገልጻሉ። “በአርሲ ውስጥ ክርስቲያን ከሆንክ፣ ኦሮሞም ብትሆን ጉራጌም አማራ ተብለህ ነው የምትታይው” ሲሉም ያክላሉ። በእነዚህ ጥቃቶች ወቅት ለአርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ ደውለን የተሰጠን ምላሽ፣ “ከመንግሥት ጋር እየተነጋገርን ነው፤ ራሳችሁን ለመከላከል ሞክሩ” ከሚል ውጪ ውጤታማ የሚባል አልነበረም ይላሉ። ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም. በመርቲ ወረዳ ስጋት እንዳለ ለወረዳው ፖሊስ አዛዥና ለአቡነ ያሬድ በተደጋጋሚ ማሳወቃቸውን የገለጹ ነዋሪዎች፣ “የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እየመጣላችሁ ነው፤ ተረጋጉ” ተብለው እንደነበር ይናገራሉ። ነገር ግን ሌሊት ታጣቂዎች ሲገቡ “ልዩ ኃይሎች ናቸው” በሚል ከለላ ሳይይዙ በመቅረታቸው፣ በዚያ ጥቃት ብዙ ምዕመናን እንደተገደሉ ያስረዳሉ። ከሁለት ሰዓታት በኋላ የመጡት ልዩ ኃይሎች ቀሪውን ምዕመን ለመከላከል እንደሞከሩና፣ የተገደሉትም በፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ አንድ ላይ እንደተቀበሩ ተገልጿል። በህዳር 1/2018 ዓ.ም. በቀጠለው ጥቃት እህል በመውቃት ላይ የነበሩ 3 ምዕመናን ተገድለዋል። ግድያው በተፈጸመበት ቦታ ቅርብ ርቀት ላይ የመንግሥት ኃይሎች እንደነበሩ ተገልጿል። “ለምን አልተከላከላችሁልንም?” በሚል የህዝብ ቁጣ ሲነሳ፣ “መረጃ እያቀበላችሁ ስማችንን እያጠፋችሁ ነው” የሚል ንቀት የተሞላበት ምላሽ እንደተሰጣቸው ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ደግሞ፣ ተገድለው ከሚቀበሩት በተጨማሪ ታፍነው የተወሰዱና ያሉበት ያልታወቀ በርካታ ወጣቶች መኖራቸው ነው። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት፣ ስጋቱ በየጊዜው እየጨመረ ሲሆን፣ ሰዎችም ያላቸውን ሁሉ ትተው ወደ ተለያዩ ከተሞች እየተሰደዱ ነው። በአካባቢው በመዘዋወር ለመመልከት እንደቻልነውም፣ ብዙ ቤቶች ተዘግተው ኗሪ አልባ ሆነው ለመመልከት ችለናል። ከሃይማኖት ጉባኤ አጣሪ ኮሚቴ ወደ ወረዳዎች በመጡበት ወቅት፣ መረጃ እንዲሰጡ የተደረጉት እውነተኛ ነዋሪዎች ሳይሆኑ፣ በወረዳ አስተዳደርና በዞን ፖሊስ ትዕዛዝ የተመረጡ ሰዎች እንደነበሩ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። በዚሁ ወቅት በርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ አማካኝነት ከወረዳዎች የተለያዩ ሰዎችና አመራሮችን ለማነጋገር በተደረገ ስብሰባ፣ በአካል የማይታወቁ አንዳንድ የሃይማኖት አባቶች ጥቃቱን በትክክል ከማስረዳት ይልቅ የማሞገስ ንግግር እንዳደረጉና፣ ሁለት ጳጳሳትም የሚፈጸመውን ጥቃት ለማቃለል እንደሞከሩ ተነግሯል። በመጨረሻም ለነዋሪው ዘላቂ መፍትሄ ሳይቀርብ ስብሰባው መበተኑ ተገልጿል። የካቲት 20/2018 ዓ.ም. በሽርካ ወረዳ ጃዌ ዋጩ ቀበሌ በሁለት ቀናት ውስጥ 28 ምዕመናን ተገድለዋል። 8 ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ደግሞ እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ አይታወቅም። “ሞተው ከሆነም እንኳ እርማችንን አላወጣንላቸውም” በማለት ነዋሪዎቹ ሐዘናቸውን ገልጸዋል። በዕለቱ በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ አንድ ቤተ ክርስቲያንም ተዘርፎ፣ ደጀ ሰላሙና አዳራሽ ቤቱ ተቃጥለዋል። ይህ ጥቃት የተፈጸመው በጃዊ አቦ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ነው። 7 ሰዎች ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ አስከሬናቸው ተገኝቷል። ከሰባቱ ውስጥ አንድ አገልጋይ መነኩሲትና ሁለት በመቃብር ቤት የሚኖሩ የኔቢጤዎች ነበሩ።