uz
Feedback
Life In Truth - በእውነት መንገድ ህይወት

Life In Truth - በእውነት መንገድ ህይወት

Kanalga Telegram’da o‘tish

“የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥” 2ኛ ቆሮ 10፥5 NB: I am here to give not to receive. Facebook https://www.facebook.com/Intruthlife Email intruthlife@gmail.com Tik Tok tiktok.com/@life_in_truth

Ko'proq ko'rsatish
442
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+27 kun
+9430 kun

Ma'lumot yuklanmoqda...

O'xshash kanallar
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Sentabr '26
Sentabr '26
+8
0 kanalda
Avgust '26
+100
1 kanalda
Get PRO
Iyul '26
+8
0 kanalda
Get PRO
Iyun '26
+2
0 kanalda
Get PRO
May '26
+7
0 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+13
1 kanalda
Get PRO
Mart '26
+11
0 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+23
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+46
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+33
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+90
1 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+185
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
10 Sentabr0
09 Sentabr0
08 Sentabr+1
07 Sentabr0
06 Sentabr0
05 Sentabr+1
04 Sentabr0
03 Sentabr+1
02 Sentabr+3
01 Sentabr+2
Kanal postlari
2
God is faithful to His promise that whoever seeks Him will find Him, whoever asks will receive, and whoever knocks, the door
God is faithful to His promise that whoever seeks Him will find Him, whoever asks will receive, and whoever knocks, the door will be opened.” --------‐-------- God has made Himself known to those who seek Him. We do not discover God through human wisdom alone, but through His revelation in creation, His Word, His Son, and the work of the Holy Spirit. Knowing God is a lifelong journey in which He continually draws us closer to Himself and transforms us into the likeness of Christ. James 4:8 (KJV) •••••••••• "Draw nigh to God, and he will draw nigh to you." From the book "Who is the God we worship?", page 50-57 Get your free copy following the link 👇 https://t.me/Intruthlife/311 To become part of the family of our Life Intruth Ministry, join our social media platforms through the links below: ▶️ YouTube: http://www.youtube.com/@Intruthlife 📱 Telegram: https://t.me/Intruthlife 📘 Facebook: https://web.facebook.com/Intruthlife/ 🎵 TikTok: https://www.tiktok.com/@life_in_truth
423
3
እግዚአብሔር የፈለገ እንደሚያገኝ፣ የለመነ እንደሚሰጠው ደግሞ ማንም በር ያንኳኳ እንደሚከፈትለት ቃል የገባ፣ እንደ ቃሉም የሆነ እና ሲፈለግ በሙላት የሚገኝ ታማኝ አምላክ ነው። ---------‐---
እግዚአብሔር የፈለገ እንደሚያገኝ፣ የለመነ እንደሚሰጠው ደግሞ ማንም በር ያንኳኳ እንደሚከፈትለት ቃል የገባ፣ እንደ ቃሉም የሆነ እና ሲፈለግ በሙላት የሚገኝ ታማኝ አምላክ ነው። ---------‐----- እግዚአብሔር በቅን ልብ ለሚፈልጉት ራሱን ገልጧል። እግዚአብሔርን በሰው ጥበብና በራሳችን ምርምር ብቻ አናገኘውም፤ እርሱ በፍጥረት፣ በቃሉ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ራሱን ስለገለጠልን እናውቀዋለን። እግዚአብሔርን ማወቅ በአንድ ቀን የሚያበቃ ጉዞ ሳይሆን ዕድሜ ልክ የሚቀጥል መንፈሳዊ ጉዞ ነው። በዚህ ጉዞ ውስጥ እግዚአብሔር በየቀኑ ወደ ራሱ ይበልጥ ያቀርበናል፣ ባሕርያችንንም ወደ ክርስቶስ መልክ ይለውጣል። ስለዚህ የእኛ ፍላጎት ሁልጊዜ እርሱን የበለጠ ማወቅና ከእርሱ ጋር ያለንን ኅብረት ማሳደግ ሊሆን እንደሚገባ ማስታወስ ያስፈልጋል። የያዕቆብ መልእክት 4:8 (NASV) •••••••••• ⁸ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ፤ እርሱም ወደ እናንተ ይቀርባል።  የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? ከሚለው መጽሐፍ ከገፅ 18-23 ካለው ክፍል የተወሰደ መጽሐፉን ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/296 . . . . . . በእውነት መንገድ ሕይወት /Life in Truth/ ቤተሰብ ለመሆን ከስር ያሉትን ሊንኮች ይከተሉ! Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ቴሌግራም፦ https://t.me/Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
66
4
እንደነዚህ ካሉት ራቅ - Avoid people like these // Habtamu Lulseged https://youtube.com/watch?v=EtvFO4UUfWE&si=nUNn8e-OjJKmNn-q
132
5
እያንዳንዱ ዕለት የራሱ የሆነ በቂ ችግር አለው! የማቴዎስ ወንጌል 6:34 (NASV) •••••••••• ³⁴ ስለዚህ ለነገ በማሰብ አትጨነቁ፤ የነገ ጭንቀት ለነገ ይደር፤ እያንዳንዱ ዕለት የራሱ የሆነ
እያንዳንዱ ዕለት የራሱ የሆነ በቂ ችግር አለው! የማቴዎስ ወንጌል 6:34 (NASV) •••••••••• ³⁴ ስለዚህ ለነገ በማሰብ አትጨነቁ፤ የነገ ጭንቀት ለነገ ይደር፤ እያንዳንዱ ዕለት የራሱ የሆነ በቂ ችግር አለውና።
127
6
አልፎ መሄድ // ራዕይን መጠበቅ // እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ // ሀብታሙ ሉልሰገድ // Habtamu L... https://youtube.com/watch?v=EO3KGyHV0-U&si=wrOroGNrpmexG97y
138
7
አልፎ መሄድ // ራዕይን መጠበቅ // እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ // ሀብታሙ ሉልሰገድ // Habtamu L... https://youtube.com/watch?v=EO3KGyHV0-U&si=wrOroGNrpmexG97y
1
8
》 የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው?《 --------------------- እንደ አንድ አማኝ በእርግጥ የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? የእኔ እግዚአብሔር እነዚህ ሁሉ በአለም ላይ የሚገኙ ሌሎች የእምነት ክፍሎች ከሚጠሩት እግዚአብሔር በምን ይለያል? እንደሚገባ በአክብሮትና በፍርሃት በእውነተኛም ፍቅር ከልብ በሆነ በእውነትና በመንፈስ የሆነ አምልኮ እርሱን ለማምለክ ስለ እርሱ ማወቅ የሚገባኝ ምንድን ነው? ወዘተ የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ በእጅጉ ያስፈልገናል። እግዚአብሔር አምላካችን ራሱን የደበቀ እናውቀውም ዘንድ የማይወድ ድብብቆሽ የሚጫወት አምላክ አይደለም። ነገር ግን ከልብ ሲፈልጉት የሚገኝ፣ መታወቅንም የሚወድ ከእስትንፋሳችን ሁሉ ይልቅ ወደ እኛ ቀርቦ በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ራሱን የገለጠ የእውቀት አምላክ ነው። በተቃራኒው እግዚአብሔር አለማወቅን በእጅጉ የሚጠላ የምናደርገውን ሁሉ በእውነት፣ በእውቀትም እንድናደርገው የሚፈልግ አምላክ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በምሳሌ መጽሐፍ ምዕራፍ 9፡10 ላይ እንደሚናገረው የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ሲሆን እርሱን ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል እንደሆነ ይነግረናል። ፍቅር ከእውቀት የሚመነጭ ነገር ሲሆን እግዚአብሔርን እንደሚገባ በፍጹም ልብ፣ በፍጹም ሃሳብ፣ በፍጹም ኃይልና በፍጹም ነፍስ ለመውደድየእርሱን ፍቅር፣ በጎነት፣ ምህረት፣ ርህራሄ፣ ትዕግስት ወዘተ ማወቅ በእጅጉ ጠቃሚ ነው። ይሄው እምነታችን የተገኘበት ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል በ2ኛ ጴጥሮስ 1:4 ላይ እንደሚናገረው በእውነት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ባለው እውነተኛ ብርሃን ይኸውም ከእግዚአብሔር አፍ የወጣ ህያው ቃል የሚያምን እና ከዚሁም የተወለደ አንድ አማኝ የመለኮት ባህርይ ተካፋይ ለመሆን እና አምላኩን እግዚአብሔርን ለመምሰል የተጠራ ነው። ይህንኑ የተጠራበትን ግብም ለመምታትና ትርጉም ያለው እውነተኛ ኅብረትን ከአምላኩ ጋር ለማድረግ እርሱንም ለመምሰል አምላኩንም ሊመለክ እንደሚገባው በእውነትና በመንፈስ ለማምለክ የሚያመልከው ይህ ዝነኛ ባለ ታላቅም ስም አምላክ እግዚአብሔር በእርግጥ ማን እንደሆነ ማወቅ የግዴታ ያስፈልገዋል። ይህንንም በአማኙ ማህበረሰብ መካከል የሚታይ ትልቅ ክፍተት ለመሙላት እና ህዝቡን ከአምላኩ ጋር ለማስተዋወቅ ይህ “የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? የሚል መጽሐፍ በእጅጉ የሚረዳ እንደሚሆን አምናለሁ። ታዲያ በእርግጥ ይህ የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? “ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቷል። ዕውቀትን ስለ ናቃችሁ፣ እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤“ — ትንቢተ ሆሴዕ 4:6 — የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? ከሚለው መጽሐፍ የመግቢያ ክፍል የተወሰደ መጽሐፉን ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/296 . . . . . . በእውነት መንገድ ሕይወት /Life in Truth/ ቤተሰብ ለመሆን ከስር ያሉትን ሊንኮች ይከተሉ! Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ቴሌግራም፦ https://t.me/Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
243
9
Every believer must wrestle with certain essential questions: Who, truly, is the God whom we worship? In what way is the God I confess different from the gods proclaimed by the countless religious traditions of the world? What must I know about Him in order to worship Him rightly—with reverence and holy fear, with genuine love, and in spirit and in truth? Our God is not one who hides Himself or delights in remaining unknown. He does not play games with His creation. Rather, He is a God who desires to be known and who reveals Himself to those who seek Him sincerely. Closer to us than our very breath, He has made Himself known through all that He has created. He is the God of knowledge, and He despises ignorance. Indeed, He desires that everything we do be done in truth and with understanding. As the Scriptures declare in Proverbs 9:10, “The fear of the Lord is the beginning of wisdom, and the knowledge of the Holy One is understanding.” Love springs from knowledge, and if we are to love God with all our heart, all our mind, all our strength, and all our soul, we must come to know His goodness, His mercy, His compassion, His patience, His faithfulness, and His love. The Word of God, upon which our faith is founded, teaches us in 2 Peter 1:4 that through His promises believers become “partakers of the divine nature.” Everyone who believes the living Word that proceeds from the mouth of God and is born again through it has been called to reflect the character of God and to become more like Him. In order to fulfill this calling, to enjoy true fellowship with the Creator, and to worship Him in spirit and in truth, every believer must know who this glorious and majestic God truly is. It is my conviction that one of the great needs within the Christian community today is a deeper knowledge of God. It is precisely to help address this need and to introduce believers to the God whom they worship that this book, Who Is the God We Worship? has been written. My prayer is that it will serve as a useful guide, helping many to know God more deeply and to grow into a richer fellowship with Him. And so, we arrive at the question with which this book begins: Who, then, is the God whom we worship? You can find your free copy of the eBook “Who Is the God We Worship?” by following the link below. 👇 📖 Free eBook: https://t.me/Intruthlife/311 To become part of the family of our Life Intruth Ministry, join our social media platforms through the links below: ▶️ YouTube: http://www.youtube.com/@Intruthlife 📱 Telegram : https://t.me/Intruthlife 📘 Facebook: https://web.facebook.com/Intruthlife/ 🎵 TikTok: https://www.tiktok.com/@life_in_truth
162
10
》》 ምክር ለሁላችን 《《 -----‐--------------- እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ የሚወድ ለሰው ልጆች ያለው ሃሳቡም ሰላም አና ህይወት የሆነ ለዚህም አላማ ክብሩን ሁሉ ትቶ ከሰማይ ወርዶ የሰው ልጅ እስከ መሆን እና ለጠላቶቹ እስከ መሞት በመድረስ የገለጠው እውነት ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። ይሁን እንጅ የሰው ልጅ ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ ከዚህ ህይወት ባለመታዘዝ እየሸሸ በጥፋት እና በሞት ማዕበል እየተመላለሰ ይታያል። የሰው ልጆችን የሚወደው መልካም አምላክ እግዚአብሔር ሰው ከጥፋቱ ተመልሶ እንደገና በህይወት ይኖር ዘንድ ወደ ማስተዋሉ እንዲመለስ እና ይቅር ተብሎ እንዲኖር ባገኘው መንገድ ሁሉ ማሳሰቢያን እና ማሰጠንቀቂያን ይሰጣል። በአንድም በሌላም መንገድ እግዚአብሔር ሲናገር የማያሰተውለው ሰው ከጥፋቱ ከመመለስ ይልቅ በሀጢአት ላይ ሌላ ሀጢአትን እየጨመረ በንስሃ ተመልሶ ይቅር ሳይባል ለክፉ መሻቱ እና ምኞቱ ተላልፎ ሲሰጥ ይታያል። ይህም ዛሬ ላይ በሀገራችን እንደሚታየው አይነት ለመኖር የሚያስፈራ ዘመንን ያመጣል። በሽታ፣ ቸነፈር፣ ችግር፣ ርሃብ፣ ሞት፣ ጦርነት፣ ሰላም ማጣት፣ ፍርሃት ወዘተ የመሳሰሉት ሁኔታዎች የሰው ልጆችን ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት የሚናገሩ የእግዚአብሔር ቋንቋዎች ሲሆኑ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የሚያልፉ የሰው ልጆች ግን ንስሃ ከመግባት ይልቅ በደነደነ አንገት በጥፋታቸው ሲቀጥሉ፣ ለጥፋታቸው የተለያየ ማስተባበያ እና ማብራሪያን ሲሰጡ፣ በጣኦት አምልኮ ሲመላለሱ፣ እግዚአብሔርን ሲበድሉ አለፍ ሲልም ሲሳደቡ ይታያሉ። ሀገራችን ባለፉት አመታት በምድር ላይ ያለውን ሁሉ ችግር እያስተናገደች የምትገኝ ሲሆን ዛሬም ፈፅማ ያልተፈወሰች በሽታዋን ታቅፋ ህዝቧን ለፈውስ የምትጠብቅ የምታሳዝን ሀገር ናት። በሌሎች አገሮች የሚሆነው ነገር ህዝባችንን ሀገር የማጣትን ጉዳት ሊያስተምረው ያልቻለ ሲሆን ዛሬም ድረስ በሌላ ከዚህ የባሰ ጥፋት አገሩን አፍርሶ በራሱ ለመማር በሞኝነት እየታገለ ይገኛል። የእግዚአብሔር ፍላጎት በደረሰብን መከራ /በእምነታችን ምክንያት ከሚደርስ የተገባ መከራ በስተቀር/ በእርግጥ እግዚአብሔርን እንደበደልን በማስተዋል በንስሃ ተመልሰን በሰላም እንድንኖር ነው። ከላይ በተደጋጋሚ ለመግለፅ እንደሞከርኩት የአንዲት ሃገር ሁኔታ የሚወሰነው በአገሪቱ ውስጥ ባሉ ህዝቦች የህይወት ምልልስ ሲሆን በሀጢአት ወይም በፅድቅ ህይወት ውስጥ መሆናቸው የሚነሳላቸውን ንጉስ ክፉ/ደግ ሊያደርገው የሚችል ነው። ከዚህም በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስ ስልጣን ሁሉ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ እንደሆነ በመግለጽ ሰዎች ሁሉ ለነገስታት በመገዛት እንዲኖሩ የሚያዝ ሲሆን መቃወምንም የስልጣኑን ምንጭ እግዚአብሔርን እንደመቃወም የሚቆጥር ነው። ይህ ማለት በምርጫ የወደዱትን መምረጥ አይቻልም ማለት ግን አይደለም። በየትኛውም አይነት አገዛዝ ውስጥ አንድ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ሰው ለመኳንንት እና ለገዥዎች እየፀለየ ለጌታ እንደሚገዛ በፍፁም መታዘዝ በመገዛት ፅድቅን በመውደድ እንዲኖር በፈጣሪው የታዘዘ ነው። ፀሎት ገዥን የማውረድ እና የማንሳት አቅም ያለው ሲሆን በአዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው ከትጥቅ ትግል የበረታ ያለ ምንም ኪሳራ ሰላምን በምድር ላይ የሚያስቀጥል አዋጭ መንገድ ነው። ሀገራችን የሁላችንም የጋራ ሃብት የሆነች ጊዜያዊ መኖሪያችን ስትሆን ዛሬ ላይ ያለን የዛሬ ትውልዶች በጋራ በማስተዋል ክፋቱ እየጨመረ በሚሄድ አለም ውስጥ እግዚአብሔርን በመፍራት በመኖር እና እግዚአብሔርን መፍራት ለልጆቻችን በኑሮ በማስተማር ነገ ልጆቻችን የሚኖሩባትን የተሻለች ሰላማዊ ሀገር ለመስራት መረባረብ ይኖርብናል። ይህም የሁላችንንም አስተዋፅኦ የሚፈልግ ሲሆን ርቀን ከሄድንበት የጣኦት አምልኮ በመመለስ፣ ሀጢአትን በመጥላት፣ ከእግዚአብሔር ጋር በመስማማት፣ ሰላምን በመውደድ በመመላለስ የሚገለፅ ነው። ከሌሎች ሀገራት በመማር ከእልከኝነታችን በመመለስ እግዚአብሔር በምድራችን ውስጥ ያስቀመጠውን የተፈጥሮ ሃብት በሰላም እና በፍቅር አውጥተን መጠቀም እንድንችል ወደ አንድነት መምጣት ያስፈልገናል። ይህም በየቤታችሁ በዝምታ ውስጥ ሆናችሁ አገሪቱ ስትጠፋ የምትመለከቱ በዘረኝነት በሽታ ያልታመማችሁ ሀገር ወዳድ ጤነኛ ዜጎችን ድምፅ የሚፈልግ በየተሰማራንበት ስፍራ በጥላቻ ፋንታ ፍቅርን፣ በልዩነት ፋንታ አንድነትን፣ በሀጢአት ፋንታ ፅድቅን በመስበክ እና በመኖር የሚመጣ ነው። በማህበራዊ ሚዲያ ውስጥ ከሚገኙ ተሳዳቢ፣ ፀብን የሚወዱ፣ መለያየትን የሚሰብኩ፣ ጦርነት የገቢ ምንጫቸው ከሆኑ ማስተዋል የጎደላቸው ሰዎች ራስን በማራቅ፣ ብሎም ወደ ማስተዋል እንዲመጡ በመፀለይ፣ ከውሸታቸው የሚበልጥ እውነትን በመግለጥ፣ ለከንቱ ከፋፋይ ስብከታቸው ጆሮ ባለመስጠት ተባብረን ሰላምን ማምጣት ከሁላችን ይጠበቃል። የጣልናቸውን የጋራ ሀገራዊ መልካም እሴቶች እንደገና ለማንሳት በመወሰን እንደገና በህይወት ልንኖር ያስፈልገናል። እንደገና_በህይወት_መኖር /ሪቫይቫል ለኢትዮጲያ/ ከሚለው መፅሐፍ ገፅ 414 ጀምሮ የተወሰደ ሙሉ መፅሃፉን በነፃ ለማግኘት ከታች ያለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/5 . . . . . . Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
128
11
Today is my birthday, and as I reflect on my journey, all I can see is God’s grace, favor, and protection that brought me thi+1
Today is my birthday, and as I reflect on my journey, all I can see is God’s grace, favor, and protection that brought me this far. And on this special day, I wanted to give rather than receive. So, as a gift to the Church of Christ, I present my third book and my very first book in English: “Who Is the God We Worship?” I did not translate this book simply to have another book in English. I did it because the problem of not knowing who God is is not limited to Ethiopia. It reaches across Africa and beyond. In many parts of the world, the problem has gone even further—from not knowing God to denying His very existence. Although there are already many books on this subject, we never know what God may do through one more book to edify His bride and remind us that the Church is one and universal. This book is offered freely from the beginning—not as a product for profit, but as a gift. All praise to the Lord, for from Him, by Him, and to Him are all things Pray for me & don't forget to say happy birthday😆😁
173
12
Today is my birthday, and as I reflect on my journey, all I can see is God’s grace, favor, and protection that brought me this far. And on this special day, I wanted to give rather than receive. So, as a gift to the Church of Christ, I present my third book and my very first book in English: “Who Is the God We Worship?” I did not translate this book simply to have another book in English. I did it because the problem of not knowing who God is is not limited to Ethiopia. It reaches across Africa and beyond. In many parts of the world, the problem has gone even further—from not knowing God to denying His very existence. Although there are already many books on this subject, we never know what God may do through one more book to edify His bride and remind us that the Church is one and universal. This book is offered freely from the beginning—not as a product for profit, but as a gift. All praise to the Lord, for from Him, by Him, and to Him are all things Pray for me & don't forget to say happy birthday😆😁
1 165
13
》 እግዚአብሔርን አለማወቅ ዋጋ ያስከፍላል።《 --------------------- እግዚአብሔርን ማወቅ ሐይማኖታዊ ግዴታ ብቻ ሳይሆን የእውነተኛ አምልኮ መሠረቱ ነው። ቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን እ
》 እግዚአብሔርን አለማወቅ ዋጋ ያስከፍላል።《 --------------------- እግዚአብሔርን ማወቅ ሐይማኖታዊ ግዴታ ብቻ ሳይሆን የእውነተኛ አምልኮ መሠረቱ ነው። ቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን እንደሚገባ ማወቅ ያልወደዱን ሰዎች ሕይወታቸው ወደ ጨለማ፣ ወደ መደናገርና ወደ ጥፋት እንደሚያመራ ደጋግመው ያሳያሉ። በተቃራኒው ወደ እርሱ የሚመለሱ ምሕረትን፣ መታደስንና ሕይወትን ያገኛሉ። ስለዚህ ስለ እግዚአብሔር መስማት ወይም መረጃ መያዝ ብቻ አይበቃም፤ እርሱን በግል ልምምድና በቀረበ ኅብረት ማወቅን ልንከታተል ይገባናል። እግዚአብሔርን በምናውቀው መጠን እንኖረው ዘንድ ያዘጋጀልንን እውነተኛ ሕይወት እናገኛለን። “ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቷል። ዕውቀትን ስለ ናቃችሁ፣ እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤“ — ትንቢተ ሆሴዕ 4:6 — የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? ከሚለው መጽሐፍ ከገፅ 13-17 ካለው ክፍል የተወሰደ መጽሐፉን ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/296 . . . . . . በእውነት መንገድ ሕይወት /Life in Truth/ ቤተሰብ ለመሆን ከስር ያሉትን ሊንኮች ይከተሉ! Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ቴሌግራም፦ https://t.me/Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
150
14
Matn yo'q...
162
15
በጊዜው በአለም ሃያል የነበረችው የባቢሎን ገዥ ናቡከደናፆር እግዚአብሔር የሰጠውን ታላቅነት ረስቶ በታበየ ጊዜ፣ በእርግጥ የስልጣን ሁሉ ምንጭ ደግሞ የነገስታት ሁሉ ንጉስ እግዚአብሔር እርሱ እንደሆነ ያውቅ ዘንድ በምህረት ለሰባት አመታት ማስተዋሉ የተወሰደ፣ ሰው ያልሆነ፣ እንደ እንስሳ ጫካ የሚኖር፣ ጥፍሩና ፀጉሩ ያደገ፣ በቤተ መንግስቱ የተረሳ እንስሳ የሆነ ሰው እንዲሆን አደረገው። በሐዋርያት ስራ 12 ታሪክ ውስጥ የሚገኘው ሔሮድስ ሌላው ምስክር ሲሆን ራሱን እንደ እግዚአብሔር መቁጠሩ ብሎም በህዝቡ ላይ ያከበዳት እጁ ስልጣኑ ሳያስመልጠው በመላዕክ ተመትቶ በትል ተበልቶ እንዲሞት አደረገው። ማስተዋል ለሚችል ሰው ይህ የመዝራትና የማጨድ ህግ በማህበረሰቡ መካከል ሁሉም ሰው ትናንትናው ዛሬውን እየወሰነለት ሲኖር ማየቱ በቂ ትምህርት ነው። ዛሬ /አሁን/ ማንም ሰው መልካም ወይም ክፉ ለማድረግ እድል እና መብት ያለው ሲሆን ይህም ነገውን የሚወስን ወዶ እንደዘራው በግዱ ሊያጭደው የተገባ ዘር ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንደኛ የነገስታት መጽሃፍ የሚገኙት ኢዮርብዓም፣ ባኦስ፣ እና አክአብ መልካም ያደርጉ ዘንድ እግዚአብሔር ከአፈር ላይ ያነሳቸው እና ስልጣን የሰጣቸው ነገስታት ሲሆኑ ታምነው ከተሰጡት ኃላፊነት በመጉደል፣ ክፉ በማድረግ እና በእግዚአብሔር ላይ በማመፅ ህዝቡን ለጥፋት የዳረጉ፣ እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ ዘራቸው ሁሉ ፈፅሞ እንዲጠፋ ስልጣኑን በሰጣቸው የአለም ሁሉ ጌታ በእግዚአብሔር የተፈረደባቸው እንደዛውም የተደረገባቸው ዛሬ ህያዋን ለሆንን ለእኛ ትምህርት የሚሆኑ ምስክሮች ናቸው። ዛሬ እጃችሁ ላይ ያለው ስልጣን፣ ሀብት፣ ገንዘብ እና ከፍታ ከሰው እንጅ ከእግዚአብሔር ታመልጡ ዘንድ የማያደርጋችሁ ነገር ግን በተሰጣችሁ ነገር ራሳችሁን ከሙስና፣ ድሃን ከመበደል፣ ከክፋት እና ከሀጢአት ሁሉ አርቃችሁ ለሰማይ ቤት ሽልማት በቻላችሁት አቅም ሁሉ መልካም እንድታደርጉበት የተሰጣችሁ የአገልግሎት እድል ነው። በየዘመናቱ የመጡ የአለም ሁሉ ገዥ ከነበረው አዳም ጀምሮ በኢሳ 14፣ በህዝ 28፣ በአብድዩ ወዘተ የተመዘገቡ የታሪክ እውነቶች ዛሬ በህይወት ላለነው ነጋችንን ለማስተካከል እድል ያለን ህያዋን ሁሉ የተመሳሳይ ጥፋት ሰለባ እንዳንሆን በጻድቅ ፈራጁ የፍጥረት ሁሉ ጌታ የተሰጡን መማሪያዎች ናቸው። እንደገና_በህይወት_መኖር /ሪቫይቫል ለኢትዮጲያ/ ከሚለው መፅሐፍ ገፅ 405-409 ካለው ክፍል የተወሰደ ሙሉ መፅሃፉን በነፃ ለማግኘት ከታች ያለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/5 . . . . . . Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
215
16
ሰው ብቻ ናችሁና፣ ሰው ሁኑ! ----‐----------- "የአገሪቱን የስልጣን እና የሀብት ማማዎች ሁሉ ተቆጣጥረው የሚደርስባቸው ማንም ያለ እስከማይመስል ድረስ የዚህን አለም ከፍታ ይዘው ሰው መሆናቸውን ረስተው የኖሩ የባለፉት አስርት አመታት ባለስልጣናት ከከፍታቸው ወርደው በየምድረበዳው እንደ እንስሳ እየታደኑ መገደል ዛሬ ላይ በቦታው ለምትገኙ ሁሉ ትምህርት ሊሆን ይገባዋል።" ዛሬ ላይ በየትኛውም አይነት የስልጣን ደረጃ ላይ የሚገኝ ሌላን ሰው ማገልገል የሚችልበትን ስፍራ እግዚአብሔር የሰጠው ከቀበሌ እስከ ቤተ መንግስት እና ከጥበቃ እስከ ጠቅላይ ሚኒስቴር ደረጃ የሚገኝ ማንኛውም ሰው እንደ ሌላው ሁሉ ሰው የሆነ ተመሳሳይ የህይወት ጐዳና ያለው ፍጡር ነው። ከባለስልጣናት ባሻገር ሁሉም ዛሬ ላይ የተለያየ የህይወት ከፍታ ላይ የደረሰ ማንኛውም ሰው ፈፅሞ ከሌላው ሰው የተለየ ያልሆነ ህይወት ያለው ፍጡር ነው።ነገር ግን በተለያየ አቅጣጫ እያንዳንዱ ሰው በሚያራምደው የህይወት መስመር እና በደረሰበት ምድራዊ የህይወት ከፍታ የማይለወጠውን ለሰው ሁሉ የተሰጠ ጅማሬ እና ፍፃሜ ሲዘነጋ ይታያል።ይህም በርካቶችን የደረሱበት ጊዜያዊ ከፍታ ሲያታልላቸው እና ባልተገባ መንገድ ብዙ ቀውሶችን በራሱ ብሎም በሌሎች ላይ እንዲፈጥሩ ሲያደርጋቸው ይታያሉ። እነዚሁ ጊዜያዊ ከፍታዎች ሰውን ከሰውነት ጎዳና አውጥተው ሟች መሆኑን እንዲረሳ እና ዋና የሆነውን የነገ ህይወቱን ለዘላለም እንዲያበላሽ ሲያደርጉት የሚታይ ሲሆን ዛሬ እጃቸው ላይ ባለው ጊዜያዊ የሆነ አላፊ እና ጠፊ ነገር ዘላለማዊ የሆነውን በእግዚአብሔር እጅ ያለችውን ነፍሳቸውን ሲያጠፋ ይታያሉ። ለሰው ሁሉ በጋራ የተሰጠው ከስልጣን፣ ከሃብት፣ ከእውቀት ወዘተ ጋር ያልተገናኘ ሁሉም የሚያልፍበት ጎዳናው ውልደት እና ሞት ነው። በእነዚህ በሁለቱ መካከል ማንኛውም ሰው የሚያልፍበት የህይወት መስመር እግረ መንገድ የሆነ ጊዜያዊ ምልልስ ነው። መወለድ እና መሞት በመክብብ 3፡19 ላይ እንደተገለፀው ለሰው እንዲሁም ለእንስሳ ብሎም ለፍጥረት ሁሉ የተሰጠ የማይቀር የህይወት ጎዳና ሲሆን ሰውን ከሌላው የሚለየው ግን በፈጠረው አምላኩ አምሳል የተፈጠረ ነፍሱም እንደ እንስሳ ነፍስ ወደ ምድር ሳይሆን ወደ ፈጠራት አምላኳ ለፍርድ ወደ እግዚአብሔር ወደ ሰማይ የምትወጣ ማስተዋል የተሰጠው ፍጡር መሆኑ ነው። ታዲያ በተለያየ ደረጃ ለሚገኙ ባለስልጣናት እንዲሁም ለሁሉም በሚሆን ውልደት እና ሞት መካከል መንገድ ላይ ለሚገኙ ዛሬ ላይ በተለያየ ጊዜያዊ የህይወት ከፍታ ላይ ላሉ ወንድም እና እህቶቼ ሁሉ ያለኝ ምክር ንጉስ ዳዊት የሚሞትበት ቀን በቀረበ ጊዜ በወቅቱ በነበረው አለም ከፍታ ላይ ያለችን ሀገር እንዲመራ ሊረከብ ያለውን ልጁን ሰለሞንን የመከረውን ቀላል የምትመስል ነገር ግን ብዙ ጥበብ ያለባት ምክር ናት። እርሷም ‘’ሰው ሁኑ!’’ ብቻ የምትል ናት። ሰው መሆንን ማወቅ እንደ እንስሳ እና ሌላው ፍጥረት ተወልዶ ከመሞት ያለፈ ማንነት ያለበት ነው። ይህ ቀላል የሚመስል ንግግር ዛሬ ላይ በደረሰበት የተለያየ የህይወት ከፍታ ምክንያት ትናንትናውን በቀላሉ ለሚረሳ ህይወቱ በፈጣሪ እጅ ለተያዘች ምስኪን የሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ናት። ዛሬ ይህንን እውነት ላስታውሳችሁ እና ዛሬ የምትገኙበት ልዩ ልዩ ከፍታ እንዳይሸውዳችሁ እና ዘላለማችሁን እንዳያበላሸው፣ በየትኛውም ጊዜ ከእናንተ በተለያየ መንገድ ሊወሰድ የሚችል ፍጻሜ ያለው የዚህ አለም ማባበያ እንደሆነ እንድታስቡ እና እንድትነቁ ላስታውሳችሁ እወዳለሁ። ዛሬ ላይ ያላችሁበት የትኛውም ስልጣን፣ ሀብት፣ መታወቅ፣ እውቀት ከመኖሩ በፊት አንድ ቀን እዚህ ምድር ላይ አልነበራችሁም። ያለ እናት እና አባታችሁ /ከግንኙነት በቀር/ አስተዋፅኦ ራሱ እግዚአብሔር በፈቃዱ በሆነ ቤተሰብ በኩል ፅንስ እንድትሆኑ፣ ውርጃ እንዳያጋጥማችሁ፣ በመወለድ ጊዜ እንዳትሞቱ አድርጎ በማህፀን ውስጥ ያኖራችሁ ለሰው በማይገባ መንገድ በዚያው ማህፀን ውስጥ ራሱ በራሱ መንገድ የመገባችሁ ፍጥረት ናችሁ። በመወለድ ለቤተሰቦቻችሁ ከተሰጣችሁ በኋላ እንደ ማንኛውም ሰው በተገኛችሁበት ቤተሰብ የኑሮ አቅም ልክ በብዙ ፈተና ነገር ግን በእግዚአብሔር ምህረት ምድሪቱን ከሞላው ሞት አምልጣችሁ ዛሬ የደረሳችሁ ናችሁ። ዛሬ ላይ ያላችሁበት ስፍራ ትናንት አልነበረም፤ ነገም ለመኖሩ ዋስትና የላችሁም። ይህ ሁሉ ያልፍና አንድ ቀን ደግሞ ከዚህ አለም እንደ ማንኛውም ፍጥረት በልዩ ልዩ መንገድ ከዚህ ጊዜያዊ የሆነ የምድር ህይወት በሞት ታልፋላችሁ። ሰው ናችሁ! የሰው ልጅ በምድር ላይ ባለው ቆይታ በአግባብ እና በስርዓት ይኖር ዘንድ ማህበራዊ አድርጎ የፈጠረው ሲሆን ለዚህም የሚያስፈልግ መዋቅር እና ደረጃን ለሰው ልጆች አብሮ ሰጥቷል። በዚህም መሰረት በራሱ ፈቃድ ወደ መኖር ያመጣውን ሰው ምድርን ይገዛ ያስተዳድር እና ያበጅ ዘንድ በሰማይ ያለውን ፈቃዱን በምድር እንድያደርግለት የተለያየ ሁኔታ ውስጥ ያኖረዋል። ስልጣን፣ ሀብት፣ እውቀት፣ እና ሌሎችም ነገሮች በእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ ለሰው ጥቅም የሚሰጡ ደግም የሚቀሙ በጊዜያዊነት ብቻ በሰው እጅ ላይ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰው ይኖርበት ዘንድ በተሰጠው ዘመን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ፈፅሞ ለሰው ጥቅም ኖሮ እንዲያልፍ የተሰራ ነው። ይሁን እንጅ በአንድም በሌላም የክፉ ልብ ባለቤት የሆነው የሰው ልጅ ዛሬ ላይ በደረሰበት ሁኔታ ምክንያት ትናንትናውን በቀላሉ የሚረሳ የዛሬ ከፍታው ነገ ላይኖር የሚችል ነፋስ መሆኑን የሚዘነጋ ሆኖ ይታያል። ይህም በህይወት ዘመኑ በስልጣኑ፣ በሀብቱ፣ በዝናው፣ በእውቀቱ አና መሰል የከፍታ ጊዜያቱ የዘራቸውን መልካም/ክፉ ዘሮች መልሶ የሚያጭድበትን ሁኔታ ይፈጥራል። ይህ የህይወት ዑደት ከፍጥረት ጅማሬ አንስቶ የመጣ እውነት ሲሆን የሰው የነገ እጣ ፈንታ ዛሬ ላይ የሚወሰንበት ከፍተኛ የጥንቃቄ አካሄድን የሚፈልግ ጥበብ ነው። እያንዳንዱ ሰው በእለት ከእለት ምልልሱ ውስጥ መልካም ወይም ክፉ ለማድረግ ፈቃድ ያለው ሲሆን በምርጫው ያደረጋቸው ነገሮች ሁሉ በጊዜያቸው በቅለው፣ አድገው፣ አብበው እና አፍርተው የሚታጨዱ ይሆናሉ። ይህም ማስተዋል የሚችል ሰው ለሆነ ሰው በየቀኑ የሚታዩ እንደ ሀገር ህያው ምስክር ሆነን ደጋግመን ያየናቸው የቅርብ ትዝታዎች እና የዛሬ እውነቶች ናቸው። የአገሪቱን የስልጣን እና የሀብት ማማዎች ሁሉ ይዘው የሚደርስባቸው ማንም ያለ እስከማይመስል ድረስ የዚህን አለም ከፍታ ይዘው ሰው መሆናቸውን ረስተው የኖሩ የባለፉት አስርት አመታት ባለስልጣናት ከከፍታቸው ወርደው በየምድረበዳው እንደ እንስሳ እየታደኑ መገደል ዛሬ ላይ በቦታው ለምትገኙ ሁሉ ትምህርት ሊሆን ይገባዋል። በምድር ዘመን ሁሉ መዝራትና ማጨድ፣ ብርድና ሙቀት፣ በጋና ክረምት፣ ቀንና ሌሊት እንዳይቋረጡ ያዘዘው እግዚአብሔር እንደ ቃሉ ያው ነውና ሰው ሁሉ የዘራውን ያንኑ በማጨድ ዘመኑን ይጨርስ ዘንድ አዟል። እስራኤላዊያን በአምላካቸው ላይ ባመፁ ጊዜ ህዝቡን ይቀጣ ዘንድ በምድር ላይ ያስነሳቸው ታላላቅ ነገስታት አሦርና ባቢሎን ለዚህ ጥሩ ማሳያዎች ናቸው። ከዘፍጥረት 10 የጀመረ ታሪክ ያለው አሦር በኢሳይያስ 10፡ 5-19 እንደተገለፀው የወቅቱ ታላቅ ንጉስ ሰው መሆኑን መርሳቱ የብዙ ሽህ አመታት አገዛዙን ዳግም እንዳይታሰብ አድርጎ ፍፃሜው ይሆን ዘንድ አደረገው።
1 384
17
መዝሙረ ዳዊት 22:1-11 (AMH) •••••••••• ¹ አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳንና ከጩኸቴ ቃል ሩቅ ነህ። ² አምላኬ፥ በቀን ወደ አንተ እጠራለሁ፥ አልመለስህልኝም፤ በሌሊትም
መዝሙረ ዳዊት 22:1-11 (AMH) •••••••••• ¹ አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳንና ከጩኸቴ ቃል ሩቅ ነህ። ² አምላኬ፥ በቀን ወደ አንተ እጠራለሁ፥ አልመለስህልኝም፤ በሌሊትም እንኳ ዕረፍት የለኝም። ³ በእስራኤል የተመሰገንህ አንተ ግን በቅድስና ትኖራለህ። ⁴ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ፥ ተማመኑ አንተም አዳንሃቸው። ⁵ ወደ አንተ ጮኹ አመለጡም፥ አንተንም ተማመኑ አላፈሩም። ⁶ እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ። ⁷ የሚያዩኝ ሁሉ ይላገዱብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ፦ ⁸ በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው። ⁹ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ። ¹⁰ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ¹¹ ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።
137
18
1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 6:6-10 (NASV) •••••••••• ⁶ ነገር ግን እውነተኛ መንፈሳዊነት ባለን ነገር ከመርካት ጋር ትልቅ ትርፍ ነው። ⁷ ምክንያቱም ወደ ዓለም ያመጣነው ምንም ነገር የለም፤ ም
1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 6:6-10 (NASV) •••••••••• ⁶ ነገር ግን እውነተኛ መንፈሳዊነት ባለን ነገር ከመርካት ጋር ትልቅ ትርፍ ነው። ⁷ ምክንያቱም ወደ ዓለም ያመጣነው ምንም ነገር የለም፤ ምንም ነገር ይዘን መሄድም አንችልም። ⁸ ነገር ግን ምግብና ልብስ ካለን፣ ያ ይበቃናል። ⁹ ባለጠጋ ለመሆን የሚፈልጉ ግን ወደ ፈተናና ወደ ወጥመድ፣ እንዲሁም ሰዎችን ወደ መፍረስና ወደ ጥፋት ወደሚያዘቅጠው ወደ ብዙ ከንቱና ክፉ ምኞት ይወድቃሉ። ¹⁰ ምክንያቱም የገንዘብ ፍቅር የክፋት ሁሉ ሥር ነው። አንዳንዶች ባለጠጋ ለመሆን ካላቸው ጕጕት የተነሣ ከእምነት መንገድ ስተው ሄደዋል፤ ራሳቸውንም በብዙ ሥቃይ ወግተዋል። . . . . . . በእውነት መንገድ ሕይወት /Life in Truth/ ቤተሰብ ለመሆን ከስር ያሉትን ሊንኮች ይከተሉ! Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ቴሌግራም፦ https://t.me/Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth #revivalforethiopia ##mindtransformation #thegodweworship
172
19
ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የማቴዎስ ወንጌል 6:25-33 (AMH) •••••••••• ²⁵ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ
ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የማቴዎስ ወንጌል 6:25-33 (AMH) •••••••••• ²⁵ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን? ²⁶ ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን? ²⁷ ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው? ²⁸ ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤ ²⁹ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም። ³⁰ እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? ³¹ እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ³² ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ³³ ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። #revivalforethiopia #mindtransformaion #thegodweworship #Lifeintruth
175
20
《እግዚአብሔር ይታወቅ ዘንድ ራሱን ገልጧል።》 -------------‐--------- እግዚአብሔር እርሱን በቅን ልብ ለሚፈልጉት ራሱን አይሰውርም። በፍጥረት፣ በቃሉ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንዲሁ
《እግዚአብሔር ይታወቅ ዘንድ ራሱን ገልጧል።》 -------------‐--------- እግዚአብሔር እርሱን በቅን ልብ ለሚፈልጉት ራሱን አይሰውርም። በፍጥረት፣ በቃሉ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ ራሱን ለእኛ ገልጧል። ነገር ግን የእርሱ መገለጥ እርሱን እንድናደንቅ ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋር የቅርብ ኅብረት እንድኖረን ነው። ስለዚህ ጥያቄው እግዚአብሔር ራሱን ለመግለጥ ፈቃደኛ ነውን? የሚለው ሳይሆን፣ እኛ እርሱን በእውነት ለማወቅ እንፈልጋለንን?የሚለው ነው። በትሕትናና በታዛዥነት ወደ እርሱ በቀረብን መጠን፣ እርሱም ራሱን በሚያስደንቅ መንገድ ይበልጥ እየገለጠልን ይሄዳል። ይህንን እውነት በየቀኑ በሕይወታችን ልናስታውሰው ያስፈልገናል። "ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ፥ እርሱም ወደ እናንተ ይቀርባል።" — የያዕቆብ መልእክት 4፥8 — የምናመልከው እግዚአብሔር ማን ነው? ከሚለው መጽሐፍ ከገፅ 9-12 ካለው ክፍል የተወሰደ መጽሐፉን ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት! https://t.me/Intruthlife/296 . . . . . . በእውነት መንገድ ሕይወት /Life in Truth/ ቤተሰብ ለመሆን ከስር ያሉትን ሊንኮች ይከተሉ! Youtube (ዩቲዩብ)፦ http://www.youtube.com/@Intruthlife ቴሌግራም፦ https://t.me/Intruthlife ፌስቡክ፦ https://web.facebook.com/Intruthlife/ ቲክቶክ፦ ‎https://www.tiktok.com/@life_in_truth
172