Eotc Task Force
Kanalga Telegram’da o‘tish
7 365
Obunachilar
-224 soatlar
+1857 kunlar
+33230 kunlar
Postlar arxiv
7 365
ጥሩምባ ሰው ታውቃላችሁ?
ከገዳዮቻችን ቀጥሎ ዋጋ እያስከፈለን ያለው ጥሩምባ የሆነ ሰው ነው።ወሬኛ ማለት ነው።በፍጹም ወሬ መቋጠር አይችልም።አርሲ ላይ ኦርቶዶክሱ እንዳይደራጅ ፈተና የሆኑት ጡሩምባዎች ናቸው።ራሳችንን እንከላከል ብለህ አውርተኸው ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መረጃውን ከሌሎች ትሰማዋለህ።
7 365
+4
ማስታወቂያ
ዛሬ ሰኞ ምሽት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 2:00 ሰዓት ጀምሮ ውይይት አለን።የዛሬ ተጋባዥ እንግዶቻችን፦
1) መምህር ፋንታሁን ዋቄ እና
2) ዲያቆን ዮሴፍ ከተማ ሆርዶፋ
ርዕስ፦ ማንነት ምንድን ነው? ኦርቶዶክስ ኦሮሞን ነጥሎ የመምታት ሴራ፣በኦርቶዶክስ ላይ የተባበሩ ኀይሎች
Eenyummaan Maali? Shira Ortdoksii Oromoo Foo'anii Rukutuu,Humnoota Ortodoksii Ballessuuf Waliin Hiriiran
7 365
🚨 አጣዳፊ የሰብአዊ እርዳታ ጥሪ ለአርሲ ተፈናቃዮች! 🚨
በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በደረሰው ጥቃት የወገኖቻችን ህይወትና ንብረት መውደሙ ይታወሳል። አሁን ላይ ከቀያቸው ተፈናቅለው በከባድ ችግር ውስጥ የሚገኙትን ወገኖቻችንን ወደ ቀደመ ሰላማዊ ኑሯቸው ለመመለስና የወቅቱን አጣዳፊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የእናንተን ድጋፍ ይሻሉ።
ምዕመናን፣ ባለሀብቶችና በጎ አድራጊዎች ሁሉ በሀገረ ስብከቱ እውቅና በተከፈተው በዚህ አካውንት የተቻላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉ በቅዱስ ገብርኤል ስም እንማጸናለን።
📌 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦
👉 ቁጥር፦ 1000772136394
👉 ስም፦ ጠለታ ቅ/ገብርኤል ተፈናቃዮች ገቢ ማሰባሰቢያ
የተሰደዱትን ማጽናናት የሁላችንም ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው!
7 365
Yaa Hawaasa Ortodoksii Dhagayi፦
Harkaa fi miila kee marattee Teessee hamtootaan hin ajjeefamin, lafa qe’ee keerraas hin buqqa’in, ofirraa ittisi. "Biyyi ni diigamti" jedhanii kanneen si burjaajessan hin dhaga’in; yeroo warra nama ajjeesanii fi nama qalanitti kan hin diigamne Ortodoksiin yommuu of ittisu garuu biyyi diigamtu si'a tokko miti, si’a kudhan haa diigamtu.
7 365
ኦርትዶክሳዊው ማኅበረሰብ ሆይ፦
እጅህና እግርህን አጣጥፈህ ተቀጠህ በጨካኞች አትገደል ከገዛ ርስትህም አትሰደድ ራስህን ተከላከል ።ሀገር ትፈርሳለች እያሉ የሚያደነዝዙ ምንደኞችን አትስማ ፣ ለገዳዮችና ለአራጆች ሲሆን የማትፈርስ ኦርቶዶክስ ሲከላከል ግን የምትፈርስ ሀገር እንኳን አንድ ጊዜ አሥር ጊዜ ትፍረስ
7 365
እንዲህ የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ አምምሮዬ ላይ ይመጣብኛል፦
ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰሜኑ ኦርቶዶክስ ቢዳከም " አንተ ከእኛ ወገን ነህ እያሉ የሚያታልሉት" የኦሮሞን ኦርቶዶክስ ሁለት ቀን ያሳድሩታል ወይ?
እናንተስ ምን ትላላችሁ?
7 365
👉እኔ በዘርና በሰፈር የማላስብ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነኝ!!
◈አንተስ? አንቺስ?
◈ከሁሉ በላይ በሆነች ሐዋርያዊት ኦርቶዶክሳዊት አስተሳስብ እመራለሁ እንጂ በቋንቋ፣በሰፈር ታጥሬ የማልኖር ክርስቲያን ነኝ።
◈ከማይጠፋ ዘር ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማሕፀነ ዮርዳኖስ የተወለድሁት ምድራዊ ዘር ልቆጥር እና ልመነዝር አይደለም።
◈በኦርቶዶክሳዊነቴ አባቴም እናቴም እግዚአብሔር ነው።"አንተ አቡነ ወአንተ እምነ-አንተ አባታችን አንተ እናታችን ነህ።"እንዲል።
◈የአንዲት የሐዋርያዊት ሰማያዊት ጉባኤ ማኅበርተኛ ስለሆንሁ በቡድን የማልታጠር ክርስቲያን ነኝ።
◈አንተ አንቺ ኦርቶዶክስ ከንህ? ከሆንሽ? ሰፈርህ? ሰፈርሽ ወዴት ነው?
◈ኦርቶዶክሳውያንን ከፋፍሎ ማማሰል የኦርቶዶክሳውያን ተግባር አይደለም ብየ በጥብቅ ቡድንተኝነትን አቃወማለሁ።
◈ስለሆነም እምነት አልባ ፖለቲከኞች ነውራቸውን ለመሸፈን እና ሥሁት ሀሳባቸውን ለማስፈን በጎሳ፣በሰፈር፣በቋንቋ አጥር ውስጥ ዘግተውብህ እንዳይሆን አእምሮህን ፈትሽ።
◈ዲያቆን፣ካህን፣መምህር፣ጳጳስ፣ሁኖ እግዚአብሔርን አገለግላለሁ የመንግሥተ ሰማያትን በር አሳያለሁ እያለ በሰፈር በቋንቋ የሚከፋፍል ከሆነ እሱ አባት ሳይሆን የገሀነም አጋፋሪ ነው።
◈እኛ ኦርቶዶክሶች የወይን ግንዳችን አንድ ክርስቶስ ሲሆን እኛም የአንዱ ግንድ ቅርጫፎቹ ነን።ዮሐ.፲፭፥፭
◈ራሳችን ክርስቶስ አንድ ሲሆን እኛም ኅዋሳቶቹ ነን።ቆላ.፩፥፲፰
የተቀበልነው በአንዲት ሃይማኖት በአንዲት ህሊና ሁነን አንዱን ክርስቶስን ነው።
◈ለእኛ፦አንድ ሃይማኖት፣አንድ ወንጌል፣አንድ አረዳድ፣አንዲት ጥምቀት፣አንድ ሥጋ አንድ ደም፣አንድ መስቀል፣አንድ ኅብረት፣አንድ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት አለን።
◈ከዚህ ውጪ የሰፈር ኦርቶዶክስነትየለም።አለ የሚል ሰው ካለ እሱ ገና በክርስቶስ የማያምን ከ-ሀ-ዲ ነው።
◈ቅዱስ ሚካኤል፣ቅ.ገብርኤል፣ቅ.ሩፋኤል.ቅዱሳን መላእክት የእኛ ሰፈር ሰዎች ናቸው እንዴ?
◈ቅድስት ማርያም፣ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ቅ.ቂርቆስ የእኛ ሰፈር ሰዎች ነበሩ እንዴ?
◈ቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅ.ጳውሎስ፣ቅ.ዮሐንስ፣ቅ.ዮሐንስ የእኛ ሰፈር ሰዎች ናቸው እንዴ?
◈ሄኖክ፣ኖኅ፣አብርሃም፣ኢዮብ፣ኤልያስ፣ኢሳይያስ፣ኤርምያስ፣ዳንኤል..የእኛ ሰፈር ነቢያት ናቸው እንዴ?
◈ቅዱስ አትናቴዎስ፣ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፣ቅ.ቄርሎስ፣ቅ.ዲዮስቆሮስ..የእኛ ሰፈስ ሊቆች ነበሩ እንዴ?
◈ታዲያ ኦርቶዶክስ ሁነህ እንዴት እንዲህ ቀበሌኛ ትሆናለህ?
◈በተለይም ዲያቆን፣ካህን፣መምህር፣ጳጳስ ሁኖ እንዴት የሰፈር አጥር ውስጥ ይቀመጣል?
እንዲህ አይነት ሰው የምር ሃይማኖት አለው?በወንጌል ያምናል? አያምንም
◈ሰፈርተኛ ሰው በየትኛ ክርስቶስ እያመነ ይሆን?መችም የክርስቲያኖች ክርስቶስ በሰማይ በምድር የመላ ያለ እና የሚኖር ነውና።
"እውነቱን ስለ ነገርኋችሁ ጠላት ሆንሁባችሁን?"ገላ.፬፥፲፮
የኔታ ገብረመድኅን እንየው
7 365
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
👉እኔ በዘርና በሰፈር የማላስብ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነኝ!!
◈አንተስ? አንቺስ?
◈ከሁሉ በላይ በሆነች ሐዋርያዊት ኦርቶዶክሳዊት አስተሳስብ እመራለሁ እንጂ በቋንቋ፣በሰፈር ታጥሬ የማልኖር ክርስቲያን ነኝ።
◈ከማይጠፋ ዘር ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማሕፀነ ዮርዳኖስ የተወለድሁት ምድራዊ ዘር ልቆጥር እና ልመነዝር አይደለም።
◈በኦርቶዶክሳዊነቴ አባቴም እናቴም እግዚአብሔር ነው።"አንተ አቡነ ወአንተ እምነ-አንተ አባታችን አንተ እናታችን ነህ።"እንዲል።
◈የአንዲት የሐዋርያዊት ሰማያዊት ጉባኤ ማኅበርተኛ ስለሆንሁ በቡድን የማልታጠር ክርስቲያን ነኝ።
◈አንተ አንቺ ኦርቶዶክስ ከንህ? ከሆንሽ? ሰፈርህ? ሰፈርሽ ወዴት ነው?
◈ኦርቶዶክሳውያንን ከፋፍሎ ማማሰል የኦርቶዶክሳውያን ተግባር አይደለም ብየ በጥብቅ ቡድንተኝነትን አቃወማለሁ።
◈ስለሆነም እምነት አልባ ፖለቲከኞች ነውራቸውን ለመሸፈን እና ሥሁት ሀሳባቸውን ለማስፈን በጎሳ፣በሰፈር፣በቋንቋ አጥር ውስጥ ዘግተውብህ እንዳይሆን አእምሮህን ፈትሽ።
◈ዲያቆን፣ካህን፣መምህር፣ጳጳስ፣ሁኖ እግዚአብሔርን አገለግላለሁ የመንግሥተ ሰማያትን በር አሳያለሁ እያለ በሰፈር በቋንቋ የሚከፋፍል ከሆነ እሱ አባት ሳይሆን የገሀነም አጋፋሪ ነው።
◈እኛ ኦርቶዶክሶች የወይን ግንዳችን አንድ ክርስቶስ ሲሆን እኛም የአንዱ ግንድ ቅርጫፎቹ ነን።ዮሐ.፲፭፥፭
◈ራሳችን ክርስቶስ አንድ ሲሆን እኛም ኅዋሳቶቹ ነን።ቆላ.፩፥፲፰
የተቀበልነው በአንዲት ሃይማኖት በአንዲት ህሊና ሁነን አንዱን ክርስቶስን ነው።
◈ለእኛ፦አንድ ሃይማኖት፣አንድ ወንጌል፣አንድ አረዳድ፣አንዲት ጥምቀት፣አንድ ሥጋ አንድ ደም፣አንድ መስቀል፣አንድ ኅብረት፣አንድ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት አለን።
◈ከዚህ ውጪ የሰፈር ኦርቶዶክስነትየለም።አለ የሚል ሰው ካለ እሱ ገና በክርስቶስ የማያምን ከ-ሀ-ዲ ነው።
◈ቅዱስ ሚካኤል፣ቅ.ገብርኤል፣ቅ.ሩፋኤል.ቅዱሳን መላእክት የእኛ ሰፈር ሰዎች ናቸው እንዴ?
◈ቅድስት ማርያም፣ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ቅ.ቂርቆስ የእኛ ሰፈር ሰዎች ነበሩ እንዴ?
◈ቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅ.ጳውሎስ፣ቅ.ዮሐንስ፣ቅ.ዮሐንስ የእኛ ሰፈር ሰዎች ናቸው እንዴ?
◈ሄኖክ፣ኖኅ፣አብርሃም፣ኢዮብ፣ኤልያስ፣ኢሳይያስ፣ኤርምያስ፣ዳንኤል..የእኛ ሰፈር ነቢያት ናቸው እንዴ?
◈ቅዱስ አትናቴዎስ፣ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፣ቅ.ቄርሎስ፣ቅ.ዲዮስቆሮስ..የእኛ ሰፈስ ሊቆች ነበሩ እንዴ?
◈ታዲያ ኦርቶዶክስ ሁነህ እንዴት እንዲህ ቀበሌኛ ትሆናለህ?
◈በተለይም ዲያቆን፣ካህን፣መምህር፣ጳጳስ ሁኖ እንዴት የሰፈር አጥር ውስጥ ይቀመጣል?
እንዲህ አይነት ሰው የምር ሃይማኖት አለው?በወንጌል ያምናል? አያምንም
◈ሰፈርተኛ ሰው በየትኛ ክርስቶስ እያመነ ይሆን?መችም የክርስቲያኖች ክርስቶስ በሰማይ በምድር የመላ ያለ እና የሚኖር ነውና።
"እውነቱን ስለ ነገርኋችሁ ጠላት ሆንሁባችሁን?"ገላ.፬፥፲፮
7 365
ልብ በሉ፦
ይኽ የግፍ ግፍ የሚፈጸመው፦
👉አልቃይዳ በሚንቀሳቀስባቸው በኢራቅ በረሃና ኮርብቶች አይደለም
👉ቦኮሃራም በሚንቀሳቀስባቸው በናይጄሪያ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉 መንግሥት በማይደርስባቸው ISIS በሚንቀሳቀሱባቸው በሊቢየ በረሃ አይደለም
👉ISIS በተቆጣጠራቸው በፑንትላንድ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉አልሸባብ በሚንቀሳቀስባቸው በሶማሊያና በሶማሊንድ ኮረብቶች አይደለም ፦
እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።ሥርዐቱስ ኦርቶዶክሳውያን ማጽዳት የተቋቋመበት ዋና ዓላማው ነውና ዝም ቢል አያስገርምም የእኛ ዝም ማለት ግን ያናድዳል።
ወያኔ ወያኔ እያሉ እሬሳውን የጎተቱትም ሆነ በግድ ማዕተባቸውን በጥሰው እንዲሰልሙ የተደረጉ ኦርቶዶክሳውያን በነፍስ የሚጠብቃቸው፦
👉 ቤተ ክህነት የሚባል መዋቅር አላቸው
👉ሲኖዶስ የሚባል የጳጳሳት ጉባኤ አላቸው
👉ፓትርያርክ አላቸው
👉የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አለ
👉የወረዳው ቤተ ክህነት አለ
👉የአጥቢያው አስተዳዳሪ አለ
👉ወንጌል የሚያስተምራቸው መምህር አላቸው
👉የንስሐ አባት አላቸው
👉 በጥምቀት የሚመስለው ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ አለ
ከእነዚህ ሁሉ ግን ለምን ብሎ የጠየቀ የተቆጣም የለም።እኛም ምዕመናን መከራን ተለማመድነው። አትግደሉን ማለትን እንደ ፖለቲካ ቆጠርነው።
እስከመቼ በዚህ ድንዛዜያችን እንቀጥል ወገን?
7 365
+2
STOP THE KILLING OF ORTHODOX PRIESTS IN ARSI Ethiopia 🇪🇹 💕🙏💕
Ethiopian American civil society
